⬆️
ከኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጋዜጣዊ መግለጫ!
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) መጋቢት 2 ቀን 2014 ዓ.ም. የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎችና በርካታ ተመልካቾች በተሰበሰቡበት አስክሬኖች እና አንድ በሕይወት የነበረ ሰው በአሰቃቂ ሁኔታ እሳት ውስጥ ሲጨመር የሚያሳይና በማኅበራዊ ሚድያ በተሰራጨ የቪድዮ ምስል በደረሱት ጥቆማዎች መሰረት ስለሁኔታው አፋጣኝ ማጣራት አድርጓል።
ኢሰመኮ ምስክሮችን በማነጋገር እንዳጣራው ክስተቱ የተፈጸመው በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን በጉባ ወረዳ አይሲድ ቀበሌ ውስጥ የካቲት 24 ቀን 2014 ዓ.ም. መሆኑን፣ ከዳኝነት ውጪ የተፈጸመ ግድያ (extra-judicial killing) እና አስከሬኖችን አንድ በሕይወት ከነበረ ሰው ጭምር የማቃጠል ድርጊቱ የተፈጸመው በመንግሥት የፀጥታ አባላትና ሌሎችም ሰዎች ተሳትፎ ጭምር የነበረ መሆኑን አረጋግጧል። እንዲሁም ለዚህ ክስተት መነሻ ስለሆነው ድርጊቱ ከተፈጸመበት አንድ ቀን በፊት ቢያንስ በ 20 የመንግሥት ፀጥታ አባላት እና በሲቪል ሰዎች ላይ በታጣቂዎች ስለተፈጸመው ግድያ ሁኔታም አረጋግጧል፡፡
የካቲት 23 ቀን 2014 ዓ.ም. በመተከል ዞን፣ በጉባ ወረዳ፣ አይሲድ ቀበሌ፣ አፍሪካ እርሻ ልማት ማኅበር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ገደማ፣ ከግልገል በለስ ከተማ በመኪና ተሳፍረው፣ በአካባቢው ካለው የደኅንነት ስጋት አንጻር በተለመደው አሰራር መሰረት በመከላከያ ሠራዊት ታጅበው ወደ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ፤ ወደ ማንኩሽና ወደ አሶሳ ከተማ ሲጓዙ የነበሩ ሰዎች ላይ ታጣቂዎች በከባድ መሳሪያ የታገዘ ጥቃት ፈጸሙ። በጥቃቱም 1 መኪና አሽከርካሪ፣ 1 በንግድ ሥራ የሚተዳደሩ ሰው እና 1 መምህር በአጠቃላይ 3 ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል፤ መንገደኞቹን አጅቦ በመጓዝ ላይ የነበሩት የመከላከያ ሠራዊት አባላት መኪና በከባድ መሳሪያ ተመትቶ ሻለቃ አመራሩን ጨምሮ ቢያንስ 20 የመከላከያ ሠራዊት አባላት ሞተዋል፣ እንዲሁም 14 የመከላከያ ሠራዊት አባላት ላይ ደግሞ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል፡፡
በዕለቱ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎችና እና ጥቃቱን በፈጸሙ የታጠቁ ኃይሎች መካከል የተደረገው ውጊያ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እስከ ረፋዱ 12፡00 ሰዓት የቆየ ሲሆን፣ በማግስቱ የካቲት 24 ቀን 2014 ዓ.ም. ተጨማሪ የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በቦታው ደርሰው ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት እስከ 4፡00 ሰዓት ድረስ በቆየ የተኩስ ልውውጥ ከታጣቂዎቹ መካከል ወደ 30 የሚሆኑ መገደላቸውንና ቀሪዎቹ ታጣቂዎች መሸሻቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡
ይህንን ተከትሎ የመከላከያ ሠራዊት የመንግሥት ፀጥታ አባላቱና የሲቪል ሰዎች መንገደኞች መኪኖች የካቲት 24 ቀን 2014 ዓ.ም. ከቀኑ 6፡00 ሰዓት አካባቢ አይሲድ ከተማ ደረሱ። በተከሰተው አደጋም የከተማው ፀጥታ ሁኔታ ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ እንደነበር የአካባቢው ነዋሪዎች ያስረዳሉ።
የመንግሥት የፀጥታ አባላቱ አግኝተናል ባሉት ጥቆማዎች መሰረት በአካባቢው በነበሩ ተሽከርካሪዎችና በመኖሪያ ቤቶች ላይ እንዲሁም ከግልገል በለስ ከተማ ወደ ማንኩሽና ባምዛ የሚጓዙ የነበሩ ሲቪል ሰዎች ላይ ፍተሻ ማካሄድ ጀመሩ።
በፍተሻው ሂደት ውስጥ በቅርቡ ከእስር ተፈትተው ከመተከል ዞን ማረሚያ ቤት የይለፍ ወረቀት በመያዝ ወደ መኖሪያቸው የተመለሱና የአካባቢው ነዋሪዎች የነበሩ 8 የትግራይ ተወላጆችን “እናንተ ናችሁ መረጃ ሰጥታችሁ ጥቃቱን ያስፈጸማችሁት” በማለት ከተሳፈሩበት መኪና እንዳስወረዱና በፍተሻውም አንድ የወታደራዊ መገናኛ ሬዲዮ፣ የተለያዩ ፎቶግራፎች እና ከ40,000 ብር በላይ ገንዘብ እንደተገኘ ተገልጿል። የመንግሥት ፀጥታ አባላቱም ተጠርጣሪዎቹን እየደበደቡ ተጨማሪ መረጃ መጠየቅ ጀመሩ።
ከዚህ ተከትሎም ከተጠርጣሪዎቹ መካከል አንዱ “በአካባቢው በተፈጸመው ጥቃት ላይ እጃችን አለበት፤ ባምዛ በሚባለውና በግልገል በለስ ቦታዎች ሰዎች አሉን” ማለቱን ተከትሎ፣ የመንግሥት የፀጥታ ኃይል አባላቱ ሁኔታውን የተቃወሙ ሁለት የጉሙዝ ተወላጆችን ጨምሮ 10 ሰዎችን ተኩሰው ገድለዋል።
ከዚህ በመቀጠልም የፀጥታ ኃይል አባላቱ የተገደሉትን ሰዎች አስከሬኖች ከከተማዋ ወጣ ብሎ ወደሚገኝ ጫካ ስፍራ በመውሰድ አስክሬናቸውን ማቃጠል መጀመራቸውን የዓይን ምስክሮች አስረድተዋል። በዚህ መካከልም ከተጠርጣሪዎቹ ተገዳዮች ጋር ግንኙነት አለው የተባለን አንድ ሌላ የትግራይ ተወላጅ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በተሳፈረበት መኪና ውስጥ ተደብቆ በጥቆማ ካገኙት በኋላ በገመድ አስረው በመውሰድ ቀድሞ በመቃጠል ላይ ከነበሩት አስክሬኖች ላይ እንደጨመሩት እና በእሳት ተቃጥሎ እንደሞተ ምስክሮች ለኮሚሽኑ አስረድተዋል፡፡
በአካባቢው የነበሩት የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች የመከላከያ ሠራዊት አባላት፣ የአማራ ክልል ልዩ ፖሊስ አባላትና የደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ልዩ ፖሊስ አባላት ሲሆኑ፤ በአጠቃላይ ሁኔታው በቀጥታ ድርጊት በመፈጸም ወይም አስገዳጅ ተግባሮችን ባለመፈጸም (by commission or omission) የነበራቸው የተለያየ የተሳትፎ መጠን በተጨማሪ የወንጀል ምርመራ ሊጣራ የሚገባው ነው፡፡
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ እንደገለጹት የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እጅግ ፈታኝ በሆኑ አካባቢዎች በከፍተኛ መስዋዕትነት የሕዝብ ደኅንነት የሚጠብቁ መሆኑ የማይዘነጋ ሕዝባዊ አገልግሎት መሆኑ እንደሚታወቅ ገልጸው፤ ሆኖም ግን በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችን ከዳኝነት ሂደት ውጭ መግደል እና በተለይም በእሳት አቃጥሎ መግደል ፈጽሞ ከሕግ አስከባሪ አባሎች የማይጠበቅ ግፍና ጭካኔ የተሞላበት የሰብአዊ መብቶች ጥሰት በመሆኑ የሕግ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ በተጠርጣሪዎች ላይ ተገቢውን የወንጀል ምርመራ በአፋጣኝ
እንዲደረግ አሳስበዋል።
ዶ/ር ዳንኤል በቀለ አክለውም “የመንግሥት ሕግ አስከባሪ አባሎች እራሳቸው በግልጽ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ፈጻሚዎች ሆነው መታየታቸው፤ ሰዎች በሕጋዊ ሥርዓት ላይ የሚኖራቸውን እምነት የሚሸረሽርና ለተጨማሪ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የሚያጋልጥ በመሆኑ፤ መንግሥት የምርመራውን ሂደትና ውጤት በተመለከተ የተሟላ መረጃ
ለሕዝብ ይፋ ሊያደርግና ፍትሕን ለማረጋገጥም የሟች ቤተሰቦችን ሊክስ ይገባል” ብለዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
ከኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጋዜጣዊ መግለጫ!
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) መጋቢት 2 ቀን 2014 ዓ.ም. የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎችና በርካታ ተመልካቾች በተሰበሰቡበት አስክሬኖች እና አንድ በሕይወት የነበረ ሰው በአሰቃቂ ሁኔታ እሳት ውስጥ ሲጨመር የሚያሳይና በማኅበራዊ ሚድያ በተሰራጨ የቪድዮ ምስል በደረሱት ጥቆማዎች መሰረት ስለሁኔታው አፋጣኝ ማጣራት አድርጓል።
ኢሰመኮ ምስክሮችን በማነጋገር እንዳጣራው ክስተቱ የተፈጸመው በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን በጉባ ወረዳ አይሲድ ቀበሌ ውስጥ የካቲት 24 ቀን 2014 ዓ.ም. መሆኑን፣ ከዳኝነት ውጪ የተፈጸመ ግድያ (extra-judicial killing) እና አስከሬኖችን አንድ በሕይወት ከነበረ ሰው ጭምር የማቃጠል ድርጊቱ የተፈጸመው በመንግሥት የፀጥታ አባላትና ሌሎችም ሰዎች ተሳትፎ ጭምር የነበረ መሆኑን አረጋግጧል። እንዲሁም ለዚህ ክስተት መነሻ ስለሆነው ድርጊቱ ከተፈጸመበት አንድ ቀን በፊት ቢያንስ በ 20 የመንግሥት ፀጥታ አባላት እና በሲቪል ሰዎች ላይ በታጣቂዎች ስለተፈጸመው ግድያ ሁኔታም አረጋግጧል፡፡
የካቲት 23 ቀን 2014 ዓ.ም. በመተከል ዞን፣ በጉባ ወረዳ፣ አይሲድ ቀበሌ፣ አፍሪካ እርሻ ልማት ማኅበር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ገደማ፣ ከግልገል በለስ ከተማ በመኪና ተሳፍረው፣ በአካባቢው ካለው የደኅንነት ስጋት አንጻር በተለመደው አሰራር መሰረት በመከላከያ ሠራዊት ታጅበው ወደ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ፤ ወደ ማንኩሽና ወደ አሶሳ ከተማ ሲጓዙ የነበሩ ሰዎች ላይ ታጣቂዎች በከባድ መሳሪያ የታገዘ ጥቃት ፈጸሙ። በጥቃቱም 1 መኪና አሽከርካሪ፣ 1 በንግድ ሥራ የሚተዳደሩ ሰው እና 1 መምህር በአጠቃላይ 3 ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል፤ መንገደኞቹን አጅቦ በመጓዝ ላይ የነበሩት የመከላከያ ሠራዊት አባላት መኪና በከባድ መሳሪያ ተመትቶ ሻለቃ አመራሩን ጨምሮ ቢያንስ 20 የመከላከያ ሠራዊት አባላት ሞተዋል፣ እንዲሁም 14 የመከላከያ ሠራዊት አባላት ላይ ደግሞ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል፡፡
በዕለቱ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎችና እና ጥቃቱን በፈጸሙ የታጠቁ ኃይሎች መካከል የተደረገው ውጊያ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እስከ ረፋዱ 12፡00 ሰዓት የቆየ ሲሆን፣ በማግስቱ የካቲት 24 ቀን 2014 ዓ.ም. ተጨማሪ የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በቦታው ደርሰው ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት እስከ 4፡00 ሰዓት ድረስ በቆየ የተኩስ ልውውጥ ከታጣቂዎቹ መካከል ወደ 30 የሚሆኑ መገደላቸውንና ቀሪዎቹ ታጣቂዎች መሸሻቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡
ይህንን ተከትሎ የመከላከያ ሠራዊት የመንግሥት ፀጥታ አባላቱና የሲቪል ሰዎች መንገደኞች መኪኖች የካቲት 24 ቀን 2014 ዓ.ም. ከቀኑ 6፡00 ሰዓት አካባቢ አይሲድ ከተማ ደረሱ። በተከሰተው አደጋም የከተማው ፀጥታ ሁኔታ ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ እንደነበር የአካባቢው ነዋሪዎች ያስረዳሉ።
የመንግሥት የፀጥታ አባላቱ አግኝተናል ባሉት ጥቆማዎች መሰረት በአካባቢው በነበሩ ተሽከርካሪዎችና በመኖሪያ ቤቶች ላይ እንዲሁም ከግልገል በለስ ከተማ ወደ ማንኩሽና ባምዛ የሚጓዙ የነበሩ ሲቪል ሰዎች ላይ ፍተሻ ማካሄድ ጀመሩ።
በፍተሻው ሂደት ውስጥ በቅርቡ ከእስር ተፈትተው ከመተከል ዞን ማረሚያ ቤት የይለፍ ወረቀት በመያዝ ወደ መኖሪያቸው የተመለሱና የአካባቢው ነዋሪዎች የነበሩ 8 የትግራይ ተወላጆችን “እናንተ ናችሁ መረጃ ሰጥታችሁ ጥቃቱን ያስፈጸማችሁት” በማለት ከተሳፈሩበት መኪና እንዳስወረዱና በፍተሻውም አንድ የወታደራዊ መገናኛ ሬዲዮ፣ የተለያዩ ፎቶግራፎች እና ከ40,000 ብር በላይ ገንዘብ እንደተገኘ ተገልጿል። የመንግሥት ፀጥታ አባላቱም ተጠርጣሪዎቹን እየደበደቡ ተጨማሪ መረጃ መጠየቅ ጀመሩ።
ከዚህ ተከትሎም ከተጠርጣሪዎቹ መካከል አንዱ “በአካባቢው በተፈጸመው ጥቃት ላይ እጃችን አለበት፤ ባምዛ በሚባለውና በግልገል በለስ ቦታዎች ሰዎች አሉን” ማለቱን ተከትሎ፣ የመንግሥት የፀጥታ ኃይል አባላቱ ሁኔታውን የተቃወሙ ሁለት የጉሙዝ ተወላጆችን ጨምሮ 10 ሰዎችን ተኩሰው ገድለዋል።
ከዚህ በመቀጠልም የፀጥታ ኃይል አባላቱ የተገደሉትን ሰዎች አስከሬኖች ከከተማዋ ወጣ ብሎ ወደሚገኝ ጫካ ስፍራ በመውሰድ አስክሬናቸውን ማቃጠል መጀመራቸውን የዓይን ምስክሮች አስረድተዋል። በዚህ መካከልም ከተጠርጣሪዎቹ ተገዳዮች ጋር ግንኙነት አለው የተባለን አንድ ሌላ የትግራይ ተወላጅ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በተሳፈረበት መኪና ውስጥ ተደብቆ በጥቆማ ካገኙት በኋላ በገመድ አስረው በመውሰድ ቀድሞ በመቃጠል ላይ ከነበሩት አስክሬኖች ላይ እንደጨመሩት እና በእሳት ተቃጥሎ እንደሞተ ምስክሮች ለኮሚሽኑ አስረድተዋል፡፡
በአካባቢው የነበሩት የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች የመከላከያ ሠራዊት አባላት፣ የአማራ ክልል ልዩ ፖሊስ አባላትና የደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ልዩ ፖሊስ አባላት ሲሆኑ፤ በአጠቃላይ ሁኔታው በቀጥታ ድርጊት በመፈጸም ወይም አስገዳጅ ተግባሮችን ባለመፈጸም (by commission or omission) የነበራቸው የተለያየ የተሳትፎ መጠን በተጨማሪ የወንጀል ምርመራ ሊጣራ የሚገባው ነው፡፡
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ እንደገለጹት የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እጅግ ፈታኝ በሆኑ አካባቢዎች በከፍተኛ መስዋዕትነት የሕዝብ ደኅንነት የሚጠብቁ መሆኑ የማይዘነጋ ሕዝባዊ አገልግሎት መሆኑ እንደሚታወቅ ገልጸው፤ ሆኖም ግን በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችን ከዳኝነት ሂደት ውጭ መግደል እና በተለይም በእሳት አቃጥሎ መግደል ፈጽሞ ከሕግ አስከባሪ አባሎች የማይጠበቅ ግፍና ጭካኔ የተሞላበት የሰብአዊ መብቶች ጥሰት በመሆኑ የሕግ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ በተጠርጣሪዎች ላይ ተገቢውን የወንጀል ምርመራ በአፋጣኝ
እንዲደረግ አሳስበዋል።
ዶ/ር ዳንኤል በቀለ አክለውም “የመንግሥት ሕግ አስከባሪ አባሎች እራሳቸው በግልጽ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ፈጻሚዎች ሆነው መታየታቸው፤ ሰዎች በሕጋዊ ሥርዓት ላይ የሚኖራቸውን እምነት የሚሸረሽርና ለተጨማሪ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የሚያጋልጥ በመሆኑ፤ መንግሥት የምርመራውን ሂደትና ውጤት በተመለከተ የተሟላ መረጃ
ለሕዝብ ይፋ ሊያደርግና ፍትሕን ለማረጋገጥም የሟች ቤተሰቦችን ሊክስ ይገባል” ብለዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 4ኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተ ቀብር በዛሬው ዕለት (መጋቢት 4/2014 ዓ.ም ) የቤተክርስቲያኗ ሥርዓተ ቀኖና በሚያዘው መልኩ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴደራል ተፈጽሟል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 4ኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተ ቀብር በዛሬው ዕለት (መጋቢት 4/2014 ዓ.ም ) የቤተክርስቲያኗ ሥርዓተ ቀኖና በሚያዘው መልኩ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴደራል ተፈጽሟል።
@YeneTube @FikerAssefa
በዩክሬን ያሉ ኢትዮጵያውያን "ለዩክሬን እንድንዋጋ እየጠየቁን ነው፣ በቅርቡ በግዳጅ ወደ ጦርሜዳ ሊወስዱን ይችላሉ ብለን ሰግተናል" ብለውኛል ሲል ጋዜጠኛ ኤልያስ መሠረት ጽፏል።
ጋዜጠኛው በአንድ ዩክሬን ውስጥ በሚገኝ ካምፕ ውስጥ ተይዘው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከዩክሬን ጦር ጋር ሆነው እንዲዋጉ መጠየቃቸውን፣ ወደፊት ደግሞ በአስገዳጅነት እንዲዋጉ ሊደረጉ እንደሚችሉ ስጋት እንዳላቸው ዛሬ በስልክ ነግረውኛል ብሏል።
ለደህንነታቻው ሲባል ስማቸው እና ያሉበት ካምፕ እንዳይጠቀስ የጠየቁ እነዚህ ኢትዮጵያውያን ቢያንስ ሰባት የሚሆኑ ናቸው፣ በካምፑ ውስጥ ባጠቃላይ የሌሎች ሀገራት ዜጎችን ጨምሮ ከ100- 120 የሚደርሱ ሰዎች አሉ ብለዋል። ጋዜጠኛው ሰጡኝ ያለው መረጃ የሚከተለውን ይመስላል:
"ብዙዎቻችን ዩክሬን ለትምህርት ሄደን ከዛም ስራ ስንሰራ (አንዳንዶች ደግሞ ድንበር አቋርጠው ሲሄዱ) ተይዘን በኢሚግሬሽን ህጋቸው መሰረት እንደ እስር ቤት ያለ የስደተኞች ካምፕ ውስጥ መኖር ከጀመርን አስር ወራት ሆኖኗል። ይህ ጫካ ውስጥ ያለ ካምፕ ውስጥ ሆነን የፍርድ ቤት ቀጠሮ እየጠበቅን እያለ የሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ጀመረ። ካምፑ ዝግ ነው፣ ለመውጣት ስንሞክር በጣም ደብድበው መለሱን። ከሰሞኑ የዩክሬን ወታደሮች ወደካምፑ መጥተው ነበር።ለዩክሬን ከተዋጋችሁ ዜግነት እንሰጣችኋለን አሉን።አሁን ያቀረቡት ጥያቄ ቢሆንም በግድ ተዋጉ እንዳይሉን ከፍተኛ ስጋት አለን።ጦርነቱ ካምፑ ጋር ቢደርስ ምን እንደሚፈጠር እና ወዴት እንደምንሄድ አናውቅም።ጉዳያችንን ጀርመን ያለው ኤምባሲ ያይልናል ብለን እየጠበቅን ነበር፣ የሚቻለውን ሁሉ እናረጋለን ብለውን ነበር። ከዛ ወዲህ ለውጥ የለም። ያለንበት ሁኔታ መጥፎ ነው፣ ስልክ እንኳን ቀምተውን በድብቅ በገባ ስልክ ነው የምናወራው። በቀን ሁለቴ የሚሰጡን ምግብ እንኳን ጥሩ አይደለም። ከዛ በላይ ደግሞ ለጥቁሮች ያላቸው አመለካከት ደስ አይልም።"
" በዚህ ጉዳይ ዙርያ ጀርመን ያለውን ኤምባሲ ለማናገር ሞክሬ ለግዜው አልተሳካም።አዲስ አበባ የሚገኘውን የዩክሬን ኤምባሲም በማናገር ተጨማሪ መረጃ ሲደርሰኝ እመለስበታለሁ።" -ኤልያስ መሠረት
@YeneTube @FikerAssefa
ጋዜጠኛው በአንድ ዩክሬን ውስጥ በሚገኝ ካምፕ ውስጥ ተይዘው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከዩክሬን ጦር ጋር ሆነው እንዲዋጉ መጠየቃቸውን፣ ወደፊት ደግሞ በአስገዳጅነት እንዲዋጉ ሊደረጉ እንደሚችሉ ስጋት እንዳላቸው ዛሬ በስልክ ነግረውኛል ብሏል።
ለደህንነታቻው ሲባል ስማቸው እና ያሉበት ካምፕ እንዳይጠቀስ የጠየቁ እነዚህ ኢትዮጵያውያን ቢያንስ ሰባት የሚሆኑ ናቸው፣ በካምፑ ውስጥ ባጠቃላይ የሌሎች ሀገራት ዜጎችን ጨምሮ ከ100- 120 የሚደርሱ ሰዎች አሉ ብለዋል። ጋዜጠኛው ሰጡኝ ያለው መረጃ የሚከተለውን ይመስላል:
"ብዙዎቻችን ዩክሬን ለትምህርት ሄደን ከዛም ስራ ስንሰራ (አንዳንዶች ደግሞ ድንበር አቋርጠው ሲሄዱ) ተይዘን በኢሚግሬሽን ህጋቸው መሰረት እንደ እስር ቤት ያለ የስደተኞች ካምፕ ውስጥ መኖር ከጀመርን አስር ወራት ሆኖኗል። ይህ ጫካ ውስጥ ያለ ካምፕ ውስጥ ሆነን የፍርድ ቤት ቀጠሮ እየጠበቅን እያለ የሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ጀመረ። ካምፑ ዝግ ነው፣ ለመውጣት ስንሞክር በጣም ደብድበው መለሱን። ከሰሞኑ የዩክሬን ወታደሮች ወደካምፑ መጥተው ነበር።ለዩክሬን ከተዋጋችሁ ዜግነት እንሰጣችኋለን አሉን።አሁን ያቀረቡት ጥያቄ ቢሆንም በግድ ተዋጉ እንዳይሉን ከፍተኛ ስጋት አለን።ጦርነቱ ካምፑ ጋር ቢደርስ ምን እንደሚፈጠር እና ወዴት እንደምንሄድ አናውቅም።ጉዳያችንን ጀርመን ያለው ኤምባሲ ያይልናል ብለን እየጠበቅን ነበር፣ የሚቻለውን ሁሉ እናረጋለን ብለውን ነበር። ከዛ ወዲህ ለውጥ የለም። ያለንበት ሁኔታ መጥፎ ነው፣ ስልክ እንኳን ቀምተውን በድብቅ በገባ ስልክ ነው የምናወራው። በቀን ሁለቴ የሚሰጡን ምግብ እንኳን ጥሩ አይደለም። ከዛ በላይ ደግሞ ለጥቁሮች ያላቸው አመለካከት ደስ አይልም።"
" በዚህ ጉዳይ ዙርያ ጀርመን ያለውን ኤምባሲ ለማናገር ሞክሬ ለግዜው አልተሳካም።አዲስ አበባ የሚገኘውን የዩክሬን ኤምባሲም በማናገር ተጨማሪ መረጃ ሲደርሰኝ እመለስበታለሁ።" -ኤልያስ መሠረት
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በጋና አቻው 3 ለ 0 ተሸነፈ!
