YeneTube
118K subscribers
31.4K photos
485 videos
79 files
3.87K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
መንግሥት በሱዳን የሚገኙ ስደተኞችን በአጭር ጊዜ እመልሳለሁ አለ፡፡

በትግራይ የተፈጠረውን ጦርነት ተከትሎ ወደ ሱዳን የተሰደዱ ዜጎችን በአጭር ጊዜ በመመለስ ለማቋቋም እንደሚሰራ የጠቅላይ ሚንስትር ጽህፈት ቤት በእንግሊዘኛ ባውጣው መግለጫ ገልጿል፡፡በክልሉ በነበረው ግጭት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ከሚኖሩበት መፈናቀላቸውን እንዲሁም ወደ ሱዳን መሰደዳቸውን የተባበሩት መንግሥታት መረጃ ያሳያል፡፡መንግሥት በማንኛውም ጊዜ ለዜጎች ደህንነት ቅድሚያ የሚሰጥ መሆኑን የጠቀሰው የጽህፈት ቤቱ መግለጫ፤ በትግራይ ክልል ሰብኣዊ ድጋፍን ለማቅረብ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በተባበሩት መንግሥታት መካከል ስምምነት መፈረሙን አስታውሷል፡፡

በክልሉ በነበረው ጦርነት ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች እና በስደተኞች ካምፕ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላልሆኑ ዜጎች ሰብኣዊ ድጋፍ ለማቅረብ መንግሥት ከሰብአዊ ድጋፍ ሰጪ ተቋማት እና ከተባበሩት መንግሥታቱ አጋሮች ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑ ተገልጿል፡፡ወንጀለኞችን ለሕግ ማቅረብ፣ ሕግና ስርዓትን መመለስ፣ ሰብኣዊ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች የሰብዓዊ እርዳታ እንዲያገኙ ማድረግ፣ ድንበር አቋርጠው የተሰደዱ ዜጎችን መልሶ ማቋቋም እና በወንጀለኛው ቡድን የወደሙና አገልግሎት ያቋረጡ የትራንስፖርትና መገናኛ መሰረተ ልማቶችን መልሶ መገንባት የፌደራል መንግሥት ዋነኛ ተግባራት መሆናቸውን ጽህፈት ቤቱ አስታውቋል።

Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሚያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ከቻይናው ሳይንስ አካዳሚ የአፕላይድ ኢኮሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር በግብርና ምርምር ዘርፍ አብሮ ለመሥራት የሚያስችል የጋራ የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

ሁለቱ ተቋማት በጋራ በመተባበር የግብርና ምርምርና የልማት ስራዎችን፣ የአካባቢ እና ሥነ-ምህዳር ምርምር፣ በመስኩ ለተሰማሩ ባለሙያዎች ነፃ ትምህርት ዕድል እና የገንዘብ ድጋፍ በማፈላለግ የሰው ሀይል አቅም ግንባታ ለማካሄድ ከስምምነት ደርሰዋል፡፡

የቻይና-ኢትዮጵያ የግብርና እና አካባቢ የምርምር ማዕከል ለመመስረት እንዲሁም በኢትዮጵያም ተመሳሳይ ማዕከል ለመክፈት መታቀዱን በቻይና ከኢትዮጵያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

[ኢ.ፕ.ድ]
@YeneTube @FikerAssefa
ጌታቸው ረዳን ጨምሮ የህወሓት ቡድን መሪዎች በእግራቸው መሸሽ ከመጀመራቸው በፊት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ ከ40 በላይ የመንግስት ተሽከርካሪዎች በመከላከያ ሰራዊቱ እጅ ገብተዋል ተባለ።

ቡድኑ ሰራዊቱን መቋቋም ተስኖት ወደ ገጠራማ ስፍራ በእግር መጓዝ ሲጀምር በታጣቂዎቹ በኩል ለማጥቃት ቢሞክርም እንዳልተሳካለት የ32ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ደጀኔ ፀጋዬ ተናግረዋል።ቡድኑ የመንገድ መሰረተ ልማት በሌለበት ከማይጨው 60 ኪሎ ሜትር ርቃ በምትገኘው ዴላ ወረዳ ከ40 በላይ የመንግስት እና በርካታ የግል ተሽከርካሪዎችን ይዞ ለመደበቅ ያደረገው ሙከራም መክሸፉን ነው ኮሎኔል ደጀኔ የተናገሩት።

ተሽከርካሪዎቹን ከፅንፈኛው ቡድን ሀይሎች አስጥሎ በቁጥጥር ስር ያዋለው ሰራዊቱ ባደረገው ፍተሻ በተሽከርካሪዎቹ ውስጥ መታወቂያ እና ፓስፖርቶች ተገኝተዋል።የተለያዩ ሰነዶቻቸውን ጥለው ከሸሹት መካከል የቀድሞው የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት፣ የማይጨው አስተዳዳሪ የነበረው ሀፍቱ ኪሮስ እና ሌሎች የወረዳ አመራር የነበሩ ሰዎች ሰነድ ይገኝበታል።

የአካባቢው ነዋሪዎች በሰጡት ጥቆማ መሰረት ጌታቸው ረዳ በዴላ በኩል ከሸሸው ቡድን ውስጥ እንደሚገኝበትም ነው ኮሎኔል ፀጋዬ የገለጹት፡፡በመከላከያ ሰራዊቱ ከተያዙት ተሽከርካሪዎች መካከል ስድስቱ በአሻራ የሚከፈቱ እጅግ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎች ሲሆኑ አራቱ ለኮሮና ወረርሽኝ መከላከል ስራ ከፌደራል መንግስቱ ለትግራይ ክልል የተበረከቱ አምቡላንሶች ይገኙበታል።ፅንፈኛው ቡድን ሲጠቀምባቸው የነበሩ የጭነት ተሽከርካሪዎች እና ቦቴዎችንም ሰራዊቱ ወደ ማይጨው ከተማ እንዲገቡ አድርጓል ብለዋል።በአሻራ የሚከፈቱትን ተሽከርካሪዎችም ከሞኤንኮ ጋር በመነጋገር ከአካባቢው ለማንሳትና ፍተሻ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም አውስተዋል።

Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ሰዓሊ ሚካኤል ቤተ ስላሴ ከዚህ አለም በሞት ተለየ!

ሰዓሊ እና ቀራፂ ሚካኤል ቤተ ስላሴ ፓፒዬ ማሼ (papier mâché) በተሰኘው ቅርፃ-ቅርፅ ሥራው ዓለም አቀፍ እውቅንናን ያገኘ ኢትዮጵያዊ የጥበብ ሰው ነበር።በወጥ የስዕል አይነት፣ የባለደማቅ ቀለም ውሁድ ስዕላትእና የሃውልት ቅርፅ ስራዎች ኢትዮጵያን ከሚያስጠሩት ቀደምት የጥበብ ስዎች አንዱ የነበረው አርቲስቱ ለረዥም አመታት በኖረባት የፓሪስ ከተማ በተፈጥሮአዊ ምክንያት በ69 አመቱ ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።

አርቲስት ሚካኤል የካቲት 8 ቀን 1943 በምስራቅ ኢትዮጵያ በምትገኘው ድሬ-ዳዋ ከተማ ውስጥ ነበር የተወለደው፡፡ሚካኤል የምድር ባቡር ተቀጣሪ ከነበሩት ከአባቱ ቤተ ስላሴ እና ከህክምና ባለሙያዋ እናቱ ተወልዶ 3 ዓመት ሲሞላው ወደ አዲስ አበባ ሄደ፡፡የመጀመርያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምርቱን የተከታተለው በሊሴ ገብረ ማሪያም ተምሯል፡፡ ከዚያም በሃያ አመቱ ወደ ፈረንሳይ በመሄድ ፊዚክስ እና ኬሚስትሪ ለሶስት አመት ተማረ፡፡

ከዚህ ፍፁም ወደተለየው ወደ ጥበብ ያዘነበለው እና ቅርፃ-ቅርፅ መስራት የጀመረው ደግሞ በ30 ዓመቱ ነበር፡፡የሰዓሊ ሚካኤል ሥራዎች በዋሽንግተን ዲሲ በብሔራዊ የአፍሪካ ሥነጥበብ ሙዚየም ውስጥ ይገኛሉ፡፡ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባው የአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሴስና የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ከስመ ጥር ኢትዮጵያን ጋር የጥበብ ስራዎቹንም አቅርቦ እንደነበር ይታወሳል፡፡

[@addiszeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
ቤቶች ኮርፖሬሽን  በሕገወጥ መሬት ወረራና ቤቶች ዕደላ ላይ ለመነጋገር ፈቃደኛ አለመሆኑን ዕንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ!

የፌዴራል ዋና ዕንባ ጠባቂ ተቋም በአዲስ አበባ ከተማ በሕገወጥ አሠራር በርከት ያሉ የጋራ ቤቶች ስለመታደላቸውና የመሬት ወረራ ስለመከናወኑ በወጣው መረጃ ላይ፣ ምርመራ ለማድረግ ቢሞክርም፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ኮርፖሬሽን ማብራሪያ ለመስጠት ፈቃደኛ አይደለም ሲል ወቀሳ አቀረበ።

የፌዴራል ዕንባ ጠባቂ ተቋም ሪፖርቱን 
መሠረት አድርጎ የችግሩን ሁኔታ 
ለማጣራት ዋና ሥራ አስኪያጁን ለማነጋገርና መልስ ለማግኘት ቢጠይቅም፣ ምንም ዓይነት መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ሲል ዋና ዕንባ ጠባቂ እንዳለ ኃይሌ 
(ዶ/ር) ለሪፖርተር ገልጸዋል።

ተጨማሪ ለማንበብ: https://bit.ly/2Im5yFg

@YeneTube @FikerAssefa
በአገር ክህደት እና በሰብአዊ መብት ጥሰት ወንጀል የተጠረጠሩ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በነበሩ አመራሮች ላይ የመያዣ ትዕዛዝ መውጣቱን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ!

ተጠርጣሪዎቹ መንግስት እና ህዝብ የተጣለባቸውን ከባድ ኃላፊነት ወደ ጐን በመተው መቀመጫቸውን ትግራይ ክልል በማድረግ የህዋሃት ፀረ-ሠላም እና ፀረ-ህዝብ ከሆኑ ከፍተኛ አመራሮች ተልዕኮ በመቀበል በጽንፈኝነት አስተሳሰብ በመነሣት በሀይል ወደ ስልጣን የመምጣት ፍላጎትን ካነገቡ ፀረ-ሠላም ሀይሎች ተልዕኮ በመቀበል በሀገር ውስጥ ሌሎችን በማደራጀት ሀገር የመበተን፣ ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር እና ህገ-መንግስታዊ ሥርአቱን አደጋ ላይ የሚጥል ተግባር ውስጥ በቀጥታ እና በተዘዋዋሪ መንገድ በመሳተፍ ህዝብ በመንግስት ላይ አመኔታ እንዳይኖረው በማድረግ በአገር ክህደት እና በሰብአዊ መብት ጥሰት ወንጀል የተጠረጠሩ በተለያዩ የአመራር ደረጃ ላይ የነበሩ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች የመያዣ ትዕዛዝ ወጥቶባቸዋል፡-
1) ኮማንደር ሰለሞን አብርሃ ብስራት
2) ኮማንደር ሀይለማርያም ብርሃኔ ገ/ማርያም
3) ም/ኢ/ር ክብሮም ገብሩ ገ/እግዚአብሄር
4) ም/ኢ/ር አረጋዊ ገ/ሂወት አስፋዉ
5) ረ/ኢንስፔክተር ገዛኢ ገ/ሂወት ገ/ስላሴ
6) ረ/ኢንስፔክተር ተስፋ ኪሮስ ግደይ
7) ረ/ኢንስፔክተር አርአያ ገ/አናንያ ኪዳኑ
8)ረ/ኢንስፔክተር ሰለሞን ወላይ ወ/አብዝጊ
9) ዋ/ሳጅን ሀይላይ ወልዱ ገ/ማርያም
10) ዋ/ሳጅን ሀፍቱ ካህሳይ አብርሃ ናቸው።
በመሆኑም መላው የሃገራችን ህዝቦች በተለይም ደግሞ ሰላም ወዳዱ የትግራይ ህዝብ፤ እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት፤ የአገራችን የፖሊስ ሰራዊትና የደህንነት ተቋማት እነዚህን የጁንታው የህዋሃት የጥፋት ቡድን ተፈላጊዎች አባላት አድኖ ለህግ ለማቅረብ እየተደረገ ባለው ተግባር በያላችሁበት የድርሻችሁን እንድትወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ እያቀረበ፤ በቀጣይም የጁንታው ርዝራዥ ቡድን ተጠርጣሪዎችን ተከታትሎ በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ የማድረግ ስራው አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን እየገለፀ በጉዳዩ ዙሪያ ተከታታይ መረጃዎችን በመገናኛ ብዙሃን በኩል ለህብረተሰቡ ይፋ የሚያደርግ መሆኑን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ለ6ኛው አገራዊ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች የአየር ሠዓትና የጋዜጣ አምድ ድልድል እያበለፀገ ያለውን መተግበሪያ በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ።

