YeneTube
Photo
የጀርመኑ መራሂተ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ወደ ሩሲያ አቅንተዋል፡፡
ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃልኪዳን ጦርን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ እና ሩሲያ ጉዳዩን እንደማትቀበል በማሳወቋ በምስራቅ አውሮፓ ጦርነት ይቀሰቀሳል የሚል ስጋት ተደቅኗል፡፡የሩሲያን ውሳኔ ተከትሎም የኔቶ አባል ሀገራት እንደ ተቋም እና እንደ አገር ከፍተኛ መጠን ያለው ጦር ወደ አካባቢው በማስፈር ላይ ሲሆኑ ሩሲያም ከ150 ሺህ በላይ ጦር ወደ ዩክሬን አስጠግታለች፡፡
በዚህ ምክንያትም በአካባቢው ጦርነት እንዳይቀሰቀስ የጠለያዩ አገራት ጉዳዩ በዲፕሎማሲ እንዲፈታ ግፊት በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ባሳለፍነው ሳምንት የፈረንሳዩ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ወደ ሞስኮ ተጉዘው ሩሲያ ዩክሬንን እንዳትወር ጉዳዩ በዲፕሎማሲ እንዲፈታ ለማግባባት ሞክረው ወደ አገራቸው ተመልሰዋል፡፡
አሁን ደግሞ የጀርመኑ መራሂተ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ወደ ሞስኮ የተጓዙ ሲሆን የጉዟቸው ዓላምም ኔቶ እና ሩሲያ በዩክሬን ጉዳይ የገቡበትን ውጥረት ማርገብ እንደሆነ የጀርመን ዜና ወኪል ዘግቧል፡፡
ኦላፍ ሾልዝ በትናንትናው ዕለት ወደ ዩክሬን መጥተው የነበረ ሲሆን ከሀገሪቱ ፕሬዘዳንት ዘለንስኪ ጋር በውጥረቱ ዙሪያ ተወያይተው ነበር፡፡
በዛሬው የሞስኮ የአንድ ቀን ቆይታቸውም ከሩሲያ ፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር እንደሚወያዩ የሚጠበቁት ኦላፍ ሾልዝ ሩሲያ ዩክሬንን እንዳትወር እና ጉዳዩ በዲፕሎማሲ ብቻ እንዲፈታ ለማግባባት እንደሚሞከሩ ይጠበቃል፡፡
ጀርመን የሩሲያ ዋነኛ የንግድ አጋር ስትሆን በዩክሬን ጉዳይ የዲፕሎማሲ ጥረቱ ካልተሳካ ጀርመንን እና አሜሪካንን ጨምሮ የአውሮፓ አገራት ጠንካራ ማዕቀብ እንደሚጣልባት አገራት ከወዲሁ በማስጠንቀቅ ላይ ናቸው፡፡
ሩሲያ በበኩሏ ዩክሬንን የመውረር ሃሳብ እንደሌላት ገልጻ ዩክሬን ኔቶን ከተቀላቀለች የጸጥታ እና ደህንነት ስምምነት ግን ይኑረን ስትል በተደጋጋሚ በማሳወቅ ላይ ትገኛለች፡፡
Via Al Ain
@Yenetube @Fikerassefa
ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃልኪዳን ጦርን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ እና ሩሲያ ጉዳዩን እንደማትቀበል በማሳወቋ በምስራቅ አውሮፓ ጦርነት ይቀሰቀሳል የሚል ስጋት ተደቅኗል፡፡የሩሲያን ውሳኔ ተከትሎም የኔቶ አባል ሀገራት እንደ ተቋም እና እንደ አገር ከፍተኛ መጠን ያለው ጦር ወደ አካባቢው በማስፈር ላይ ሲሆኑ ሩሲያም ከ150 ሺህ በላይ ጦር ወደ ዩክሬን አስጠግታለች፡፡
በዚህ ምክንያትም በአካባቢው ጦርነት እንዳይቀሰቀስ የጠለያዩ አገራት ጉዳዩ በዲፕሎማሲ እንዲፈታ ግፊት በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ባሳለፍነው ሳምንት የፈረንሳዩ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ወደ ሞስኮ ተጉዘው ሩሲያ ዩክሬንን እንዳትወር ጉዳዩ በዲፕሎማሲ እንዲፈታ ለማግባባት ሞክረው ወደ አገራቸው ተመልሰዋል፡፡
አሁን ደግሞ የጀርመኑ መራሂተ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ወደ ሞስኮ የተጓዙ ሲሆን የጉዟቸው ዓላምም ኔቶ እና ሩሲያ በዩክሬን ጉዳይ የገቡበትን ውጥረት ማርገብ እንደሆነ የጀርመን ዜና ወኪል ዘግቧል፡፡
ኦላፍ ሾልዝ በትናንትናው ዕለት ወደ ዩክሬን መጥተው የነበረ ሲሆን ከሀገሪቱ ፕሬዘዳንት ዘለንስኪ ጋር በውጥረቱ ዙሪያ ተወያይተው ነበር፡፡
በዛሬው የሞስኮ የአንድ ቀን ቆይታቸውም ከሩሲያ ፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር እንደሚወያዩ የሚጠበቁት ኦላፍ ሾልዝ ሩሲያ ዩክሬንን እንዳትወር እና ጉዳዩ በዲፕሎማሲ ብቻ እንዲፈታ ለማግባባት እንደሚሞከሩ ይጠበቃል፡፡
ጀርመን የሩሲያ ዋነኛ የንግድ አጋር ስትሆን በዩክሬን ጉዳይ የዲፕሎማሲ ጥረቱ ካልተሳካ ጀርመንን እና አሜሪካንን ጨምሮ የአውሮፓ አገራት ጠንካራ ማዕቀብ እንደሚጣልባት አገራት ከወዲሁ በማስጠንቀቅ ላይ ናቸው፡፡
ሩሲያ በበኩሏ ዩክሬንን የመውረር ሃሳብ እንደሌላት ገልጻ ዩክሬን ኔቶን ከተቀላቀለች የጸጥታ እና ደህንነት ስምምነት ግን ይኑረን ስትል በተደጋጋሚ በማሳወቅ ላይ ትገኛለች፡፡
Via Al Ain
@Yenetube @Fikerassefa
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አነሳ
አዋጁ 63 ተቃውሞ እና 21 ድምፀ ተአቅቦ ቀርቦበታል !!
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በአገሪቱ ተጥሎ የቆየውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አነስቷል፡፡
ምክር ቤቱ በስብሰባው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ በቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በ63 ተቃውሞ በ21 ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ እንዲነሳ ወስኗል፡፡
ይህን ውሳኔ ተከትሎ፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ ያላጠናቀቃቸው ጅምር ሥራዎች ካሉ ይህ ውሳኔ ከተላለፈበት ከዛሬ ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት እንዲያደርግ መወሰኑን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል፡፡
በተመሳሳይ የፍትህ አካላት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ የጀመሯቸውን ጉዳዮች በመደበኛው የፍትህ አሰሰጣጥ ሥርዓት እንዲያጠናቅቁም ምክር ቤቱ ወስኗል።
#ዳጉ_ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa
አዋጁ 63 ተቃውሞ እና 21 ድምፀ ተአቅቦ ቀርቦበታል !!
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በአገሪቱ ተጥሎ የቆየውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አነስቷል፡፡
ምክር ቤቱ በስብሰባው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ በቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በ63 ተቃውሞ በ21 ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ እንዲነሳ ወስኗል፡፡
ይህን ውሳኔ ተከትሎ፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ ያላጠናቀቃቸው ጅምር ሥራዎች ካሉ ይህ ውሳኔ ከተላለፈበት ከዛሬ ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት እንዲያደርግ መወሰኑን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል፡፡
በተመሳሳይ የፍትህ አካላት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ የጀመሯቸውን ጉዳዮች በመደበኛው የፍትህ አሰሰጣጥ ሥርዓት እንዲያጠናቅቁም ምክር ቤቱ ወስኗል።
#ዳጉ_ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa
በረሃ ላይ ብቻውን ምግብ እያበሰለ የነበረውን ታዳጊ ፎቶ ያነሳው ኢትዮጵያዊው ጋዜጠኛ ከፎቶው ጀርባ ስላለው ታሪክ ለቢቢሲ ተናግሯል።
ፎቶውን በተለያዩ ማህበራዊ ትስስር ገጾች ብዙዎች ያጋሩት ሲሆን ለልጁ ገንዘብና የተለያዩ እርዳታዎችም ተሰባስበውለታል።ፎቶውን ያነሳው ጋዜጠኛ ቦሩ ኮንሶ ይባላል።በፎቶው ላይ ታዳጊው ብቻውን በረሃ ላይ ምግብ እያበሰለ የሚታይ ሲሆን በማህበራዊ ሚዲያም ለተመለከቱትም ከፍተኛ ኃዘኔታን አሳድሯል።
ፎቶውን ያነሳው ጋዜጠኛ በሞተር ሳይክል ሚዮ በተባለች ገጠራማ ሰፈር ሪፖርት ለመስራት እየሄደ በነበረበት ወቅት ነው ልጁን ያገኘው።በጣም መሽቶም ነበር።"ትንሽ ልጅ ነው ምናልባትም ዕድሜው ከ10 ዓመት በታች።ብቻውን እሳት አንድዶ ምግብ እያበሰለ ነበር።ብቻውን በረሃ ውስጥ እያበሰለ ሳየው ደነገጥኩ።
በ10 ኪሎሜትር ርቀት ካልሆነ በአካባቢው ምንም አይነት ቤት የለም።ሞተር ሳይክሌን አቁሜም ፎቶ አነሳሁት" ይላል ቦሩ።ልጁ ለጋዜጠኛው የገለጸለት ቤተሶቦቹ በሌላ ወረዳ ውስጥ እንደሚኖሩና ውሃና ግጦሽ ፍለጋም ከብቶቹን ይዞ ከቦታ ቦታ እንደሚንቀሳቀስ ነው።ቦሩ የልጁን ፎቶ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ማጋራቱን ተከትሎ በርካቶችም ታዳጊውን መርዳት እንደሚፈልጉም ነገሩት።
ህፃኑን ከጎበኙት መካከል ነጋዴዋ ሙና ባካሬ የምትባል ግለሰብ አንደኛዋ ስትሆን ለልጁ ፣ለቤተሰቦቹ እና ለጎረቤቶች የምግብና ሌሎች ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጋለች።"የዚህን ትንሸ ልጅ ፎቶ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ማየቴ ልቤን ነክቶታል። መተኛት አልቻልኩም ነበር።ልጄ እንደሆነ ተሰማኝ፣ ስለዚህ እሱን መፈለግ ጀመርኩ" ብላለች ሙና።ሙና የልጁን የትምህርት ወጪ እንደምትሸፍን የተናገረች ሲሆን ኮሌጅ እስኪጨርስ ድረስ ለመክፈል ቃል ገብታለች።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ፎቶውን በተለያዩ ማህበራዊ ትስስር ገጾች ብዙዎች ያጋሩት ሲሆን ለልጁ ገንዘብና የተለያዩ እርዳታዎችም ተሰባስበውለታል።ፎቶውን ያነሳው ጋዜጠኛ ቦሩ ኮንሶ ይባላል።በፎቶው ላይ ታዳጊው ብቻውን በረሃ ላይ ምግብ እያበሰለ የሚታይ ሲሆን በማህበራዊ ሚዲያም ለተመለከቱትም ከፍተኛ ኃዘኔታን አሳድሯል።
ፎቶውን ያነሳው ጋዜጠኛ በሞተር ሳይክል ሚዮ በተባለች ገጠራማ ሰፈር ሪፖርት ለመስራት እየሄደ በነበረበት ወቅት ነው ልጁን ያገኘው።በጣም መሽቶም ነበር።"ትንሽ ልጅ ነው ምናልባትም ዕድሜው ከ10 ዓመት በታች።ብቻውን እሳት አንድዶ ምግብ እያበሰለ ነበር።ብቻውን በረሃ ውስጥ እያበሰለ ሳየው ደነገጥኩ።
በ10 ኪሎሜትር ርቀት ካልሆነ በአካባቢው ምንም አይነት ቤት የለም።ሞተር ሳይክሌን አቁሜም ፎቶ አነሳሁት" ይላል ቦሩ።ልጁ ለጋዜጠኛው የገለጸለት ቤተሶቦቹ በሌላ ወረዳ ውስጥ እንደሚኖሩና ውሃና ግጦሽ ፍለጋም ከብቶቹን ይዞ ከቦታ ቦታ እንደሚንቀሳቀስ ነው።ቦሩ የልጁን ፎቶ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ማጋራቱን ተከትሎ በርካቶችም ታዳጊውን መርዳት እንደሚፈልጉም ነገሩት።
ህፃኑን ከጎበኙት መካከል ነጋዴዋ ሙና ባካሬ የምትባል ግለሰብ አንደኛዋ ስትሆን ለልጁ ፣ለቤተሰቦቹ እና ለጎረቤቶች የምግብና ሌሎች ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጋለች።"የዚህን ትንሸ ልጅ ፎቶ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ማየቴ ልቤን ነክቶታል። መተኛት አልቻልኩም ነበር።ልጄ እንደሆነ ተሰማኝ፣ ስለዚህ እሱን መፈለግ ጀመርኩ" ብላለች ሙና።ሙና የልጁን የትምህርት ወጪ እንደምትሸፍን የተናገረች ሲሆን ኮሌጅ እስኪጨርስ ድረስ ለመክፈል ቃል ገብታለች።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ሞሮኮ ከእስራኤል ጋር የ500 ሚሊዮን ዶላር የጦር መሳሪያ ስምምነት ተፈራረመች
እስራኤል ለሞሮኮ የአየር ጥቃት መከላከያ መሳሪያን ለማቅረብ የ500 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ላይ ደርሳለች፡፡
ከእስራኤል ኤሮስፔስ ጋር የተደረገው ውል ባለፈው ህዳር ወር ሁለቱ ሀገራት በመከላከያ ትብብር ዙሪያ የመግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸውን ተከትሎ ነው።
ሞሮኮ እ.ኤ.አ በ2020 መገባደጃ ላይ በአሜሪካ አደራዳሪነት የክፍለ ዘመኑ የሰላም ስምምነት(የአብራሃም ስምምነት) በተባለዉ ሂደት ከእስራኤል ጋር ይፋዊ የሁለትዮሽ ግንኙነት ማድረግ መጀመሯ ይታወሳል፡፡
Via:- Al ain
@Yenetube @Fikerassefa
እስራኤል ለሞሮኮ የአየር ጥቃት መከላከያ መሳሪያን ለማቅረብ የ500 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ላይ ደርሳለች፡፡
ከእስራኤል ኤሮስፔስ ጋር የተደረገው ውል ባለፈው ህዳር ወር ሁለቱ ሀገራት በመከላከያ ትብብር ዙሪያ የመግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸውን ተከትሎ ነው።
ሞሮኮ እ.ኤ.አ በ2020 መገባደጃ ላይ በአሜሪካ አደራዳሪነት የክፍለ ዘመኑ የሰላም ስምምነት(የአብራሃም ስምምነት) በተባለዉ ሂደት ከእስራኤል ጋር ይፋዊ የሁለትዮሽ ግንኙነት ማድረግ መጀመሯ ይታወሳል፡፡
Via:- Al ain
@Yenetube @Fikerassefa
ለዜጎች መብት መከበር የሚሟገተው ጋዜጠኛ መብት ይከበር ሲል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር አሳሰበ።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ከጋዜጠኞች መብት እና የሙያ ነፃነት ጋር በተያያዘ እየተፈፀሙ ያሉትን ጥሰቶች አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል።
የማህበሩ መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦
ለዜጎች መብት መከበር የሚሟገተው ጋዜጠኛ መብት ይከበር!
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት መሻሻል እያሳየ እንደነበር ማህበራችን እና ዓለም ዓቀፍ ተቋማት ሲመሰክሩ እንደነበር ይታወሳል፡፡
ይሁንና ይህ መሻሻል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተሸረሸረ መሄዱን በብዙ ማሳያዎችን መግለጽ ይቻላል፡፡
ለአብነትም የሚከተሉትን ማሳያዎች መጥቀስ ይቻላል፡፡
1. በአንድ ወቅት የአሐዱ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ባልደረባ የነበረው ጋዜጠኛ ታምራት አበራ ስቲዲዮ በሥራ ላይ እያለ ትጥቅ ባነገቱ የጸጥታ አካላት ወደ ሰንዳፋ ተወስዶ ታስሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡
በየትኛውም አግባብ የታጠቁ ኃይሎች ወደ መገናኛ ብዙኃን ስቱዲዮዎች ፈጽሞ መግባት እንደሌለባቸው እሙን ቢሆንም በኢትዮጵያ ግን ይህ ተደርጎ አይተናል፡፡
2. የአሐዱ ኤፍ ኤም ሬድዮ ባልደረባ የነበረው ጌጥዬ ያለው የታሰረ ባልደረባውን ለመጠየቅ ሰንዳፋ ፖሊስ ጣቢያ ባመራበት ወቅት የክልሉ ጸጥታ አካላት "ጋዜጠኞች መታሰር አለባቸው” በሚል እንዳሰሩት ሙሉ መረጃ አለ፡፡
3. የፍትሕ መጽሔት ማኔጅንግ ኤዲተር ተመስገን ደሳለኝ ያለምንም የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ከቢሮው ተወስዶ እና በእስር ቆይቶ ከቀናት በኋላ መለቀቁ ይታወሳል፡፡
4. የባላገሩ ቴሌቪዥን ጣብያ ባልደረባ ጋዜጠኛ አስናቀ ማርሸትም በኦሮሚያ ክልል አሌልቱ ከተማ "አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ቀለማትን የያዘ ልብስ ለበሳችሁ” በሚል ታስሮ ፍርድ ቤትም ሳይቀርብ መለቀቁ ይታወሳል፡፡
5. የአሐዱ ኤፍ ኤም ሬድዮ ባልደረባ ክብሮም ወርቁ በመንግስት ኃይሎች ተወስዶ የት እንዳለ ሳይታወቅ ቆይቶ ከወራት በኋላ ተለቋል፡፡ ይህ ጋዜጠኛን ማፈን እና መሰወር ከመንግስት የማይጠበቅ ድርጊት ነው።
6. የአውሎ ሚዲያ ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረውም ታስሮ ለወራት ከቆየ በኋላ ቢለቀቅም ንብረቶቹ ሙሉ በሙሉ በጸጥታ ኃይሎች እጅ ሥር ይገኛሉ፡፡
7. ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድም ታስራ ፍርድ ቤት ሳትቀርብ ከአንድ ወር በላይ ቆይታ ተለቃለች።
8. "የአሸባሪውን ሸኔ ቡድንን በዓለም አቀፍ ደረጃ የማስተዋወቅ ስራ ሲሰሩ ነበር" ያላቸውን ሶስት ተጠርጣሪ ጋዜጠኞች ማለትም አሚር አማን - የአሶሺየትድ ፕሬስ ጋዜጠኛ፣ ቶማስ እንግዳ - የካሜራ ባለሞያ እና አዲሱ ሙሉነህ የፋና ብሮድካስቲንግ ጋዜጠኛ በቁጥጥር ሥር አውሏል። በቅርቡም ጋዜጠኛ አዲሱ ሙሉነህ ከአንድ ወር ተኩል እስር በኋላ ሲለቀቅ ሌሎቹ በእስር ላይ ይገኛሉ።
ይሁን እንጂ በተጠርጣሪነት የተያዙት ጋዜጠኞች ወንጀለኛነታቸው በፍርድ ቤት ባልተረጋገጠበት ሁኔታና አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከሚደነግገው ውጭ አስቀድሞ እንደወንጀለኛ እንዲቆጠሩ በማድረግ ምስላቸው በሚዲያ እንዲሰራጭ በማድረግ ከፍተኛ የሥም ማጥፋት ተፈጽሞባቸዋል።
9. ሌላው የተራራ ኔትወርክ ዩትዩብ አዘጋጅ የሆነው ታምራት ነገራም ባልታወቀ ምክንያት ታግቶ እስካሁን ድረስ በገላን ከተማ እንደሚገኝ ማህበራችን ከቤተሰቦቹ አረጋግጧል። ንብረቶቹም በሙሉ በመንግስት ተወስደዋል፡፡ ታምራት ነገራ ፍርድ ቤት ሳይቀርብ እስካሁን በእስር ላይ መቆየቱ እጅግ አሳዛኝ እና ተገቢነት የሌለው ተግባር መሆኑን ማህበራችን ያምናል፡፡
በአጠቃላይ ጋዜጠኞችን ካለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ መያዝ እንዲሁም ይህንን ያህል ጊዜ እስር ቤት ማቆየት ከሕግም ከሞራልም ያፈነገጠ መሆኑ ግልጽ ቢሆንም በኢትዮጵያ ግን ይህ ጉዳይ የተለመደ ሆኗል፡፡
ጋዜጠኛ የህዝብ አንደበትና ጆሮ በመሆኑ የሚያራምዳቸው ሀሳቦችን ከተለያዩ ምንጮች ሊያገኝ ስለሚችል የግል አቋም ተደርጎ መወሰዱ ብቻውን አግባብ አይደለም።
ማንኛውም ጋዜጠኛ ወይም የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያ የሚታሰረው ለሕዝብ ባስተላለፈው መልዕክት ይዘት ከሆነ ያስተላለፈው ሀሳብ የእርሱ ወይም የሌላ ሰው ሊሆን ስለሚችል እርሱ ብቻ በሀሳቡ ብቻ ሊጠየቅ አይገባም።
ያም ሆኖ በዘገባ ወቅት የተፈጠረ የመረጃ እና/ወይም የእውነታ ስህተት ቢኖር እንኳን ተመጣጣኝ ማስተካከያ በዚያው ሚዲያ ላይ ማድረግ የሚችልበት አሰራር እያለ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ወደእስር መውሰድ ተገቢ አይደለም።
ከዚህም በተጨማሪ ማንኛውም ጋዜጠኛ የመረጃ ምንጩን ምስጢራዊነት የመጠበቅ ሙያዊ መብቱ ሊከበርለት እንደሚገባ መንግስት ማጤን ይኖርበታል።
ጋዜጠኞች በታፈኑ ቁጥር የሀሳብ የበላይነት እየከሰመ የአገሪቱ የፕሬስ ዕድገትም እየቀጨጨ ይሄዳል።
ማህበራችን ጋዜጠኞች በተደጋጋሚ ታስረው ሲፈቱ ችግሮች በሂደት ይስተካከላሉ የሚል ተስፋ የነበረው ቢሆንም ችግሩ ግን እየተባባሰ መሄዱን አረጋግጧል፡፡
ባለፉት አሰርት ዓመታት ጋዜጠኞች ሲታሰሩ፣ ሲሰደዱና ሲገደሉ ሁላችንም አዝነን ለሀገራችን የምንችለውን አድርገን ለውጥ መምጣቱ ቢታወቅም ለውጡ ግን ለመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የተለየ ነገር ይዞ አልመጣም።
በመሆኑም ጋዜጠኞች ሙያዊ ነጻነታቸውን ሳያጡ እንዲሰሩ ሊፈቅድላቸው ሲገባ በተደጋጋሚ ማሰርና ማንገላታቱ መቆም እንዳለበት እናሳስባለን፡፡
መንግስት ጋዜጠኞችን መጠየቅና ማብራሪያ መጠየቅ ሲፈልግ በአገሪቱ ሕግ እንዲሁም አገሪቱ በተቀበለቻቸው ዓለም ዓቀፋዊ ስምምነቶች መሰረት የተፈራረመቻቸውን መብቶች ግምት ውስጥ አስገብቶ ሊሆን ይገባል፡፡ በመርህ ደረጃ አንድ ጋዜጠኛ፣ አንድ መሃንዲስ፣ አንድ ሚኒስትር እኩል መሆኑን ማመን ያስፈልገናል፡፡
ይህ ማለት ግን አጥፊ ግለሰቦችና ባለሙያዎች ሲኖሩ በሕግ አግባብ እንደማንኛውም ዜጋ ሊጠየቁ ይገባል።
ይህ ሲሆን ግን ፈጸሙት በተባለው ድርጊት በሕግ አግባብ ብቻ የሚጠየቁበት አግባብ ተከብሮ፣ በትክክለኛው ጊዜ ክስ ተመስርቶባቸው፣ በሕግ ጥላ ሥር ባረፉበት ቦታ በቤተሰቦቻቸው የመጠየቅ መብታቸው ተከብሮላቸው ሊሆን ይገባል።
ጋዜጠኞች አሁን ባለው ሁኔታ እየተሳደዱ የሚቀጥሉ ከሆነ አዲሱ ትውልድ የጋዜጠኝነትን ሙያ እንደወንጀል እየቆጠረ ከሙያው እንዲሸሽ የሚያደርግ፣ ባለሙያው በሚሰራው ስራ ነጻ ሆኖ ከመስራት ይልቅ እንዲሸማቀቅ የሚያደርግ፣ የምንናፍቀው የፕሬስ ነጻነትም ሆነ የአገር ብልጽግና ጥያቄ ውስጥ እንዲገባ ስለሚያደርግ ለብዙ ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ድምጽ ለሚሆነው ባለሙያ ክብር ይሰጥ እንላለን፡፡
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ከጋዜጠኞች መብት እና የሙያ ነፃነት ጋር በተያያዘ እየተፈፀሙ ያሉትን ጥሰቶች አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል።
የማህበሩ መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦
ለዜጎች መብት መከበር የሚሟገተው ጋዜጠኛ መብት ይከበር!
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት መሻሻል እያሳየ እንደነበር ማህበራችን እና ዓለም ዓቀፍ ተቋማት ሲመሰክሩ እንደነበር ይታወሳል፡፡
ይሁንና ይህ መሻሻል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተሸረሸረ መሄዱን በብዙ ማሳያዎችን መግለጽ ይቻላል፡፡
ለአብነትም የሚከተሉትን ማሳያዎች መጥቀስ ይቻላል፡፡
1. በአንድ ወቅት የአሐዱ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ባልደረባ የነበረው ጋዜጠኛ ታምራት አበራ ስቲዲዮ በሥራ ላይ እያለ ትጥቅ ባነገቱ የጸጥታ አካላት ወደ ሰንዳፋ ተወስዶ ታስሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡
በየትኛውም አግባብ የታጠቁ ኃይሎች ወደ መገናኛ ብዙኃን ስቱዲዮዎች ፈጽሞ መግባት እንደሌለባቸው እሙን ቢሆንም በኢትዮጵያ ግን ይህ ተደርጎ አይተናል፡፡
2. የአሐዱ ኤፍ ኤም ሬድዮ ባልደረባ የነበረው ጌጥዬ ያለው የታሰረ ባልደረባውን ለመጠየቅ ሰንዳፋ ፖሊስ ጣቢያ ባመራበት ወቅት የክልሉ ጸጥታ አካላት "ጋዜጠኞች መታሰር አለባቸው” በሚል እንዳሰሩት ሙሉ መረጃ አለ፡፡
3. የፍትሕ መጽሔት ማኔጅንግ ኤዲተር ተመስገን ደሳለኝ ያለምንም የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ከቢሮው ተወስዶ እና በእስር ቆይቶ ከቀናት በኋላ መለቀቁ ይታወሳል፡፡
4. የባላገሩ ቴሌቪዥን ጣብያ ባልደረባ ጋዜጠኛ አስናቀ ማርሸትም በኦሮሚያ ክልል አሌልቱ ከተማ "አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ቀለማትን የያዘ ልብስ ለበሳችሁ” በሚል ታስሮ ፍርድ ቤትም ሳይቀርብ መለቀቁ ይታወሳል፡፡
5. የአሐዱ ኤፍ ኤም ሬድዮ ባልደረባ ክብሮም ወርቁ በመንግስት ኃይሎች ተወስዶ የት እንዳለ ሳይታወቅ ቆይቶ ከወራት በኋላ ተለቋል፡፡ ይህ ጋዜጠኛን ማፈን እና መሰወር ከመንግስት የማይጠበቅ ድርጊት ነው።
6. የአውሎ ሚዲያ ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረውም ታስሮ ለወራት ከቆየ በኋላ ቢለቀቅም ንብረቶቹ ሙሉ በሙሉ በጸጥታ ኃይሎች እጅ ሥር ይገኛሉ፡፡
7. ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድም ታስራ ፍርድ ቤት ሳትቀርብ ከአንድ ወር በላይ ቆይታ ተለቃለች።
8. "የአሸባሪውን ሸኔ ቡድንን በዓለም አቀፍ ደረጃ የማስተዋወቅ ስራ ሲሰሩ ነበር" ያላቸውን ሶስት ተጠርጣሪ ጋዜጠኞች ማለትም አሚር አማን - የአሶሺየትድ ፕሬስ ጋዜጠኛ፣ ቶማስ እንግዳ - የካሜራ ባለሞያ እና አዲሱ ሙሉነህ የፋና ብሮድካስቲንግ ጋዜጠኛ በቁጥጥር ሥር አውሏል። በቅርቡም ጋዜጠኛ አዲሱ ሙሉነህ ከአንድ ወር ተኩል እስር በኋላ ሲለቀቅ ሌሎቹ በእስር ላይ ይገኛሉ።
ይሁን እንጂ በተጠርጣሪነት የተያዙት ጋዜጠኞች ወንጀለኛነታቸው በፍርድ ቤት ባልተረጋገጠበት ሁኔታና አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከሚደነግገው ውጭ አስቀድሞ እንደወንጀለኛ እንዲቆጠሩ በማድረግ ምስላቸው በሚዲያ እንዲሰራጭ በማድረግ ከፍተኛ የሥም ማጥፋት ተፈጽሞባቸዋል።
9. ሌላው የተራራ ኔትወርክ ዩትዩብ አዘጋጅ የሆነው ታምራት ነገራም ባልታወቀ ምክንያት ታግቶ እስካሁን ድረስ በገላን ከተማ እንደሚገኝ ማህበራችን ከቤተሰቦቹ አረጋግጧል። ንብረቶቹም በሙሉ በመንግስት ተወስደዋል፡፡ ታምራት ነገራ ፍርድ ቤት ሳይቀርብ እስካሁን በእስር ላይ መቆየቱ እጅግ አሳዛኝ እና ተገቢነት የሌለው ተግባር መሆኑን ማህበራችን ያምናል፡፡
በአጠቃላይ ጋዜጠኞችን ካለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ መያዝ እንዲሁም ይህንን ያህል ጊዜ እስር ቤት ማቆየት ከሕግም ከሞራልም ያፈነገጠ መሆኑ ግልጽ ቢሆንም በኢትዮጵያ ግን ይህ ጉዳይ የተለመደ ሆኗል፡፡
ጋዜጠኛ የህዝብ አንደበትና ጆሮ በመሆኑ የሚያራምዳቸው ሀሳቦችን ከተለያዩ ምንጮች ሊያገኝ ስለሚችል የግል አቋም ተደርጎ መወሰዱ ብቻውን አግባብ አይደለም።
ማንኛውም ጋዜጠኛ ወይም የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያ የሚታሰረው ለሕዝብ ባስተላለፈው መልዕክት ይዘት ከሆነ ያስተላለፈው ሀሳብ የእርሱ ወይም የሌላ ሰው ሊሆን ስለሚችል እርሱ ብቻ በሀሳቡ ብቻ ሊጠየቅ አይገባም።
ያም ሆኖ በዘገባ ወቅት የተፈጠረ የመረጃ እና/ወይም የእውነታ ስህተት ቢኖር እንኳን ተመጣጣኝ ማስተካከያ በዚያው ሚዲያ ላይ ማድረግ የሚችልበት አሰራር እያለ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ወደእስር መውሰድ ተገቢ አይደለም።
ከዚህም በተጨማሪ ማንኛውም ጋዜጠኛ የመረጃ ምንጩን ምስጢራዊነት የመጠበቅ ሙያዊ መብቱ ሊከበርለት እንደሚገባ መንግስት ማጤን ይኖርበታል።
ጋዜጠኞች በታፈኑ ቁጥር የሀሳብ የበላይነት እየከሰመ የአገሪቱ የፕሬስ ዕድገትም እየቀጨጨ ይሄዳል።
ማህበራችን ጋዜጠኞች በተደጋጋሚ ታስረው ሲፈቱ ችግሮች በሂደት ይስተካከላሉ የሚል ተስፋ የነበረው ቢሆንም ችግሩ ግን እየተባባሰ መሄዱን አረጋግጧል፡፡
ባለፉት አሰርት ዓመታት ጋዜጠኞች ሲታሰሩ፣ ሲሰደዱና ሲገደሉ ሁላችንም አዝነን ለሀገራችን የምንችለውን አድርገን ለውጥ መምጣቱ ቢታወቅም ለውጡ ግን ለመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የተለየ ነገር ይዞ አልመጣም።
በመሆኑም ጋዜጠኞች ሙያዊ ነጻነታቸውን ሳያጡ እንዲሰሩ ሊፈቅድላቸው ሲገባ በተደጋጋሚ ማሰርና ማንገላታቱ መቆም እንዳለበት እናሳስባለን፡፡
መንግስት ጋዜጠኞችን መጠየቅና ማብራሪያ መጠየቅ ሲፈልግ በአገሪቱ ሕግ እንዲሁም አገሪቱ በተቀበለቻቸው ዓለም ዓቀፋዊ ስምምነቶች መሰረት የተፈራረመቻቸውን መብቶች ግምት ውስጥ አስገብቶ ሊሆን ይገባል፡፡ በመርህ ደረጃ አንድ ጋዜጠኛ፣ አንድ መሃንዲስ፣ አንድ ሚኒስትር እኩል መሆኑን ማመን ያስፈልገናል፡፡
ይህ ማለት ግን አጥፊ ግለሰቦችና ባለሙያዎች ሲኖሩ በሕግ አግባብ እንደማንኛውም ዜጋ ሊጠየቁ ይገባል።
ይህ ሲሆን ግን ፈጸሙት በተባለው ድርጊት በሕግ አግባብ ብቻ የሚጠየቁበት አግባብ ተከብሮ፣ በትክክለኛው ጊዜ ክስ ተመስርቶባቸው፣ በሕግ ጥላ ሥር ባረፉበት ቦታ በቤተሰቦቻቸው የመጠየቅ መብታቸው ተከብሮላቸው ሊሆን ይገባል።
ጋዜጠኞች አሁን ባለው ሁኔታ እየተሳደዱ የሚቀጥሉ ከሆነ አዲሱ ትውልድ የጋዜጠኝነትን ሙያ እንደወንጀል እየቆጠረ ከሙያው እንዲሸሽ የሚያደርግ፣ ባለሙያው በሚሰራው ስራ ነጻ ሆኖ ከመስራት ይልቅ እንዲሸማቀቅ የሚያደርግ፣ የምንናፍቀው የፕሬስ ነጻነትም ሆነ የአገር ብልጽግና ጥያቄ ውስጥ እንዲገባ ስለሚያደርግ ለብዙ ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ድምጽ ለሚሆነው ባለሙያ ክብር ይሰጥ እንላለን፡፡
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያዊቷ ሥራ ፈጣሪ አጊቱ ጉደታ ገዳይ የ20 ዓመት እስራት ተፈረደበት!
በጣሊያን የትሬንቶ ፍርድ ቤት ትናንት የካቲት 07 ቀን 2014 በዋለው ችሎት በኢትዮጵያዊቷ ሥራ ፈጣሪ አጊቱ ጉደታ ላይ አሰቃቂ ጥቃት በማድረስ ለህልፈተ ህይወት የዳረገው የ33 ዓመቱ ጋናዊ ሱሌማን አዳምስ ላይ የ20 ዓመት ፅኑ እስራት ፈርዶበታል።
አጊቱ በትሬንትኖ ሊጠፉ የተቃረቡ የፍየል ዝርያዎችን ከመጥፋት በመታደግና ፍየል እርባታ፣ በአካባቢ እንክብካቤ፣ በወተትና ወተት ተዋፅኦ ምርት በጣም ውጤታማ የነበረች እና በጣሊያን ህዝብና መንግሰት እንዲሁም በዳያስፖራው ማህበረሰብ ዘንድ በውጤታማነቷ ሞዴል የነበረች ትጉህ ሴት ነበረች ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመልክቷል።
ለዚህ ፍትህ መገኘት የአካባቢው የመንግስት ኃላፊዎችና ነዋሪዎች እንዲሁም የትሬንቲኖ የኢትዮጵያ ዳያስፓራ ኮሚኒቲ በጣሊያን የኢፌዲሪ ኤምባሲ ጋር በመስራት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውን ኤምባሲው ገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
በጣሊያን የትሬንቶ ፍርድ ቤት ትናንት የካቲት 07 ቀን 2014 በዋለው ችሎት በኢትዮጵያዊቷ ሥራ ፈጣሪ አጊቱ ጉደታ ላይ አሰቃቂ ጥቃት በማድረስ ለህልፈተ ህይወት የዳረገው የ33 ዓመቱ ጋናዊ ሱሌማን አዳምስ ላይ የ20 ዓመት ፅኑ እስራት ፈርዶበታል።
አጊቱ በትሬንትኖ ሊጠፉ የተቃረቡ የፍየል ዝርያዎችን ከመጥፋት በመታደግና ፍየል እርባታ፣ በአካባቢ እንክብካቤ፣ በወተትና ወተት ተዋፅኦ ምርት በጣም ውጤታማ የነበረች እና በጣሊያን ህዝብና መንግሰት እንዲሁም በዳያስፖራው ማህበረሰብ ዘንድ በውጤታማነቷ ሞዴል የነበረች ትጉህ ሴት ነበረች ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመልክቷል።
ለዚህ ፍትህ መገኘት የአካባቢው የመንግስት ኃላፊዎችና ነዋሪዎች እንዲሁም የትሬንቲኖ የኢትዮጵያ ዳያስፓራ ኮሚኒቲ በጣሊያን የኢፌዲሪ ኤምባሲ ጋር በመስራት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውን ኤምባሲው ገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
ላለፉት አምስት አመታት በከተማችን የ ሴትና የወንድ ሠዓቶች ቦርሳዎች ሽቶዎች እና ቀበቶና ዋሌት ቦርሣዎችን በማስመጣት የሚታወቀው brand watch and bag shop .. በ አዲስ መልክ ከ አዳዲስ እቃዎች ጋር እነሆ
አድራሻችን 22 ጎላጎል አጠገብ ሀናን ኬ ፕላዛ 1ኛ ፎቅ
ስልክ 0993014846/ 0938042570
እዚህ ይጎብኙን 👉 https://tttttt.me/+Q1fJRNqbpYxXr-Ga