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በሴቶች ከ20 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ዙር የመጀመርያ ጨዋታ በጋና አቻው 3 ለ0 በሆነ ውጤት ተሸነፈ፡፡የሁለቱ ብሄራዊ ቡድኖች የመልስ ጨዋታቸውን ከ10 ቀናት በኋላ በጋና እንደሚያከናውኑ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በሴቶች ከ20 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ዙር የመጀመርያ ጨዋታ በጋና አቻው 3 ለ0 በሆነ ውጤት ተሸነፈ፡፡የሁለቱ ብሄራዊ ቡድኖች የመልስ ጨዋታቸውን ከ10 ቀናት በኋላ በጋና እንደሚያከናውኑ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የብልፅግና ፓርቲ አንደኛ ጉባዔ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን መረጠ!
የብልፅግና ፓርቲ አንደኛ ጉባዔ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት መምረጡን ፓርቲው አስታወቀ፡፡በጉባኤው 225 አባላትን የያዘ የማዕከላዊ ኮሚቴ እና 45 ሰዎች ያሉበት የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ተመርጧል።ላለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ጉባኤ የፓርቲውን የወደፊት የትኩረት አቅጣጫ ያመላከቱ ባለስድስት ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት መጠናቀቁን ከፓርቲው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
የብልፅግና ፓርቲ አንደኛ ጉባዔ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት መምረጡን ፓርቲው አስታወቀ፡፡በጉባኤው 225 አባላትን የያዘ የማዕከላዊ ኮሚቴ እና 45 ሰዎች ያሉበት የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ተመርጧል።ላለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ጉባኤ የፓርቲውን የወደፊት የትኩረት አቅጣጫ ያመላከቱ ባለስድስት ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት መጠናቀቁን ከፓርቲው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
በሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ምክንያት ሰሜን አፍሪቃ ላይ የምግብ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ ተገለፀ።
የፈረንሳይ ዜና ምንጭ እንደዘገበው ቱኒዚያ፣ ሞሮኮ እና ሊቢያ የመሳሰሉ ሀገራት በተለይ የስንዴ ምርቶችን ካሁኑ ማጠራቀም ጀምረዋል።ሩሲያ እና ዩክሬን ለእነዚህ ሀገራት ዋና የስንዴ አቅራቢዎች ነበሩ። እንደ አንድ የቱኒዚያ ሱፐር ማርኬት ባለቤት ገለፃ ባለፉት ቀናት ውስጥ የአንድ «ኩስኩስ» ምግብ ዋጋ በ 700 በመቶ ጨምሯል።የዱቄት ዋጋ በሶስት እጥፍ ጨምሯል።
እንደ አውሮፓ ህብረት ገለፃ ባለፈው አመት ሩሲያ በዓለም ትልቋ ስንዴ ሻጭ ሀገር ነበረች።ዩክሬን ደግሞ ከዓለም አምስተኛን ስፍራ ይዛ ነበር።ከዚህ ጋር በተያያዘ ጦርነቱ በዚሁ ከቀጠለ ሀገራቱ የሚያቀርቡት የጥራ ጥሬ መጠን ስለሚቀንስ በተለይ ደሀ ሀገራት ይበልጥ ተጎጂ እንደሚሆኑ የጀርመን የልማት ሚኒስትር አሳስበዋል። ሚኒስትር ስቬንያ ሹልሰ ለአንድ የጀርመን ጋዜጣ እንደገለፁት የስንዴ እጥረቱ በደሀ ሀገሮች ላይ ፖለቲካዊ አለመረጋጋትም ሊፈጥር ይችላል። ስለሆነም የዓለም አቀፍ የድጋፍ መርሃ ግብሮች ሌሎች አማራጮችን ማጤን እንዳለባቸው ሚንስትሯ ተናግረዋል።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
የፈረንሳይ ዜና ምንጭ እንደዘገበው ቱኒዚያ፣ ሞሮኮ እና ሊቢያ የመሳሰሉ ሀገራት በተለይ የስንዴ ምርቶችን ካሁኑ ማጠራቀም ጀምረዋል።ሩሲያ እና ዩክሬን ለእነዚህ ሀገራት ዋና የስንዴ አቅራቢዎች ነበሩ። እንደ አንድ የቱኒዚያ ሱፐር ማርኬት ባለቤት ገለፃ ባለፉት ቀናት ውስጥ የአንድ «ኩስኩስ» ምግብ ዋጋ በ 700 በመቶ ጨምሯል።የዱቄት ዋጋ በሶስት እጥፍ ጨምሯል።
እንደ አውሮፓ ህብረት ገለፃ ባለፈው አመት ሩሲያ በዓለም ትልቋ ስንዴ ሻጭ ሀገር ነበረች።ዩክሬን ደግሞ ከዓለም አምስተኛን ስፍራ ይዛ ነበር።ከዚህ ጋር በተያያዘ ጦርነቱ በዚሁ ከቀጠለ ሀገራቱ የሚያቀርቡት የጥራ ጥሬ መጠን ስለሚቀንስ በተለይ ደሀ ሀገራት ይበልጥ ተጎጂ እንደሚሆኑ የጀርመን የልማት ሚኒስትር አሳስበዋል። ሚኒስትር ስቬንያ ሹልሰ ለአንድ የጀርመን ጋዜጣ እንደገለፁት የስንዴ እጥረቱ በደሀ ሀገሮች ላይ ፖለቲካዊ አለመረጋጋትም ሊፈጥር ይችላል። ስለሆነም የዓለም አቀፍ የድጋፍ መርሃ ግብሮች ሌሎች አማራጮችን ማጤን እንዳለባቸው ሚንስትሯ ተናግረዋል።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
በመጀመሪያው የብልፅግና ፓርቲ ጉባኤ ላይ ለፓርቲው ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የተመረጡ አባላት ስም ዝርዝር!
1. ዶ/ር ዐቢይ አህመድ
2. አቶ አደም ፋራህ
3. አቶ ደመቀ መኮንን
4. አቶ ደስታ ሌዳሞ
5. ዶ/ር ፍጹም አሰፋ
6. አቶ አብርሃም ማርሻሎ
7. አቶ አሻድሊ ሀሰን
8. አቶ ጌታሁን አብዲሳ
9. አቶ ኡሙድ ኡጁሉ
10. አቶ ተንኳይ ጆክ
11. አቶ ኦርዲን በድሪ
12. አቶ አሪፍ መሃመድ
13. ዶ/ር አብርሃም በላይ
14. ዶ/ር ሊያ ታደሰ
15. ሀጂ አወል አርባ
16. ሀጅሊሴ አደም
17. አቶ ኤሌማ አቡበከር
18. ወ/ሮ ሀሊማ ሀሰን
19. አቶ ሙስጠፌ መሀመድ
20. አቶ አህመድ ሽዴ
21. ዶ/ር ነጋሽ ዋጌሾ
22. አቶ ፀጋዬ ማሞ
23. ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል
24. አቶ ተስፋዬ በልጅጌ
25. አቶ ርስቱ ይርዳው
26. አቶ ተስፋዬ ይገዙ
27. አቶ ሞገስ ባልቻ
28. አቶ ጥላሁን ከበደ
29. አቶ መለሰ ዓለሙ
30. አቶ ሽመልስ አብዲሳ
31. አቶ ፍቃዱ ተሰማ
32. ዶ/ር አለሙ ስሜ
33. ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ
34. አቶ አወሉ አብዲ
35. አቶ ሳዳት ነሻ
36. ወ/ሮ አዳነች አቤቤ
37. ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ
38. ዶ/ር ቢቂላ ሁሪሳ
39. ዶ/ር ይልቃል ከፍያለ
40. ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ
41. አቶ ተመስገን ጥሩነህ
42. አቶ መላኩ አለበል
43. ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ
44. ዶ/ር ሰማ ጥሩነህ
45. አቶ ግርማ የሺጥላ ናቸው።
@YeneTube @FikerAssefa
1. ዶ/ር ዐቢይ አህመድ
2. አቶ አደም ፋራህ
3. አቶ ደመቀ መኮንን
4. አቶ ደስታ ሌዳሞ
5. ዶ/ር ፍጹም አሰፋ
6. አቶ አብርሃም ማርሻሎ
7. አቶ አሻድሊ ሀሰን
8. አቶ ጌታሁን አብዲሳ
9. አቶ ኡሙድ ኡጁሉ
10. አቶ ተንኳይ ጆክ
11. አቶ ኦርዲን በድሪ
12. አቶ አሪፍ መሃመድ
13. ዶ/ር አብርሃም በላይ
14. ዶ/ር ሊያ ታደሰ
15. ሀጂ አወል አርባ
16. ሀጅሊሴ አደም
17. አቶ ኤሌማ አቡበከር
18. ወ/ሮ ሀሊማ ሀሰን
19. አቶ ሙስጠፌ መሀመድ
20. አቶ አህመድ ሽዴ
21. ዶ/ር ነጋሽ ዋጌሾ
22. አቶ ፀጋዬ ማሞ
23. ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል
24. አቶ ተስፋዬ በልጅጌ
25. አቶ ርስቱ ይርዳው
26. አቶ ተስፋዬ ይገዙ
27. አቶ ሞገስ ባልቻ
28. አቶ ጥላሁን ከበደ
29. አቶ መለሰ ዓለሙ
30. አቶ ሽመልስ አብዲሳ
31. አቶ ፍቃዱ ተሰማ
32. ዶ/ር አለሙ ስሜ
33. ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ
34. አቶ አወሉ አብዲ
35. አቶ ሳዳት ነሻ
36. ወ/ሮ አዳነች አቤቤ
37. ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ
38. ዶ/ር ቢቂላ ሁሪሳ
39. ዶ/ር ይልቃል ከፍያለ
40. ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ
41. አቶ ተመስገን ጥሩነህ
42. አቶ መላኩ አለበል
43. ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ
44. ዶ/ር ሰማ ጥሩነህ
45. አቶ ግርማ የሺጥላ ናቸው።
@YeneTube @FikerAssefa
❤1
አስደሳች ዜና 12ኛ ክፍል ለጨረሳቹ እና በመማር ላይ ላላቹ!!!
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን መቀበል ጀመረ!
በአሸባሪው የህወሓት ቡድን ከፍተኛ ውድመት ተፈፅሞበት ተዘግቶ የቆየው የወልድያ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት ተማሪዎቹን መቀበል መጀመሩን አስታውቋል።
ተማሪዎቹ ከጧት ጀምረው ወደ ግቢ በመግባት ላይ መሆናቸውን የጠቀሰው ዩኒቨርሲቲው የተቋሙ የጥበቃና ደህንነት ሰራተኞችም በግቢው በር ላይ አስፈላጊውን የፍተሻ ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጿል።
ቀደም ሲል ተማሪዎች መጋቢት 5 እና 6 ቀን 2014 ዓ.ም በቅጥር ግቢው በመገኘት እንዲመዘገቡ ጥሪ ያደረገው ዩኒቨርሲቲው በተጠቀሱት ቀናት ወልድያ ከተማ ለሚገቡ ተማሪዎች የትራንስፖርት አገልግሎት ያመቻቸ መሆኑን ገልጿል።
ተማሪዎች በተጠቀሱት ቀናት ከጧቱ 2:30 ጀምሮ በመናኸሪያ፣ በፒያሳ፣ በአዳጎና ጎንደርበር ፌርማታዎች ላይ በመገኘት አገልግሎት ማግኘት የሚችሉ መሆኑን አስታውቋል።
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
በአሸባሪው የህወሓት ቡድን ከፍተኛ ውድመት ተፈፅሞበት ተዘግቶ የቆየው የወልድያ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት ተማሪዎቹን መቀበል መጀመሩን አስታውቋል።
ተማሪዎቹ ከጧት ጀምረው ወደ ግቢ በመግባት ላይ መሆናቸውን የጠቀሰው ዩኒቨርሲቲው የተቋሙ የጥበቃና ደህንነት ሰራተኞችም በግቢው በር ላይ አስፈላጊውን የፍተሻ ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጿል።
ቀደም ሲል ተማሪዎች መጋቢት 5 እና 6 ቀን 2014 ዓ.ም በቅጥር ግቢው በመገኘት እንዲመዘገቡ ጥሪ ያደረገው ዩኒቨርሲቲው በተጠቀሱት ቀናት ወልድያ ከተማ ለሚገቡ ተማሪዎች የትራንስፖርት አገልግሎት ያመቻቸ መሆኑን ገልጿል።
ተማሪዎች በተጠቀሱት ቀናት ከጧቱ 2:30 ጀምሮ በመናኸሪያ፣ በፒያሳ፣ በአዳጎና ጎንደርበር ፌርማታዎች ላይ በመገኘት አገልግሎት ማግኘት የሚችሉ መሆኑን አስታውቋል።
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
ቻይና ለሩሲያ ወታደራዊ ድጋፍ የምትሰጥ ከሆነ ከባድ መዘዝ እንደሚጠብቃት አሜሪካ አስጠነቀቀች!
ሩሲያ በዩክሬን በምታካሂደው ወታደርዊ ዘመቻ ላይ ቻይና ድጋፍ የምትሰጥ ከሆነ ከባድ መዘዝ እንደሚጠብቃት የአሜሪካ ባለስልጣናትን በመጥቀስ የዩናይትድ ስቴትስ መገናኛ ብዙሃን በመዘገብ ላይ ይገኛሉ።ሩሲያ ዩክሬን ላይ ጦርነት ከጀመረች በኋላ ቻይና ወታደራዊ እርዳታ እንድትሰጣት ሩሲያ ጥያቄ ማቅረቧን ስማቸው ያልተጠቀሰ የአሜሪካ ባለስልጣናት መናገራቸው ተዘግቧል።
በዋሽንግተን የሚገኘው የቻይና ኤምባሲ በጉዳዩ ላይ መንም አይነት መርጃ እንደሌለው አስታውቋል።አሜሪካ ማስጠንቀቄያውን የሰጠችው በዛሬው ዕለት በጣልያን ይካሄዳል ተብሎ የሚጠበቀው የዩናይትድ ስቴትስ እና የቻይና ከፍተኛ ባለስልጣናት ስብሰባ በፊት ነው።
የሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ቤጂንግ የረዥም ጊዜ አጋሯ ለሆነችው ሞስኮ ምንም አይነት ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ድጋፍ እንዳደረገች በይፋ የታወቀ ነገር የለም።የአሜሪካ ባለስልጣናትን በመጥቀስ ሩሲያ ከቅርብ ቀናት ወዲህ በተለይም የሰው አልባ አውሮፕላኖችን ጨምሮ ወታደራዊ ቁሳቁሶችን ቻይና ድጋፍ እንድታደርግላት መጠየቋን እየተዘገበ ይገኛል።ለነዚህ የሩሲያ ጥያቄዎች ግን የቻይና ምላሽ ምን እንደሆነ እስከ አሁን የታወቀ ነገር የለም።
✍Asham
@YeneTube @FikerAssefa
ሩሲያ በዩክሬን በምታካሂደው ወታደርዊ ዘመቻ ላይ ቻይና ድጋፍ የምትሰጥ ከሆነ ከባድ መዘዝ እንደሚጠብቃት የአሜሪካ ባለስልጣናትን በመጥቀስ የዩናይትድ ስቴትስ መገናኛ ብዙሃን በመዘገብ ላይ ይገኛሉ።ሩሲያ ዩክሬን ላይ ጦርነት ከጀመረች በኋላ ቻይና ወታደራዊ እርዳታ እንድትሰጣት ሩሲያ ጥያቄ ማቅረቧን ስማቸው ያልተጠቀሰ የአሜሪካ ባለስልጣናት መናገራቸው ተዘግቧል።
በዋሽንግተን የሚገኘው የቻይና ኤምባሲ በጉዳዩ ላይ መንም አይነት መርጃ እንደሌለው አስታውቋል።አሜሪካ ማስጠንቀቄያውን የሰጠችው በዛሬው ዕለት በጣልያን ይካሄዳል ተብሎ የሚጠበቀው የዩናይትድ ስቴትስ እና የቻይና ከፍተኛ ባለስልጣናት ስብሰባ በፊት ነው።
የሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ቤጂንግ የረዥም ጊዜ አጋሯ ለሆነችው ሞስኮ ምንም አይነት ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ድጋፍ እንዳደረገች በይፋ የታወቀ ነገር የለም።የአሜሪካ ባለስልጣናትን በመጥቀስ ሩሲያ ከቅርብ ቀናት ወዲህ በተለይም የሰው አልባ አውሮፕላኖችን ጨምሮ ወታደራዊ ቁሳቁሶችን ቻይና ድጋፍ እንድታደርግላት መጠየቋን እየተዘገበ ይገኛል።ለነዚህ የሩሲያ ጥያቄዎች ግን የቻይና ምላሽ ምን እንደሆነ እስከ አሁን የታወቀ ነገር የለም።
✍Asham
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊሶችን ቁጥር 50 ሺሕ ለማድረስ ታቀደ!
የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን በከተማ ውስጥ ያለውን የነዋሪ ቁጥርና የፖሊስ ኃይል ምጥጥን ለማስተካከል፣ የከተማዋን ፖሊስ ቁጥር ወደ 50 ሺሕ ለማሳደግ መታቀዱን አስታወቀ፡፡ ኮሚሽኑ የፖሊስ ኃይሉን ቁጥር ለማሳደግ ተከታታይ ምልመላ እንደሚያደርግ አስታውቆ፣ በዚህ ዓመትም ከትግራይ ክልል ውጪ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች መልማዮችን መላኩን ገልጿል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከጊዜ ወደ ጊዜ የነዋሪዎቿ ቁጥር በከፍተኛ መጠን እየጨመረና አሁን ላይ 6.8 ሚሊዮን ነዋሪዎች እንደሚገኙባት አስታውቋል፡፡ ይሁንና በከተማ ውስጥ ያለው የፖሊስ ኃይል ይህንን የሕዝብ ቁጥር የማይመጥንና የብዙዎቹን የከተማዋን አከባቢዎች የማይሸፍን መሆኑን፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ፋሲካ ፋንታው ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
የከተማ አስተደዳሩ ያደረገው ጥናት እንደሚያመላክተው፣ በከተማዋ ውስጥ ያለው የፖሊስ ቁጥር በዓለም አቀፍ ደረጃ ካለው ምጣኔ በሁለት እጥፍ ያነሰ ነው፡፡ በዚህም የተነሳ አንድ የፖሊስ አባል እየሸፈነ ያለው ቢያንስ የአራት ፖሊሶችን ተግባርና ኃላፊነት ነው፡፡
እንደ ኮማንደር ፋሲካ ገለጻ፣ የፖሊስ ቁጥሩ ከነዋሪው ብዛት ጋር ካለመመጣጠኑም ባሻገር፣ በከተማዋ 11 ክፍላተ ከተማዎች ከሚገኙ 121 ወረዳዎች ውስጥ፣ የፖሊስ ጣቢያዎች ያሉት በ72 ያህሉ ብቻ ነው፡፡ ይህንን ችግር ለመቅረፍ በቀሪዎቹ ወረዳዎች ላይ አዳዲስ የፖሊስ ጣቢያዎችን ለመክፈት እየተሠራ መሆኑን ተናግረው፣ ጣቢያዎቹን ለመክፈት የሰው ኃይል፣ የቢሮና የቁሳቁስ ዝግጅት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
ኮማንደር ፋሲካ የከተማዋ ስፋትና የነዋሪው ብዛት በፍጥነት እየጨመረ መሆኑንና ችግሩን ለመቅረፍ፣ “አንድ ፖሊስ ስንት ሰዎችን መጠበቅ አለበት?” የሚለው ሳይንሳዊና ዓለም አቀፋዊ ደረጃዎችን መሠረት በማድረግ እየተሠራበት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በዚህ መሠረት ኮሚሽኑ ቢያንስ በአምስት ዓመት ውስጥ የአዲስ አበባ ፖሊስን ቁጥር 50 ሺሕ ለማድረስ ማቀዱን አስታውቀዋል፡፡
ሙሉ ዘገባ : http://bit.ly/3CF5UOV
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን በከተማ ውስጥ ያለውን የነዋሪ ቁጥርና የፖሊስ ኃይል ምጥጥን ለማስተካከል፣ የከተማዋን ፖሊስ ቁጥር ወደ 50 ሺሕ ለማሳደግ መታቀዱን አስታወቀ፡፡ ኮሚሽኑ የፖሊስ ኃይሉን ቁጥር ለማሳደግ ተከታታይ ምልመላ እንደሚያደርግ አስታውቆ፣ በዚህ ዓመትም ከትግራይ ክልል ውጪ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች መልማዮችን መላኩን ገልጿል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከጊዜ ወደ ጊዜ የነዋሪዎቿ ቁጥር በከፍተኛ መጠን እየጨመረና አሁን ላይ 6.8 ሚሊዮን ነዋሪዎች እንደሚገኙባት አስታውቋል፡፡ ይሁንና በከተማ ውስጥ ያለው የፖሊስ ኃይል ይህንን የሕዝብ ቁጥር የማይመጥንና የብዙዎቹን የከተማዋን አከባቢዎች የማይሸፍን መሆኑን፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ፋሲካ ፋንታው ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
የከተማ አስተደዳሩ ያደረገው ጥናት እንደሚያመላክተው፣ በከተማዋ ውስጥ ያለው የፖሊስ ቁጥር በዓለም አቀፍ ደረጃ ካለው ምጣኔ በሁለት እጥፍ ያነሰ ነው፡፡ በዚህም የተነሳ አንድ የፖሊስ አባል እየሸፈነ ያለው ቢያንስ የአራት ፖሊሶችን ተግባርና ኃላፊነት ነው፡፡
እንደ ኮማንደር ፋሲካ ገለጻ፣ የፖሊስ ቁጥሩ ከነዋሪው ብዛት ጋር ካለመመጣጠኑም ባሻገር፣ በከተማዋ 11 ክፍላተ ከተማዎች ከሚገኙ 121 ወረዳዎች ውስጥ፣ የፖሊስ ጣቢያዎች ያሉት በ72 ያህሉ ብቻ ነው፡፡ ይህንን ችግር ለመቅረፍ በቀሪዎቹ ወረዳዎች ላይ አዳዲስ የፖሊስ ጣቢያዎችን ለመክፈት እየተሠራ መሆኑን ተናግረው፣ ጣቢያዎቹን ለመክፈት የሰው ኃይል፣ የቢሮና የቁሳቁስ ዝግጅት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
ኮማንደር ፋሲካ የከተማዋ ስፋትና የነዋሪው ብዛት በፍጥነት እየጨመረ መሆኑንና ችግሩን ለመቅረፍ፣ “አንድ ፖሊስ ስንት ሰዎችን መጠበቅ አለበት?” የሚለው ሳይንሳዊና ዓለም አቀፋዊ ደረጃዎችን መሠረት በማድረግ እየተሠራበት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በዚህ መሠረት ኮሚሽኑ ቢያንስ በአምስት ዓመት ውስጥ የአዲስ አበባ ፖሊስን ቁጥር 50 ሺሕ ለማድረስ ማቀዱን አስታውቀዋል፡፡
ሙሉ ዘገባ : http://bit.ly/3CF5UOV
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ወደ ውጪ ሀገር ጉዞ የምታደርግ ግለሰብን ለመሸት የወጡ ሰባት ሰዎች በትራፊክ አደጋ ህይወታቸውን አጡ!
በአዲስ አበባ ከተማ ቅዳሜ ምሽት 3ሰዓት ከ30 ደቂቃ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለከተማ ወረዳ 11 ልዩ ቦታዉ ሀና ማርያም ቀለበት መንገድ ላይ ባጋጠመ የትራፊክ አደጋ ወደዉጪ ሀገር ጉዞዋን የምታደርግ ግለሰብን ጨምሮ ለመሸኘት የወጣ ቤተሰብ በአደጋውን ህይወታቸውን አጥተዋል።
በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 -35609 ዶልፊን ተሽከርካሪ ዉስጥ ከነበሩት 11 ተሳፋሪዎች ዉስጥ ሰባቱ ወዲያዉ ህይወታቸዉ ሲያልፍ አራት ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸዉ ህክምና እየተደረገላቸዉ ይገኛል። ከሟቾቹ ዉስጥም የምትሸኘዋ ተጓዥና እሷን ለመሸኘት ከኤርትራ የመጡ እናቷ ይገኙበታል ሲሉ የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
ቀሪዎቹ አምስት ሰዎች ቤተሰብና ጎረቤቶች ሲሆኑ ከአደጋዉ የተረፉት ከእናታቸዉ ጋር የሚጓዙ የ4 አመት እና የ6 አመት ህጻናት አንዲሁም አሽከርካሪዉ ናቸዉ ። ሟቾቹ ሁሉም ሴቶች ሲሆኑ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ሰራተኞች ተጎጂዎችን ከአካባቢዉ ማህበረሰብ ጋር በመተባበር ህክምና ቦታ እንዲደርሱ መደረጉን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ጨምረው ተናግረዋል።
[Bisrat FM]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ ቅዳሜ ምሽት 3ሰዓት ከ30 ደቂቃ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለከተማ ወረዳ 11 ልዩ ቦታዉ ሀና ማርያም ቀለበት መንገድ ላይ ባጋጠመ የትራፊክ አደጋ ወደዉጪ ሀገር ጉዞዋን የምታደርግ ግለሰብን ጨምሮ ለመሸኘት የወጣ ቤተሰብ በአደጋውን ህይወታቸውን አጥተዋል።
በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 -35609 ዶልፊን ተሽከርካሪ ዉስጥ ከነበሩት 11 ተሳፋሪዎች ዉስጥ ሰባቱ ወዲያዉ ህይወታቸዉ ሲያልፍ አራት ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸዉ ህክምና እየተደረገላቸዉ ይገኛል። ከሟቾቹ ዉስጥም የምትሸኘዋ ተጓዥና እሷን ለመሸኘት ከኤርትራ የመጡ እናቷ ይገኙበታል ሲሉ የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
ቀሪዎቹ አምስት ሰዎች ቤተሰብና ጎረቤቶች ሲሆኑ ከአደጋዉ የተረፉት ከእናታቸዉ ጋር የሚጓዙ የ4 አመት እና የ6 አመት ህጻናት አንዲሁም አሽከርካሪዉ ናቸዉ ። ሟቾቹ ሁሉም ሴቶች ሲሆኑ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ሰራተኞች ተጎጂዎችን ከአካባቢዉ ማህበረሰብ ጋር በመተባበር ህክምና ቦታ እንዲደርሱ መደረጉን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ጨምረው ተናግረዋል።
[Bisrat FM]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጸጥታ ችግር ለመፍጠር የሞከሩ ተማሪዎች እና በግቢው ግጭት ለመፍጠር የሞከሩ አካላት ከፀጥታ ሃይሎች ጋር በቅንጅት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ዩኒቨርሲቲው አስታውቋል፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና÷ የጸጥታ ሁኔታውን ለማረጋገጥ ከከተማው የጸጥታ ሃ አካላት ጋር በመሆን አስፈላጊው ጥበቃ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በዩኒቨርሲቲው የፀጥታ ችግር ለመፍጠር የሞከሩ ተማሪዎች እና በግቢው ግጭት ለመፍጠር የሞከሩ አካላት ከፀጥታ ሃይሎች ጋር በቅንጅት በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ጠቁመዋል፡፡
አሁን ላይም ዩኒቨርሲቲው መደበኛ የመማር ማስተማር ተግባሩ እንደቀጠለ መግለጻቸውን ከዩኒቨርሲቲው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና÷ የጸጥታ ሁኔታውን ለማረጋገጥ ከከተማው የጸጥታ ሃ አካላት ጋር በመሆን አስፈላጊው ጥበቃ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በዩኒቨርሲቲው የፀጥታ ችግር ለመፍጠር የሞከሩ ተማሪዎች እና በግቢው ግጭት ለመፍጠር የሞከሩ አካላት ከፀጥታ ሃይሎች ጋር በቅንጅት በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ጠቁመዋል፡፡
አሁን ላይም ዩኒቨርሲቲው መደበኛ የመማር ማስተማር ተግባሩ እንደቀጠለ መግለጻቸውን ከዩኒቨርሲቲው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የዲጂታል መታወቂያ በአምስት ክፍለ ከተሞች መሠጠት ተጀመረ!
በመዲናዋ ሕገ ወጥ የመታወቂያ ሥርጭትን ይከላከላል ተብሎ የታመነበት የዲጂታል መታወቂያ፣ በአምስት ክፍለ ከተሞች መሠጠት መጀመሩን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ ለአዲስ ማለዳ አስታወቀ።
በአዲስ አበባ በአራዳ፣ በቦሌ፣ በየካ፣ በጉለሌ እና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ሕገ ወጥ የመታወቂያ ሥርጭትን እና አሠራርን ይቀርፋል ተብሎ ዕምነት የተጣለበት የዲጂታል መታወቂያ ማተሚያ ማሽን እና መታወቂያ የመሥጠት ሥራ በቅርንጫፎቹ በኩል ሙሉ ለሙሉ መጀመራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ ከፍተኛ አማካሪ መላክ መኮንን ለአዲስ ማለዳ አስታውቀዋል።
ይህ ዲጂታል መታወቂያ በክፍለ ከተሞቹ ታትሞ ለነዋሪዎች መሰጠቱ ሕገ ወጥነትን ከመከላከል ጎን ለጎን፣ ደንበኞችን በፍጥነት ለማስተናገድ እንደሚረዳ እና በከተማዋ ነዋሪዎች መስተንግዶ ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመቅረፍ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተጠቁሟል።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
በመዲናዋ ሕገ ወጥ የመታወቂያ ሥርጭትን ይከላከላል ተብሎ የታመነበት የዲጂታል መታወቂያ፣ በአምስት ክፍለ ከተሞች መሠጠት መጀመሩን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ ለአዲስ ማለዳ አስታወቀ።
በአዲስ አበባ በአራዳ፣ በቦሌ፣ በየካ፣ በጉለሌ እና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ሕገ ወጥ የመታወቂያ ሥርጭትን እና አሠራርን ይቀርፋል ተብሎ ዕምነት የተጣለበት የዲጂታል መታወቂያ ማተሚያ ማሽን እና መታወቂያ የመሥጠት ሥራ በቅርንጫፎቹ በኩል ሙሉ ለሙሉ መጀመራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ ከፍተኛ አማካሪ መላክ መኮንን ለአዲስ ማለዳ አስታውቀዋል።
ይህ ዲጂታል መታወቂያ በክፍለ ከተሞቹ ታትሞ ለነዋሪዎች መሰጠቱ ሕገ ወጥነትን ከመከላከል ጎን ለጎን፣ ደንበኞችን በፍጥነት ለማስተናገድ እንደሚረዳ እና በከተማዋ ነዋሪዎች መስተንግዶ ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመቅረፍ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተጠቁሟል።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
ክፍት የስራ ማስታወቂያ
ድርጅታችን ዴሊቨሪ ሀዋሳ ከስር በተዘረዘረው ክፍት የስራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
መስፈርቶች
የስራው ዘርፍ፥ ፡ ሴልስ
ደመወዝ፥ ፡ ከ2000፡ 3000 እንዲሁም ጥቅማ ጥቅም ያለው።
የትምህርት ደረጃ፥ ፡ 10 ክፍል ያጠናቀቀች
አድራሻ፥ ፡ ሀዋሳ አዋሽ ህንፃ ላይ አራተኛ ፎቆ R12
ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈቶች የምታሟሉ አመልካቾች በአካል በመክረብ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ፩፭ ተከታታይ ቀናት በአካል ቀርባችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ።
Check our @Deliveryhawassa
ድርጅታችን ዴሊቨሪ ሀዋሳ ከስር በተዘረዘረው ክፍት የስራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
መስፈርቶች
የስራው ዘርፍ፥ ፡ ሴልስ
ደመወዝ፥ ፡ ከ2000፡ 3000 እንዲሁም ጥቅማ ጥቅም ያለው።
የትምህርት ደረጃ፥ ፡ 10 ክፍል ያጠናቀቀች
አድራሻ፥ ፡ ሀዋሳ አዋሽ ህንፃ ላይ አራተኛ ፎቆ R12
ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈቶች የምታሟሉ አመልካቾች በአካል በመክረብ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ፩፭ ተከታታይ ቀናት በአካል ቀርባችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ።
Check our @Deliveryhawassa
የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ማለፊያ ነጥብ ይፋ ሆነ።
የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታ ሳሙኤል (ዶ/ር) ለጋዜጠኞች የ12ኛ ክፍል መለቀቂያ ፈተና መቁረጫ ነጥብ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።
በሁለት ዙር ለተሰጠው የመልቀቂያ ፈተና የተሰጠው የማለፊያ ነጥብ የተለያየ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዚህም መሰረት በመጀመሪያ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤት የሚከተለውን ይመስላል
በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 363 ለሴት 351 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 351 ለሴት 339 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 300 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 380 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል።
በመጀመሪያው ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 300 ሆኗል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 264፣ ለሴት 254 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 254፣ ለሴት 250 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 250 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 280 እንደሆነ ተገልጿል።
በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 250 ሆኗል።
በሁለተኛ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤትም ይፋ የሆነ ሲሆን በዚህም መሰረት
በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 423 ለሴት 409 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 410 ለሴት 396 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 350 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 443 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል።
በሁለተኛ ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ350 በላይ መሆኑ ተነግሯል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 317 ፣ ለሴት 305 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 305፣ ለሴት 300 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 300 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 335 እንደሆነ ተገልጿል።
በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ 300 በላይ መሆኑም ተገለጿል።
ውጤቱ ለመጀመርያ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ600 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ500 የተያዘ መሆኑን እና በሁለተኛ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ700 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ600 የተያዘ መሆኑ ተገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታ ሳሙኤል (ዶ/ር) ለጋዜጠኞች የ12ኛ ክፍል መለቀቂያ ፈተና መቁረጫ ነጥብ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።
በሁለት ዙር ለተሰጠው የመልቀቂያ ፈተና የተሰጠው የማለፊያ ነጥብ የተለያየ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዚህም መሰረት በመጀመሪያ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤት የሚከተለውን ይመስላል
በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 363 ለሴት 351 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 351 ለሴት 339 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 300 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 380 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል።
በመጀመሪያው ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 300 ሆኗል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 264፣ ለሴት 254 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 254፣ ለሴት 250 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 250 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 280 እንደሆነ ተገልጿል።
በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 250 ሆኗል።
በሁለተኛ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤትም ይፋ የሆነ ሲሆን በዚህም መሰረት
በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 423 ለሴት 409 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 410 ለሴት 396 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 350 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 443 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል።
በሁለተኛ ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ350 በላይ መሆኑ ተነግሯል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 317 ፣ ለሴት 305 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 305፣ ለሴት 300 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 300 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 335 እንደሆነ ተገልጿል።
በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ 300 በላይ መሆኑም ተገለጿል።
ውጤቱ ለመጀመርያ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ600 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ500 የተያዘ መሆኑን እና በሁለተኛ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ700 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ600 የተያዘ መሆኑ ተገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
The dates are getting closer to witness one of Largest Global Hybrid Expo, which shall be taking place at the newly built state of the art library, Abrehot Library.
Exhibitors can take part either Onsite or Virtual, form any part of the globe.
List of Exhibitors:
Schools & Colleges/Universities
School Management Solution Providers
Software developers
App developers & Coders
Start-ups & TECH Entrepreneurs
Education Consultants
STEM Education Incubators,
Digital Service Providers
Education Material Producers & Suppliers
Digital Libraries
NGOs & related.
To Reserve Your Booth:
Call us:
+251 974 0820 36
+251 974 0820 37
Book online via:
www.backtoschoolafrica.com
Exhibitors can take part either Onsite or Virtual, form any part of the globe.
List of Exhibitors:
Schools & Colleges/Universities
School Management Solution Providers
Software developers
App developers & Coders
Start-ups & TECH Entrepreneurs
Education Consultants
STEM Education Incubators,
Digital Service Providers
Education Material Producers & Suppliers
Digital Libraries
NGOs & related.
To Reserve Your Booth:
Call us:
+251 974 0820 36
+251 974 0820 37
Book online via:
www.backtoschoolafrica.com