የባለስልጣኑ የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክተር አቶ አብዮት ለሚታ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ መተግበሪያው ተሻሽሎ እየበለጸገ ያለው ለፓርቲዎች የሚሰጠውን የአየር ሠዓትና የጋዜጣ አምድ ድልድል ከእጅ ንክኪ ነጻ ለማድረግ ነው።መተግበሪያውን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ፣ ምርጫ ቦርድና ብሮድካስት ባለስልጣን በጋራ እያዘጋጁት መሆኑንም ተናግረዋል።"የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ መገናኛ ብዙሃንና የተመደበውን የአየር ሠዓት ወደ ሲስተሙ በማስገባት መተግበሪያው ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው ቀመር መሰረት ለእያንዳንዱ የፖለቲካ ፓርቲና ሚዲያ የተዘጋጀውን ሠዓት ይደለድላል" ብለዋል።

መተግበሪያው የሰው ጉልበት፣ ጊዜና ሀብት በመቆጠብ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎችና መገናኛ ብዙሀን በድልድሉ መሰረት መረጃቸውን በፍጥነት እንዲያገኙም ያስችላል።ቴክኖሎጂው መገናኛ ብዙሃን የአየር ሠዓትና የጋዜጣ አምድ ለማንና በየትኛው ሠዓት መስጠት እንዳለባቸው ጊዜ ሳይፈጁ ለማወቅ እንደሚያስችላቸውም ተገልጿል።መተግበሪያው በ2007 ዓ.ም በተካሄደው ምርጫ ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን አስፈላጊው ማሻሻያ ተደርጎበት በቅርቡ እንደሚጠናቀቅ ነው አቶ አብዮት የገለጹት።መተግበሪያው በ2007 ዓ.ም በአጭር ጊዜና በችኮላ በመዘጋጀቱ ያልተካተቱበት ክልሎችና ቋንቋዎች እንደነበሩ የኢዜአ ዘገባ አስታውሷል።

@YeneTube @FikerAssefa
ጠ/ሚ ዐብይ ከነገ በስቲያ ረቡዕ ወደ ኬንያ አቅንተው የሞያሌ የድንበር መተላለፊያ በርን ይመርቃሉ!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ከነገ በስቲያ ረቡዕ ጀምሮ ወደ ኬንያ ሊያቀኑ ነው፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ኬንያ የሚያቀኑት ለሁለት ይፋዊ የጉብኝት ቀናት ነው፡፡በመጀመሪያው ቀን (ረቡዕ) በመርሳቢት ግዛት ከፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር ተገናኝተው የሞያሌ የድንበር መተላለፊያ በርን ይጎበኛሉ፤ በይፋ መርቀው ይከፍታሉም ተብሏል፡፡መሪዎቹ በዚያኑ ቀን ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ ያለውን እና የኬንያ፣ደቡብ ሱዳን እና ኢትዮጵያ የትራንስፖርት ፕሮጄክት አካል የሆነውን አዲሱን የላሙ ወደብን እንደሚጎበኙ የፕሬዝዳንት ኡሁሩ ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ከዛሬ 2 ገደማ ዓመታት በፊት ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ እና ከቀድሞው የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ጋር በመሆን የደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክን መመረቃቸው የሚታወስ ነው፡፡

[Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ዶክተር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ይገኙበት በነበረ ቢሮ ውስጥ ለውስጥ ከ300 ሜትር በላይ የኮንክሪት ዋሻ ተገኝቷል ሲል ፋና ዘግቧል።

@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ተንቀሳቃሽ ንብረቶች የሚመዘገቡበት ዘመናዊ የኤሌክትሮኒክ ማዕከል እንዳቋቋመ እና ወደ ሥራ እንዳስገባ የባንኩ የፋይናሻል ኢንክሉዢን ዳይሬክተር ተመስገን ዘለቀ ለአዲስ ማለዳ አስታወቁ።

ተንቀሳቃሽ ንብረቶች የሚመዘገቡበት ማዕከል ከባንኮች ብድር ለመውሰድ የሚፈልጉ ደንበኞች ያሏቸውን ተንቀሳቃሽ ንብረቶች በማስመዝገብ እና የተለየ መለያ ቁጥር ወይንም ኮድ ለንብረቱ ከተሰጠ በኋላ ባለንብረቶቹ ለመበደር ወደ መደበኛ ባንኮችም ሆነ ወደ ‹ማይክሮ›ፋይናንስ ተkማት ሲሄዱ የተመዘገበበትን ቁጥር ብቻ በመያዝ አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ ተጠቁሟል።

[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
"የፌደራል መንግስት ወይ ሀላፊነቱን ይወጣ አልያም ግዳጁን ለኛ ይስጠን" -ኮሚሽነር አበረ አዳሙ

<<ልዩ ኃይላችን የአማራ ልዩ ኃይል ተባለ እንጅ የኢትዮጵያ ልጅ (የኢትዮጵያ ሰራዊት)ነው፤

"ነፍሰጡር ሴት ሆዷ ተቀዶ ህፃኑ ወጦ የተበላበት፤

ሰው በቀስት ሆዱን ተመቶ አንጀቱ ተጎልጉሎ እዲወጣ የተደረገበት በአለም ላይ ከመተከል ውጭ የትም አልተፈፀመም፤

ይሄን ድርጊት የፌዴራል መንግስት እንዲያስቆም ወይም ግዳጁን ለኛ እንዲሰጠን እየወተወትነ ነው።

ሀገር እንዳይፈርስ፣መጥፎ ታሪክ እንዳይሰራ በማሰብ እንዲሁም ጥቂቶች ባጠፉት ሁላችንም እንዳንሳሳት እንጅ የምንታገሰው ቤኒሻንጉል እየተፈፀመ ያለው ግፍ አይደለም መሳሪያ ሌላም ነገር እንድትጠቀም የሚያስገድድ ነው።>>

የአማራ ፖሊስ ኮሚሸን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ ከአማራ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለ-መጠይቅ የተናገሩት።

@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንዚት አገልግሎት በኃይል ገመድና ኬብል ስርቆት መቸገሩን አስታወቀ!

የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንዚት አገልግሎት የኃይል ገመዶች እና ኬብሎች ስርቆት መቸገሩን አስታወቀ። በዚህም ተገልጋዮቹ መንገላታቸውና ኮርፖሬሽኑም ለተደጋጋሚ ኪሳራ መዳረጉን ገለጸ።

የአገልግሎት ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ሙሉቀን አሰፋ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት ፣የኃይል ገመዶች እና ኬብሎች በሌቦች ተቆርጠው በመወሰዳቸው ምክንያት ሰሞኑን ከመሿለኪያ ሚኒሊክ አደባባይ እና ከጦርኃይሎች ስቴዲየም ያለው መስመር በከፊል አገልግሎቱ ተቋርጧል። በዚህም ደንበኞቹ ለችግር ተጋልጠዋል።

እስካሁን 750 የሚደርሱ የኃይል ኬብሎች እና 15 የኃይል ማሰራጫ ገመዶች ስርቆት እንዳጋጠመ የገለጹት ኢንጂነር ሙሉቀን ፣ለችግሩ ዘላቂ መፍትሔ ማበጀት ባለመቻሉ አገልግሎቱ ከፍተኛ ችግር ውስጥ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

[ኢ ፕ ድ]
@YeneTube @FikerAssefa
የመተከል ዞን ኮማንድ ፖስት 23 የጸረ-ሠላም ኃይሎች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ!

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን 23 የጸረ-ሠላም ኃይሎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የዞኑ ኮማንድ ፖስት አስታወቀ።የመተከል ዞን ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ኮሎኔል አያሌው በየነ፣ በዞኑ ዳንጉር ወረዳ ልዩ ስሙ ቁጥር 3 ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሠላምን ሲያውኩ በነበሩ ኃይሎች ላይ በተወሰደው እርምጃ 23 ጸረ-ሠላም ኃይሎችን መደምሰሳቸውን ገልጸዋል።የመከላከያ ሠራዊት፣ የፌዴራል ፖሊስና የክልሉ የጸጥታ አካላት በወሰዱት እርምጃ ከተደመሰሱት የጽረ-ሠላም ኃይሎች በተጨማሪ ለጥፋት ሲጠቀሙበት የነበረ 3 የጦር- መሣሪያዎች በቁጥጥር ስር መዋሉንም ኮሎኔሉ ተናግረዋል።

በአካባቢው የሚንቀሳቀሰው የጥፋት ቡድኑ በሠላማዊ መንገድ እጅ እንዲሰጥ በክልሉ መንግሥት ጥሪ መቅረቡን ያስታወሱ ሲሆን፣ በጥሪው መሠረት መጠቀም ካልቻለ በዋናው ጁንታ ላይ የተወሰደው የማያዳግም እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አሳስበዋል።በጸረ-ሠላም ኃይሉ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ኮሎኔል አያሌው፣ ህብረተሰቡም እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ የአካባቢውን ሠላም በተደራጀ መንገድ በመጠበቅ ረገድ የጀመረውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ማቅረባቸውን ከቤንሻንጉል ጉሙዝ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

@YeneTube @FikerAssefa
15ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አገር አቀፍ ሲምፖዚየም መርሐግብር እየተካሄደ ነው፡፡

15ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አገር አቀፍ ሲምፖዚየም መርሐግብር በአዲስ አበባ በመካሔድ ላይ ይገኛል።በመርሐግብሩ ላይ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አደም ፋራህ፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ ሚኒስትሮችና የብሔር ብሔረሰብ ተወካዮች እና የሐይማኖት መሪዎች መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡መርሐግብሩ በትህነግ ቡድን ክህደት ተፈፅሞባቸው ለተሰው የሰራዊት አባላት የህሊና ጸሎት ተደርጎ ተጀምሯል።

@YeneTube @FikerAssefa
የኩላሊት ዕጥበት ሕክምና ክፍያ በግል ሆስፒታሎች ጭማሪ አሳይቷል ተባለ

የኩላሊት ዕጥበት (ዲያሊስስ) ሕክምና የሚሰጡ ሦስት የግል ሆስፒታሎች ለአንድ ጊዜ ዕጥበት ከ 150 እስከ 800 ብር ጭማሪ ማድረጋቸውን የኩላሊት ህሙማን በጎ አድራጎት ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሰለሞን አሰፋ ለአዲስ ማለዳ ተናገሩ።

ቤተዛታ ሆስቲታል 150 ብር፣ አዲስ ሕይወት ሆስፒታል 500 ብር እና ኮሪያ ሆስፒታል 800 ብር ለአንድ ጊዜ ዕጥበት እንደጨመሩ ሰለሞን ገልጸዋል። ይህ ማለት አንድ የኩላሊት ታካሚ በሳምንት ሦስት ጊዜ ሕክምናውን ሲያደርግ ከ450 ብር እስከ ኹለት ሺሕ 400 ብር ተጨማሪ ወጪ በአንድ ሳምንት ውስጥ ያወጣል ብለዋል።

[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
በትግራይ ክልል የህግ የበላይነት በፍጥነት እንዲረጋገጥ የተመድ ዋና ጸኃፊ ጥሪ አቀረቡ!

ዋና ጸኃፊው አንቶኒዮ ጉተሬዝ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ተነጋግረዋል፡፡የተባበሩት መንግስታት ሰብዓዊ ድጋፎችን ለመስጠት ዝግጁ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

[Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት የደራርቱ ቱሉ ተወዳዳሪ የነበሩት ራሳቸውን አግልለዋል እናም ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ ተወዳደሪ ሆናለች።

@Yenetube @Fikerassefa
ለኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ሁለገብ መረጃ የሚያቀርብ “የጉዞ ስንቅ” የተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ በዛሬው ዕለት ይፋ ሆኗል፡፡

በአለም አቀፉ የስራ ድርጅት/ILO/ ተጋጅቶ ይፋ የደረገው መተግበሪያ ለስደተኞች የተሟላ መረጃ እንዲኖራቸው ያለመ ነው ተብሏል፡፡ስደተኞች መረጃ ባለማግኘታቸው ምክንያት ለእንግልት ይዳረጋሉ ያለው ድርጅቱ፣ አዲሱ የሞባይል መተግበሪያ ግን ከስደት ሕይወት ጋር በተገናኘ የሥራ ዕድል አማራጮችን፣ የየአገራት ህግጋትንና የሚደርሱ ችግሮችን በዘርፉ ከሚሰሩ ተቋማት እና ኢምባሲዎች ጋር ጭምር በማስተሳሰር መረጃዎች በማቅረብ ለስደተኞች እገዛ ያደርጋል ተብሏል፡፡መተግበሪያው በእንግሊዘኛ በአማርኛ በአፋን ኦሮሞ እና በትግረኛ ቋንቋዎች አገልግሎት እዲሰጥ ተደርጎ ነው የተዘጋጀው፡፡የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ የሞባይል መተግበሪያው ተደራሽ እንዲሆንም ይሰራል ብለዋል፡፡

[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ የተመሰረተባቸው የሙስና ክስ የሚሰማበት ጊዜ ለ2 ወር ከ15 ቀን መራዘሙን የሀገሪቱ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ጃኮብ ዙማ ደቡብ አፍሪካን በመሩበት ዘመን በህገወጥ መንገድ የተገኘ ገንዘብን ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብና ህገወጥ የጦር መሳሪያ ንግድ ውስጥ እጃቸው ነበረበት በሚል እንደተከሰሱ አይዘነጋም።

@YeneTube @FikerAssefa
እነ እስክንድር ነጋን ጨምሮ 5 ተከሳሾች ላይ ዐቃቤ ህግ ለምስክሮቼ ደህንነት ከመጋረጃ ጀርባ ይመስክሩልኝ ሲል ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ ሆነ።

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የህገ መንግስት እና የፀረ ሽብር ጉዳዮች ወንጀል ችሎት የተከሳሾችን የክስ መቃወሚያ ተከትሎ ዐቃቤ ህግ ያቀረበውን ምላሽን ተመልክቶ ትዕዛዝ ለመስጠት ነበር ለዛሬ ተለዋጭ ቀጠሮ የሰጠው።ዐቃቤ ህግ ከዚህ በፊት በነበረው ቀጠሮ የማሰማቸው ምስክሮቼ ለደህንነታቸው ሲባል በምስክር ጥበቃ አዋጅ መሰረት ከመጋረጃ ጀርባ እንዲመሰክሩልኝ ሲል ማመልከቱን ተከትሎ ተከሳሾች ከመጋረጃ ጀርባ መባሉ ተገቢነት የለውም ሲሉ መቃወሚያ ማሰማታቸው ይታወሳል፡፡

ምስክሩ መስማትና ማየት እንደሚችል ማረጋገጥ ካልቻሉ የመስቀለኛ ጥያቄ ለማቅረብ አያስችልም፤ ምስክሩ ከመጋረጃ ጀርባ ሲመሰክር ተጨማሪ ሰነድ ይዞ እያነበበ ስለመሆኑ ምንም የምናውቀው ነገር አይኖርም ሲሉም ተቃውመው ተከራክረው ነበር።በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ መዝገቡን መርምሮ ዐቃቤ ህግ ያቀረበው ምስክሮቼን ከመጋረጃ በስተጀርባ ላሰማ ጥያቄን ውድቅ አድርጓል።

በተያያዘ በችሎቱ ያልተገኙ 6ኛ እና 7ኛ ተከሳሾችን ከዚህ በፊት የፌደራል ፖሊስ አፈላልጎ ለችሎት እንዲያቀርብ በታዘዘው መሰረት ፖሊስ አድራሻቸውን ማግኘት አልቻልኩም በማለቱ ፍርድ ቤቱ ክሳቸው እንዲቋረጥ ትዕዛዝ ሰጥቷል።ችሎቱ የተከሳሾቹን አድራሻ ማወቅ ባለመቻሉ ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ክሳቸው እየተሰማ ያሉ ተከሳሾችን የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብታቸውን የሚያጣብብ በመሆኑ ነው ክሳቸው እንዲቋረጥ ያዘዘው።የተሻሻለውን ክስ ለመጠባበቅ ለታህሳስ 13 ቀን 2013 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa