ኢትዮጵያ ውስጥ ወንጀለኞች ቴክኖሎጂን በመጠቀም ፖሊስን እንደሚቀድሙ ተገለጸ!
ወንጀለኞች የተወሳሰበ እና ዘመናዊ ቴክሎጂዎችን በመጠቀም ፖሊስን እየተገዳደሩ መሆኑን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። ፖሊስ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ቀድሞ መታጠቅና ወንጀልን ቀድሞ መከላከል ላይ ማተኮር አለበት በሚል ታቅዶ እየተሠራ መሆኑም ተገልጿል።
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል እና የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ፕሬዚዳንት አቶ መስፍን አበበ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት፤ በዓለምም ሆነ በኢትዮጵያ ውስጥ በአሁኑ ወቅት ቴክኖሎጂን ተገን አድርገው በርካታ ወንጀሎች እየተፈፀሙ መሆናቸውን ጠቁመዋል።ይህም የፖሊስን ሥራ ፈታኝ እና በእጅጉ ጥንቃቄ በታከለበት ሁኔታ እንደሚሠራ እያስገደደ መሆኑን አብራርተዋል።
በኢትዮጵያ ውስጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመታጠቅ ብዙ ጥረቶች እየተደረጉ ቢሆንም አሁንም ያለው በጣም ኋላቋር ነው ያሉት ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን፤ ‹‹ወንጀለኞች ቴክኖሎጂ በመታጠቅ በንፅፅር ይቀድማሉ። በሳይበር እና በሶሻል ሚዲያ የሚፈፀም ወንጀልም እየረቀቀ ነው። ለአብነት በቴሌ ላይ እየተሰሩ ያሉ ወንጀሎችን በሚሊዮኖች እና በቢሊዮኖች ኪሳራ አደረሱ ሲባል ይሰማል። ይህን ከወንጀለኞች ሰምተን እንጂ ቀድመን አውቀን የማስቀረት አቅም የለንም›› ብለዋል።
በመሆኑም እንደ ፖሊስ ቴክኖሎጂን ቀድሞ መታጠቅና ወንጀልን ቀድሞ መከላከል አለብን በሚል ታቅዶ እየተሠራ ነው ያሉት ኮሚሽነር ጄኔራል መስፍን፤ ወንጀል ቢፈፀም እንኳን በፍጥነት ማወቅ አለብን ብለዋል። በቀጣይም በቴክኖሎጂ የትምህርት ክፍል የቴክኖሎጂ ፖሊሲንግ የመከፈት ውጥን ያለ ሲሆን በዚህም ምርምር ማድረግ፣ ባለሙያ የማፍራት እና ቴክኖሎጂን የመታጠቅ አስፈላጊነት ታምኖበት እየተሠራ ነው ብለዋል።
[ኢ.ፕ.ድ]
@YeneTube
ወንጀለኞች የተወሳሰበ እና ዘመናዊ ቴክሎጂዎችን በመጠቀም ፖሊስን እየተገዳደሩ መሆኑን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። ፖሊስ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ቀድሞ መታጠቅና ወንጀልን ቀድሞ መከላከል ላይ ማተኮር አለበት በሚል ታቅዶ እየተሠራ መሆኑም ተገልጿል።
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል እና የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ፕሬዚዳንት አቶ መስፍን አበበ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት፤ በዓለምም ሆነ በኢትዮጵያ ውስጥ በአሁኑ ወቅት ቴክኖሎጂን ተገን አድርገው በርካታ ወንጀሎች እየተፈፀሙ መሆናቸውን ጠቁመዋል።ይህም የፖሊስን ሥራ ፈታኝ እና በእጅጉ ጥንቃቄ በታከለበት ሁኔታ እንደሚሠራ እያስገደደ መሆኑን አብራርተዋል።
በኢትዮጵያ ውስጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመታጠቅ ብዙ ጥረቶች እየተደረጉ ቢሆንም አሁንም ያለው በጣም ኋላቋር ነው ያሉት ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን፤ ‹‹ወንጀለኞች ቴክኖሎጂ በመታጠቅ በንፅፅር ይቀድማሉ። በሳይበር እና በሶሻል ሚዲያ የሚፈፀም ወንጀልም እየረቀቀ ነው። ለአብነት በቴሌ ላይ እየተሰሩ ያሉ ወንጀሎችን በሚሊዮኖች እና በቢሊዮኖች ኪሳራ አደረሱ ሲባል ይሰማል። ይህን ከወንጀለኞች ሰምተን እንጂ ቀድመን አውቀን የማስቀረት አቅም የለንም›› ብለዋል።
በመሆኑም እንደ ፖሊስ ቴክኖሎጂን ቀድሞ መታጠቅና ወንጀልን ቀድሞ መከላከል አለብን በሚል ታቅዶ እየተሠራ ነው ያሉት ኮሚሽነር ጄኔራል መስፍን፤ ወንጀል ቢፈፀም እንኳን በፍጥነት ማወቅ አለብን ብለዋል። በቀጣይም በቴክኖሎጂ የትምህርት ክፍል የቴክኖሎጂ ፖሊሲንግ የመከፈት ውጥን ያለ ሲሆን በዚህም ምርምር ማድረግ፣ ባለሙያ የማፍራት እና ቴክኖሎጂን የመታጠቅ አስፈላጊነት ታምኖበት እየተሠራ ነው ብለዋል።
[ኢ.ፕ.ድ]
@YeneTube
ጓደኛዋን የገደለችው ግለሰብ 25 አመት ተፈረደባት!