አድራሻችን 22 ጎላጎል አጠገብ ሀናን ኬ ፕላዛ 1ኛ ፎቅ
ስልክ 0993014846/ 0938042570
እዚህ ይጎብኙን 👉 https://tttttt.me/+Q1fJRNqbpYxXr-Ga
Forwarded from YeneTube
#የኢትዮጵያ_ታሪክ_ከንግስተ_ሳባ_እስከ_አዲስ_አበባ
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
የኢትዮጵያን ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ አዲስ አበባ የሚቃኘውና በአማዞን የምንጊዜም የኢትዮጵያ ታሪክ መጻህፍት ሽያጭ ከፍተኛ ደረጃን የተቆናጠጠው መጽሐፍ በአማርኛ ተተርጉሞ ቀረበ፡፡
ይህ አለም በጣም ያደነቀው መጽሐፍ ኢትዮጵያን በትናንት፣ በዛሬና በነገ መነጽር የሚያሳይ የ30 ዓመታት ምርምር ውጤት የሆነ በቅጡ ሊነበብ የሚገባው መጽሐፍ ነው፡፡
የአጼ ኃይለስላሴ የልጅ ልጅ ልጅ የሆኑት ልዑል አስፋ ወሰን አስራቴ ስለመጽሐፉ እንዲህ ነው ያሉት፡-
“አንብቤ ለመጨረስ ሶስት ሌሊቶች ብቻ ነው የወሰደብኝ፡፡ ይህ መጽሐፍ በኢትዮጵያ ታሪክ ጥንታዊ፣ ኃይማኖታዊ ልምምድ ላይ ባልተለመደና ቀልብን በሚያነሆልል ሁኔታ የተጻፈ ነው፡፡ መጽሐፉ በአፍሪካ ምድር ከሚገኙ መሳጭ ስልጣኔዎች መካከል አንዱ ስለሆነው የኢትዮጵያ ስልጣኔ ያለንን ግንዛቤ የሚያፋፋ እጽ ነው፡፡”
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛል፡፡
ቤተሰብ ይሁኑ👇
https://tttttt.me/teklu_tilahun
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
የኢትዮጵያን ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ አዲስ አበባ የሚቃኘውና በአማዞን የምንጊዜም የኢትዮጵያ ታሪክ መጻህፍት ሽያጭ ከፍተኛ ደረጃን የተቆናጠጠው መጽሐፍ በአማርኛ ተተርጉሞ ቀረበ፡፡
ይህ አለም በጣም ያደነቀው መጽሐፍ ኢትዮጵያን በትናንት፣ በዛሬና በነገ መነጽር የሚያሳይ የ30 ዓመታት ምርምር ውጤት የሆነ በቅጡ ሊነበብ የሚገባው መጽሐፍ ነው፡፡
የአጼ ኃይለስላሴ የልጅ ልጅ ልጅ የሆኑት ልዑል አስፋ ወሰን አስራቴ ስለመጽሐፉ እንዲህ ነው ያሉት፡-
“አንብቤ ለመጨረስ ሶስት ሌሊቶች ብቻ ነው የወሰደብኝ፡፡ ይህ መጽሐፍ በኢትዮጵያ ታሪክ ጥንታዊ፣ ኃይማኖታዊ ልምምድ ላይ ባልተለመደና ቀልብን በሚያነሆልል ሁኔታ የተጻፈ ነው፡፡ መጽሐፉ በአፍሪካ ምድር ከሚገኙ መሳጭ ስልጣኔዎች መካከል አንዱ ስለሆነው የኢትዮጵያ ስልጣኔ ያለንን ግንዛቤ የሚያፋፋ እጽ ነው፡፡”
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛል፡፡
ቤተሰብ ይሁኑ👇
https://tttttt.me/teklu_tilahun
Forwarded from YeneTube
🇭🇺የስራ ጉዞ ወደ #Hungary 🇭🇺
#Schengen_visa
👉 የሚሰራበት አገር - Budapest, Hungary
👉 የስራው አይነት - Construction work
👉 የስራ ቀናት - 6 ቀናት/ week
👉 የስራ ሰዓት - 8 - 10 hr/day
👉 የወር ደሞዝ - €1500 and more
👉 ፆታ - ወንድ
👉 ዕድሜ - 18 እስከ 45
👉 መኖሪያ ቤት - በነፃ
👉 ፕሮሰሱ የሚፈጀው ግዜ ከ 2 - 3 ወር ነው
#30_persons
#Requirements
👉 Passport
👉 Photo
Contact:
@Sabinavisa
+251118683939
0936363639
0936363680
info@sabinaadvisor.com
http://Sabinaadvisor.com
https://tttttt.me/sabinavisaa
#Schengen_visa
👉 የሚሰራበት አገር - Budapest, Hungary
👉 የስራው አይነት - Construction work
👉 የስራ ቀናት - 6 ቀናት/ week
👉 የስራ ሰዓት - 8 - 10 hr/day
👉 የወር ደሞዝ - €1500 and more
👉 ፆታ - ወንድ
👉 ዕድሜ - 18 እስከ 45
👉 መኖሪያ ቤት - በነፃ
👉 ፕሮሰሱ የሚፈጀው ግዜ ከ 2 - 3 ወር ነው
#30_persons
#Requirements
👉 Passport
👉 Photo
Contact:
@Sabinavisa
+251118683939
0936363639
0936363680
info@sabinaadvisor.com
http://Sabinaadvisor.com
https://tttttt.me/sabinavisaa
🎁 #ArtLand_gifts 🎁
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
✿ "እማይረሱ ስጦታዎችን ለሚወዷቸው" 🎁
✔️የወደዱትን "ፎቶ ወይም ምስል" እንጨት እና ቆዳ(ሌዘር) ላይ እንሰራለን 👌
✔️እንዲሁም MUG, PUZZLE, ሀብል እና ፕላስቲክ MDF ላይ የወደዱትን ፎቶ ወይም ፅሁፍ ያሰሩ 🎁
🔘☎️contact us: 0931465618
🔘For Order @Artlandgifts
Join our telegram channel👇
@artlandengraving
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
✿ "እማይረሱ ስጦታዎችን ለሚወዷቸው" 🎁
✔️የወደዱትን "ፎቶ ወይም ምስል" እንጨት እና ቆዳ(ሌዘር) ላይ እንሰራለን 👌
✔️እንዲሁም MUG, PUZZLE, ሀብል እና ፕላስቲክ MDF ላይ የወደዱትን ፎቶ ወይም ፅሁፍ ያሰሩ 🎁
🔘☎️contact us: 0931465618
🔘For Order @Artlandgifts
Join our telegram channel👇
@artlandengraving
ሩሲያ በዩክሬን ላይ አሁንም ጥቃት ልትፈጽም ትችላለች ሲሉ ባይደን ተናገሩ
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እንደተናገሩት ሩስያ በዩክሬን ላይ አሁንም ጥቃት ልትፈጽም እንደምትችል በመግለጽ ሊደርስ የሚችለዉ ሰብዓዊ ኪሳራ እጅግ ግዙፍ ነዉ ሲሉ አስታዉቀዋል፡፡በአገር አቀፍ ደረጃ በቴሌቪዥን በተላለፈው የፕሬዝዳንቱ መልዕክት ዩናይትድ ስቴትስ ለእንደዚህ ዓይነቱ እርምጃ ቆራጥ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል ።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ሩሲያ ከዩክሬን ጋር በሚያዋስናት ድንበር 150,000 ወታደሮችን አስፍራለች ሲሉ ገልጸዋል፡፡የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር በበኩሉ አንዳንድ ሃይሎች አካባቢዉን ለቀዉ መውጣታቸውን ቢያሳዉቅም ባይደን ግን ይህ አልተረጋገጠም ሲሉ ተናግረዋል፡፡ባይደን የሩሲያ ጦር መልቀቅ ጥሩ ነበር ነገርግን እስካሁን አላረጋገጥንም ሲሉ አክለዋል፡፡
ባይደን ይህንን መልዕክት ያስተላለፉት የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሞስኮ የጸጥታ ስጋት ትኩረት ሊሰጠው እና በቁም ነገር መታየት እንዳለበት ከተናገሩ ከሰዓታት በኋላ ነው።ፑቲን በተደጋጋሚ ዩክሬንን ለመዉረር አቅደዋል መባሉን ያስተባብላሉ፡፡ ፣ ሩሲያ በአውሮጳ ምድር ሌላ ጦርነት ሀገራቸዉ እንደማትፈልግ ቢናገሩም ከህዳር ወር ጀምሮ ያለዉ ውጥረት ግን እየጨመረ ይገኛል፡፡
#ዳጉ_ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እንደተናገሩት ሩስያ በዩክሬን ላይ አሁንም ጥቃት ልትፈጽም እንደምትችል በመግለጽ ሊደርስ የሚችለዉ ሰብዓዊ ኪሳራ እጅግ ግዙፍ ነዉ ሲሉ አስታዉቀዋል፡፡በአገር አቀፍ ደረጃ በቴሌቪዥን በተላለፈው የፕሬዝዳንቱ መልዕክት ዩናይትድ ስቴትስ ለእንደዚህ ዓይነቱ እርምጃ ቆራጥ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል ።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ሩሲያ ከዩክሬን ጋር በሚያዋስናት ድንበር 150,000 ወታደሮችን አስፍራለች ሲሉ ገልጸዋል፡፡የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር በበኩሉ አንዳንድ ሃይሎች አካባቢዉን ለቀዉ መውጣታቸውን ቢያሳዉቅም ባይደን ግን ይህ አልተረጋገጠም ሲሉ ተናግረዋል፡፡ባይደን የሩሲያ ጦር መልቀቅ ጥሩ ነበር ነገርግን እስካሁን አላረጋገጥንም ሲሉ አክለዋል፡፡
ባይደን ይህንን መልዕክት ያስተላለፉት የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሞስኮ የጸጥታ ስጋት ትኩረት ሊሰጠው እና በቁም ነገር መታየት እንዳለበት ከተናገሩ ከሰዓታት በኋላ ነው።ፑቲን በተደጋጋሚ ዩክሬንን ለመዉረር አቅደዋል መባሉን ያስተባብላሉ፡፡ ፣ ሩሲያ በአውሮጳ ምድር ሌላ ጦርነት ሀገራቸዉ እንደማትፈልግ ቢናገሩም ከህዳር ወር ጀምሮ ያለዉ ውጥረት ግን እየጨመረ ይገኛል፡፡
#ዳጉ_ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa
ጄነራል ታደሰ ወረደን እና ሌ/ጄ ጻድቃን ገ/ተንሳይን ጨምሮ 54 ተከሳሾች በሌሉበት ጉዳያቸው እንዲታይ ፍርድ ቤቱ አዘዘ።
ትዛዙን የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የፀረሽብርና ህገመንግስታዊ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።
አጠቃላይ ክስ የቀረበባቸው ተከሳሾች 74 ሲሆኑ ጄነራል ታደሰ ወረደ እና ሌ/ጄ ጻድቃን ገ/ተንሳይን ጨምሮ 54 ተከሳሾች በቁጥጥር ስር ያልዋሉ ሲሆን:
ቀሪዎቹ ኮነሬል መሐመድ ኑር እና ኮነሬል ባህሩ ታጀብን ጨምሮ 20 ተከሳሾች ግን በቁጥጥር ስር ውለው ማረሚያ ቤት እንዲወርዱ የተደረጉ ናቸው።
በጥር 18 ቀን 2014 ዓ/ም በነበረው ቀጠሮ የተከሳሽ ጠበቆች በቁጥጥር ስር ውለው ፍርድ ቤት እየቀረቡ የሚገኙ ደንበኞቻችን የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብታቸው እንዲከበር ጉዳያቸው ተነጥሎ ይታይልን ሲሉ ፍርድ ቤቱን መጠየቃቸው ይታወሳል።
ከሳሽ ዓቃቢህግም በበኩሉ በቁጥጥር ስር ያልዋሉ እነ ጄነራል ታደረ ወረደን ጨምሮ 54 ተከሳሾች በጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቆ የነበረ ሲሆን:
ፍርድ ቤቱም ላልቀረቡ 54 ተከሳሾች በኢትዮጲያ ፕሬስ ድርጅት የጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸው ትዛዝ በመስጠት የትዛዙን ውጤት ለመጠባበቅ ለዛሬ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰቶ ነበር።
ይሁንና ፍርድ ቤቱ በትናንቱ ቀጠሮ 54ቱ ተከሳሾች በጥር 26 ቀን በጋዜጣ ጥሪ የተደረገላቸው መሆኑን አረጋግጧል።
በጋዜጣ ጥሪ ውጤት መሰረት ከ 54ቱ ተከሳሾች መካከል ችሎት የቀረበ ካለ ለማረጋገጥ ፍርድ ቤቱ የስም ጥሪ ያደረገ ቢሆንም በችሎት የቀረበ ግን አልነበረም።
በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ መዝገቡ ያልተያዙ ተከሳሾች በሌሉበት እንዲታይ ትዛዝ ሰቷል።
በዚሁ መዝገብ ተካተው ጉዳያቸው እየታዩ ያሉ የ20 ተከሳሾችን ክስ ለመመልከት ለየካቲት 22 ቀን ተለዋጭ ተሰቷል።
አጠቃላይ ተከሳሾቹ ከህውሐት የሽብር ቡድን ተልኮ በመቀበል :ወታደራዊ ቡድን በማደራጀት እና በመምራት በሰሜን ዕዝ መከላከያ አባላት በፌደራል ፖሊስ እንዲሁም በአማራና በአፋር ክልሎች ላይ ጥቃት በማድረስ ወንጀል በየደረጃው የተከሰሱ ናቸው።
ምንጭ: ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ
@Yenetube @Fikerassefa
ትዛዙን የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የፀረሽብርና ህገመንግስታዊ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።
አጠቃላይ ክስ የቀረበባቸው ተከሳሾች 74 ሲሆኑ ጄነራል ታደሰ ወረደ እና ሌ/ጄ ጻድቃን ገ/ተንሳይን ጨምሮ 54 ተከሳሾች በቁጥጥር ስር ያልዋሉ ሲሆን:
ቀሪዎቹ ኮነሬል መሐመድ ኑር እና ኮነሬል ባህሩ ታጀብን ጨምሮ 20 ተከሳሾች ግን በቁጥጥር ስር ውለው ማረሚያ ቤት እንዲወርዱ የተደረጉ ናቸው።
በጥር 18 ቀን 2014 ዓ/ም በነበረው ቀጠሮ የተከሳሽ ጠበቆች በቁጥጥር ስር ውለው ፍርድ ቤት እየቀረቡ የሚገኙ ደንበኞቻችን የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብታቸው እንዲከበር ጉዳያቸው ተነጥሎ ይታይልን ሲሉ ፍርድ ቤቱን መጠየቃቸው ይታወሳል።
ከሳሽ ዓቃቢህግም በበኩሉ በቁጥጥር ስር ያልዋሉ እነ ጄነራል ታደረ ወረደን ጨምሮ 54 ተከሳሾች በጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቆ የነበረ ሲሆን:
ፍርድ ቤቱም ላልቀረቡ 54 ተከሳሾች በኢትዮጲያ ፕሬስ ድርጅት የጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸው ትዛዝ በመስጠት የትዛዙን ውጤት ለመጠባበቅ ለዛሬ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰቶ ነበር።
ይሁንና ፍርድ ቤቱ በትናንቱ ቀጠሮ 54ቱ ተከሳሾች በጥር 26 ቀን በጋዜጣ ጥሪ የተደረገላቸው መሆኑን አረጋግጧል።
በጋዜጣ ጥሪ ውጤት መሰረት ከ 54ቱ ተከሳሾች መካከል ችሎት የቀረበ ካለ ለማረጋገጥ ፍርድ ቤቱ የስም ጥሪ ያደረገ ቢሆንም በችሎት የቀረበ ግን አልነበረም።
በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ መዝገቡ ያልተያዙ ተከሳሾች በሌሉበት እንዲታይ ትዛዝ ሰቷል።
በዚሁ መዝገብ ተካተው ጉዳያቸው እየታዩ ያሉ የ20 ተከሳሾችን ክስ ለመመልከት ለየካቲት 22 ቀን ተለዋጭ ተሰቷል።
አጠቃላይ ተከሳሾቹ ከህውሐት የሽብር ቡድን ተልኮ በመቀበል :ወታደራዊ ቡድን በማደራጀት እና በመምራት በሰሜን ዕዝ መከላከያ አባላት በፌደራል ፖሊስ እንዲሁም በአማራና በአፋር ክልሎች ላይ ጥቃት በማድረስ ወንጀል በየደረጃው የተከሰሱ ናቸው።
ምንጭ: ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ
@Yenetube @Fikerassefa
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሀይል የማመንጨት ሙከራ መጀመሩ ተዘገበ!
ባለፉት ሁለት የክረምት ወቅቶች ውሀ በያዘው በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኤሌክትሪክ ኋይል ማመንጫ ተርባይኖችን በውሀ የመሞከር ስራ መጀመሩን ዋዜማ ራዲዮ ከምንጮቿ ሰምቻለሁ ብላለች።
የሚመነጨው ኋይልም ወደ ብሄራዊ የኋይል ቋት የሚገባ ሳይሆን ለሙከራ ያህል ብቻ የሚከናወን ነው።ሆኖም ሙከራው ግድቡ የኤሌክትሪ የኋይል አመንጭቶ ወደ ብሄራዊ ቋት ለማስገባት ለሚደረገው ጥረት ግን ወሳኝ ደረጃ ነው ተብሏል።
ዝርዝሩን ለማንበብ - https://bit.ly/3HNxpYt
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፉት ሁለት የክረምት ወቅቶች ውሀ በያዘው በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኤሌክትሪክ ኋይል ማመንጫ ተርባይኖችን በውሀ የመሞከር ስራ መጀመሩን ዋዜማ ራዲዮ ከምንጮቿ ሰምቻለሁ ብላለች።
የሚመነጨው ኋይልም ወደ ብሄራዊ የኋይል ቋት የሚገባ ሳይሆን ለሙከራ ያህል ብቻ የሚከናወን ነው።ሆኖም ሙከራው ግድቡ የኤሌክትሪ የኋይል አመንጭቶ ወደ ብሄራዊ ቋት ለማስገባት ለሚደረገው ጥረት ግን ወሳኝ ደረጃ ነው ተብሏል።
ዝርዝሩን ለማንበብ - https://bit.ly/3HNxpYt
@YeneTube @FikerAssefa
በአፍሪካ ቀንድ ድርቅ በተከሰተባቸው አካባባች እስከ ግንቦት ዝናብ ካልዘነበ ድርቁ እጅግ ከባድ ጉዳት እንደሚያደርስ ፋኦ ገለፀ!
ኢትዮጵያን ጨምሮ በምስራቅ አፍሪካ በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የቤት እንስሳት መሞታቸውን የዓለም ምግብ ፕሮግራም አስታውቋል።በድርቁ የተጎዱትን ለመደገፍ 130 ሚሊዮን ዶላር ይስፈልጋል ተብሏል።
Via Alain
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያን ጨምሮ በምስራቅ አፍሪካ በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የቤት እንስሳት መሞታቸውን የዓለም ምግብ ፕሮግራም አስታውቋል።በድርቁ የተጎዱትን ለመደገፍ 130 ሚሊዮን ዶላር ይስፈልጋል ተብሏል።
Via Alain
@YeneTube @FikerAssefa
አምነስቲ ህውሓት በአማራ ክልል ከተሞች በንፁሃን ዜጎች ላይ የግድያ ፣ የመድፈር እና የዘረፋ ጥቃችን ፈጽሟል አለ!
በሰሜን ኢትዮጵያ የአማራ ክልል ሁለት አካባቢዎች ከህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሀት) ጋር ግንኙነት ያላቸው ታጣቂዎች ሆን ብለው በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ገድለዋል፣ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ሴቶችን እና ልጃገረዶችን በቡድን ደፍረዋል፡፡
ከተደፈሩት ሴቶች መካከል ዕድሜያቸው ገና 14 ዓመት የሆኑ ልጃገረዶች እንደሚገኙበት ተቋሙ ዛሬ ባወጣው አዲስ ሪፖርት ገልጿል፡፡ይህ ብቻ ሳይሆን የግል እና የህዝብ ንብረቶችን ዘርፈዋል ሲል አምነስቲ ኢንተርናሽናል በዘገባ ው አስታውቋል።
እ.አ.አ በ2021 በነሀሴ ወር መጨረሻ እና በመስከረም መጀመሪያ በጭና እና ቆቦ አካባቢዎች በንጹሀን ላይ ግፉ የተፈፀመው የትግራይ ሃይሎች በሐምሌ ወር አካባቢዎቹን በተቆጣጠሩ ሰሞን ነው ይላል ሪፖርቱ።
ጥቃቶቹ በጭካኔ ድርጊቶች የተሞሉ ሲሆን ፣ የግድያ ዛቻዎች እና የብሔር ተኮር ስድቦችን የጥቃቱ አካል ናቸው፡፡በቆቦ የአካባቢውሚሊሻዎች እና የታጠቁ ነዋሪዎች ያሳዩት የመከላከል ጥንካሬ ያበሳጫቸው የትግራይ ታጣቂዎች በሰላማዊው ህዝብ እልሃቸውን እየተወጡ ይመስላል።
"የትግራይ ሃይሎች ሁሉም ተፋላሚ ወገኖች ሊከተሏቸው የሚገቡትን መሰረታዊ የአለም አቀፍ የሰብአዊ ህግ ደንቦችን ጥሰዋል ሲሉ በአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ አፍሪካ፣ ቀንድ እና ታላላቅ ሀይቆች ምክትል ዳይሬክተር ሳራ ጃክሰን ተናግረዋል።
ከጁላይ 2021 ጀምሮ የትግራይ ሃይሎች በአማራ ክልል ስር በሚገኙ አካባቢዎች የጦር ወንጀል እና በሰው ልጆች ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን የሚያሳዩ መረጃዎች እየጨመሩ መሆናቸውንም አንስተዋል ዳይሬክተሩ፡፡
‹‹አስገድዶ መድፈር ፣ ግድያ ፣ ዘረፋ እና ሆስፒታሎች ጨምሮ ተቋማትን ማቃጠል ይጨምራል” ሲሉ በአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ አፍሪካ፣ ቀንድ እና ታላላቅ ሀይቆች ምክትል ዳይሬክተር ሳራ ጃክሰን ጨምረው ተናግረዋል።"የህወሓት ባለስልጣናት እንዲህ አይነት ግፍ በአስቸኳይ ማስቆም እና በዚህ አይነት ወንጀል የተጠረጠረውን ሰውም ለፍርድ እንዲያቀርቡ ።" ጠይቀዋል
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በሰሜን ኢትዮጵያ የአማራ ክልል ሁለት አካባቢዎች ከህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሀት) ጋር ግንኙነት ያላቸው ታጣቂዎች ሆን ብለው በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ገድለዋል፣ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ሴቶችን እና ልጃገረዶችን በቡድን ደፍረዋል፡፡
ከተደፈሩት ሴቶች መካከል ዕድሜያቸው ገና 14 ዓመት የሆኑ ልጃገረዶች እንደሚገኙበት ተቋሙ ዛሬ ባወጣው አዲስ ሪፖርት ገልጿል፡፡ይህ ብቻ ሳይሆን የግል እና የህዝብ ንብረቶችን ዘርፈዋል ሲል አምነስቲ ኢንተርናሽናል በዘገባ ው አስታውቋል።
እ.አ.አ በ2021 በነሀሴ ወር መጨረሻ እና በመስከረም መጀመሪያ በጭና እና ቆቦ አካባቢዎች በንጹሀን ላይ ግፉ የተፈፀመው የትግራይ ሃይሎች በሐምሌ ወር አካባቢዎቹን በተቆጣጠሩ ሰሞን ነው ይላል ሪፖርቱ።
ጥቃቶቹ በጭካኔ ድርጊቶች የተሞሉ ሲሆን ፣ የግድያ ዛቻዎች እና የብሔር ተኮር ስድቦችን የጥቃቱ አካል ናቸው፡፡በቆቦ የአካባቢውሚሊሻዎች እና የታጠቁ ነዋሪዎች ያሳዩት የመከላከል ጥንካሬ ያበሳጫቸው የትግራይ ታጣቂዎች በሰላማዊው ህዝብ እልሃቸውን እየተወጡ ይመስላል።
"የትግራይ ሃይሎች ሁሉም ተፋላሚ ወገኖች ሊከተሏቸው የሚገቡትን መሰረታዊ የአለም አቀፍ የሰብአዊ ህግ ደንቦችን ጥሰዋል ሲሉ በአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ አፍሪካ፣ ቀንድ እና ታላላቅ ሀይቆች ምክትል ዳይሬክተር ሳራ ጃክሰን ተናግረዋል።
ከጁላይ 2021 ጀምሮ የትግራይ ሃይሎች በአማራ ክልል ስር በሚገኙ አካባቢዎች የጦር ወንጀል እና በሰው ልጆች ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን የሚያሳዩ መረጃዎች እየጨመሩ መሆናቸውንም አንስተዋል ዳይሬክተሩ፡፡
‹‹አስገድዶ መድፈር ፣ ግድያ ፣ ዘረፋ እና ሆስፒታሎች ጨምሮ ተቋማትን ማቃጠል ይጨምራል” ሲሉ በአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ አፍሪካ፣ ቀንድ እና ታላላቅ ሀይቆች ምክትል ዳይሬክተር ሳራ ጃክሰን ጨምረው ተናግረዋል።"የህወሓት ባለስልጣናት እንዲህ አይነት ግፍ በአስቸኳይ ማስቆም እና በዚህ አይነት ወንጀል የተጠረጠረውን ሰውም ለፍርድ እንዲያቀርቡ ።" ጠይቀዋል
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ) በኢትዮጵያ ለተከሰተው ድርቅ ድጋፍ የሚዉል ተጨማሪ 2 ቢሊየን ብር (39 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር) ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ።
ድጋፉ ድርቅ በተከሰተባቸዉ የአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ደቡብ እና ሶማሌ ክልሎች ጉዳት ለደረሰባቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች እርዳታ የሚውል ነዉም ተብሏል፡፡
በሶማሌ፣ ኦሮሚያና ደቡብ ክልሎች ሙሉ በሙሉና በከፊል በተደጋጋሚ ዝናብ ወቅቱን ጠብቆ ባለመዝነቡ እንደዚሁም በአማራ ክልል በነበረው ግጭት ምክንያት በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች ለምግብ እህል እርዳታ መዳረጋቸው ይታወቃል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ድጋፉ ድርቅ በተከሰተባቸዉ የአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ደቡብ እና ሶማሌ ክልሎች ጉዳት ለደረሰባቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች እርዳታ የሚውል ነዉም ተብሏል፡፡
በሶማሌ፣ ኦሮሚያና ደቡብ ክልሎች ሙሉ በሙሉና በከፊል በተደጋጋሚ ዝናብ ወቅቱን ጠብቆ ባለመዝነቡ እንደዚሁም በአማራ ክልል በነበረው ግጭት ምክንያት በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች ለምግብ እህል እርዳታ መዳረጋቸው ይታወቃል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
እስረኞች እንዲለቀቁ ኢሰመኮ ጠየቀ!
የኢትዮጵያ መንግስት ካለፈዉ ጥቅምት እስከ ትናንት ፀንቶ በነበረዉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሠረት ያሰራቸዉን ተጠርጣሪዎች እንዲለቅ የሐገሪቱ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ጠየቀ።የኢትዮጵያ መንግስት በአሸባሪነት የፈረጀዉ ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ወደ አዲስ አበባ ተቃርቦ በነበረበት ባለፈዉ ጥቅምት 23 የተደነገገዉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ትናንት ተነስቷል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አዋጁ እንዲነሳ በድምፅ ከመወሰኑ በፊት በተደረገዉ ዉይይት የተወሰኑ የምክር ቤቱ አባላት አዋጁ እንዳይነሳ አጥብቀዉ ተከራክረዉ ነበር።መንግሥት የሚቆጣጠረዉ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በፌስ ቡክ ገፁ ባሰራጨዉ መልዕት እንዳለዉ ግን «አዋጁ እንዲነሳ መወሰኑን በበጎ ተመልክቶታል።»አዋጁ ባለፈዉ ከተደነገገ በኋላ ከሕወሓትና ከኦነግ ሸኔ ጋር ግንኙነት አላቸዉ ተብለዉ የተጠረጠሩ በርካታ ሰዎች ታስረዋል።ከእስረኞቹ የተወሰኑት ግን ተለቅቀዋል።
ኢሰመኮ ዛሬ ባሰራጨዉ መልዕክቱ በአዋጁ መሠረት ታስረዉ እስካሁን ያልተለቀቁ ሰዎች «በአፋጣኝ» እንዲለቀቁ አሳስቧል።ከዚሕ ቀደም የተለቀቁትም ታስረዉ ስለመቆየታቸዉ ማረጋገጪያ ሥላልተሰጣቸዉ ወደ ስራ መመለስ አልቻሉም፤ መስራት ባለመቻላቸዉም ለማሕበራዊና ኤኮኖሚያዊ ችግር መጋለጣቸዉን ኢሰመኮ «በክትትል ደርሼበታለሁ» ይላል።ለተለቀቁት ሰዎች በእስር የቆዩበትን ጊዜ የሚገልፅ ማስረጃና አስፈላጊ ሰነዶችን የመስጠቱ ሒደት እንዲፋጠን ጠይቋል።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ መንግስት ካለፈዉ ጥቅምት እስከ ትናንት ፀንቶ በነበረዉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሠረት ያሰራቸዉን ተጠርጣሪዎች እንዲለቅ የሐገሪቱ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ጠየቀ።የኢትዮጵያ መንግስት በአሸባሪነት የፈረጀዉ ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ወደ አዲስ አበባ ተቃርቦ በነበረበት ባለፈዉ ጥቅምት 23 የተደነገገዉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ትናንት ተነስቷል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አዋጁ እንዲነሳ በድምፅ ከመወሰኑ በፊት በተደረገዉ ዉይይት የተወሰኑ የምክር ቤቱ አባላት አዋጁ እንዳይነሳ አጥብቀዉ ተከራክረዉ ነበር።መንግሥት የሚቆጣጠረዉ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በፌስ ቡክ ገፁ ባሰራጨዉ መልዕት እንዳለዉ ግን «አዋጁ እንዲነሳ መወሰኑን በበጎ ተመልክቶታል።»አዋጁ ባለፈዉ ከተደነገገ በኋላ ከሕወሓትና ከኦነግ ሸኔ ጋር ግንኙነት አላቸዉ ተብለዉ የተጠረጠሩ በርካታ ሰዎች ታስረዋል።ከእስረኞቹ የተወሰኑት ግን ተለቅቀዋል።
ኢሰመኮ ዛሬ ባሰራጨዉ መልዕክቱ በአዋጁ መሠረት ታስረዉ እስካሁን ያልተለቀቁ ሰዎች «በአፋጣኝ» እንዲለቀቁ አሳስቧል።ከዚሕ ቀደም የተለቀቁትም ታስረዉ ስለመቆየታቸዉ ማረጋገጪያ ሥላልተሰጣቸዉ ወደ ስራ መመለስ አልቻሉም፤ መስራት ባለመቻላቸዉም ለማሕበራዊና ኤኮኖሚያዊ ችግር መጋለጣቸዉን ኢሰመኮ «በክትትል ደርሼበታለሁ» ይላል።ለተለቀቁት ሰዎች በእስር የቆዩበትን ጊዜ የሚገልፅ ማስረጃና አስፈላጊ ሰነዶችን የመስጠቱ ሒደት እንዲፋጠን ጠይቋል።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ በማከናወንና አስፈላጊ የሰነድ ማሻሻያዎችን በማድረግ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያስገቡ ምርጫ ቦርድ አሳሰበ!
ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ በማከናወንና አስፈላጊ የሰነድ ማሻሻያዎችን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በማድረግ እንዲያስገቡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አሳሰበ፡፡
ምርጫ ቦርዱ ህዳር 23 ቀን 2014 ከፓርቲዎች ጋር ባደረገው ምክክር በአዋጅ ቁጥር 1162/11 እና በመመሪያ ቁጥር 3/2011 መሠረት ከ6ኛው አገራዊ ምርጫ መጠናቀቅ በኋላ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያካሂዱና የሰነድ ማሻሻያ እንዲያደርጉ የተገለፀላቸው ፓርቲዎች የሚጠበቅባቸውን አጠናቀው ባለማቅረባቸው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በተነሳ በአንድ ወር ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤያቸውን እንዲያከናውኑ እና ለቦርዱ እንዲያስገቡ መወሰኑ በምክክሩ ወቅትም ለፓርቲዎች መገለጹን አስታውሷል።
በዚህም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ መወሰኑን ተከትሎ ከስር ስማቸው የተዘረዘረ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ በማከናወን እንዲሁም አስፈላጊ የሰነድ ማሻሻያዎችን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በማድረግ እንዲያስገቡ ምርጫ ቦርድ አሳስቧል።
አገራዊ ፓርቲዎችም ፥ የኦሮሞ ነፃነት ንቅናቄ፣ የኢትዮጵያ ነፃነት ፓርቲ ፣ የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ፣ ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ፣ የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት፣ የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር፣ ብልፅግና ፓርቲ ፣ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ፣ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ፣ ኅብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ናቸው፡፡
በተጨማሪም ክልላዊ ፓርቲዎች ፥ የሲዳማ አርነት ንቅናቄ፣ ካፋ አረንጓዴ ፓርቲ፣ የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ፣ ሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ ኅዳሴ ፓርቲ፣ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የአፋር ሕዝቦች ፍትሐዊ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ፣ ቦሮ ዴሞክራቲክ ፓርቲ፣ ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲ ሉዓላዊነት፣ የአርጎባ ብሔረሰብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣ የአርጎባ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅትእና የጋሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ መሆናቸውን ምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ በማከናወንና አስፈላጊ የሰነድ ማሻሻያዎችን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በማድረግ እንዲያስገቡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አሳሰበ፡፡
ምርጫ ቦርዱ ህዳር 23 ቀን 2014 ከፓርቲዎች ጋር ባደረገው ምክክር በአዋጅ ቁጥር 1162/11 እና በመመሪያ ቁጥር 3/2011 መሠረት ከ6ኛው አገራዊ ምርጫ መጠናቀቅ በኋላ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያካሂዱና የሰነድ ማሻሻያ እንዲያደርጉ የተገለፀላቸው ፓርቲዎች የሚጠበቅባቸውን አጠናቀው ባለማቅረባቸው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በተነሳ በአንድ ወር ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤያቸውን እንዲያከናውኑ እና ለቦርዱ እንዲያስገቡ መወሰኑ በምክክሩ ወቅትም ለፓርቲዎች መገለጹን አስታውሷል።
በዚህም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ መወሰኑን ተከትሎ ከስር ስማቸው የተዘረዘረ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ በማከናወን እንዲሁም አስፈላጊ የሰነድ ማሻሻያዎችን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በማድረግ እንዲያስገቡ ምርጫ ቦርድ አሳስቧል።
አገራዊ ፓርቲዎችም ፥ የኦሮሞ ነፃነት ንቅናቄ፣ የኢትዮጵያ ነፃነት ፓርቲ ፣ የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ፣ ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ፣ የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት፣ የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር፣ ብልፅግና ፓርቲ ፣ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ፣ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ፣ ኅብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ናቸው፡፡
በተጨማሪም ክልላዊ ፓርቲዎች ፥ የሲዳማ አርነት ንቅናቄ፣ ካፋ አረንጓዴ ፓርቲ፣ የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ፣ ሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ ኅዳሴ ፓርቲ፣ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የአፋር ሕዝቦች ፍትሐዊ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ፣ ቦሮ ዴሞክራቲክ ፓርቲ፣ ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲ ሉዓላዊነት፣ የአርጎባ ብሔረሰብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣ የአርጎባ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅትእና የጋሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ መሆናቸውን ምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ሀገራዊ ምክክሩ በፓርላማ በአሸባሪነት የተፈረጁ አካላትን እንደማያካትት ብልፅግና ፓርቲ ገለፀ!
በኮሚሽነሮች ምርጫ ሂደት ላይ የሚገኘው ሀገራዊ የምክክር መድረክ “በህዝብ እንደራሴዎች በኩል አሸባሪ ተብለው ከተፈረጁ አካላት ጋር መደራደር ማለት አይደለም” ሲል ዛሬ በማህበራዊ የትስስር ገጹ ላይ ባሰፈረዉ ጽሁፍ አመለከተ።
በታህሳስ ወር 2014 ዓ.ም. አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ለአናዶሉ ኤጀንሲ እንደገለፁት “ጉዳዩ እኔ የምናገርበት ባይሆንም፤ ህወሓት ወታደራዊ ትጥቁን የሚፈታ እና በውስጡ የሚገኙ ወንጀለኞችን አሳልፎ የሚሰጥ ከሆነ በሀገርዊ ምክክሩ ሊሳተፍ ይችላል” ማለታቸው መዘገቡ የሚታወስ ነው።
የሀገራዊ ምክክሩ ዋና ዓላማ እንደ ህገ መንግስት እና ሰንደቅ ዓላማ ባሉ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከፋፋይ ሀሳቦችን በሚያቀራርቡ ሀሳቦች መተካት ማስቻል ነው ሲል ፓርቲዉ በጽሁፉ ገልጿል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ 42 እጩ ኮሚሽነሮችን በህዝብ ድምፅ ሰብስቦ ይፋ ያደረገ ሲሆን የምክክር ኮሚሽኑ በ11 ኮሚሽነሮች እንደሚመራ መገልፁ ይታወሳል።
[@AddisZeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
በኮሚሽነሮች ምርጫ ሂደት ላይ የሚገኘው ሀገራዊ የምክክር መድረክ “በህዝብ እንደራሴዎች በኩል አሸባሪ ተብለው ከተፈረጁ አካላት ጋር መደራደር ማለት አይደለም” ሲል ዛሬ በማህበራዊ የትስስር ገጹ ላይ ባሰፈረዉ ጽሁፍ አመለከተ።
በታህሳስ ወር 2014 ዓ.ም. አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ለአናዶሉ ኤጀንሲ እንደገለፁት “ጉዳዩ እኔ የምናገርበት ባይሆንም፤ ህወሓት ወታደራዊ ትጥቁን የሚፈታ እና በውስጡ የሚገኙ ወንጀለኞችን አሳልፎ የሚሰጥ ከሆነ በሀገርዊ ምክክሩ ሊሳተፍ ይችላል” ማለታቸው መዘገቡ የሚታወስ ነው።
የሀገራዊ ምክክሩ ዋና ዓላማ እንደ ህገ መንግስት እና ሰንደቅ ዓላማ ባሉ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከፋፋይ ሀሳቦችን በሚያቀራርቡ ሀሳቦች መተካት ማስቻል ነው ሲል ፓርቲዉ በጽሁፉ ገልጿል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ 42 እጩ ኮሚሽነሮችን በህዝብ ድምፅ ሰብስቦ ይፋ ያደረገ ሲሆን የምክክር ኮሚሽኑ በ11 ኮሚሽነሮች እንደሚመራ መገልፁ ይታወሳል።
[@AddisZeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአውሮፓ ሕብረት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ቻርልስ ሚሼል ጋር ተወያዩ።
"ከአፍሪካ ኅብረት እና ከአውሮፓ ኅብረት የጋራ ጉባኤ አስቀድሞ ከወዳጄ ፕሬዚደንት ቻርልስ ሚሼል ጋር ተገናኝተናል" ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሑፍ።
የአውሮፓ ኅብረት እና የኢትዮጵያን ግንኙነት፣ ቀጣናዊ እንዲሁም አህጉራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውንም ገልፀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
"ከአፍሪካ ኅብረት እና ከአውሮፓ ኅብረት የጋራ ጉባኤ አስቀድሞ ከወዳጄ ፕሬዚደንት ቻርልስ ሚሼል ጋር ተገናኝተናል" ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሑፍ።
የአውሮፓ ኅብረት እና የኢትዮጵያን ግንኙነት፣ ቀጣናዊ እንዲሁም አህጉራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውንም ገልፀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa