በ2011 ዓ.ም. በቻይና ሀገር ያላግባብ በአደንዛዥ እፅ ዝውውር ለተያዘችው ኢትዮጵያዊ ምክንያት የሆነችው ግለሰብ ተፈረደባት!
ናዝራዊት አበራ የተባለችውን ግለሰብ በታህሳስ ወር 2011 ዓ.ም. አደንዛዥ እፅ ወደ ቻይና እንድትወስድ ያደረገችው ስምረት ካሕሳይ የተባለች ተከሳሽ የ15 ዓመት እስራት እና የ100 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ተላለፈባት።
የፍትሕ ሚኒስቴር ዛሬ እንዳስታወቀው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት ተከሳሽ ቀርባ በሰጠችው ቃል መሰረት፣ “በዐቃቤ ህግ የተመሰረተብኝን ክስ ተረድቼዋለሁ፤ በተመሰረተብኝ ክስ ግን ጥፋተኛ አይደለሁም ምክንያቱም ለጓደኛዬ ለናዝራዊት አበራ የሰጠኋት የኮኬን ዕፅ ሳይሆን የፀጉር መታጠቢያ ሻምፖ ነው በዚህም ጥፋተኛ አይደለሁም” ስትል የእምነት ክህደት ቃሏን ሰጥታለች።
ይሁን እንጂ ዐቃቤ ህግ በተከሳሿ ላይ ስምንት የሰው እንዲሁም ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ከኢሜግሬሽን ዜግነትና የወሳኝ ኩነት ኤጄንሲ የሰነድ ማስረጃዎች አቅርቦ ጥፋተኛነቷን አሳይቷል ተብሏል። ተከሳሿም የሚቀጥለው ቀጠሮ ላይ ሳትገኝ ለጊዜው መሰወሯን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ተከሳሽ ስምረት ካህሳይ ልዩ ፍቃድ ሳይኖራት ህዳር 2011 ዓ.ም ወደ ሀገር ያስገባችውን 5 / አምስት / በሻምፖ እቃ የታሸገ ኮኬን ዕፅ ተበዳይ ናዝራዊት አበራ የተባለች ጓደኛዋን ወደ ቻይና ሀገር አብረን እንሂድ ብላ በማግባባት ቪዛ እና የአየር ትኬት ካስጨረሰች በኋላ ታህሳስ 11/2011 ዓ.ም ለናዝራዊት አበራ የሂውማን ሄር ማጠቢያ ነው ቻይና ውሰጅልኝ ብላ ከላከቻት በኋላ እርሷግን የአባቷን ሞት ምክንያት በማድረግ መቅረቷም ተገልጿል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት የቅጣት ውሳኔውን ባስተላለፈበት የካቲት 25 ቀን 2014 ዓ.ም. ግለሰቦች እና ተቋማት ተከሳሿን ባገኙበት ወቅት ጥቆማ እንዲያደርጉ እንዲሁም ፌደራል ፖሊስ ተከሳሿን አፈላልጎ ለማረሚያ ቤት እንዲያስረክብ በማዘዝ መዝገቡን ዘግቷል።
@YeneTube @FikerAssefa
ናዝራዊት አበራ የተባለችውን ግለሰብ በታህሳስ ወር 2011 ዓ.ም. አደንዛዥ እፅ ወደ ቻይና እንድትወስድ ያደረገችው ስምረት ካሕሳይ የተባለች ተከሳሽ የ15 ዓመት እስራት እና የ100 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ተላለፈባት።
የፍትሕ ሚኒስቴር ዛሬ እንዳስታወቀው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት ተከሳሽ ቀርባ በሰጠችው ቃል መሰረት፣ “በዐቃቤ ህግ የተመሰረተብኝን ክስ ተረድቼዋለሁ፤ በተመሰረተብኝ ክስ ግን ጥፋተኛ አይደለሁም ምክንያቱም ለጓደኛዬ ለናዝራዊት አበራ የሰጠኋት የኮኬን ዕፅ ሳይሆን የፀጉር መታጠቢያ ሻምፖ ነው በዚህም ጥፋተኛ አይደለሁም” ስትል የእምነት ክህደት ቃሏን ሰጥታለች።
ይሁን እንጂ ዐቃቤ ህግ በተከሳሿ ላይ ስምንት የሰው እንዲሁም ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ከኢሜግሬሽን ዜግነትና የወሳኝ ኩነት ኤጄንሲ የሰነድ ማስረጃዎች አቅርቦ ጥፋተኛነቷን አሳይቷል ተብሏል። ተከሳሿም የሚቀጥለው ቀጠሮ ላይ ሳትገኝ ለጊዜው መሰወሯን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ተከሳሽ ስምረት ካህሳይ ልዩ ፍቃድ ሳይኖራት ህዳር 2011 ዓ.ም ወደ ሀገር ያስገባችውን 5 / አምስት / በሻምፖ እቃ የታሸገ ኮኬን ዕፅ ተበዳይ ናዝራዊት አበራ የተባለች ጓደኛዋን ወደ ቻይና ሀገር አብረን እንሂድ ብላ በማግባባት ቪዛ እና የአየር ትኬት ካስጨረሰች በኋላ ታህሳስ 11/2011 ዓ.ም ለናዝራዊት አበራ የሂውማን ሄር ማጠቢያ ነው ቻይና ውሰጅልኝ ብላ ከላከቻት በኋላ እርሷግን የአባቷን ሞት ምክንያት በማድረግ መቅረቷም ተገልጿል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት የቅጣት ውሳኔውን ባስተላለፈበት የካቲት 25 ቀን 2014 ዓ.ም. ግለሰቦች እና ተቋማት ተከሳሿን ባገኙበት ወቅት ጥቆማ እንዲያደርጉ እንዲሁም ፌደራል ፖሊስ ተከሳሿን አፈላልጎ ለማረሚያ ቤት እንዲያስረክብ በማዘዝ መዝገቡን ዘግቷል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
ዩክሬን ኃይሏን ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተልዕኮዎች ልታስወጣ መሆኑ ተገለጸ፡፡
ዩክሬን ከሩሲያ ጋር እያደረገች ላለው ውጊያ አቅሟን ለማጠናከር በአፍሪካ እና በአውሮፓ ፤ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ የሚገኙ ወታደሮቿን ፤ ትጥቅዋን እና ሄሊኮፕተሮችን ልታስወጣ ነው ሲል ሮይተርስ ዘግቧል።
የዩክሬን መገናኛ ብዙሃን እንዳስታቀው ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በተባበሩት መንግስታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ ያሉ የዩክሬን ወታደሮች እና መኮንኖች ወደ አገራቸው በመመለስ ከሩሲያ ጋር የገጠሙትን ጦርነት እንዲቀላቀሉ ትእዛዝ ሰጥተዋል ብሏል፡፡
ትልቁ የዩክሬናውያን ወታደራዊ ኃይል በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ ሞኑጎ ውስጥ እያገለገሉ ሲሆን፤ሌሎች ዩክሬናውያን በማሊ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳን፣ ቆጵሮስ እና ኮሶቮ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ተልዕኮዎች ለመወጣት በተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ ይገኛሉ።ይሁን እንጂ የዩክሬን መንግስት ባቀረበው ጥሪ መሰረት ወታደሮቹ ትጥቃቸውን እና ሄሊኮፕተሮችን ይዘው ወደ ዩክሬን ሊመለሱ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል።
✍Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ዩክሬን ከሩሲያ ጋር እያደረገች ላለው ውጊያ አቅሟን ለማጠናከር በአፍሪካ እና በአውሮፓ ፤ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ የሚገኙ ወታደሮቿን ፤ ትጥቅዋን እና ሄሊኮፕተሮችን ልታስወጣ ነው ሲል ሮይተርስ ዘግቧል።
የዩክሬን መገናኛ ብዙሃን እንዳስታቀው ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በተባበሩት መንግስታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ ያሉ የዩክሬን ወታደሮች እና መኮንኖች ወደ አገራቸው በመመለስ ከሩሲያ ጋር የገጠሙትን ጦርነት እንዲቀላቀሉ ትእዛዝ ሰጥተዋል ብሏል፡፡
ትልቁ የዩክሬናውያን ወታደራዊ ኃይል በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ ሞኑጎ ውስጥ እያገለገሉ ሲሆን፤ሌሎች ዩክሬናውያን በማሊ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳን፣ ቆጵሮስ እና ኮሶቮ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ተልዕኮዎች ለመወጣት በተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ ይገኛሉ።ይሁን እንጂ የዩክሬን መንግስት ባቀረበው ጥሪ መሰረት ወታደሮቹ ትጥቃቸውን እና ሄሊኮፕተሮችን ይዘው ወደ ዩክሬን ሊመለሱ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል።
✍Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የዩክሬን መንግስት ስንዴን ጨምሮ የምግብ አቅርቦቶች ለውጭ ገበያ እንዳይዉሉ እገዳ አስተላለፈ!
ዩክሬን ከሩሲያ ጋር በገባችበት ጦርነት ሳቢያ ሊከሰት የሚችለውን ሰብዓዊ ቀውስ ለመቋቋም ያግዛል በማለት የግብርና እና የአርብቶ አደር ውጤቶች ለውጭ ገበያ እንዳይዉሉ ወሰነች።ታይም የዜና ምንጭ እንደዘገበው በግብርና ምርቶች ለዓለም አቀፍ የምግብ ዋስትና ተደራሽነት ከፍተኛ ሚና ያላት ዩክሬን በወቅታዊው ጦርነት ሳቢያ ምርቶች ለየትኛውም ሀገር እንዳይቀርቡ አሳስባለች።
ስንዴ፣ አጃ፣ ማሽላ፣ ስኳር፣ የቁም እንስሳትና ተዋፅኦዎቻቸውን ጨምሮ ለምግብነት የሚያገለግሉ በርካታ ምርቶችን ነው የዩክሬን የግብርና እና የምግብ ፖሊሲ ሚኒስቴር ያገደው።ይህ ውሳኔ ከዩክሬን ምርቶችን የሚያስገቡ የአውሮፓ፣ እስያ እና የአፍሪካ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ጫና ያሳድራል ተብሎ ተሰግቷል።
ስንዴ ለውጭ ገበያ በማቅረብ ከዓለም አምስተኛ ደረጃን የያዘችው ዩክሬን እ.ኤ.አ በ2019 ከ3 ቢልየን ዶላር በላይ በውጪ ንግድ ከስንዴ ማግኘት ችላለች። ግብፅ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ቱርክ እና ቱኒዝያ ደግሞ ዋነኛ የዩክሬን ስንዴ ደንበኞች ናቸው። ኢትዮጵያም ከዩክሬን ከፍተኛ የስንዴ ግዢ ከሚፈፅሙ ሀገራት አንዷ ስትሆን በ 2018 እአአ የ43 ሚልየን ዶላር ስንዴ ገዝታለች።
[@AddisZeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
ዩክሬን ከሩሲያ ጋር በገባችበት ጦርነት ሳቢያ ሊከሰት የሚችለውን ሰብዓዊ ቀውስ ለመቋቋም ያግዛል በማለት የግብርና እና የአርብቶ አደር ውጤቶች ለውጭ ገበያ እንዳይዉሉ ወሰነች።ታይም የዜና ምንጭ እንደዘገበው በግብርና ምርቶች ለዓለም አቀፍ የምግብ ዋስትና ተደራሽነት ከፍተኛ ሚና ያላት ዩክሬን በወቅታዊው ጦርነት ሳቢያ ምርቶች ለየትኛውም ሀገር እንዳይቀርቡ አሳስባለች።
ስንዴ፣ አጃ፣ ማሽላ፣ ስኳር፣ የቁም እንስሳትና ተዋፅኦዎቻቸውን ጨምሮ ለምግብነት የሚያገለግሉ በርካታ ምርቶችን ነው የዩክሬን የግብርና እና የምግብ ፖሊሲ ሚኒስቴር ያገደው።ይህ ውሳኔ ከዩክሬን ምርቶችን የሚያስገቡ የአውሮፓ፣ እስያ እና የአፍሪካ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ጫና ያሳድራል ተብሎ ተሰግቷል።
ስንዴ ለውጭ ገበያ በማቅረብ ከዓለም አምስተኛ ደረጃን የያዘችው ዩክሬን እ.ኤ.አ በ2019 ከ3 ቢልየን ዶላር በላይ በውጪ ንግድ ከስንዴ ማግኘት ችላለች። ግብፅ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ቱርክ እና ቱኒዝያ ደግሞ ዋነኛ የዩክሬን ስንዴ ደንበኞች ናቸው። ኢትዮጵያም ከዩክሬን ከፍተኛ የስንዴ ግዢ ከሚፈፅሙ ሀገራት አንዷ ስትሆን በ 2018 እአአ የ43 ሚልየን ዶላር ስንዴ ገዝታለች።
[@AddisZeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የተከሰተውን የዘይት አቅርቦትና ስርጭት ችግሮችን በአፋጣኝ ለመፍታት እየተሰራ መሆኑን የንግድ ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ መስፍን አሰፋ አስታወቁ።
በሸማች ህብረት ስራ ማህበራት በኩል እንዲቀርብ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡አቶ መስፍን አሰፋ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በከተማ ደረጃ የዘይት ምርት አቅርቦት ማነስና የዋጋ መጨመር መከሰቱን ጠቅሰው ነገር ግን የምርቱን አቅርቦትና ስርጭት ችግሮች ለመፍታት ከሀገር ውስጥ ዘይት አምራቾችና አቅራቢዎች ጋር በመቀናጀት እየተሰራ ነው።
ምርቱ ከዛሬ ጀምሮ በሸማች ህብረት ስራ ማህበራት ሱቆች በኩል ይሰራጫል። ፌቤላ የዘይት አምራች ድርጅት 3.1 ሚሊዮን ሊትር፤ሸሙ የዘይት አምራች ድርጅት 1.5 ሚሊዮን ሊትር፤የኢትዮጵያ ንግድ ስራ ኮርፖሬሽን 2 ሚሊዮን ሊትር ፓልም ዘይት በማቅረብ ስርጭት እንደሚካሄድ ተናግረዋል።
የፌቤላ የዘይት ምርት 5 ሊትር ዋጋ 470 ብር፤ ሸሙ የዘይት ምርት 5 ሊትር ዋጋ 472 ብር እንዲሁም የኢትዮጵያ ንግድ ስራ ኮርፖሬሽን የዘይት ምርት 5 ሊትር ዋጋ 412 ብር መሆኑን ጠቁመው ከሰኞ ጀምሮ እስከዛሬ እሮብ ድረስ 674ሺ ሊትር ዘይት በህብረት ስራ ማህበራት በኩል እየተሰራጨ መሆኑን ጨምረው አስረድተዋል፡፡የሸገር ዳቦ ፍብሪካ በአዲስ መልክ ወደ ምርት የገባ ሲሆን የከተማ አስተዳደሩ የገንዘብ ድጎማ በማድረግ ምርቱ መጀመሩን ተጠቅሰዋል፡፡
[EPA]
@YeneTube @FikerAssefa
በሸማች ህብረት ስራ ማህበራት በኩል እንዲቀርብ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡አቶ መስፍን አሰፋ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በከተማ ደረጃ የዘይት ምርት አቅርቦት ማነስና የዋጋ መጨመር መከሰቱን ጠቅሰው ነገር ግን የምርቱን አቅርቦትና ስርጭት ችግሮች ለመፍታት ከሀገር ውስጥ ዘይት አምራቾችና አቅራቢዎች ጋር በመቀናጀት እየተሰራ ነው።
ምርቱ ከዛሬ ጀምሮ በሸማች ህብረት ስራ ማህበራት ሱቆች በኩል ይሰራጫል። ፌቤላ የዘይት አምራች ድርጅት 3.1 ሚሊዮን ሊትር፤ሸሙ የዘይት አምራች ድርጅት 1.5 ሚሊዮን ሊትር፤የኢትዮጵያ ንግድ ስራ ኮርፖሬሽን 2 ሚሊዮን ሊትር ፓልም ዘይት በማቅረብ ስርጭት እንደሚካሄድ ተናግረዋል።
የፌቤላ የዘይት ምርት 5 ሊትር ዋጋ 470 ብር፤ ሸሙ የዘይት ምርት 5 ሊትር ዋጋ 472 ብር እንዲሁም የኢትዮጵያ ንግድ ስራ ኮርፖሬሽን የዘይት ምርት 5 ሊትር ዋጋ 412 ብር መሆኑን ጠቁመው ከሰኞ ጀምሮ እስከዛሬ እሮብ ድረስ 674ሺ ሊትር ዘይት በህብረት ስራ ማህበራት በኩል እየተሰራጨ መሆኑን ጨምረው አስረድተዋል፡፡የሸገር ዳቦ ፍብሪካ በአዲስ መልክ ወደ ምርት የገባ ሲሆን የከተማ አስተዳደሩ የገንዘብ ድጎማ በማድረግ ምርቱ መጀመሩን ተጠቅሰዋል፡፡
[EPA]
@YeneTube @FikerAssefa
የአፍሪቃ ቀንድ ሐገራትን በመታዉ ድርቅ ለረሐብ ለተጋለጠዉ ሕዝብ መርጃ የሚያዉለዉ ገንዘብ አለማግኘቱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታወቀ።ድርጅቱ እንደሚለዉ ለጋሹ ዓለም ትኩረቱን ዩክሬን ጦርነት ላይ በማድረጉ ርዳታ ፈላጊዉ ሕዝብ ለከፋ ችግር እንዳይጋለጥ ያሰጋል።ድርጅቱ በተለይ ለሶማሊያ ችግረኞች መርጃ ከጠየቀዉ ገንዘብ እስካሁን ያገኘዉ 3 ከመቶ ብቻ ነዉ።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
አስደሳች ዜና 12ኛ ክፍል ለጨረሳቹ እና በመማር ላይ ላላቹ!!!
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
📌 ጥራት ያላቸው ኦሪጅናል የኤሌክትሮኒክስ ምርቶች ከ T-max ኤሌክትሮኒክስ
ምርቶችቻችንን ለማየት ሊንኩን ይጠቀሙ:
👉 https://tttttt.me/tmaxelct
📌 አድራሻ: መርካቶ ይርጋ ሃይሌ ህንፃ ምድር ላይ ሱቅ ቁጥር፡ ጂ-96
ብዛት ለማዘዝ ይደውሉ
🤳 09 33 11 11 11 / 09 74 55 55 55
ምርቶችቻችንን ለማየት ሊንኩን ይጠቀሙ:
👉 https://tttttt.me/tmaxelct
📌 አድራሻ: መርካቶ ይርጋ ሃይሌ ህንፃ ምድር ላይ ሱቅ ቁጥር፡ ጂ-96
ብዛት ለማዘዝ ይደውሉ
🤳 09 33 11 11 11 / 09 74 55 55 55
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የዩክሬን እና የሩሲያ የሰላም ተደራዳሪዎች ቱርክ ደረሱ!
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ እና የዩክሬኑ አቻቸው ድምትሮ ኩሌባ ለሰላም ንግግር ቱርክ ተገኝተዋል።
ፕሬዝደንት ረሲፕ ታይፕ ኤርዶሃን በሚገኙበት ሁለቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በቱርኳ አንታላይ ከተማ ዛሬ ንግግር ይጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የቱርኩ ፕሬዝደንት ሁለቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የሚያደርጉት ውይይት፤ “ቋሚ ለሆነ የተኩስ አቁም ስምምነት በር የሚከፍት ይሆናል ብዬ ተስፋ አድርጋለሁ” ብለዋል።
ሩሲያ በዩክሬን ላይ የከፈተችው ወታደራዊ ወረራ ሁለት ሳምንት ሊሞላው የተቃረበ ቢሆንም እስካሁን የተደረጉ ንግግሮች ጦርነቱን ለማስቆም የሚያስችል ይህ ነው የሚባል ውጤት አላስገኙም።
@YeneTube @FikerAssefa
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ እና የዩክሬኑ አቻቸው ድምትሮ ኩሌባ ለሰላም ንግግር ቱርክ ተገኝተዋል።
ፕሬዝደንት ረሲፕ ታይፕ ኤርዶሃን በሚገኙበት ሁለቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በቱርኳ አንታላይ ከተማ ዛሬ ንግግር ይጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የቱርኩ ፕሬዝደንት ሁለቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የሚያደርጉት ውይይት፤ “ቋሚ ለሆነ የተኩስ አቁም ስምምነት በር የሚከፍት ይሆናል ብዬ ተስፋ አድርጋለሁ” ብለዋል።
ሩሲያ በዩክሬን ላይ የከፈተችው ወታደራዊ ወረራ ሁለት ሳምንት ሊሞላው የተቃረበ ቢሆንም እስካሁን የተደረጉ ንግግሮች ጦርነቱን ለማስቆም የሚያስችል ይህ ነው የሚባል ውጤት አላስገኙም።
@YeneTube @FikerAssefa
39 በርሜል ነዳጅ በህገ ወጥ መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ አሶሳ ከተማ ለማጓጓዝ የሞከሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለፀ!
የንግድ ህጉን በመተላለፍ 39 በርሜል ነዳጅ በህገ ወጥ መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ አሶሳ ከተማ ለማጓጓዝ የሞከሩ ግለሰቦች በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ።
የካቲት 27 ቀን 2014 ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ገርጂ ማርያም አካባቢ ከሚገኝ ኖክ ፈጣን ነዳጅ ማደያ በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 A 10734 አ/አ በሆነ ኤፍ ኤስ አር ተሽከርካሪ 39 በርሜል ነዳጅ በመቅዳት ጭነው ከአዲስ አበባ ወደ አሶሳ ከተማ ሲያጓጉዙ የተገኙ ኹለት ግለሰቦችና ሁለት የማደያው ሰራተኞች ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ ተይዘዋል፡፡
ፖሊስ ከህብረተሰቡ የደረሰውን ጥቆማ መሰረት በማድረግ በተወሰደ እርምጃ 50 በርሜል ተዘጋጅቶ ሰላሳ ዘጠኝ በርሜል ናፍጣ ተቀድቶ የተያዘ ሲሆን፤ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸው አራት ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን እና የተያዘው ነዳጅ 7 ሺህ 800 ሊትር መሆኑን ተረግጧል፡፡
ግለሰቦቹ መመሪያ ቁጥር 12/2011 አንቀፅ 14 ንዑስ አንቀፅ 16 ላይ የተደነገገውን በመተላለፍ ምንም አይነት ህጋዊ ሰነድ ሳይኖራቸው ነዳጁን ለማጓጓዝ ሲሞክሩ መያዛቸውን ነው ፖሊስ ያስታወቀው።
ህገወጦቹ በህብረተሰቡ ጥቆማ መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልፆ፤ መሰል ድርጊቶች ሲያጋጥሙ ጥቆማ የመስጠት ልምዱን አጠናክሮ እንዲቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
ከአገር ጥቅም ይልቅ የግል ጥቅማቸውን በማስቀደም የሚንቀሳቀሱ አካላት እና በህጋዊ የንግድ ፍቃድ ሽፋን ህገወጥ ተግባር የሚፈፅሙ ግለሰቦችም ሆኑ ተቋማት ከህገወጥ ተግባራቸው ሊታቀቡ እንዲሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል።
@YeneTube
የንግድ ህጉን በመተላለፍ 39 በርሜል ነዳጅ በህገ ወጥ መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ አሶሳ ከተማ ለማጓጓዝ የሞከሩ ግለሰቦች በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ።
የካቲት 27 ቀን 2014 ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ገርጂ ማርያም አካባቢ ከሚገኝ ኖክ ፈጣን ነዳጅ ማደያ በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 A 10734 አ/አ በሆነ ኤፍ ኤስ አር ተሽከርካሪ 39 በርሜል ነዳጅ በመቅዳት ጭነው ከአዲስ አበባ ወደ አሶሳ ከተማ ሲያጓጉዙ የተገኙ ኹለት ግለሰቦችና ሁለት የማደያው ሰራተኞች ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ ተይዘዋል፡፡
ፖሊስ ከህብረተሰቡ የደረሰውን ጥቆማ መሰረት በማድረግ በተወሰደ እርምጃ 50 በርሜል ተዘጋጅቶ ሰላሳ ዘጠኝ በርሜል ናፍጣ ተቀድቶ የተያዘ ሲሆን፤ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸው አራት ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን እና የተያዘው ነዳጅ 7 ሺህ 800 ሊትር መሆኑን ተረግጧል፡፡
ግለሰቦቹ መመሪያ ቁጥር 12/2011 አንቀፅ 14 ንዑስ አንቀፅ 16 ላይ የተደነገገውን በመተላለፍ ምንም አይነት ህጋዊ ሰነድ ሳይኖራቸው ነዳጁን ለማጓጓዝ ሲሞክሩ መያዛቸውን ነው ፖሊስ ያስታወቀው።
ህገወጦቹ በህብረተሰቡ ጥቆማ መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልፆ፤ መሰል ድርጊቶች ሲያጋጥሙ ጥቆማ የመስጠት ልምዱን አጠናክሮ እንዲቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
ከአገር ጥቅም ይልቅ የግል ጥቅማቸውን በማስቀደም የሚንቀሳቀሱ አካላት እና በህጋዊ የንግድ ፍቃድ ሽፋን ህገወጥ ተግባር የሚፈፅሙ ግለሰቦችም ሆኑ ተቋማት ከህገወጥ ተግባራቸው ሊታቀቡ እንዲሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል።
@YeneTube
ዛሬ በአለም አቀፍ ደረጃ የዓለም የኩላሊት ቀን ታስቦ ይውላል!
👉አጫጭር መረጃዎች ኩላሊትን በተመለከተ
~የኩላሊት አማካይ ክብደት የሞባይል ስልክ ያሃ ሲሆን ከ114 እስከ-170 ግራም ድረስ ይመዝናል።ምንም እንኳን ኩላሊቱ በአማካይ የሰውነት ክብደት 0.5% ብቻ ቢይዝም ከጉበት በመቀጠል ከሌሎች የአካል ክፍሎች የበለጠ ደም ይቀበላል፤ወይም በመጠን የኮምፒውተር ማውዝ ያክላሉ።
~በአለም ከሚኖረው ህዝብ 10በመቶ የሚሆነው በከባድ የኩላሊት በሽታ የተጠቃ ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ደግሞ ተመጣጣኝ ህክምና ባለማግኘት በየዓመቱ ህይወታቸውን ያጣሉ።
~እ.ኤ.አ በ1990 በዓለም አቀፍ ደረጃ የኩላሊት በሽታ 27ኛው ገዳይ በሽታ የነበረ ሲሆን በ2010 ማብቂያ ግን ወደ 18ኛ ደረጃ ከፍ ብሏል።
~አብዛኛው የሰው ልጅ የተወለደው ከ2 ኩላሊት ጋር ነው። ነገር ግን ካሉት ኩላሊት አንዱ ቢወጣ ሰውነቱ የኩላሊት ስራን የሚያጣው 25% ብቻ ነው። በከፍተኛ የደም ግፊት (hypertrophy) ምክንያት የቀረው ኩላሊት ሰውነቱን ማቆየቱን ይቀጥላል።
~በአሁኑ ጊዜ በዓለም ዙሪያ ከ2 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በህይወት ለመቆየት የኩላሊት እጥበት(ዳያሊስስ) ወይም የኩላሊት ንቅለ ተከላ ህክምና ያደርጋሉ።ነገር ግን ይህ ቁጥር ህክምና ከሚያስፈልጋቸው ሰዎች 10% ብቻ ይወክላል።
~ኩላሊት በቀን ወደ 170 ሊትር ደም ያጣራል።ከመጠን በላይ ኢቡፕሮፌን እና አስፕሪን ኩላሊትን ሊጎዱ ይችላሉ።
~ኩላሊት ሰውነታችን ውስጥ የሆርሞን ምርት፣ የንጥረ ነገሮች ምርትና ምጣኔ፣ የሰውነት ፈሳሽን ምጣኔ እና ሌሎች በርካታ ተግባራትን ያከናውናል።
~በአለም የተመዘገበው ትልቁ የኩላሊት ጠጠር 1.1 ኪሎ ግራም ይመዝናል።
[Bisrat FM]
@YeneTube @FikerAssefa
👉አጫጭር መረጃዎች ኩላሊትን በተመለከተ
~የኩላሊት አማካይ ክብደት የሞባይል ስልክ ያሃ ሲሆን ከ114 እስከ-170 ግራም ድረስ ይመዝናል።ምንም እንኳን ኩላሊቱ በአማካይ የሰውነት ክብደት 0.5% ብቻ ቢይዝም ከጉበት በመቀጠል ከሌሎች የአካል ክፍሎች የበለጠ ደም ይቀበላል፤ወይም በመጠን የኮምፒውተር ማውዝ ያክላሉ።
~በአለም ከሚኖረው ህዝብ 10በመቶ የሚሆነው በከባድ የኩላሊት በሽታ የተጠቃ ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ደግሞ ተመጣጣኝ ህክምና ባለማግኘት በየዓመቱ ህይወታቸውን ያጣሉ።
~እ.ኤ.አ በ1990 በዓለም አቀፍ ደረጃ የኩላሊት በሽታ 27ኛው ገዳይ በሽታ የነበረ ሲሆን በ2010 ማብቂያ ግን ወደ 18ኛ ደረጃ ከፍ ብሏል።
~አብዛኛው የሰው ልጅ የተወለደው ከ2 ኩላሊት ጋር ነው። ነገር ግን ካሉት ኩላሊት አንዱ ቢወጣ ሰውነቱ የኩላሊት ስራን የሚያጣው 25% ብቻ ነው። በከፍተኛ የደም ግፊት (hypertrophy) ምክንያት የቀረው ኩላሊት ሰውነቱን ማቆየቱን ይቀጥላል።
~በአሁኑ ጊዜ በዓለም ዙሪያ ከ2 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በህይወት ለመቆየት የኩላሊት እጥበት(ዳያሊስስ) ወይም የኩላሊት ንቅለ ተከላ ህክምና ያደርጋሉ።ነገር ግን ይህ ቁጥር ህክምና ከሚያስፈልጋቸው ሰዎች 10% ብቻ ይወክላል።
~ኩላሊት በቀን ወደ 170 ሊትር ደም ያጣራል።ከመጠን በላይ ኢቡፕሮፌን እና አስፕሪን ኩላሊትን ሊጎዱ ይችላሉ።
~ኩላሊት ሰውነታችን ውስጥ የሆርሞን ምርት፣ የንጥረ ነገሮች ምርትና ምጣኔ፣ የሰውነት ፈሳሽን ምጣኔ እና ሌሎች በርካታ ተግባራትን ያከናውናል።
~በአለም የተመዘገበው ትልቁ የኩላሊት ጠጠር 1.1 ኪሎ ግራም ይመዝናል።
[Bisrat FM]
@YeneTube @FikerAssefa
በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ያሉ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የቅድመ ዝግጅት ስራ መጠናቀቁን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ!
በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ያሉ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ሲካሄድ የቆየው የቅድመ ዝግጅት ስራ መጠናቀቁን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፡- በሳዑዲ አረቢያ በተለያዩ እስር ቤቶችና ካምፖች በፈታኝ ሁኔታ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ለመመለስ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል፡፡
የዜጎቹን ማንነት፤ ያሉበትንሁኔታና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎችን ለማጠናቀር ወደ ስፍራው አቅንቶ የነበረው ልዑክ መመለሱን ያወሱት ቃል አቀባዩ፤ ዜጎቹን መመለስ የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን አስታውቀዋል፡፡ለተልዕኮው ስኬትም በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የሚመራ 16 ተቋማትን ያካተተ ብሄራዊ ኮሚቴ ተቋቁሞ ጉዳዩን በትኩረት እየተከታተለው ስለመሆኑ አንስተዋል፡፡
በተያያዘም ዩክሬንና ሩሲያ በመካከላቸው የተፋፋመው ግጭትና ውጊያ በማቆም ዓለም ጎራ ለይቶ እንዲዋጋ ከሚያነሳሱ ትንኮሳዎች እንዲቆጠቡ ኢትዮጵያ ጥሪ ማቅረቧን አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገልፀዋል፡፡በሁለቱ ሀገራት መካከል የተካረረው ሁኔታ ዓለምን በጎራ ወደ ውጊያ እንዳያስገባ ተንኳሽ እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ ችግሩ የንግግር መፍትሄ እንዲበጅለት ኢትዮጵያ ፅኑ አቋም አላት ብለዋል አምባሳደር ዲና።ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ያንፀባረቀችው ድምፅ አልባ ውሳኔም የዚሁ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ያሉ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ሲካሄድ የቆየው የቅድመ ዝግጅት ስራ መጠናቀቁን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፡- በሳዑዲ አረቢያ በተለያዩ እስር ቤቶችና ካምፖች በፈታኝ ሁኔታ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ለመመለስ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል፡፡
የዜጎቹን ማንነት፤ ያሉበትንሁኔታና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎችን ለማጠናቀር ወደ ስፍራው አቅንቶ የነበረው ልዑክ መመለሱን ያወሱት ቃል አቀባዩ፤ ዜጎቹን መመለስ የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን አስታውቀዋል፡፡ለተልዕኮው ስኬትም በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የሚመራ 16 ተቋማትን ያካተተ ብሄራዊ ኮሚቴ ተቋቁሞ ጉዳዩን በትኩረት እየተከታተለው ስለመሆኑ አንስተዋል፡፡
በተያያዘም ዩክሬንና ሩሲያ በመካከላቸው የተፋፋመው ግጭትና ውጊያ በማቆም ዓለም ጎራ ለይቶ እንዲዋጋ ከሚያነሳሱ ትንኮሳዎች እንዲቆጠቡ ኢትዮጵያ ጥሪ ማቅረቧን አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገልፀዋል፡፡በሁለቱ ሀገራት መካከል የተካረረው ሁኔታ ዓለምን በጎራ ወደ ውጊያ እንዳያስገባ ተንኳሽ እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ ችግሩ የንግግር መፍትሄ እንዲበጅለት ኢትዮጵያ ፅኑ አቋም አላት ብለዋል አምባሳደር ዲና።ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ያንፀባረቀችው ድምፅ አልባ ውሳኔም የዚሁ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮ ኤርትራ ግንኙነት ባለበት ትልቅ ትሩፋት ነው ሲሉ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናገሩ!
የኢትዮ ኤርትራ ግንኙነት ባለበት ትልቅ ትሩፋት ነው ሲሉ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናግረዋል።አምባሳደር ዲና በዛሬው እለት ሳምንታዊ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን የስራ ማብራሪያ በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።
የኢትዮ ኤርትራ ጉዳይን በተመለክተ ተቋማዊ አለመሆኑ ችግር አይፈጥርም ወይ በሚል ለቀረበው ጥያቄ በዋናነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ሰላም ነው ሲሉ ተናግረዋል።እንዲሁም በጋራ ጉዳዮች ላይ መደጋጋፍ በተለያዩ መድረኮች ላይ ተደጋግፎ መታየቱ ነው ዋናው ነው ሲሉ አክለዋል።
ይሄ ሰላም ከተፈጠረ ገና 3 ዓመት ነው በዚህ መሃል የተሻለ አፈጻጸም እንዳይታይ ያደረጉ እንቅፋቶች አሉ ግን ደግሞ በአጠቃላይ ሲታይ የሰጠው ትሩፋት ትልቅ ነው ሲሉ ተናግረዋል።በሀገራቱ መካከል ለሁለት አስርት ዓመታት ተቋርጦ የቆየው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ዳግም እንዲጀመር ግንባር ቀደም ሚና የተጫወቱት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እንደሆኑ ይታወሳል።
[ዳጉ ጆርናል]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮ ኤርትራ ግንኙነት ባለበት ትልቅ ትሩፋት ነው ሲሉ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናግረዋል።አምባሳደር ዲና በዛሬው እለት ሳምንታዊ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን የስራ ማብራሪያ በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።
የኢትዮ ኤርትራ ጉዳይን በተመለክተ ተቋማዊ አለመሆኑ ችግር አይፈጥርም ወይ በሚል ለቀረበው ጥያቄ በዋናነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ሰላም ነው ሲሉ ተናግረዋል።እንዲሁም በጋራ ጉዳዮች ላይ መደጋጋፍ በተለያዩ መድረኮች ላይ ተደጋግፎ መታየቱ ነው ዋናው ነው ሲሉ አክለዋል።
ይሄ ሰላም ከተፈጠረ ገና 3 ዓመት ነው በዚህ መሃል የተሻለ አፈጻጸም እንዳይታይ ያደረጉ እንቅፋቶች አሉ ግን ደግሞ በአጠቃላይ ሲታይ የሰጠው ትሩፋት ትልቅ ነው ሲሉ ተናግረዋል።በሀገራቱ መካከል ለሁለት አስርት ዓመታት ተቋርጦ የቆየው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ዳግም እንዲጀመር ግንባር ቀደም ሚና የተጫወቱት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እንደሆኑ ይታወሳል።
[ዳጉ ጆርናል]
@YeneTube @FikerAssefa
አረብ ኤሚሬት ለኢትዮጵያ የሚሆን የ85 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ይፋ አደረገች!
ድጋፉ ለአንገብጋቢ ሰብዓዊ ፍላጎቶች ምላሽ ለመስጠት የሚውል ነው ተብሏል
የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ለኢትዮጵያ የሚሆን የ85 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ይፋ አደረገች፡፡ድጋፉ በተለያዩ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ እርዳታዎች አስተባባሪ ተቋማት በኩል ለተጠቃሚዎች የሚደርስ ነው ተብሏል፡፡ከዓለም የምግብ ፕሮግራም፣ ከዓለም የቀይ መስቀል እና ቀይ ጨረቃ ማህበራት፣ ከዩኒሴፍ እና ሌሎች የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ድጋፍ ማስተባበሪያ ተቋማት ጋር እንደሚሰራም ነው የተገለጸው፡፡
ዩኤኢ ድጋን እንደምታደርግ ያስታወቀችው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታዋ ሼክ ሻክቦት ቢን ናህያን አል ናህያን፣ የተመድ የሰብዓዊ እና የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ አስተባባሪ ማርቲን ግሪፊትስ እንዲሁም በተመድ የኢትዮጵያ ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ በተገኙበት በተካሄደ የበይነ መረብ ስብሰባ ነው፡፡ግሪፊትስ ለድጋፉ ዩኤኢን አመስግነዋል፡፡አምባሳደር ታዬ ስለ ድጋፉ ያሉት ነገር እንዳለ አላስታወቁም፡፡
Via Alain
@YeneTube @FikerAssefa
ድጋፉ ለአንገብጋቢ ሰብዓዊ ፍላጎቶች ምላሽ ለመስጠት የሚውል ነው ተብሏል
የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ለኢትዮጵያ የሚሆን የ85 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ይፋ አደረገች፡፡ድጋፉ በተለያዩ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ እርዳታዎች አስተባባሪ ተቋማት በኩል ለተጠቃሚዎች የሚደርስ ነው ተብሏል፡፡ከዓለም የምግብ ፕሮግራም፣ ከዓለም የቀይ መስቀል እና ቀይ ጨረቃ ማህበራት፣ ከዩኒሴፍ እና ሌሎች የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ድጋፍ ማስተባበሪያ ተቋማት ጋር እንደሚሰራም ነው የተገለጸው፡፡
ዩኤኢ ድጋን እንደምታደርግ ያስታወቀችው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታዋ ሼክ ሻክቦት ቢን ናህያን አል ናህያን፣ የተመድ የሰብዓዊ እና የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ አስተባባሪ ማርቲን ግሪፊትስ እንዲሁም በተመድ የኢትዮጵያ ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ በተገኙበት በተካሄደ የበይነ መረብ ስብሰባ ነው፡፡ግሪፊትስ ለድጋፉ ዩኤኢን አመስግነዋል፡፡አምባሳደር ታዬ ስለ ድጋፉ ያሉት ነገር እንዳለ አላስታወቁም፡፡
Via Alain
@YeneTube @FikerAssefa
የሮማን አብራሞቪች ቼልሲ እግር ኳስ ክለብን የመሸጥ እቅድ ችግር ላይ ወድቋል ተባለ
እገዳው አብራሞቪች ቼልሲን ለመሸጥ በያዙት ውጥን ላይ ችግር መፍጠሩ ነው የተነገረው
የእንግሊዝ መንግስት መንግስት የቼልሲ እግር ኳስ ክለብ ባለቤት ሮማን አብራሞቪችን ጨምሮ በሰባት ሩሲያውያን ቱጃሮች ላይ አዲስ የሃብትና የጉዞ እገዳ መጣሉን አስታወቀ።
በቦሪስ ጆንሰን ጠቅላይ ሚኒስትርነት የሚመራው የእንግሊዝ መንግስት የክለቡ ባለቤት ከእንግሊዛውያን ባለሃብቶች ጋር ምንም ዐይነት ግብይቶችንም ሆነ የቢዝነስ ስምምነቶችን ማድረግ እንደማይችሉ አታውቋል።
ሩሲያዊው ቢሊየነር ሮማን አብራሞቪች የቼልሲ እግር ኳስ ክለብን ለመሸጥ መወሰናቸው አስታወቁ ይህም ማለት አብራሞቪች እንዳሰቡት ሁሉ ቼልሲን ለመሸጥ አይችሉም ማለት ነው።
በአንድ ወቅት የአብራሞቪች የንግድ ሸሪክ የነበሩት ኦሌግ ዴሪፓስካ ተመሳሳይ እጣ ፋንታ ከገጠማቸው ቱጃሮች መካከል ናቸው።
የሩሲያ የነዳጅ ኩባንያ ሮዝኔፍት ኃላፊ ኢጎር ሼሺን ጨምሮ ሌሎች የፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቅርብ ሰዎች ናቸው የተባሉ አራት ሰዎች የእገዳው ሰለባ ናቸውም ተብሏል፡፡ እገዳው በቀጣዩ ሳምንት ተግባራዊ እንደሚደረግም ነው የተገለጸው።
ለፑቲን ደጋፊዎች የሚሆን ምቹ ሁኔታ እንደማይኖርም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ጆንሰን የተናገሩት።
እገዳው ለዩክሬናውያን ያለንን ድጋፍ የሚያሳይ ነውም ብለዋል ጆንሰን። የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ በሩሲያ እንዳይደረግ ተወሰነ በዩክሬናውያን ደም እጃቸው አለበት በሚል ቱጃሮቹን የከሰሱት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሊዝ ትረስ በበኩላቸው አንገታቸውን ሊደፉ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
በድምሩ 15 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገደማ የሚገመት የ7ቱ ቱጃሮች ሃብት ነው እገዳ የተጣለበት።
Via :- Al ain
@Yenetube @Fikerassefa
እገዳው አብራሞቪች ቼልሲን ለመሸጥ በያዙት ውጥን ላይ ችግር መፍጠሩ ነው የተነገረው
የእንግሊዝ መንግስት መንግስት የቼልሲ እግር ኳስ ክለብ ባለቤት ሮማን አብራሞቪችን ጨምሮ በሰባት ሩሲያውያን ቱጃሮች ላይ አዲስ የሃብትና የጉዞ እገዳ መጣሉን አስታወቀ።
በቦሪስ ጆንሰን ጠቅላይ ሚኒስትርነት የሚመራው የእንግሊዝ መንግስት የክለቡ ባለቤት ከእንግሊዛውያን ባለሃብቶች ጋር ምንም ዐይነት ግብይቶችንም ሆነ የቢዝነስ ስምምነቶችን ማድረግ እንደማይችሉ አታውቋል።
ሩሲያዊው ቢሊየነር ሮማን አብራሞቪች የቼልሲ እግር ኳስ ክለብን ለመሸጥ መወሰናቸው አስታወቁ ይህም ማለት አብራሞቪች እንዳሰቡት ሁሉ ቼልሲን ለመሸጥ አይችሉም ማለት ነው።
በአንድ ወቅት የአብራሞቪች የንግድ ሸሪክ የነበሩት ኦሌግ ዴሪፓስካ ተመሳሳይ እጣ ፋንታ ከገጠማቸው ቱጃሮች መካከል ናቸው።
የሩሲያ የነዳጅ ኩባንያ ሮዝኔፍት ኃላፊ ኢጎር ሼሺን ጨምሮ ሌሎች የፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቅርብ ሰዎች ናቸው የተባሉ አራት ሰዎች የእገዳው ሰለባ ናቸውም ተብሏል፡፡ እገዳው በቀጣዩ ሳምንት ተግባራዊ እንደሚደረግም ነው የተገለጸው።
ለፑቲን ደጋፊዎች የሚሆን ምቹ ሁኔታ እንደማይኖርም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ጆንሰን የተናገሩት።
እገዳው ለዩክሬናውያን ያለንን ድጋፍ የሚያሳይ ነውም ብለዋል ጆንሰን። የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ በሩሲያ እንዳይደረግ ተወሰነ በዩክሬናውያን ደም እጃቸው አለበት በሚል ቱጃሮቹን የከሰሱት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሊዝ ትረስ በበኩላቸው አንገታቸውን ሊደፉ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
በድምሩ 15 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገደማ የሚገመት የ7ቱ ቱጃሮች ሃብት ነው እገዳ የተጣለበት።
Via :- Al ain
@Yenetube @Fikerassefa
ባልደራስ 46 የፓርቲው አባላት እና የአዲስ አበባ እስረኞች ከተማ ዳር ወደሚገኘው አባ ሳሙኤል እስር ቤት መወሰዳቸውን አስታወቀ!
በአድዋ እና ካራማራ ሳቢያ የተከሰሱት 34 የባልደራስ እስረኞችን ጨምሮ 46 የአዲስ አበባ ወጣቶች ዛሬ በምሳ ሰዓት ታስረው ከሚገኙበት አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከተማ ዳር ወደሚገኘው አባ ሳሙኤል መዘዋወራቸውን ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ አስታወቀ፡፡
ይህ ፍፁም ያልተጠበቀ እና ህገ ወጥ እርምጃ ነው ያለው ፓርቲው፣ እስካሁን ባለው አሰራር ተጠርጣሪዎች መደበኛ የክስ ፋይል እስካልተከፈተባቸው ድረስ ወደ አባ ሳሙኤል እንደማይሄዱ ገልጿል፡፡ “ተጠርጣሪዎች የምርመራ ጊዜያቸውን የሚያሳልፉት ጊዮርጊስ በሚገኘው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እስር ቤት ወይም በየወረዳው ባሉ የፖሊስ ጣቢያ እስር ቤቶች ነው፡፡ እርምጃው መንግሥት በህገወጥ እና በጉልበት አካሄዱ እየገፋበት እንደሆነ ያመላክታል፡፡” ሲልም ባልደራስ ገልጿል።
ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የፓርቲው አባላት እና ሌሎች የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ተጠርጥረው በተያዙበት ጉዳይ ዛሬ ማለዳ አራዳ ጊዮርጊስ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በ3 የጊዜ ቀጠሮ መዝገብ መቅረባቸውን አስታውቋል፡፡
ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ፣ “ተጠርጣሪዎቹ በአድዋና በካራማራ ክብረ-በዓላት ላይ ሁከትና ብጥብጥ በማነሳሳት፣ ህዝብ በመንግሥት ላይ እንዲያምጽ በማድረግ፣ የመንግሥት ባለስልጣናትን በመሳደብና በማዋረድ ተግባር ላይ ሲሰማሩ አግኝቻቸዋለሁ፤ እንዲሁም፣ የተከለከለ ሰንደቅ ዓላማ በመያዝ በመንግሥት ላይ አመጽ ለማነሳሳት ሞክረዋል፡፡ ስለሆነም፣ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ምርመራ እንድናደርግባቸው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ይሰጠኝ” ብሏል፡፡
የተከሳሾቹ ጠበቆች ባቀረቡት ክርክር፣ “ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለማየት የሥረ-ነገር ሥልጣን የለውም፤ ጉዳዩም መታየት ካለበት የወንጀል ተግባሩ ተፈፀመ በተባለበት በልደታ ክፈለ ከተማ አጥቢያ ፍርድ ቤት ነው፣ በአንድ የወንጀል ጉዳይ ሁለት የጊዜ ቀጠሮ መዝገብ ልደታ እና አራዳ ክፍለ ከተማ ሊከፈት አይገባም፣ ፖሊስ 48 ሰዓት ካለፈ በኋላ ያቀረበው የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ ውቅድ ሊሆን ይገባል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ከ5ኛ ፖሊስ ጣቢያ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የተዛወሩት እስረኞችን ለመበቀል፣ ሆን ብሎ ለማንገላታትና በረዥም ጊዜ ቀጠሮ ያለአግባብ ለማጉላላት ነው።” ማለታቸው ተገልጿል፡፡
ጠበቆቹ አክለውም ተከሳሾቹ 5ኛ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እያሉ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀርበው የ3 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ከተሰጣቸው በኋላ፣ ፖሊስ በዕለቱ ለይግባኝ ሰሚ ችሎት የይግባኝ አቤቱታ ቢያቀርብም፣ ችሎቱ የፖሊስን አቤቱታ ውድቅ በማድረግ በ3 ቀን ውስጥ አጣርቶ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ በተሰጠበት ሁኔታ፣ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ የምርመራ ሥራውን ሰርቶ ማቅረብ ሲገባው፣ ይህንን ወደ ጎን በመተው ለፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት አዲስ የጊዜ ቀጠሮ መዝገብ ማስከፈቱ ተጠርጣሪዎቹን ለመበቀል አላማ እንደሆነ መረዳት ይቻላል” ብለዋል፡፡
በተጨማሪም፣ ፖሊስ በቀን የካቲት 23 የአድዋ በዓል እና የካራማራ የድል በዓል ላይ ሁከትና ብጥብጥ ተፈፀመ ቢልም፣ በእለቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሰጠው መግለጫ በዓሉ በሰላም ተጠናቋል የሚል መግለጫ አውጥቶ እያለ፣ መስተዳድሩ የማያውቀው ሁከትና ብጥብጥ እንደተፈፀመ ተደርጎ በፖሊስ የቀረበው ክርክር ውድቅ እንዲደረግ ተጠይቋል፡፡
እንዲሁም፣ ፖሊስ ባቀረበው አቤቱታ የድል በዓላቱ በሚከበርበት ጊዜ የባለሥልጣናት ሥም ተነስቶ የስድብ እና ማዋረድ እንደተፈፀመ ቢያቀርብም፣ ጉዳዩ በግል አቤቱታ አቅራቢነት የሚቀርብ ሆኖ ሳለ፣ ባለሥልጣናቱ ቀርበው ምርመራ እንዲጣራላቸው አቤቱታ ወይም ማመልከቻ ለፖሊስ ባላቀረቡበት ሁኔታ፣ ፖሊሰ በራሱ ተነሳሽነት ሊያጣራው የሚችለው ባለመሆኑና ጊዜ ቀጠሮ የሚያስጠይቅ ባለመሆኑ የፖሊስ አቤቱታ ውድቅ እንዲደረግ ተጠይቋል፡፡
በተጨማሪም፣ የተከለከለ ሰንደቅ አላማ ይዘው ወጥተዋል በሚል ያቀረበውን በተመለከተም፣ በአዋጅ ቁጥር 654/2001 መሠረት ጥፋተኛ ሆነው ቢገኙ እንኳን፣ በገንዘብ አማራጭ የሚያስቀጣ ቀላል ጉዳይ በመሆኑ፣ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ፖሊስ ያቀረበው አቤቱታ ከወንጀለኛ መቅጫ ሥነ-ሥርዓት ህጉ አላማና ግብ ያፈነገጠ በመሆኑ ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ ሊሰጥ አይገባም ሲሉ ጠበቆቹ ተከራክረዋል፡፡
ፖሊስ አሰባስባችኋል ያላቸው የሰነድ፣ የሰው እና የስልክ ማስረጃዎች ቀጠሮ ለማሰጠት በቂ አይደሉም፡፡ የማያውቋቸው ምስክሮች እና አባሪዎች ሊያሸሹብኝ ይችላሉ ያለውን ሥማቸው ተጠቅሶ ያላወቅናቸው ስለሆነ ተገቢነት ያለው አይደለም ብለው ጠበቆች መከራከራቸውን ባልደራስ ገልጿል፡፡ፍርድ ቤቱም በጠበቆች ክርክር ላይ ፖሊስ መልስ እንዲሰጥ ካደረገ በኋላ ትዕዛዝ ለመስጠት ለመጋቢት 5 ቀን 2014 በ8፡00 ሰዓት ቀጠሮ መስጠቱ ታውቋል፡፡
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
በአድዋ እና ካራማራ ሳቢያ የተከሰሱት 34 የባልደራስ እስረኞችን ጨምሮ 46 የአዲስ አበባ ወጣቶች ዛሬ በምሳ ሰዓት ታስረው ከሚገኙበት አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከተማ ዳር ወደሚገኘው አባ ሳሙኤል መዘዋወራቸውን ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ አስታወቀ፡፡
ይህ ፍፁም ያልተጠበቀ እና ህገ ወጥ እርምጃ ነው ያለው ፓርቲው፣ እስካሁን ባለው አሰራር ተጠርጣሪዎች መደበኛ የክስ ፋይል እስካልተከፈተባቸው ድረስ ወደ አባ ሳሙኤል እንደማይሄዱ ገልጿል፡፡ “ተጠርጣሪዎች የምርመራ ጊዜያቸውን የሚያሳልፉት ጊዮርጊስ በሚገኘው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እስር ቤት ወይም በየወረዳው ባሉ የፖሊስ ጣቢያ እስር ቤቶች ነው፡፡ እርምጃው መንግሥት በህገወጥ እና በጉልበት አካሄዱ እየገፋበት እንደሆነ ያመላክታል፡፡” ሲልም ባልደራስ ገልጿል።
ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የፓርቲው አባላት እና ሌሎች የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ተጠርጥረው በተያዙበት ጉዳይ ዛሬ ማለዳ አራዳ ጊዮርጊስ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በ3 የጊዜ ቀጠሮ መዝገብ መቅረባቸውን አስታውቋል፡፡
ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ፣ “ተጠርጣሪዎቹ በአድዋና በካራማራ ክብረ-በዓላት ላይ ሁከትና ብጥብጥ በማነሳሳት፣ ህዝብ በመንግሥት ላይ እንዲያምጽ በማድረግ፣ የመንግሥት ባለስልጣናትን በመሳደብና በማዋረድ ተግባር ላይ ሲሰማሩ አግኝቻቸዋለሁ፤ እንዲሁም፣ የተከለከለ ሰንደቅ ዓላማ በመያዝ በመንግሥት ላይ አመጽ ለማነሳሳት ሞክረዋል፡፡ ስለሆነም፣ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ምርመራ እንድናደርግባቸው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ይሰጠኝ” ብሏል፡፡
የተከሳሾቹ ጠበቆች ባቀረቡት ክርክር፣ “ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለማየት የሥረ-ነገር ሥልጣን የለውም፤ ጉዳዩም መታየት ካለበት የወንጀል ተግባሩ ተፈፀመ በተባለበት በልደታ ክፈለ ከተማ አጥቢያ ፍርድ ቤት ነው፣ በአንድ የወንጀል ጉዳይ ሁለት የጊዜ ቀጠሮ መዝገብ ልደታ እና አራዳ ክፍለ ከተማ ሊከፈት አይገባም፣ ፖሊስ 48 ሰዓት ካለፈ በኋላ ያቀረበው የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ ውቅድ ሊሆን ይገባል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ከ5ኛ ፖሊስ ጣቢያ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የተዛወሩት እስረኞችን ለመበቀል፣ ሆን ብሎ ለማንገላታትና በረዥም ጊዜ ቀጠሮ ያለአግባብ ለማጉላላት ነው።” ማለታቸው ተገልጿል፡፡
ጠበቆቹ አክለውም ተከሳሾቹ 5ኛ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እያሉ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀርበው የ3 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ከተሰጣቸው በኋላ፣ ፖሊስ በዕለቱ ለይግባኝ ሰሚ ችሎት የይግባኝ አቤቱታ ቢያቀርብም፣ ችሎቱ የፖሊስን አቤቱታ ውድቅ በማድረግ በ3 ቀን ውስጥ አጣርቶ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ በተሰጠበት ሁኔታ፣ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ የምርመራ ሥራውን ሰርቶ ማቅረብ ሲገባው፣ ይህንን ወደ ጎን በመተው ለፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት አዲስ የጊዜ ቀጠሮ መዝገብ ማስከፈቱ ተጠርጣሪዎቹን ለመበቀል አላማ እንደሆነ መረዳት ይቻላል” ብለዋል፡፡
በተጨማሪም፣ ፖሊስ በቀን የካቲት 23 የአድዋ በዓል እና የካራማራ የድል በዓል ላይ ሁከትና ብጥብጥ ተፈፀመ ቢልም፣ በእለቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሰጠው መግለጫ በዓሉ በሰላም ተጠናቋል የሚል መግለጫ አውጥቶ እያለ፣ መስተዳድሩ የማያውቀው ሁከትና ብጥብጥ እንደተፈፀመ ተደርጎ በፖሊስ የቀረበው ክርክር ውድቅ እንዲደረግ ተጠይቋል፡፡
እንዲሁም፣ ፖሊስ ባቀረበው አቤቱታ የድል በዓላቱ በሚከበርበት ጊዜ የባለሥልጣናት ሥም ተነስቶ የስድብ እና ማዋረድ እንደተፈፀመ ቢያቀርብም፣ ጉዳዩ በግል አቤቱታ አቅራቢነት የሚቀርብ ሆኖ ሳለ፣ ባለሥልጣናቱ ቀርበው ምርመራ እንዲጣራላቸው አቤቱታ ወይም ማመልከቻ ለፖሊስ ባላቀረቡበት ሁኔታ፣ ፖሊሰ በራሱ ተነሳሽነት ሊያጣራው የሚችለው ባለመሆኑና ጊዜ ቀጠሮ የሚያስጠይቅ ባለመሆኑ የፖሊስ አቤቱታ ውድቅ እንዲደረግ ተጠይቋል፡፡
በተጨማሪም፣ የተከለከለ ሰንደቅ አላማ ይዘው ወጥተዋል በሚል ያቀረበውን በተመለከተም፣ በአዋጅ ቁጥር 654/2001 መሠረት ጥፋተኛ ሆነው ቢገኙ እንኳን፣ በገንዘብ አማራጭ የሚያስቀጣ ቀላል ጉዳይ በመሆኑ፣ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ፖሊስ ያቀረበው አቤቱታ ከወንጀለኛ መቅጫ ሥነ-ሥርዓት ህጉ አላማና ግብ ያፈነገጠ በመሆኑ ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ ሊሰጥ አይገባም ሲሉ ጠበቆቹ ተከራክረዋል፡፡
ፖሊስ አሰባስባችኋል ያላቸው የሰነድ፣ የሰው እና የስልክ ማስረጃዎች ቀጠሮ ለማሰጠት በቂ አይደሉም፡፡ የማያውቋቸው ምስክሮች እና አባሪዎች ሊያሸሹብኝ ይችላሉ ያለውን ሥማቸው ተጠቅሶ ያላወቅናቸው ስለሆነ ተገቢነት ያለው አይደለም ብለው ጠበቆች መከራከራቸውን ባልደራስ ገልጿል፡፡ፍርድ ቤቱም በጠበቆች ክርክር ላይ ፖሊስ መልስ እንዲሰጥ ካደረገ በኋላ ትዕዛዝ ለመስጠት ለመጋቢት 5 ቀን 2014 በ8፡00 ሰዓት ቀጠሮ መስጠቱ ታውቋል፡፡
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
ብልፅግና ፓርቲ ጠቅላላ ጉባዔውን ነገ ይጀምራል!
ገዢው ፓርቲ ብልፅግና ጠቅላላ ጉባኤውን ከነገ ጀምሮ ያካሂዳል።ጉባኤውን አስመልክቶ የፓርቲው የህዝብና ዓለም አቀፍ ግኑኝነት ዘርፍ ሀላፊ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ መግለጫ ሰጥተዋል።ዶክተር ቢቂላ የብልጽግና አንደኛ ጉባኤ ባለፉት ሶስት አመታት ፓርቲው በሁሉም መስክ የተጎናጸፋቸውን ድሎች ይገመግማል ብለዋል።
የገጠሙትን ችግሮች እና ተግዳሮቶች በጥልቀት ገምግሞ ለማረም ታሪካዊ ውሳኔ ያሳልፋልም ብለዋል።ጉባኤው በጸጥታ ሁኔታ፣ በኢኮኖሚ እንዲሁም በሀገረ መንግስት ግንባታ ላይ ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚመክርም ገልጸዋል።
በዚህም ለዜጎች ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚያመጡ ውሳኔዎች ይተላለፋሉ ነው ያሉት።የብልጽግና ፓርቲ አንደኛ ጉባኤ ነገ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ይጀምራል።በጉባኤው 1 ሺህ 600 የፓርቲው አባላት በድምፅ የሚሳተፉ ሲሆን፥ 400 ከተለያየ የህብረተሰብ ክፍሎች እና ከውጭ ሀገራት የተጋበዙ እንግዶች ያለ ድምፅ ይሳተፋሉ።
ጉባኤው የፓርቲው አመራሮች፣ አባላት እና ደጋፊዎች የአስተሳሰብ እና የተግባር አንድነት የሚጎናጸፉበት፣ ፓርቲው በአደረጃጀት እና አሰራር ራሱን የሚያጠናክርበት እንዲሁም ፓርቲውን ሊያሻግሩ እና የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና ሊያረጋግጡ የሚችሉ ጠንካራ የፓርቲ አመራሮች የሚመረጡበትም ይሆናል ብለዋል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ገዢው ፓርቲ ብልፅግና ጠቅላላ ጉባኤውን ከነገ ጀምሮ ያካሂዳል።ጉባኤውን አስመልክቶ የፓርቲው የህዝብና ዓለም አቀፍ ግኑኝነት ዘርፍ ሀላፊ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ መግለጫ ሰጥተዋል።ዶክተር ቢቂላ የብልጽግና አንደኛ ጉባኤ ባለፉት ሶስት አመታት ፓርቲው በሁሉም መስክ የተጎናጸፋቸውን ድሎች ይገመግማል ብለዋል።
የገጠሙትን ችግሮች እና ተግዳሮቶች በጥልቀት ገምግሞ ለማረም ታሪካዊ ውሳኔ ያሳልፋልም ብለዋል።ጉባኤው በጸጥታ ሁኔታ፣ በኢኮኖሚ እንዲሁም በሀገረ መንግስት ግንባታ ላይ ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚመክርም ገልጸዋል።
በዚህም ለዜጎች ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚያመጡ ውሳኔዎች ይተላለፋሉ ነው ያሉት።የብልጽግና ፓርቲ አንደኛ ጉባኤ ነገ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ይጀምራል።በጉባኤው 1 ሺህ 600 የፓርቲው አባላት በድምፅ የሚሳተፉ ሲሆን፥ 400 ከተለያየ የህብረተሰብ ክፍሎች እና ከውጭ ሀገራት የተጋበዙ እንግዶች ያለ ድምፅ ይሳተፋሉ።
ጉባኤው የፓርቲው አመራሮች፣ አባላት እና ደጋፊዎች የአስተሳሰብ እና የተግባር አንድነት የሚጎናጸፉበት፣ ፓርቲው በአደረጃጀት እና አሰራር ራሱን የሚያጠናክርበት እንዲሁም ፓርቲውን ሊያሻግሩ እና የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና ሊያረጋግጡ የሚችሉ ጠንካራ የፓርቲ አመራሮች የሚመረጡበትም ይሆናል ብለዋል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
#BACK_TO_SCHOOL_AFRICA_EXPO_2022
ጥቂት ሳምንታት የቀሩት አለም አቀፍ የትምህርት ኤክስፖ በታላቁ አብርሆት ቤተ መፃህፍትና በቨርቹዋል መድረክ ላይ ይካሄዳል።
ብዙዎች ተመዝግበዋል! እርሶስ?
ከነዚህ መሃል ከሆኑ አሁኑኑ ይመዝገቡ
ትምህርት ቤቶች፣ ኮሌጆች እና ዩኒቨርሲቲዎች፣ የት/ቤት አስተዳደር ዲጂታል መፍትሔ አቅራቢዎች፣ የሶፍትዌር ገንቢዎች፣ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች፣ አለም አቅፍ የትምህርት እድል አማካሪዎች ፣ የትምህርት ኢንኩቤተሮች፣ የዲጂታል አገልግሎት አቅራቢዎች፣ የትምህርት ቁሳቁስ አምራቾች እና አቅራቢዎች፣ ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት እና ሌሎች ተያያዥነት ያላቸው።
ለመመዝገብ ይህችን ሊንክ ይጫኑ!
www.backtoschoolafrica.com
ለበለጠ መረጃ +251 974 0820 36/37
ጥቂት ሳምንታት የቀሩት አለም አቀፍ የትምህርት ኤክስፖ በታላቁ አብርሆት ቤተ መፃህፍትና በቨርቹዋል መድረክ ላይ ይካሄዳል።
ብዙዎች ተመዝግበዋል! እርሶስ?
ከነዚህ መሃል ከሆኑ አሁኑኑ ይመዝገቡ
ትምህርት ቤቶች፣ ኮሌጆች እና ዩኒቨርሲቲዎች፣ የት/ቤት አስተዳደር ዲጂታል መፍትሔ አቅራቢዎች፣ የሶፍትዌር ገንቢዎች፣ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች፣ አለም አቅፍ የትምህርት እድል አማካሪዎች ፣ የትምህርት ኢንኩቤተሮች፣ የዲጂታል አገልግሎት አቅራቢዎች፣ የትምህርት ቁሳቁስ አምራቾች እና አቅራቢዎች፣ ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት እና ሌሎች ተያያዥነት ያላቸው።
ለመመዝገብ ይህችን ሊንክ ይጫኑ!
www.backtoschoolafrica.com
ለበለጠ መረጃ +251 974 0820 36/37