በአዳማ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ጎሮ ቀበሌ ውስጥ የሴት ጓደኛዋን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል የተከሰሰችው ሴት ላይ የ25 አመት ፅኑ እስራት ፍርድ ተላለፈ።
ሩሃማ ጀማል የተባለችው ግለሰብ ለ12 አመታት አብራት የኖረችውን ሟች ከዲራ አሊን ሀምሌ 7 ቀን 2012 ዓም ከሌሊቱ 5 ሰዓት ገደማ ባልታወቀ ምክንያት ሟች በተኛችበት በጥርሶቿ የሟችን ጆር፣ አፍንጫ ፣ጉንጯን እና ከንፈሯን ከነከሰቻት በኋላ በዱላ በመደብደብ እንዲሁም የሟችን ደም በመምጠጥ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሷን ፖሊስ በማስረጃ ማረጋገጥ ችሏል።
በወቅቱም ሟች በንክሻው ሰዓት ባሰማችው የድረሱልኝ ጥሪ ጎረቤቶቿ ፖሊስ በመጥራት በስፍራው ፖሊስ ሲደርስ ሟች ተዘርራ መመልከቱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
ተጎጂዋን በፍጥነት በማንሳት ወደ አዳማ ሆስፒታል ቢያደርሷትም ነገር ግን ከፍተኛ ጉዳት በመድረሱ ወደ አዲስ አበባ ባልቻ ሆስፒታል ሪፈር እንደተደረገችና ባልቻ ሆስፒታል ለ15 ቀናት ህክምና ስትከታተል ቆይታ ህይወቷ መለፉን መረጃው አካቷል።
ከሳሽ አቃቤ ህግም በአሰቃቂ ግድያ ወንጀል የምርመራ መዝገብ በመክፈት ለአዳማ ከተማ ከፍተኛ ዞን ፍርድ ቤት አቀርቧል።ፍርድ ቤቱም በተከሳሽ ላይ የቀረበውን የሰው ምስክር እና የሰነድ ማሥረጃ በመመርመር ትናንት ታህሳስ 5 ቀን 2013 በዋለው ችሎት ተከሳሽ በፈፀመችው አሰቃቂ ግድያ በ25 አመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ መወሰኑን የአዳማ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግኑኝነት ባለሞያ ኢንስፔክተር ወርቅነሽ ገልሜቻ ለአዲስ ዘይቤ ገልፃለች።
[@addiszeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዳማ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ጎሮ ቀበሌ ውስጥ የሴት ጓደኛዋን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል የተከሰሰችው ሴት ላይ የ25 አመት ፅኑ እስራት ፍርድ ተላለፈ።
ሩሃማ ጀማል የተባለችው ግለሰብ ለ12 አመታት አብራት የኖረችውን ሟች ከዲራ አሊን ሀምሌ 7 ቀን 2012 ዓም ከሌሊቱ 5 ሰዓት ገደማ ባልታወቀ ምክንያት ሟች በተኛችበት በጥርሶቿ የሟችን ጆር፣ አፍንጫ ፣ጉንጯን እና ከንፈሯን ከነከሰቻት በኋላ በዱላ በመደብደብ እንዲሁም የሟችን ደም በመምጠጥ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሷን ፖሊስ በማስረጃ ማረጋገጥ ችሏል።
በወቅቱም ሟች በንክሻው ሰዓት ባሰማችው የድረሱልኝ ጥሪ ጎረቤቶቿ ፖሊስ በመጥራት በስፍራው ፖሊስ ሲደርስ ሟች ተዘርራ መመልከቱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
ተጎጂዋን በፍጥነት በማንሳት ወደ አዳማ ሆስፒታል ቢያደርሷትም ነገር ግን ከፍተኛ ጉዳት በመድረሱ ወደ አዲስ አበባ ባልቻ ሆስፒታል ሪፈር እንደተደረገችና ባልቻ ሆስፒታል ለ15 ቀናት ህክምና ስትከታተል ቆይታ ህይወቷ መለፉን መረጃው አካቷል።
ከሳሽ አቃቤ ህግም በአሰቃቂ ግድያ ወንጀል የምርመራ መዝገብ በመክፈት ለአዳማ ከተማ ከፍተኛ ዞን ፍርድ ቤት አቀርቧል።ፍርድ ቤቱም በተከሳሽ ላይ የቀረበውን የሰው ምስክር እና የሰነድ ማሥረጃ በመመርመር ትናንት ታህሳስ 5 ቀን 2013 በዋለው ችሎት ተከሳሽ በፈፀመችው አሰቃቂ ግድያ በ25 አመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ መወሰኑን የአዳማ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግኑኝነት ባለሞያ ኢንስፔክተር ወርቅነሽ ገልሜቻ ለአዲስ ዘይቤ ገልፃለች።
[@addiszeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ባለ ኹለት እግር ተሽከርካሪዎች በቁጥጥር ሥር እየዋሉ ነው!
የራሳቸውን ሰሌዳ ቁጥር ለጥፈው የሚንቀሳቀሱም ይገኙበታል።ማንኛውንም ባለ ሁለት እግር ተሽከርካሪ በሰዓት ከ40ኪሜ እና ከዛ በላይ የሚጓዙ ያለ ሰሌዳ ቁጥር መንቀሳቀስ እንደማይችሉ በ2011 የወጣ መመሪያ እንዳለ እና አሁን ተሽከርካሪዎቹን በቁጥጥር ሥር እያዋሉ እንደሚገኙ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ለአዲስ ማለዳ አስታወቋል።
በሞተር ብቻ የሚሠሩ፣ በኤሌትሪክ ኃይል የሚሠሩ፣ በጸሐይ ኃይል የሚሠሩ እንዲሁም በፔዳል የሚሠሩትን ተሽከርካሪዎች በጠቅላላ በቁጥጥር ላይ እያዋሉ እንዳለና ይህም አግባብነት ያለው የሕግ ማስከበር ሥራ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ስጦታው አካለ ለአዲስ ማለዳ አስታወቀዋል።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
የራሳቸውን ሰሌዳ ቁጥር ለጥፈው የሚንቀሳቀሱም ይገኙበታል።ማንኛውንም ባለ ሁለት እግር ተሽከርካሪ በሰዓት ከ40ኪሜ እና ከዛ በላይ የሚጓዙ ያለ ሰሌዳ ቁጥር መንቀሳቀስ እንደማይችሉ በ2011 የወጣ መመሪያ እንዳለ እና አሁን ተሽከርካሪዎቹን በቁጥጥር ሥር እያዋሉ እንደሚገኙ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ለአዲስ ማለዳ አስታወቋል።
በሞተር ብቻ የሚሠሩ፣ በኤሌትሪክ ኃይል የሚሠሩ፣ በጸሐይ ኃይል የሚሠሩ እንዲሁም በፔዳል የሚሠሩትን ተሽከርካሪዎች በጠቅላላ በቁጥጥር ላይ እያዋሉ እንዳለና ይህም አግባብነት ያለው የሕግ ማስከበር ሥራ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ስጦታው አካለ ለአዲስ ማለዳ አስታወቀዋል።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
የአረና ፓርቲ ሊቀመንበር አብርሃ ደስታ የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሾሙ!
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የተፎካካሪ ፓርቲዎች አመራሮችና አባላት ማካተቱን እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ወደ ስራ መግባቱን አስታውቋል፡፡
[Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የተፎካካሪ ፓርቲዎች አመራሮችና አባላት ማካተቱን እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ወደ ስራ መግባቱን አስታውቋል፡፡
[Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
"በክልሎች መካከል እየታየ ያለው የብሽሽቅ ፖለቲካ ስንጥቅ ሊደፈን የሚችለው ኃላፊነት የሚሰማው ውሳኔ እስከተወሰነ ድረስ ብቻ ነው" ሲሉ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አብርሃም አለኸኝ ተናገሩ።
"ቃላትን ከሰው ህይወት መጥፋት በላይ በሚመነዝር የፖለቲካ ገበያ ውስጥ ቀውስ መቆጣጠር የሚችል ገለልተኛ የአመራር አቅምና አሰላለፍ ይኖራል ብሎ ማሰብ ከብሳና ዛፍ አፕል ለመቁረጥ መሞከር ነው"፣ ስለሆነም የፌዴራል መንግስት የቀውስ ጊዜ አስቸኳይ አመራር ካላረጋገጠ በስተቀር ማንነትን ለይቶ የሚፈጸም ጥቃት ድህረ ትህነግ አገሪቷን የማትወጣበት ቅርቃር ውስጥ ሊያስገባት እንደሚችል ማወቅ አለበት።" ብለዋል።
[የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ]
@YeneTube @FikerAssefa
"ቃላትን ከሰው ህይወት መጥፋት በላይ በሚመነዝር የፖለቲካ ገበያ ውስጥ ቀውስ መቆጣጠር የሚችል ገለልተኛ የአመራር አቅምና አሰላለፍ ይኖራል ብሎ ማሰብ ከብሳና ዛፍ አፕል ለመቁረጥ መሞከር ነው"፣ ስለሆነም የፌዴራል መንግስት የቀውስ ጊዜ አስቸኳይ አመራር ካላረጋገጠ በስተቀር ማንነትን ለይቶ የሚፈጸም ጥቃት ድህረ ትህነግ አገሪቷን የማትወጣበት ቅርቃር ውስጥ ሊያስገባት እንደሚችል ማወቅ አለበት።" ብለዋል።
[የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ]
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
"በክልሎች መካከል እየታየ ያለው የብሽሽቅ ፖለቲካ ስንጥቅ ሊደፈን የሚችለው ኃላፊነት የሚሰማው ውሳኔ እስከተወሰነ ድረስ ብቻ ነው" ሲሉ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አብርሃም አለኸኝ ተናገሩ። "ቃላትን ከሰው ህይወት መጥፋት በላይ በሚመነዝር የፖለቲካ ገበያ ውስጥ ቀውስ መቆጣጠር የሚችል ገለልተኛ የአመራር አቅምና አሰላለፍ ይኖራል ብሎ ማሰብ ከብሳና ዛፍ አፕል ለመቁረጥ መሞከር ነው"፣…
ሃላፊው ይህንን ያሉት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብልፅግና ፓርቲ ታኅሣሥ 6 ባወጣው መግለጫ ‹‹በሕገ መንግሥት የተደራጀ ክልል ውስጥ ከፌደራል መንግሥት ዕውቅና ውጭ ገብቼ እዋጋለሁ ብሎ በተደጋጋሚ ዛቻ እና ማስፈራሪያ አዛል ቃላት ጭምር በመጠቀም መግላጫ መስጠት በሕዝቦች መካከል ግልፅ ጦርነት ማወጅ ነው›› ሲል በከሰሰ ማግስት ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
አንጋፋው የጥበብ ባለሙያ ተባባሪ ፕሮፌሰር ተስፋዬ ገሰሰ በ84 አመት እድሜአቸው ዛሬ ታህሳስ 7 ቀን 2013 ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ አትክልት ተራ በአዲሱ የገበያ ማዕከል ከነገ ጀምሮ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ተገለጸ፡፡
የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልፈታ የሱፍ በሰጡት መግለጫ ጃንሜዳ የሚገኘው ጊዜያዊ አትክልትና ፍራፍሬ መሸጫ የገበያ ስፍራ የከተማው አስተዳደር ባዘጋጀው የገበያ ማዕከል እንዲዘዋወሩ በተወሰነው መሰረት የዕጣ ማውጣት ስርዓቱ ተጠናቆ ውል መዋዋል ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
በዛሬው ዕለት ተጠናቆ ከነገ ጀምሮ ጃንሜዳ የነበረው አትክልት ተራ ሀይሌ ጋርመንት አካባቢ በተገነባው የአትክልትና ፍራፍሬ መሸጫ ገበያ ማዕከል ተዘዋውሮ ስራ የሚጀምር መሆኑን ከአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል ፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልፈታ የሱፍ በሰጡት መግለጫ ጃንሜዳ የሚገኘው ጊዜያዊ አትክልትና ፍራፍሬ መሸጫ የገበያ ስፍራ የከተማው አስተዳደር ባዘጋጀው የገበያ ማዕከል እንዲዘዋወሩ በተወሰነው መሰረት የዕጣ ማውጣት ስርዓቱ ተጠናቆ ውል መዋዋል ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
በዛሬው ዕለት ተጠናቆ ከነገ ጀምሮ ጃንሜዳ የነበረው አትክልት ተራ ሀይሌ ጋርመንት አካባቢ በተገነባው የአትክልትና ፍራፍሬ መሸጫ ገበያ ማዕከል ተዘዋውሮ ስራ የሚጀምር መሆኑን ከአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል ፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
የአረና ፓርቲ ሊቀመንበር አብርሃ ደስታ የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሾሙ! የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የተፎካካሪ ፓርቲዎች አመራሮችና አባላት ማካተቱን እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ወደ ስራ መግባቱን አስታውቋል፡፡ [Al-ain] @YeneTube @FikerAssefa
አቶ አበርሀ ደስታ ስለሹመቱ የሚያውቀው ነገር እንደሌለ ገለፀ!
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ ሆኖ መሾሙን የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት አስታውቋል፡፡
አዲስ ዘይቤ ለአዲሱ ተሿሚ በመደወል ስለሹመቱ ጥያቄ አቅርቤ «ምንም የማውቀው ነገር የለም፡፡ የነገረኝም ሰው የለም» ብሎኛል ሲል ዘግቧል።
አቶ አብረሃ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር እና የአረና ፓርቲ ሊቀመንበር ነው፡፡
[@addiszeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ ሆኖ መሾሙን የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት አስታውቋል፡፡
አዲስ ዘይቤ ለአዲሱ ተሿሚ በመደወል ስለሹመቱ ጥያቄ አቅርቤ «ምንም የማውቀው ነገር የለም፡፡ የነገረኝም ሰው የለም» ብሎኛል ሲል ዘግቧል።
አቶ አብረሃ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር እና የአረና ፓርቲ ሊቀመንበር ነው፡፡
[@addiszeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል በዘር ለሚተላለፍ በሽታ አዲስ ሕክምና ሊጀምር ነው!
በአገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በተፈጥሮ ከእናት እና ከአባት በዘር የሚተላለፍ ‘ Cystic fibrosis’ የተባለ የመተንፈሻ አካላትን የሚጎዳ በሽታን ለመመርመር ሥራ ሊጀምር መሆኑን ቅዱስ ጳውሎስ ሚሊንየም ሕክምና ኮሌጅ አስታወቀ።
እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ሕክምናውን ለመመርመር የሚያስችል ምንም ዓይነት የመመርመሪያ መሣሪያ አገር ውስጥ እንዳልነበር እና በአሁኑ ወቅት ግን መሣሪያውን ከመካከለኛው ምስራቅ ‘ Cystic fibrosis’ ማኅበር በእርዳታ መልክ ማግኘታቸውን እና በአሁኑ ሰዓትም መሣሪያው በሆስፒታሉ እንደሚገኝ አሳውቋል።
[አዲስ ማለዳ]
@YeneTube @FikerAssefa
በአገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በተፈጥሮ ከእናት እና ከአባት በዘር የሚተላለፍ ‘ Cystic fibrosis’ የተባለ የመተንፈሻ አካላትን የሚጎዳ በሽታን ለመመርመር ሥራ ሊጀምር መሆኑን ቅዱስ ጳውሎስ ሚሊንየም ሕክምና ኮሌጅ አስታወቀ።
እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ሕክምናውን ለመመርመር የሚያስችል ምንም ዓይነት የመመርመሪያ መሣሪያ አገር ውስጥ እንዳልነበር እና በአሁኑ ወቅት ግን መሣሪያውን ከመካከለኛው ምስራቅ ‘ Cystic fibrosis’ ማኅበር በእርዳታ መልክ ማግኘታቸውን እና በአሁኑ ሰዓትም መሣሪያው በሆስፒታሉ እንደሚገኝ አሳውቋል።
[አዲስ ማለዳ]
@YeneTube @FikerAssefa
የቀድሞው የኢህዴሪ መንግስት ጠቅላይ ሚኒስትር ፍቅረሥላሴ ወግደረስ የቀብር ስነ-ስርዓት ተፈፀመ!
የቀድሞው የኢህዲሪ መንግስት ጠቅላይ ሚኒስትር ፍቅረሥላሴ ወግደረስ የቀብር ስነ ስርዓት ነገ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈፅሟል።ፍቅረሥላሴ ወግደረስ ከጳጉሜን 5 ቀን 1979 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 29 ቀን 1982 ዓ.ም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን ያገለገሉ ናቸው።ፍቅረሥላሴ ወግደረስ የተወለዱት ሐምሌ 7 ቀን 1937 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተለምዶ ቀጨኔ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ነው።
በተለያዩ የሥልጣን እርከኖች አገራቸውን ያገለገሉት ፍቅረሥላሴ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ፓርቲ (ኢሰፓ) አደራጅ ኮሚቴ እና የደርግ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ነበሩ።"እኛና አብዮቱ እና እኔና አብዮቱ” በሚል ርዕስ ሁለት መጽሐፍት ጽፈው ለአንባቢያን አድርሰዋል።ፍቅረሥላሴ ወግደረስ የሁለት ሴት እና የአንድ ወንድ ልጅ አባት እንደነበሩ የሕይወት ታሪካቸው ያስረዳል።
Via Walta
@YeneTube @FikerAssefa
የቀድሞው የኢህዲሪ መንግስት ጠቅላይ ሚኒስትር ፍቅረሥላሴ ወግደረስ የቀብር ስነ ስርዓት ነገ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈፅሟል።ፍቅረሥላሴ ወግደረስ ከጳጉሜን 5 ቀን 1979 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 29 ቀን 1982 ዓ.ም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን ያገለገሉ ናቸው።ፍቅረሥላሴ ወግደረስ የተወለዱት ሐምሌ 7 ቀን 1937 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተለምዶ ቀጨኔ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ነው።
በተለያዩ የሥልጣን እርከኖች አገራቸውን ያገለገሉት ፍቅረሥላሴ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ፓርቲ (ኢሰፓ) አደራጅ ኮሚቴ እና የደርግ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ነበሩ።"እኛና አብዮቱ እና እኔና አብዮቱ” በሚል ርዕስ ሁለት መጽሐፍት ጽፈው ለአንባቢያን አድርሰዋል።ፍቅረሥላሴ ወግደረስ የሁለት ሴት እና የአንድ ወንድ ልጅ አባት እንደነበሩ የሕይወት ታሪካቸው ያስረዳል።
Via Walta
@YeneTube @FikerAssefa
#FactCheck
Via @EthiopiaCheck
የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ የሚሰጠውን ገንዘብ ሙሉ በሙሉ አቋረጠ፣ ግማሹን ቀነሰ ወዘተ የሚሉ መረጃዎች በስፋት እየተሰራጩ ይገኛሉ። ኢትዮጵያ ቼክ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ሀላፊ የሆኑትን አምባሳደር ዮሀን ቦርግስታምን በጉዳዩ ዙርያ አነጋግሯል።
አምባሳደሩ እንደሚሉት ህብረቱ ለኢትዮጵያ ከ2014 እስከ 2020 እአአ ላለው ግዜ 1.4 ቢልዮን ዩሮ መድቧል። ከዚህ ውስጥ 500 ሚልዮን ዩሮ ገደማው ለመንግስት በጀት ድጎማ ይውላል ያሉ ሲሆን 90 ሚልዮን ዩሮ ያክሉ የበጀት ድጎማ ግን አሁን ላይ ክፍያው እንዲዘገይ መደረጉን አረጋግጠዋል።
የአውሮፓ ህብረት ለምን 90 ሚልዮን ዩሮ የበጀት ድጎማውን እንዲዘገይ እንዳረገ ሲያስረዱ በትግራይ ክልል ካለው ሁኔታ ጋር እንደሚያያዝ ጠቅሰው "ሁሉም አካላት የሲቪሎች ደህንነትን እንዲጠብቁ፣ ዘርን መሰረት ያደረገ ጥቃት እንዲቆም፣ ስደተኞች ከለላ እንዲደረግላቸው፣ ቦታዎች ለሰብአዊ እርዳታ ክፍት እንዲሆኑ፣ ክልሉ ለሚድያዎች ክፍት እንዲሆን እንዲሁም መንግስት የጀመረው የተቋረጡ መገናኛዎች የመመለስ ስራ እንዲሰራ ህብረቱ ይፈልጋል" ብለዋል።
ህብረቱ ሙሉ ለሙሉ ድጋፉን እንዳቋረጠ እየተነገረ እና እየተፃፈ ያለው ግን ስህተት እንደሆነ ለኢትዮጵያ ቼክ ተናግረዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
Via @EthiopiaCheck
የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ የሚሰጠውን ገንዘብ ሙሉ በሙሉ አቋረጠ፣ ግማሹን ቀነሰ ወዘተ የሚሉ መረጃዎች በስፋት እየተሰራጩ ይገኛሉ። ኢትዮጵያ ቼክ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ሀላፊ የሆኑትን አምባሳደር ዮሀን ቦርግስታምን በጉዳዩ ዙርያ አነጋግሯል።
አምባሳደሩ እንደሚሉት ህብረቱ ለኢትዮጵያ ከ2014 እስከ 2020 እአአ ላለው ግዜ 1.4 ቢልዮን ዩሮ መድቧል። ከዚህ ውስጥ 500 ሚልዮን ዩሮ ገደማው ለመንግስት በጀት ድጎማ ይውላል ያሉ ሲሆን 90 ሚልዮን ዩሮ ያክሉ የበጀት ድጎማ ግን አሁን ላይ ክፍያው እንዲዘገይ መደረጉን አረጋግጠዋል።
የአውሮፓ ህብረት ለምን 90 ሚልዮን ዩሮ የበጀት ድጎማውን እንዲዘገይ እንዳረገ ሲያስረዱ በትግራይ ክልል ካለው ሁኔታ ጋር እንደሚያያዝ ጠቅሰው "ሁሉም አካላት የሲቪሎች ደህንነትን እንዲጠብቁ፣ ዘርን መሰረት ያደረገ ጥቃት እንዲቆም፣ ስደተኞች ከለላ እንዲደረግላቸው፣ ቦታዎች ለሰብአዊ እርዳታ ክፍት እንዲሆኑ፣ ክልሉ ለሚድያዎች ክፍት እንዲሆን እንዲሁም መንግስት የጀመረው የተቋረጡ መገናኛዎች የመመለስ ስራ እንዲሰራ ህብረቱ ይፈልጋል" ብለዋል።
ህብረቱ ሙሉ ለሙሉ ድጋፉን እንዳቋረጠ እየተነገረ እና እየተፃፈ ያለው ግን ስህተት እንደሆነ ለኢትዮጵያ ቼክ ተናግረዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
በ782 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል ተባለ!
በኦሮሚያ ክልል ከሕወሓት ቡድን ጋር በመቀናጀት ግጭቶች ሲያስነሱና ግድያ እና ዝርፊያ ሲፈጽሙ ነበሩ የተባሉ 782 የኦነግ ሸኔ 'የጥፋት ኃይሎች' ላይ እርምጃ መወሰዱን የኦሮሚያ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ባልቻ ገልጸዋል።
አቶ ጌታቸው ባልቻ ሰሞኑን በሆሮ ጉዱሩ ወለጋና በሌሎች ዞኖች ብሄርን መሰረት ያደረጉ ግጭት እንዲቀሰቀስ በማድረግ ግድያ በፈጸሙ የህወሓት ተላላኪዎች ላይ እርምጃ መወሰዱንም ገልጸዋል፡፡
ከወረዳ እስከ ቀበሌ ድረስ ህግን ማስከበር ባቃታቸውና ከኦነግ ሸኔ ቡድን ጋር በመሆን በንጹሃን ዜጎች ላይ የጥፋት ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ የመንግስት አመራሮች ላይ እርምጃ መወሰዱም ተገልጿል፡፡
በተደረገው ሕግ የማስከበር ስራ ቀላልና ከባድ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም አቶ ጌታቸው ገልጸዋል፡ ከዚህ በኋላም ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ብሄርን መሰረት ያደረጉ ግጭቶችን ለመቀስቀስ የሚንቀሳቀሱ የጥፋት ሃይሎችን የክልሉ መንግስት እንደማይታገስም አስረድተዋል፡፡
[ዋልታ]
@YeneTube @FikerAssefa
በኦሮሚያ ክልል ከሕወሓት ቡድን ጋር በመቀናጀት ግጭቶች ሲያስነሱና ግድያ እና ዝርፊያ ሲፈጽሙ ነበሩ የተባሉ 782 የኦነግ ሸኔ 'የጥፋት ኃይሎች' ላይ እርምጃ መወሰዱን የኦሮሚያ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ባልቻ ገልጸዋል።
አቶ ጌታቸው ባልቻ ሰሞኑን በሆሮ ጉዱሩ ወለጋና በሌሎች ዞኖች ብሄርን መሰረት ያደረጉ ግጭት እንዲቀሰቀስ በማድረግ ግድያ በፈጸሙ የህወሓት ተላላኪዎች ላይ እርምጃ መወሰዱንም ገልጸዋል፡፡
ከወረዳ እስከ ቀበሌ ድረስ ህግን ማስከበር ባቃታቸውና ከኦነግ ሸኔ ቡድን ጋር በመሆን በንጹሃን ዜጎች ላይ የጥፋት ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ የመንግስት አመራሮች ላይ እርምጃ መወሰዱም ተገልጿል፡፡
በተደረገው ሕግ የማስከበር ስራ ቀላልና ከባድ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም አቶ ጌታቸው ገልጸዋል፡ ከዚህ በኋላም ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ብሄርን መሰረት ያደረጉ ግጭቶችን ለመቀስቀስ የሚንቀሳቀሱ የጥፋት ሃይሎችን የክልሉ መንግስት እንደማይታገስም አስረድተዋል፡፡
[ዋልታ]
@YeneTube @FikerAssefa
ወደ አንድነት ፓርክ የሚወስደው መንገድ አዲስ በሚገነባ የውስጥ ለውስጥ የዋሻ መንገድ ግንባታ ምክንያት ከነገ ጀምሮ ለአንድ ወር እንደሚዘጋ ተገለፀ።
በታላቁ ቤተመንግስት ወደ አንድነት ፓርክ የሚወስደው መንገድ የውስጥ ለውስጥ የዋሻ መንገድ ግንባታ ስለሚጀመር አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ አስታውቋል።የታላቁ ቤተመንግስት እና አንድነት ፓርክን ያለ ትራፊክ መጨናነቅ መጎብኘት የሚያስችል የውስጥ ለውስጥ የዋሻ መንገድ ግንባታ ምክንያት ከነገ ህዳር 08/2013 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ወር የተወሰኑ መንገዶች ዝግ እንደሚሆኑ ኤጀንሲ አስታውቋል።
ከሂልተን ሆቴል ተነስቶ ወደ ቀኝ የሚታጠፉ ተሸከርካሪዎች እና ከካሳንችስ ወደ 4 ኪሎ የሚያስወጣው መንገድ ከነገ ህዳር 08/2013 ዓ.ም ጀምሮ የሚዘጋ በመሆኑ አሽከርካሪዎችም ኢንተርኮንትኔታል ሆቴል፣ በንግድ ሚንስቴር፣ በሂልተን ሆቴል ወደ 4 ኪሎ እና ከካሳንቺስ መለስ አካዳሚ ሴቶች አደባባይ አቧሬ አድርገው ወደ 4 ኪሎ መውጣት እንደሚችሉ ኤጀንሲው መግለፁን የከተማ አስተዳደሩ ፕሬስ ሴክሬተሪ መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
በታላቁ ቤተመንግስት ወደ አንድነት ፓርክ የሚወስደው መንገድ የውስጥ ለውስጥ የዋሻ መንገድ ግንባታ ስለሚጀመር አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ አስታውቋል።የታላቁ ቤተመንግስት እና አንድነት ፓርክን ያለ ትራፊክ መጨናነቅ መጎብኘት የሚያስችል የውስጥ ለውስጥ የዋሻ መንገድ ግንባታ ምክንያት ከነገ ህዳር 08/2013 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ወር የተወሰኑ መንገዶች ዝግ እንደሚሆኑ ኤጀንሲ አስታውቋል።
ከሂልተን ሆቴል ተነስቶ ወደ ቀኝ የሚታጠፉ ተሸከርካሪዎች እና ከካሳንችስ ወደ 4 ኪሎ የሚያስወጣው መንገድ ከነገ ህዳር 08/2013 ዓ.ም ጀምሮ የሚዘጋ በመሆኑ አሽከርካሪዎችም ኢንተርኮንትኔታል ሆቴል፣ በንግድ ሚንስቴር፣ በሂልተን ሆቴል ወደ 4 ኪሎ እና ከካሳንቺስ መለስ አካዳሚ ሴቶች አደባባይ አቧሬ አድርገው ወደ 4 ኪሎ መውጣት እንደሚችሉ ኤጀንሲው መግለፁን የከተማ አስተዳደሩ ፕሬስ ሴክሬተሪ መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
አብን ሥልታዊ የዘር ማፅዳትና ማጥፋት እንቅስቃሴዎች እየታዩ ነው አለ!
የአማራና የአገው ሕዝብ ሲፈጸሙበት ከቆዩት ሰፊ ዘር ተኮር ጥቃቶች ሳያገግም፣ በኦሮሚያና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ውስጥ፣ በአማራ ጠልነት መንፈስ ሥልታዊ የዘር ማፅዳትና ማጥፋት እንቅስቃሴዎች እንደ አዲስ ተጠናክረው እየታዩ መሆኑን መገንዘቡን የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አስታወቋል፡፡
ዘገባው የሪፖርተር ነው ተጨማሪ ለማንበብ: http://bit.ly/34mc078
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራና የአገው ሕዝብ ሲፈጸሙበት ከቆዩት ሰፊ ዘር ተኮር ጥቃቶች ሳያገግም፣ በኦሮሚያና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ውስጥ፣ በአማራ ጠልነት መንፈስ ሥልታዊ የዘር ማፅዳትና ማጥፋት እንቅስቃሴዎች እንደ አዲስ ተጠናክረው እየታዩ መሆኑን መገንዘቡን የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አስታወቋል፡፡
ዘገባው የሪፖርተር ነው ተጨማሪ ለማንበብ: http://bit.ly/34mc078
@YeneTube @FikerAssefa
በሀገር መከላከያ ሠራዊት ሰሜን ዕዝ ላይ የሕወሃት የፈጸመው ጥቃት ለሀገሪቱ ከእንግዲህ አሳሳቢ እንደማይሆን መከላከያ ሚንስትር ቀንዓ ያዴታ ትናንት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት ሪፖርት መናገራቸውን ሪፖርተር አስነብቧል።
መያዣ የወጠባቸው የአማጺው ሕወሃት አመራሮች ለምን እስካሁን እንዳልተያዙ ከምክር ቤት አባላት ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ተፈላጊዎቹ ያሉበት ቦታ የታወቀ ቢሆንም፣ ቀድመው ካዘጋጁዋቸው ጉድጓዶችና መደበቂያዎች በየጊዜው ስለሚቀያይሩ ይዞ ለማቅረብ አዳጋች እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
‹‹የሕዝቡን ፍላጎት የምንረዳው ቢሆንም በእኔ ግምገማ ሠራዊቱ ቶሎ ይዞ አላቀረበም የሚለው ትችት የፈጠነ ነው፤›› ሲሉ ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡
‹‹ዝም ብሎ እንደተቀመጠ ዕቃ ከሆነ ቦታ አንስቶ ማምጣት አይደለም፡፡ ወይም ደግሞ ከሆነ ጓሮ እንደ ጎመንና ካሮት ተቆርጦ የሚመጣ ነገር አይደለም፤›› በማለት ለፓርላማ አባላቱ ሒደቱ አስቸጋሪና ጊዜ የሚፈልግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትሩ አክለውም ሥራው ሌት ተቀን እየተከናወነ እንደሆነና የሚፈለጉት ሰዎችም መያዛቸው እንደማይቀር አስታውቀዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
መያዣ የወጠባቸው የአማጺው ሕወሃት አመራሮች ለምን እስካሁን እንዳልተያዙ ከምክር ቤት አባላት ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ተፈላጊዎቹ ያሉበት ቦታ የታወቀ ቢሆንም፣ ቀድመው ካዘጋጁዋቸው ጉድጓዶችና መደበቂያዎች በየጊዜው ስለሚቀያይሩ ይዞ ለማቅረብ አዳጋች እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
‹‹የሕዝቡን ፍላጎት የምንረዳው ቢሆንም በእኔ ግምገማ ሠራዊቱ ቶሎ ይዞ አላቀረበም የሚለው ትችት የፈጠነ ነው፤›› ሲሉ ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡
‹‹ዝም ብሎ እንደተቀመጠ ዕቃ ከሆነ ቦታ አንስቶ ማምጣት አይደለም፡፡ ወይም ደግሞ ከሆነ ጓሮ እንደ ጎመንና ካሮት ተቆርጦ የሚመጣ ነገር አይደለም፤›› በማለት ለፓርላማ አባላቱ ሒደቱ አስቸጋሪና ጊዜ የሚፈልግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትሩ አክለውም ሥራው ሌት ተቀን እየተከናወነ እንደሆነና የሚፈለጉት ሰዎችም መያዛቸው እንደማይቀር አስታውቀዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ከደምበል (ዝዋይ) ሐይቅና ከቆቃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ላይ እንቦጭን የማስወገድ ዘመቻ ነገ ይጀምራል!
ከደምበል (ዝዋይ) ሐይቅና ከቆቃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ላይ ለ30 የስራ ቀናት የሚቆይ እንቦጭን የማስወገድ ዘመቻ ከነገ ከታህሳስ 08/2013 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚካሔድ የውሃ ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡በጣና ሐይቅ ላይ በተካሔደው ዘመቻ ላይ 85 በመቶ የሚሆነውን እንቦጭ ማስወገድ እንደተቻለ የገለጸው ሚኒስቴሩ፣ በቀጣዩ ዘመቻ የጣና ተሞክሮ እንደሚተገበር አስታውቋል፡፡ከሚኒስቴሩ ተጠሪ ተቋማት እና ከኦሮሚያ ክልል መዋቅር ጋር በመሆን የእምቦጭ አረሙን በሰው ጉልበት ለማስወገድ በሞዴል ደረጃ በ980 ሄ/ር ቦታ ላይ የዘመቻ ስራው እንደሚሰራ ሚኒስቴሩ በፌስቡክ ገጹ ገልጿል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ከደምበል (ዝዋይ) ሐይቅና ከቆቃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ላይ ለ30 የስራ ቀናት የሚቆይ እንቦጭን የማስወገድ ዘመቻ ከነገ ከታህሳስ 08/2013 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚካሔድ የውሃ ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡በጣና ሐይቅ ላይ በተካሔደው ዘመቻ ላይ 85 በመቶ የሚሆነውን እንቦጭ ማስወገድ እንደተቻለ የገለጸው ሚኒስቴሩ፣ በቀጣዩ ዘመቻ የጣና ተሞክሮ እንደሚተገበር አስታውቋል፡፡ከሚኒስቴሩ ተጠሪ ተቋማት እና ከኦሮሚያ ክልል መዋቅር ጋር በመሆን የእምቦጭ አረሙን በሰው ጉልበት ለማስወገድ በሞዴል ደረጃ በ980 ሄ/ር ቦታ ላይ የዘመቻ ስራው እንደሚሰራ ሚኒስቴሩ በፌስቡክ ገጹ ገልጿል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ታጣቂዎች ከባለፈው እሁድ አንስቶ በተለያዩ ስፋራዎች ባደረሱት ጥቃት የአማራ ተወላጆች ሕይወት ማለፉን የአካቢው ነዋሪዎች ተናገሩ።
በዞኑ አሙሩ ወረዳ ጃቦ ዶበን ቀበሌ ውስጥ ከስድስት በላይ ሰዎች ከትናንት በስትያ አንስቶ እስከ ትናንትናው ዕለት ድረስ በታጣቂዎች መገደላቸውን አቶ ያሲን የተባሉ የአካባቢው ነዋሪ ለዶይቸ ቬለ በስልክ ገልጸዋል።ከሟቾቹ መካከል አምስቱ «በካራ እና በጥይት» መመታታቸውን በዛሬው እለትም ስድስት ሰዎች መቅበራቸውን ገልጠዋል።
አጋምሳ በተባለ እና ሀሮ በተባሉ ስፋራዎችም ጥቃቶች መድረሳቸውንና በሰው ላይ ጉዳት መድረሱን ነዋሪው አክለዋል።አሙሩ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት እና ከዞኑ አስተዳዳሪ በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በስልክ የተደረገው ጥረት አልተሳካም።ከምዕራብ ወለጋ የሸሹ የዐይን ምስክሮች እንደሚናገሩት ጥቃቱ በተደጋጋሚ የሚከሰት ነው።በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ሁለት ቀናት ቢያንስ በሁለት ዞኖች ብቻ 19 ንፁሃን ዜጎች በታጣቂዎች ጥቃት ተፈፅሞባቸው መሞታቸውን የክልሉ መንግስት ዛሬ አረጋግጧል፡፡
የክልሉ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ጌታቸው ባልቻ ዛሬ ለብዙኃን መገናኛ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ከትናንት በስቲያ እና ለሌት ለትናንት አጥቢያ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ በ13 የአማራ ተወላጆች፤ በምዕራብ ወለጋ ነጆ ወረዳ ደግሞ በ6 የኦሮሞ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ የጅምላ ግድያ "ኦነግ ሸኔ" ባሉት ታጣቂ ቡድን ግድያ ተፈጽሟል፡፡በ782 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ላይ ደግሞ እርምጃ መወሰዱን ሃላፊው መግለፃቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
[ዶይቸ ቬለ]
@YeneTube @FikerAssefa
በዞኑ አሙሩ ወረዳ ጃቦ ዶበን ቀበሌ ውስጥ ከስድስት በላይ ሰዎች ከትናንት በስትያ አንስቶ እስከ ትናንትናው ዕለት ድረስ በታጣቂዎች መገደላቸውን አቶ ያሲን የተባሉ የአካባቢው ነዋሪ ለዶይቸ ቬለ በስልክ ገልጸዋል።ከሟቾቹ መካከል አምስቱ «በካራ እና በጥይት» መመታታቸውን በዛሬው እለትም ስድስት ሰዎች መቅበራቸውን ገልጠዋል።
አጋምሳ በተባለ እና ሀሮ በተባሉ ስፋራዎችም ጥቃቶች መድረሳቸውንና በሰው ላይ ጉዳት መድረሱን ነዋሪው አክለዋል።አሙሩ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት እና ከዞኑ አስተዳዳሪ በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በስልክ የተደረገው ጥረት አልተሳካም።ከምዕራብ ወለጋ የሸሹ የዐይን ምስክሮች እንደሚናገሩት ጥቃቱ በተደጋጋሚ የሚከሰት ነው።በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ሁለት ቀናት ቢያንስ በሁለት ዞኖች ብቻ 19 ንፁሃን ዜጎች በታጣቂዎች ጥቃት ተፈፅሞባቸው መሞታቸውን የክልሉ መንግስት ዛሬ አረጋግጧል፡፡
የክልሉ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ጌታቸው ባልቻ ዛሬ ለብዙኃን መገናኛ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ከትናንት በስቲያ እና ለሌት ለትናንት አጥቢያ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ በ13 የአማራ ተወላጆች፤ በምዕራብ ወለጋ ነጆ ወረዳ ደግሞ በ6 የኦሮሞ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ የጅምላ ግድያ "ኦነግ ሸኔ" ባሉት ታጣቂ ቡድን ግድያ ተፈጽሟል፡፡በ782 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ላይ ደግሞ እርምጃ መወሰዱን ሃላፊው መግለፃቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
[ዶይቸ ቬለ]
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 464 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተያዙ፡፡
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 5,451 የላብራቶሪ ምርመራ 464 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡ባለፋት 24 ሰዓታት የ5 ሰዎች ሕይወት አልፏል፤ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርን 1,818 አድርሶታል።በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 1,662 ሰዎች ማገገማቸው የተነገረ ሲሆን ይህም ከበሽታው ያገገሙ ሰዎችን ቁጥር 97,969 አድርሶታል፡፡በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 118,006 ደርሷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 5,451 የላብራቶሪ ምርመራ 464 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡ባለፋት 24 ሰዓታት የ5 ሰዎች ሕይወት አልፏል፤ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርን 1,818 አድርሶታል።በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 1,662 ሰዎች ማገገማቸው የተነገረ ሲሆን ይህም ከበሽታው ያገገሙ ሰዎችን ቁጥር 97,969 አድርሶታል፡፡በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 118,006 ደርሷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ላሊበላ፣ ደሴ (ኮምቦልቻ) እና ሰመራ ተቋርጦ የነበረውን የበረራ አገልግሎት መጀመሩን አስታወቀ።መንገደኞች የአየር መንገዱን ድረ ገጽና የሞባይል መተግበሪያ በመጠቀም ግዜያቸውን በመቆጠብና በረራቸውን በማቀላጠፍ እንዲጓዙ አየር መንገዱ ጥሪ አቅርቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa