ከትግራይ ክልል ወደ ሱዳን በገቡ ኢትዮጵያውያን ዙሪያ የኢትዮጵያ መንግስት ከሱዳን መንግስት ጋር በሁሉም መስክ ተባብሮ እየሰራ ነው ሲሉ በሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ ተናገሩ።
በሱዳን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ከስካይ ኒውስ የአረብኛ ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ቃለ ምልልስ ባደረጉበት ወቅት መንግስት በትግራይ ክልል የጀመረው ሕግ የማስከበር እርምጃ ጥቂት ወንጀለኞችን ለህግ ለማቀረብ የሚደረግ ዘመቻ ነው ብለዋል።ይህም ማንኛዉም መንግስት የሚያደርገዉ እንደሆነ የገለፁት አምባሳደሩ ማንም መንግስት ህግ እየተጣሰ ቁጭ ብሎ የሚያይበት ሁኔታ እንደሌለ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት እየወሰደ በሚገኘው እርምጃ ምክንያት ችግሩ አካባቢያዊ ሊሆን የሚችልበት እድል የለምም ብለዋል።በህግ ማስከበር ሂደት ከቀያቸዉ ተፈናቀለው ወደ ሱዳን የገቡ ኢትዮጵያውያን በተለይም የምዕራቡ ትግራይ ክፍል ሙሉ በሙሉ ሰላም የተረጋገጠ በመሆኑ በቅርቡ ወደ ቀያቸው እንደሚመለሱ አረጋግጠዋል።ከዚህ ጋር በተያየዘ ከሱዳን መንግስት ጋር በሁሉም መስከ በትብብር እየሰሩ መሆኑንም አምባሳደሩ አስገንዝበዋል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
በሱዳን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ከስካይ ኒውስ የአረብኛ ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ቃለ ምልልስ ባደረጉበት ወቅት መንግስት በትግራይ ክልል የጀመረው ሕግ የማስከበር እርምጃ ጥቂት ወንጀለኞችን ለህግ ለማቀረብ የሚደረግ ዘመቻ ነው ብለዋል።ይህም ማንኛዉም መንግስት የሚያደርገዉ እንደሆነ የገለፁት አምባሳደሩ ማንም መንግስት ህግ እየተጣሰ ቁጭ ብሎ የሚያይበት ሁኔታ እንደሌለ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት እየወሰደ በሚገኘው እርምጃ ምክንያት ችግሩ አካባቢያዊ ሊሆን የሚችልበት እድል የለምም ብለዋል።በህግ ማስከበር ሂደት ከቀያቸዉ ተፈናቀለው ወደ ሱዳን የገቡ ኢትዮጵያውያን በተለይም የምዕራቡ ትግራይ ክፍል ሙሉ በሙሉ ሰላም የተረጋገጠ በመሆኑ በቅርቡ ወደ ቀያቸው እንደሚመለሱ አረጋግጠዋል።ከዚህ ጋር በተያየዘ ከሱዳን መንግስት ጋር በሁሉም መስከ በትብብር እየሰሩ መሆኑንም አምባሳደሩ አስገንዝበዋል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ ጋር እንደተያያዘ በተገመተ ምክንያት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯን አባረረች፡፡
የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞሃመድ ሁሴን ሮቤል ናቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን አህመድ ኢሴ አዋድን ከሥልጣን ያነሱት፡፡ተባራሪው ሚኒስትር አገራቸው በኢትዮጵያ በተለይም በትግራይ ክልል ባለው ወቅታዊ ጉዳይ አቋም አልያዘችም መግለጫም አላወጣችም ሲሉ በፃፉ ሰዓታት ልዩነት ከሥልጣናቸው ተነስተዋል፡፡የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለኢትዮጵያ አንድነት ድጋፍ እናደርጋለን ሲል መግለጫ ቢያወጣም፤ ሚኒስትሩ አገሪቱ ይፋዊ መግለጫ አላወጣችም ሲሉ በቲውተር ገፃቸው መፃፋቸው ለመባረራቸው ምክንያት መሆኑ ነው የተገመተው፡፡ሚኒስቴሩ ግን ሶማሊያ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አስተዳደር ለሕገ መንግሥታዊ ማዕቀፎች እና የአገሪቱ ሉኣላዊነት መከበር ከሚወስዳቸው እርምጃዎች ጎን መሆኗን ያረጋግጣል፡፡
[አሐዱ ቴሌቪዥን]
@YeneTube @FikerAssefa
የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞሃመድ ሁሴን ሮቤል ናቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን አህመድ ኢሴ አዋድን ከሥልጣን ያነሱት፡፡ተባራሪው ሚኒስትር አገራቸው በኢትዮጵያ በተለይም በትግራይ ክልል ባለው ወቅታዊ ጉዳይ አቋም አልያዘችም መግለጫም አላወጣችም ሲሉ በፃፉ ሰዓታት ልዩነት ከሥልጣናቸው ተነስተዋል፡፡የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለኢትዮጵያ አንድነት ድጋፍ እናደርጋለን ሲል መግለጫ ቢያወጣም፤ ሚኒስትሩ አገሪቱ ይፋዊ መግለጫ አላወጣችም ሲሉ በቲውተር ገፃቸው መፃፋቸው ለመባረራቸው ምክንያት መሆኑ ነው የተገመተው፡፡ሚኒስቴሩ ግን ሶማሊያ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አስተዳደር ለሕገ መንግሥታዊ ማዕቀፎች እና የአገሪቱ ሉኣላዊነት መከበር ከሚወስዳቸው እርምጃዎች ጎን መሆኗን ያረጋግጣል፡፡
[አሐዱ ቴሌቪዥን]
@YeneTube @FikerAssefa
በአቶ ልደቱ አያሌው ላይ ዐቃቤ ህግ ያቀረበው ሁለተኛው ክስ እንዲሻሻል ፍርድቤቱ አዘዘ፡፡
አቶ ልደቱ አያሌው በተከሰሱበት ሁለተኛው ህገመንግስቱን ለማፍረስ በማሰብ የሽግግር ሰነድ ማዘጋጀት ወንጀል የቀረበባቸው ክስ ነው እንዲሻሻል የታዘዘው።የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምስራቅ ምድብ ወንጀል ችሎት በባለፈው ቀጠሮው ክሱ ላይ የቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያን መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠትና አቶ ልደቱ ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ተለዋጭ ሰጥቶ ነበር፡፡በዚህ ቀጠሮ መሰረት ፍርድ ቤቱ ዛሬ ዐቃቤ ህግ ያቀረበው ክስ አንቀጽና ዝርዝሩ አይጣጣምም ሲል ክሱን አሻሽሎ እንዲያቀርብ አዟል።አቶ ልደቱ የጠየቁት ዋስትና ጥያቄን ክሱ ተሻሻሎ ሲመጣ ለመመልከትና ብይን ለመስጠት ለህዳር 24 ቀን 2013 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
Via Fana
@YeneTube @FikerAssefa
አቶ ልደቱ አያሌው በተከሰሱበት ሁለተኛው ህገመንግስቱን ለማፍረስ በማሰብ የሽግግር ሰነድ ማዘጋጀት ወንጀል የቀረበባቸው ክስ ነው እንዲሻሻል የታዘዘው።የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምስራቅ ምድብ ወንጀል ችሎት በባለፈው ቀጠሮው ክሱ ላይ የቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያን መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠትና አቶ ልደቱ ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ተለዋጭ ሰጥቶ ነበር፡፡በዚህ ቀጠሮ መሰረት ፍርድ ቤቱ ዛሬ ዐቃቤ ህግ ያቀረበው ክስ አንቀጽና ዝርዝሩ አይጣጣምም ሲል ክሱን አሻሽሎ እንዲያቀርብ አዟል።አቶ ልደቱ የጠየቁት ዋስትና ጥያቄን ክሱ ተሻሻሎ ሲመጣ ለመመልከትና ብይን ለመስጠት ለህዳር 24 ቀን 2013 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
Via Fana
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ለሮይተርስ የዜና ወኪል ሰጥቶት የነበረውን የዘገባ ፈቃድ ሰረዘ፡፡
ባለስልጣኑ በሃገሪቱ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ “በተሳሳተ መንገድ ዓለም እንዲያውቀው እና በመንግስት ላይ ጫና እንዲበረታ በሚያደርጉ” ዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማት ላይ እርምጃ በመውሰድ ላይ መሆኑን አስታውቋል፡፡እርምጃውን በማስመልከት ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 መረጃን የሰጡት የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዷለም መቀመጫቸውን አዲስ አበባ በማድረግ ፈቃድ የተሰጣቸው የውጭ ሃገር የሚዲያ ተቋማት ወቅታዊውን ሁኔታ በጥንቃቄ እና ሙያዊ ስነ ምግባርን በተከተለ መንገድ እንዲዘግቡ ማሳሰቢያ ሰጥተናል ብለዋል፡፡
ሆኖም ማሳሰቢያውን ችላ በማለት “በእምቢተኝነት በቀጠሉት ላይ እርምጃ ወስደናል” ብለዋል ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፡፡ዶቼ ቬለ፣ ቢቢሲ እና ሮይተርስ ባለስልጣኑ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እስከ መጻፍ የደረሰባቸው የውጭ የሚዲያ ተቋማት ናቸው፡፡“ሮይተርስ ከትናንትና ወዲህ ባለው ሃገር ውስጥ ያለችው ዘጋቢ በምንም ዓይነት መልኩ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ እንቅስቃሴ እንዳታደርግ እና ዘገባዎችን ዜናዎችንም እንዳትሰራ ሙሉ በሙሉ አግደናታል” ሲሉም አቶ ወንድወሰን የሮይተርስን መታገድ ተናግረዋል።“ወደ አንድ ወገን ያጋደሉ ስራዎችን በሚሰሩ ሌሎች ተቋማት ላይ ተገቢውን ቁጥጥር በማድረግ” እርምጃ መውሰዳችን ይቀጥላልም ነው ያሉት፡፡ባለስልጣኑ ለሃገር ውስጥም ሆነ ለውጭ የሚዲያ ተቋማት ወኪል ዘገባዎች ፈቃድ ሰጪ አካል መሆኑ ይታወቃል፡፡
[Sheger/Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ባለስልጣኑ በሃገሪቱ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ “በተሳሳተ መንገድ ዓለም እንዲያውቀው እና በመንግስት ላይ ጫና እንዲበረታ በሚያደርጉ” ዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማት ላይ እርምጃ በመውሰድ ላይ መሆኑን አስታውቋል፡፡እርምጃውን በማስመልከት ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 መረጃን የሰጡት የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዷለም መቀመጫቸውን አዲስ አበባ በማድረግ ፈቃድ የተሰጣቸው የውጭ ሃገር የሚዲያ ተቋማት ወቅታዊውን ሁኔታ በጥንቃቄ እና ሙያዊ ስነ ምግባርን በተከተለ መንገድ እንዲዘግቡ ማሳሰቢያ ሰጥተናል ብለዋል፡፡
ሆኖም ማሳሰቢያውን ችላ በማለት “በእምቢተኝነት በቀጠሉት ላይ እርምጃ ወስደናል” ብለዋል ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፡፡ዶቼ ቬለ፣ ቢቢሲ እና ሮይተርስ ባለስልጣኑ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እስከ መጻፍ የደረሰባቸው የውጭ የሚዲያ ተቋማት ናቸው፡፡“ሮይተርስ ከትናንትና ወዲህ ባለው ሃገር ውስጥ ያለችው ዘጋቢ በምንም ዓይነት መልኩ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ እንቅስቃሴ እንዳታደርግ እና ዘገባዎችን ዜናዎችንም እንዳትሰራ ሙሉ በሙሉ አግደናታል” ሲሉም አቶ ወንድወሰን የሮይተርስን መታገድ ተናግረዋል።“ወደ አንድ ወገን ያጋደሉ ስራዎችን በሚሰሩ ሌሎች ተቋማት ላይ ተገቢውን ቁጥጥር በማድረግ” እርምጃ መውሰዳችን ይቀጥላልም ነው ያሉት፡፡ባለስልጣኑ ለሃገር ውስጥም ሆነ ለውጭ የሚዲያ ተቋማት ወኪል ዘገባዎች ፈቃድ ሰጪ አካል መሆኑ ይታወቃል፡፡
[Sheger/Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
የሀዋሳ ከተማ የራሷ መገለጫ የሆነ ምልክትን (Logo) አጸደቀች።
የሀዋሳ ከተማ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ መልካሙ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደገለጹት አለም አቀፉን መስፈርት ታሳቢ በማድረግ ከተማዋ የራሷን ምልክት ይፋ አድርጋለች ብለዋል።
አዲሱ ምልክት የሀዋሳን ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊና ተፈጥሯዊ እና የሰው ሰራሽ ሀብቶቿን ታሳቢ ያደረገ ነውም ብለዋል።
ምልክቱ በሚቀጥሉት ጊዜያት በሁሉም የአስተዳደሩ እርከኖች ማናቸውም ከተማዋን በሚመለከቱ ተግባራት ተፈጻሚ ይሆናል ስለመባሉ ኢትዮ ኤፍ ኤም ሰምቻለው ብሏል።
@YeneTube @FikerAssefa
የሀዋሳ ከተማ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ መልካሙ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደገለጹት አለም አቀፉን መስፈርት ታሳቢ በማድረግ ከተማዋ የራሷን ምልክት ይፋ አድርጋለች ብለዋል።
አዲሱ ምልክት የሀዋሳን ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊና ተፈጥሯዊ እና የሰው ሰራሽ ሀብቶቿን ታሳቢ ያደረገ ነውም ብለዋል።
ምልክቱ በሚቀጥሉት ጊዜያት በሁሉም የአስተዳደሩ እርከኖች ማናቸውም ከተማዋን በሚመለከቱ ተግባራት ተፈጻሚ ይሆናል ስለመባሉ ኢትዮ ኤፍ ኤም ሰምቻለው ብሏል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢንተርናሽናል ክራይስ ግሩፕ ተንታኝ ዊሊያም ዴቪሰን የስራ ፍቃድ ታገደ!
የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የኢንተርናሽናል ክራይስ ግሩፕ ሲኒየር ተንታኝ የሆነውን ዊሊያም ዴቪሰን የስራ ፍቃድ ማገዱን አዲስ ዘይቤ አረጋግጫለው ብላለች፡፡ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዛሬ በፃፈው ደብዳቤ ግለሰቡ በኢትዮጵያ እንዲሰራ ከተፈቀደለት ስራ ውጭ በሌላ ስራ ላይ ስለመሰማራቱ መረጃ ደርሶኛል ብሏል፡፡
ይህም ለውጭ ሀገር ዜጎች በሀገር ውስጥ የስራ ፍቃድ ለመስጠት የተቀመጠውን መመርያ የሚጥስ መሆኑን ገልጿል፡፡በዚህም መሰረት ከዛሬ ጀምሮ የስራ ፍቃዱ የታገደ ሲሆን በጉዳዩ ላይ ክትትል በማድረግ ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱም የደብዳቤውን ግልባጭ ለጠቅላይ አቃቤ ህግ፣ ለኢንቨስትመንት ኮሚሽን ፣ ለፌደራል ፖሊስ ፎረንሲክ ምርመራ፣ የኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ልኳል፡፡
Via @AddisZeybe
@YeneTube @FikerAssefa
የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የኢንተርናሽናል ክራይስ ግሩፕ ሲኒየር ተንታኝ የሆነውን ዊሊያም ዴቪሰን የስራ ፍቃድ ማገዱን አዲስ ዘይቤ አረጋግጫለው ብላለች፡፡ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዛሬ በፃፈው ደብዳቤ ግለሰቡ በኢትዮጵያ እንዲሰራ ከተፈቀደለት ስራ ውጭ በሌላ ስራ ላይ ስለመሰማራቱ መረጃ ደርሶኛል ብሏል፡፡
ይህም ለውጭ ሀገር ዜጎች በሀገር ውስጥ የስራ ፍቃድ ለመስጠት የተቀመጠውን መመርያ የሚጥስ መሆኑን ገልጿል፡፡በዚህም መሰረት ከዛሬ ጀምሮ የስራ ፍቃዱ የታገደ ሲሆን በጉዳዩ ላይ ክትትል በማድረግ ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱም የደብዳቤውን ግልባጭ ለጠቅላይ አቃቤ ህግ፣ ለኢንቨስትመንት ኮሚሽን ፣ ለፌደራል ፖሊስ ፎረንሲክ ምርመራ፣ የኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ልኳል፡፡
Via @AddisZeybe
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
በኢትዮጵያ መንግስትም ሆነ በህወሓት በኩል የሽምግልና ፍላጎት እንደሌለ የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተናገሩ! በትግራይ ያለው ውጊያ በንግግር እንዲፈታ በቀጠና፣ አህጉር እና ዓለም አቀፍ ደረጃ ያሉ መሪዎች የማሸማገል ጥያቄ ቢያቀርቡም፤ በኢትዮጵያ መንግስትም ሆነ በህወሓት በኩል የሽምግልና ፍላጎት እንደሌለ የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቲቦር ናዥ ተናገሩ። የህወሓት አመራሮች ውጊያውን…
ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ እንደማትገባ ዐስታወቀች።
በኢትዮጵያ መንግሥት እና በሕወሓት አመራር መካከል ትግራይ ውስጥ ያለው ግጭት የሚያበቃውም በኹለቱ ኃይላት መኾኑን አሜሪካ ገለጠች።የሰላማዊ ሰዎች ደኅንነት መጠበቊ ወሳኝ እንደኾነ፤ በዋናነትም የዜጎቿን ደኅንነት ለማስጠበቅ በመንቀሳቀስ ላይ እንደምትገኝ ጠቅሳለች።ትናንት ማምሻውን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪቃ ጉዳዮች ረዳት ሚንስትር ቲቦር ናዥ እና በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ሚካኤል ራይኖር ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ ስላለው ኹኔታ በስልክ ኮንፈረንስ ለጋዜጠኞች በሰጡት ልዩ ማብራሪያ ወቅት ነበር ይኽንኑ የተናገሩት።
በማብራሪያው ወቅትም፦ «የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ግጭቱ ፍጻሜ እንዲያገኝ፤ ሰላም እንዲሰፍን፤ ሰላማዊ ሰዎች መጠበቃቸውን ለማሳሰብ የተቻለውን ጥረት ያደርጋል» ያሉት ቲቦር ናዥ፦ «ግጭቱን ማስቆም ያለበት ግን የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት አይደለም» ሲሉ አጽንዖት ሰጥተዋል። «ሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ፤ ሕወሓት ጥቅምት 24 ቀን ትግራይ ክልል ውስጥ የሚገኘው የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል ላይ የመጀመሪያውን ጥቃት ከሰነዘረበት ጊዜ አንስቶም በግልም፣ በይፋም እጅግ እንዳሳሰበን አጽንዖት ሰጥተንበታል» ሲሉም አክለዋል። ሰላማዊ ሰዎች ሆነ ተብሎ ዒላማ ውስጥ እንዲገቡና ጥቃት እንዲፈጸምባቸው መደረጉን አስመልክተው የወጠ ዘገባዎች አሁንም በጥልቅ ያሳስቡናል። በማይ ካድራ ለተፈጸመው ጭፍጨፋ ወንጀለኞች ለሕግ እንዲቀርቡም በድጋሚ ጠይቀዋል። የማይ ካድራውን ጭፍጨፋም አውግዘዋል።
ድርጊቱ የተፈጸመው ከተማዪቱን ለቀው በሚያፈገፍጉ የሕወሓት ወታደሮች እና ሚሊሺያዎች እንደኾነ ያመላክታል» ያሉት ቲቦር ናዥ፦«የሰብአዊ መብት ጥሰቶች» በመላ በገለልተኛ ወገን እንዲጣራ አሳስበዋል።ጥፋተኛ ኾነው የተገኙትም በሕግ አግባብ እንዲጠየቊ ጥሪ አስለላልፈዋል።
በተለይ አንዳንድ የውጭ ሃገራት ተንታኞች እና ጋዜጠኞች በተደጋጋሚ እንደሚገልጡት በትግራይ የተጀመረው ወታደራዊ ዘመቻ ቃጣናው ላይ ተጽእኖ ይኖረው እንደኾነም የተጠየቊት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪቃ ጉዳዮች ረዳት ሚንስትር ቲቦር ናዥ ስለኢትዮጵያ ጥንታዊ መንግሥትነት እና ነፃ ሀገር መኾን በማብራራት የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ ሚናን ጠቅሰዋል። «ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ሥልጣን ከያዙበት ጊዜ አንስቶ ኢትዮጵያ የቃጣናው አነቃቂ ኾናለች» ብለዋል።«ከመቶ ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያ የኹለት ሺህ ዓመት የመንግሥት ታሪክ ያላት ናት።ከሰሃራ በታችም ፈጽሞ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ ሀገር ናት» ሲሉም ተናግረዋል።
ሕወሓት ወደ ኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ ሚሳይሎችን አስወንጭፎ ግጭቱን ቃጣናዊ ለማድረግ ቢሞክርም ኤርትራ ከግጭት ራሷን መቆጠቧን ቲቦር ናዥ አወድሰዋል።«ከሕወሓት አመራር ዓላማዎች መካከል አንዱ ግጭቱን ቃጣናዊ ለማድረግ መሞከር ነበር» ያሉት ረዳት ሚንሥትሩ፦«በትግራይ አጠቃላይ ሕዝብ ዘንድ የጀብደንነት ነበልባልን ለመለኮስ» የተሞከረ መኾኑንም ጠቅሰዋል።ቲቦር ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ባደረጉት ውይይት መንግሥት ዋነኛ ግቡ በመቶ ሺህ የሚቆጠር አባል ካለው ሕወሓት ውስጥ አመራሩ ላይ መኾኑን አጽንዖት መስጠቱን አስምረውበታል።
አምባሳደር ሚካኤል ራይኖር በበኩላቸው ቲቦር ናዥ በተናገሩት እንደሚስማሙ ገልጠዋል።የሕወሓት ፍላጎትን በተመለከተ፦ «ፍላጎታቸውን በትክክል ማወቅ ባይቻልም ጠቅላይ ሚንሥትር ዐቢይ አህመድን አስወግዶ ላለፉት 27 ዓመታት የበላይ ወደ ኾኑበት የኢትዮጵያ የፖለቲካ አውድ ለመመለስ ያለመ ይመስላል» ያሉት ቲቦር ናዥ፦ የህወሃት ስልት ተቃራኒ ነገር እንዳስከተለ ጠቅሰዋል። የሕወሓት ድርጊት፦ «ቢያንስ አሁን ጠቅላይ ሚንሥትሩን በመደገፍ ኢትዮጵያውያንን እንደ ሀገር ያሰባሰበ ይመስላል» ብለዋል። ኹኔታው፦ «የኢትዮጵያ ብሔራዊነትን በእውነቱ አስደንግጧል» ሲሉም አክለዋል። አምባሳደር ሚካኤል ራይኖር በኹኑ ወቅት «የክልል እና የፌዴራል መንግሥታት እንዲሁም መጠነ ሰፊ ሕዝብ በመንገስት ዙሪያ መሰባሰቡንም» ተናግረዋል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ መንግሥት እና በሕወሓት አመራር መካከል ትግራይ ውስጥ ያለው ግጭት የሚያበቃውም በኹለቱ ኃይላት መኾኑን አሜሪካ ገለጠች።የሰላማዊ ሰዎች ደኅንነት መጠበቊ ወሳኝ እንደኾነ፤ በዋናነትም የዜጎቿን ደኅንነት ለማስጠበቅ በመንቀሳቀስ ላይ እንደምትገኝ ጠቅሳለች።ትናንት ማምሻውን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪቃ ጉዳዮች ረዳት ሚንስትር ቲቦር ናዥ እና በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ሚካኤል ራይኖር ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ ስላለው ኹኔታ በስልክ ኮንፈረንስ ለጋዜጠኞች በሰጡት ልዩ ማብራሪያ ወቅት ነበር ይኽንኑ የተናገሩት።
በማብራሪያው ወቅትም፦ «የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ግጭቱ ፍጻሜ እንዲያገኝ፤ ሰላም እንዲሰፍን፤ ሰላማዊ ሰዎች መጠበቃቸውን ለማሳሰብ የተቻለውን ጥረት ያደርጋል» ያሉት ቲቦር ናዥ፦ «ግጭቱን ማስቆም ያለበት ግን የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት አይደለም» ሲሉ አጽንዖት ሰጥተዋል። «ሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ፤ ሕወሓት ጥቅምት 24 ቀን ትግራይ ክልል ውስጥ የሚገኘው የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል ላይ የመጀመሪያውን ጥቃት ከሰነዘረበት ጊዜ አንስቶም በግልም፣ በይፋም እጅግ እንዳሳሰበን አጽንዖት ሰጥተንበታል» ሲሉም አክለዋል። ሰላማዊ ሰዎች ሆነ ተብሎ ዒላማ ውስጥ እንዲገቡና ጥቃት እንዲፈጸምባቸው መደረጉን አስመልክተው የወጠ ዘገባዎች አሁንም በጥልቅ ያሳስቡናል። በማይ ካድራ ለተፈጸመው ጭፍጨፋ ወንጀለኞች ለሕግ እንዲቀርቡም በድጋሚ ጠይቀዋል። የማይ ካድራውን ጭፍጨፋም አውግዘዋል።
ድርጊቱ የተፈጸመው ከተማዪቱን ለቀው በሚያፈገፍጉ የሕወሓት ወታደሮች እና ሚሊሺያዎች እንደኾነ ያመላክታል» ያሉት ቲቦር ናዥ፦«የሰብአዊ መብት ጥሰቶች» በመላ በገለልተኛ ወገን እንዲጣራ አሳስበዋል።ጥፋተኛ ኾነው የተገኙትም በሕግ አግባብ እንዲጠየቊ ጥሪ አስለላልፈዋል።
በተለይ አንዳንድ የውጭ ሃገራት ተንታኞች እና ጋዜጠኞች በተደጋጋሚ እንደሚገልጡት በትግራይ የተጀመረው ወታደራዊ ዘመቻ ቃጣናው ላይ ተጽእኖ ይኖረው እንደኾነም የተጠየቊት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪቃ ጉዳዮች ረዳት ሚንስትር ቲቦር ናዥ ስለኢትዮጵያ ጥንታዊ መንግሥትነት እና ነፃ ሀገር መኾን በማብራራት የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ ሚናን ጠቅሰዋል። «ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ሥልጣን ከያዙበት ጊዜ አንስቶ ኢትዮጵያ የቃጣናው አነቃቂ ኾናለች» ብለዋል።«ከመቶ ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያ የኹለት ሺህ ዓመት የመንግሥት ታሪክ ያላት ናት።ከሰሃራ በታችም ፈጽሞ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ ሀገር ናት» ሲሉም ተናግረዋል።
ሕወሓት ወደ ኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ ሚሳይሎችን አስወንጭፎ ግጭቱን ቃጣናዊ ለማድረግ ቢሞክርም ኤርትራ ከግጭት ራሷን መቆጠቧን ቲቦር ናዥ አወድሰዋል።«ከሕወሓት አመራር ዓላማዎች መካከል አንዱ ግጭቱን ቃጣናዊ ለማድረግ መሞከር ነበር» ያሉት ረዳት ሚንሥትሩ፦«በትግራይ አጠቃላይ ሕዝብ ዘንድ የጀብደንነት ነበልባልን ለመለኮስ» የተሞከረ መኾኑንም ጠቅሰዋል።ቲቦር ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ባደረጉት ውይይት መንግሥት ዋነኛ ግቡ በመቶ ሺህ የሚቆጠር አባል ካለው ሕወሓት ውስጥ አመራሩ ላይ መኾኑን አጽንዖት መስጠቱን አስምረውበታል።
አምባሳደር ሚካኤል ራይኖር በበኩላቸው ቲቦር ናዥ በተናገሩት እንደሚስማሙ ገልጠዋል።የሕወሓት ፍላጎትን በተመለከተ፦ «ፍላጎታቸውን በትክክል ማወቅ ባይቻልም ጠቅላይ ሚንሥትር ዐቢይ አህመድን አስወግዶ ላለፉት 27 ዓመታት የበላይ ወደ ኾኑበት የኢትዮጵያ የፖለቲካ አውድ ለመመለስ ያለመ ይመስላል» ያሉት ቲቦር ናዥ፦ የህወሃት ስልት ተቃራኒ ነገር እንዳስከተለ ጠቅሰዋል። የሕወሓት ድርጊት፦ «ቢያንስ አሁን ጠቅላይ ሚንሥትሩን በመደገፍ ኢትዮጵያውያንን እንደ ሀገር ያሰባሰበ ይመስላል» ብለዋል። ኹኔታው፦ «የኢትዮጵያ ብሔራዊነትን በእውነቱ አስደንግጧል» ሲሉም አክለዋል። አምባሳደር ሚካኤል ራይኖር በኹኑ ወቅት «የክልል እና የፌዴራል መንግሥታት እንዲሁም መጠነ ሰፊ ሕዝብ በመንገስት ዙሪያ መሰባሰቡንም» ተናግረዋል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
ግድያው አሁንም እንዳልቆመ በመተከል ዞን ድባጤ ወረዳ የተፈናቀሉ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡
በመተከል ዞን ከግድያ የተረፉ ዜጎችን የፌዴራል ፖሊስ በጸጥታ ጉዳይ ላይ እንዳወያያቸው ተፈናቃዮች ገልጸዋል፡፡ በወይይቱም በግድያው ምክንያት ትተውት የመጡት ሃብት እና ንብረት የተዘረፈ በመሆኑ ችግር ላይ መውደቃቸውንና አሁንም የሰው ህይወት እየጠፋ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ከነበሩበት ቀበሌ መፈናቀላቸውንና ቤት ንብረታቸው መውደሙን በውይይቱ እንዳነሱ ለአብመድ በስልክ ገልጸዋል።
አሁን ላይ ችግር ላይ መውደቃቸውን የተናገሩት ተፈናቃዮቹ የጸጥታው ጉዳይ መፍትሄ የሚያገኝ ከሆነ በጊዜያዊ መጠለያ ቢሆን ወደ ቀያቸው ተመልሰው የመኖር ፍላጎት እንዳላቸው ነው የገለጹት፡፡የጥቃቱን አለመቆምና ለተፈናቃዮች እየተደረገላቸው ያለውን ድጋፍ ለመጠየቅ ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሰላም ግንባታና ደህንነት ቢሮ እንዲሁም የምግብ ዋስትና እና አደጋ መከላከል ጽህፈት ቤት የስራ ኃላፊዎች በተደጋጋሚ ስልክ ቢደውልም ሊያነሱ አልቻሉም፡፡
Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
በመተከል ዞን ከግድያ የተረፉ ዜጎችን የፌዴራል ፖሊስ በጸጥታ ጉዳይ ላይ እንዳወያያቸው ተፈናቃዮች ገልጸዋል፡፡ በወይይቱም በግድያው ምክንያት ትተውት የመጡት ሃብት እና ንብረት የተዘረፈ በመሆኑ ችግር ላይ መውደቃቸውንና አሁንም የሰው ህይወት እየጠፋ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ከነበሩበት ቀበሌ መፈናቀላቸውንና ቤት ንብረታቸው መውደሙን በውይይቱ እንዳነሱ ለአብመድ በስልክ ገልጸዋል።
አሁን ላይ ችግር ላይ መውደቃቸውን የተናገሩት ተፈናቃዮቹ የጸጥታው ጉዳይ መፍትሄ የሚያገኝ ከሆነ በጊዜያዊ መጠለያ ቢሆን ወደ ቀያቸው ተመልሰው የመኖር ፍላጎት እንዳላቸው ነው የገለጹት፡፡የጥቃቱን አለመቆምና ለተፈናቃዮች እየተደረገላቸው ያለውን ድጋፍ ለመጠየቅ ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሰላም ግንባታና ደህንነት ቢሮ እንዲሁም የምግብ ዋስትና እና አደጋ መከላከል ጽህፈት ቤት የስራ ኃላፊዎች በተደጋጋሚ ስልክ ቢደውልም ሊያነሱ አልቻሉም፡፡
Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
‹‹የልደቱ አያሌው የጤንነታቸው ሁኔታ በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል›› አዳነ ታደሰ
ልደቱ አያሌው ዛሬ ኅዳር 11/2013 በኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምስራቅ ችሎት መቅረባቸው ይታወሳል።ፍርድ ቤቱም ዐቃቤ ሕግ ክሱን እንዲያሻሽል በማዘዝ፤ ክሱ ግልፅ ባልሆነበት እውነታ የዋስትና መብት ላይ ብይን አልሰጥም ማለቱን የኢትዮጵያዊያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ፕሬዝዳንት አዳነ ታደሰ ለአዲስ ማለዳ አስታውቀዋል።
‹ከታሰርኩ አራት ወር ሆኖኛል፤ የእስከዛሬው የፍርድ ቤት ሂደት የሚያሳየው ዐቃቤ ሕግ ዋና ዓላማው እኔን በወንጀል ከሶ የማስቀጣት ሳይሆን በተራዘመ የፍርድ ሂደት እኔን ማሰቃየት ነው› ልደቱ ቅሬታቸውን መግለጻቸውንም አዳነ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።
የጤንነታቸው ሁኔታ ከአዲስ ማለዳ ለቀረበላቸው ጥያቄም አሁን ጤንነታቸው እንደተሻሻለ እና በጥሩ ጤንነት ላይ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ብለዋል።
[አዲስ ማለዳ]
@YeneTube @FikerAssefa
ልደቱ አያሌው ዛሬ ኅዳር 11/2013 በኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምስራቅ ችሎት መቅረባቸው ይታወሳል።ፍርድ ቤቱም ዐቃቤ ሕግ ክሱን እንዲያሻሽል በማዘዝ፤ ክሱ ግልፅ ባልሆነበት እውነታ የዋስትና መብት ላይ ብይን አልሰጥም ማለቱን የኢትዮጵያዊያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ፕሬዝዳንት አዳነ ታደሰ ለአዲስ ማለዳ አስታውቀዋል።
‹ከታሰርኩ አራት ወር ሆኖኛል፤ የእስከዛሬው የፍርድ ቤት ሂደት የሚያሳየው ዐቃቤ ሕግ ዋና ዓላማው እኔን በወንጀል ከሶ የማስቀጣት ሳይሆን በተራዘመ የፍርድ ሂደት እኔን ማሰቃየት ነው› ልደቱ ቅሬታቸውን መግለጻቸውንም አዳነ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።
የጤንነታቸው ሁኔታ ከአዲስ ማለዳ ለቀረበላቸው ጥያቄም አሁን ጤንነታቸው እንደተሻሻለ እና በጥሩ ጤንነት ላይ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ብለዋል።
[አዲስ ማለዳ]
@YeneTube @FikerAssefa
ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው በ10ሺ ብር ዋስ ዛሬ ማምሻውን ከእስር ተለቋል።
ባለፈው ማክሰኞ በዋስ እንዲለቀቅ ፍርድ ቤቱ ወስኖ የነበረ ቢሆንም፣ ፖሊስ ይግባኝ ስለጠየቀበት በእስር እንዲቆይ እንተደረገ መዘገባችን ይታወሳል። ዛሬ በነበረው የፍርድ ቤት ውሎ በዋስ እንዲለቀቅ ተወስኖ የነበረውን ውሳኔ እንደገና በማፅደቅ፣ ጋዜጠኛ በቃሉ ከማረሚያ ቤቱ ወጥተዋል።
Via:- አውሎ ሚዲያ
@Yenetube @Fikerassefa
ባለፈው ማክሰኞ በዋስ እንዲለቀቅ ፍርድ ቤቱ ወስኖ የነበረ ቢሆንም፣ ፖሊስ ይግባኝ ስለጠየቀበት በእስር እንዲቆይ እንተደረገ መዘገባችን ይታወሳል። ዛሬ በነበረው የፍርድ ቤት ውሎ በዋስ እንዲለቀቅ ተወስኖ የነበረውን ውሳኔ እንደገና በማፅደቅ፣ ጋዜጠኛ በቃሉ ከማረሚያ ቤቱ ወጥተዋል።
Via:- አውሎ ሚዲያ
@Yenetube @Fikerassefa
ሰበር ዜና‼️
የመከላከያ ሠራዊት አክሱምን አድዋንና የአዲግራትን ዙሪያ ተቆጣጥሯል ተባለ!
በምዕራብ ግንባር የ'ሕወሐት ጁንታን' ኃይል እያጠቃ ያለው የመከላከያ ሠራዊት፣ ከሽሬ በኋላ ሰለህለሃ ላይ የመሸገ የሕወሐት ኃይል ገጥሞት ነበር። ሰለህለሃ ላይ የመሸገው የ'ጁንታው ኃይል' መንገዱን በዶዘር ቆርጦና አስፓልቱን አበላሽቶ በቦታው ከባድ መከላከል አድርጓል።
የመከላከያ ሠራዊቱ የ'ጁንታውን' ተከላካይ ኃይል ሠብሮ በመግባት አክሱምን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሯል።
ከአክሱም ወደ አድዋ በነበረው ጉዞ በአንዳንድ ቦታዎች ላይ የጁንታው ኃይል ለመከላከል ቢሞክርም፣ በመከላከያ ሠራዊቱ ድል ሆኗል።
መከላከያ እንቲጮንና የአዲግራትን ዙሪያ ተቆጣጥሮ ወደ አዲግራት ከተማ እየገሠገሠ ይገኛል።አያሌ የ'ጁንታው' ተዋጊዎች እጃቸውን የሰጡ ሲሆን ከድተው ከ'ጁንታው' ጋር ሆነው ሲዋጉ የነበሩ ወታደሮችም ይገኙበታል።
[የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ]
@YeneTube @FikerAssefa
የመከላከያ ሠራዊት አክሱምን አድዋንና የአዲግራትን ዙሪያ ተቆጣጥሯል ተባለ!
በምዕራብ ግንባር የ'ሕወሐት ጁንታን' ኃይል እያጠቃ ያለው የመከላከያ ሠራዊት፣ ከሽሬ በኋላ ሰለህለሃ ላይ የመሸገ የሕወሐት ኃይል ገጥሞት ነበር። ሰለህለሃ ላይ የመሸገው የ'ጁንታው ኃይል' መንገዱን በዶዘር ቆርጦና አስፓልቱን አበላሽቶ በቦታው ከባድ መከላከል አድርጓል።
የመከላከያ ሠራዊቱ የ'ጁንታውን' ተከላካይ ኃይል ሠብሮ በመግባት አክሱምን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሯል።
ከአክሱም ወደ አድዋ በነበረው ጉዞ በአንዳንድ ቦታዎች ላይ የጁንታው ኃይል ለመከላከል ቢሞክርም፣ በመከላከያ ሠራዊቱ ድል ሆኗል።
መከላከያ እንቲጮንና የአዲግራትን ዙሪያ ተቆጣጥሮ ወደ አዲግራት ከተማ እየገሠገሠ ይገኛል።አያሌ የ'ጁንታው' ተዋጊዎች እጃቸውን የሰጡ ሲሆን ከድተው ከ'ጁንታው' ጋር ሆነው ሲዋጉ የነበሩ ወታደሮችም ይገኙበታል።
[የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ]
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 452 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተያዙ፡፡
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 5,488 የላብራቶሪ ምርመራ 452 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡ባለፋት 24 ሰዓታት የ13 ሰዎች ሕይወት አልፏል፤ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርን 1,620 አድርሶታል።በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 342 ሰዎች ማገገማቸው የተነገረ ሲሆን ይህም ከበሽታው ያገገሙ ሰዎችን ቁጥር 65,325 አድርሶታል፡፡በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 104,879 ደርሷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 5,488 የላብራቶሪ ምርመራ 452 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡ባለፋት 24 ሰዓታት የ13 ሰዎች ሕይወት አልፏል፤ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርን 1,620 አድርሶታል።በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 342 ሰዎች ማገገማቸው የተነገረ ሲሆን ይህም ከበሽታው ያገገሙ ሰዎችን ቁጥር 65,325 አድርሶታል፡፡በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 104,879 ደርሷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የተመድ ረድዔት ድርጅቶች በቀጣዮቹ 6 ወራት የግጭት ቀጠና ከሆነው ትግራይ ክልል 200 ሺህ ያህል ስደተኞች ሱዳን ይገባሉ የሚል ዕቅድ ይዘው እየሰሩ እንደሆነ ለዐለማቀፍ ዜና አውታሮች ተናግረዋል፡፡ እስካሁን በሱዳን የተጠለሉት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ቁጥር ከ33 ሺህ በላይ ሆኗል፡፡ ሕጻናት በሚበዙባቸው አዲሶቹ ስደተኛ ጣቢያዎች ተላላፊ በሽታ ሊስፋፋ ይችላል የሚል ስጋትም ተፈጥሯል፡፡ ተመድ ለስደተኞቹ አስቸኳይ ምግብ ዕርዳታ እና ለመጠለያ ግንባታ፣ 50 ሚሊዮን ዶላር ዕርዳታ ባስቸኳይ ያስፈልገኛል ብሏል፡፡
[ዋዜማ ራዲዮ]
@YeneTube @FikerAssefa
[ዋዜማ ራዲዮ]
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ለሮይተርስ የዜና ወኪል ሰጥቶት የነበረውን የዘገባ ፈቃድ ሰረዘ፡፡ ባለስልጣኑ በሃገሪቱ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ “በተሳሳተ መንገድ ዓለም እንዲያውቀው እና በመንግስት ላይ ጫና እንዲበረታ በሚያደርጉ” ዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማት ላይ እርምጃ በመውሰድ ላይ መሆኑን አስታውቋል፡፡እርምጃውን በማስመልከት ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 መረጃን የሰጡት የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር…
ሮይተርስ በኢትዮጵያ እንዳይሰራ አልከለከልኩም ሲል የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
ባለስልጣኑ የኢትዮጵያ ወኪል ዘጋቢውን እንጂ የተቋሙን የዘገባ ስራዎች ፍቃድ አለመሰረዙንም አስታውቋል፡፡“የሚመለከታቸውን አካላት አካቶ በሚዛናዊነት ከመስራት ይልቅ የአንድ ወገን መረጃዎችን ብቻ የመጠቀም ችግሮች እንዳሉ ለወኪል ዘጋቢዋ ደጋግመን ብናስታውቅም አላረመችም” ያሉት የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዷለም “ለተቋሙ በማሳወቅ የወኪል ዘጋቢነቷን ፈቃድ አገድን እንጂ ከሮይተርስ ጋር ያለን ግንኙነት አልተቋረጠም የዘገባ ፍቃዱንም አላገድንም”ሲሉ ለአል ዐይን አማርኘ ተናግረዋል፡፡ከአሁን በኋላ “እንደ ወኪል ጋዜጠኛ ሆና ልትሰራ የምትችልበት” አግባብና እንቅስቃሴ እንደሌለ እና የሚሰጣት መረጃ እንደማይኖርም ነው ምክትል ዋና ዳይሬክተር ያስታወቁት፡፡
“ሮይተርስ ሌላ ጋዜጠኛ እንዲልክ ለዋና መስሪያ ቤቱ አሳውቀናል”ም ብለዋል አቶ ወንድወሰን፡፡የቋሚ የሚዲያ ወኪል (ጋዜጠኛ) መታወቂያዋ በባለስልጣኑ መያዙንም አስታውቀዋል፡፡እንድታርም ተደጋግሞ ስለተነገራት ነገር ምንነት አል ዐይን አማርኛ ላቀረበላቸው ጥያቄም “ምንም ዓይነት የኢንተርኔትም ሆነ የኮሙኒኬሽን ግንኙነት በሌለበት ሁኔታ ከመቀሌ መረጃ አግኝተው ይሰራሉ ሲሰሩ ግን አዲስ አበባ ከሚገኘው የመንግስት አካል ‘ባላንስ’ አድርገው አይደለም ” አይደለም ሲሉ በማሳያነት ጠቅሰዋል፡፡‘ባላንስ’ አለማድረጉ “ወደ አንድ አካል ጣት መቀሰር የአንድን አካል ፕሮፓጋንዳ ማራገብ” እንደሚሆንና ከጋዜጠኝነት ሙያ መርሆዎች እንደሚያፈነግጥም ነው ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ የተናገሩት፡፡
Via @alainamharic
@YeneTube @FikerAssefa
ባለስልጣኑ የኢትዮጵያ ወኪል ዘጋቢውን እንጂ የተቋሙን የዘገባ ስራዎች ፍቃድ አለመሰረዙንም አስታውቋል፡፡“የሚመለከታቸውን አካላት አካቶ በሚዛናዊነት ከመስራት ይልቅ የአንድ ወገን መረጃዎችን ብቻ የመጠቀም ችግሮች እንዳሉ ለወኪል ዘጋቢዋ ደጋግመን ብናስታውቅም አላረመችም” ያሉት የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዷለም “ለተቋሙ በማሳወቅ የወኪል ዘጋቢነቷን ፈቃድ አገድን እንጂ ከሮይተርስ ጋር ያለን ግንኙነት አልተቋረጠም የዘገባ ፍቃዱንም አላገድንም”ሲሉ ለአል ዐይን አማርኘ ተናግረዋል፡፡ከአሁን በኋላ “እንደ ወኪል ጋዜጠኛ ሆና ልትሰራ የምትችልበት” አግባብና እንቅስቃሴ እንደሌለ እና የሚሰጣት መረጃ እንደማይኖርም ነው ምክትል ዋና ዳይሬክተር ያስታወቁት፡፡
“ሮይተርስ ሌላ ጋዜጠኛ እንዲልክ ለዋና መስሪያ ቤቱ አሳውቀናል”ም ብለዋል አቶ ወንድወሰን፡፡የቋሚ የሚዲያ ወኪል (ጋዜጠኛ) መታወቂያዋ በባለስልጣኑ መያዙንም አስታውቀዋል፡፡እንድታርም ተደጋግሞ ስለተነገራት ነገር ምንነት አል ዐይን አማርኛ ላቀረበላቸው ጥያቄም “ምንም ዓይነት የኢንተርኔትም ሆነ የኮሙኒኬሽን ግንኙነት በሌለበት ሁኔታ ከመቀሌ መረጃ አግኝተው ይሰራሉ ሲሰሩ ግን አዲስ አበባ ከሚገኘው የመንግስት አካል ‘ባላንስ’ አድርገው አይደለም ” አይደለም ሲሉ በማሳያነት ጠቅሰዋል፡፡‘ባላንስ’ አለማድረጉ “ወደ አንድ አካል ጣት መቀሰር የአንድን አካል ፕሮፓጋንዳ ማራገብ” እንደሚሆንና ከጋዜጠኝነት ሙያ መርሆዎች እንደሚያፈነግጥም ነው ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ የተናገሩት፡፡
Via @alainamharic
@YeneTube @FikerAssefa
ከጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት የተሰጠ መግለጫ:
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአፍሪካ ኀብረት ሊቀ መንበር የሆኑትን የሲሪል ራማፎሳን ልዑካን ተቀብለው በግል ይወያያሉ።ሆኖም፣ የፌደራል መንግሥትን እና በህወሓት የሚገኙ ወንጀለኞችን ለማሸማገል ልዑካን ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ ተብሎ በመሰራጨት ላይ የሚገኘው ዜና ሀሰት መሆኑን እናረጋግጣለን።ድርድርን አስመልክቶ የፌደራል መንግሥት ያለው አቋም ፈጽሞ ያልተለወጠ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአፍሪካ ኀብረት ሊቀ መንበር የሆኑትን የሲሪል ራማፎሳን ልዑካን ተቀብለው በግል ይወያያሉ።ሆኖም፣ የፌደራል መንግሥትን እና በህወሓት የሚገኙ ወንጀለኞችን ለማሸማገል ልዑካን ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ ተብሎ በመሰራጨት ላይ የሚገኘው ዜና ሀሰት መሆኑን እናረጋግጣለን።ድርድርን አስመልክቶ የፌደራል መንግሥት ያለው አቋም ፈጽሞ ያልተለወጠ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
ግጭትን ሊያስነሱ የሚችሉ ቃላት ተለይተው ሊታተሙ ነው!
የመብቶችና የዴሞክራሲ እድገት ማዕከል(CARD) እና ዴስቲኒ ኢትዮጵያ peace teach Lab ከተሰኘ አለም አቀፍ ተቋም ጋር በመተባበር ለግጭት አስተዋጽኦ ያላቸውን ቃላት በመሰብሰብ ከአንድ ወር በኋላ በድረ ገፅ መዝገበቃላት እንደሚያሳትም የማዕከሉ ሃላፊ በፍቃዱ ሀይሉ ለአዲስ ማለዳ አስታውቀዋል።
እነዚህ ግጭት ቀስቃሽ የሆኑ ቃላት የወል ማንነትን መሰረት ያደረጉ ሲሆኑ የተሰበሰቡበት መንገድ ደግሞ የዳሰሳ ጥናቶችን በማድረግና ፌስቡክ የማህበራዊ ትስስር ድረገፅን በመጠቀም በተደጋጋሚ የሚፃፉ ቃላትን የሚሰበሰብበትን ሰው ሰራሽ እውቀት(Artificial intelligence) የተባለ መንገድ በመጠቀም መሆኑን አቶ በፍቃዱ ለአዲስ ማለዳ አስረድተዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የመብቶችና የዴሞክራሲ እድገት ማዕከል(CARD) እና ዴስቲኒ ኢትዮጵያ peace teach Lab ከተሰኘ አለም አቀፍ ተቋም ጋር በመተባበር ለግጭት አስተዋጽኦ ያላቸውን ቃላት በመሰብሰብ ከአንድ ወር በኋላ በድረ ገፅ መዝገበቃላት እንደሚያሳትም የማዕከሉ ሃላፊ በፍቃዱ ሀይሉ ለአዲስ ማለዳ አስታውቀዋል።
እነዚህ ግጭት ቀስቃሽ የሆኑ ቃላት የወል ማንነትን መሰረት ያደረጉ ሲሆኑ የተሰበሰቡበት መንገድ ደግሞ የዳሰሳ ጥናቶችን በማድረግና ፌስቡክ የማህበራዊ ትስስር ድረገፅን በመጠቀም በተደጋጋሚ የሚፃፉ ቃላትን የሚሰበሰብበትን ሰው ሰራሽ እውቀት(Artificial intelligence) የተባለ መንገድ በመጠቀም መሆኑን አቶ በፍቃዱ ለአዲስ ማለዳ አስረድተዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ፕሬዘዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ለሲሪል ራማፎዛ ገለፃ አደረጉ!
የኢፌዴሪ ፕሬዘዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበርና ለደቡብ አፍሪካ ፕሬዘዳንት ሲሪል ራማፎዛ በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ገለፃ አድርገዋል፡፡ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ህብረት ያላትን ከፍተኛ ቦታ መናሻ በማድረግ ነው ፕሬዘዳንቷ ለህብረቱ ሊቀመንበርና ለደቡብ አፍሪካ ፕሬዘዳንት በትግራይ ክልል እየተካሄደ ያለውን ህግ የማስከበር ዘመቻ በተመለከተ ማብራርያ የሰጧቸው ተብሏል።
ሁለቱ ፕሬዘዳንቶች ከዚህ ቀደም ይህንኑ ጉዳይ በተመለከተ የስልክ ውይይት አድርገው የነበረ ሲሆን ገፅ ለገፅ የተደረገው ውይይትም ነባራዊ እውነታውን ይበልጥ ለማስረዳት እድል የፈጠረ እንደነበር ተገልጿል።የደቡብ አፍሪካው ፕሬዘዳንት ሲል ራማፎዛ በፕሬዘዳንቷ ከተደረገላቸው ገለፃ በኋላ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እንደሚከታተሉት ማስታወቃቸውን ኢ.ቢ.ሲ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢፌዴሪ ፕሬዘዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበርና ለደቡብ አፍሪካ ፕሬዘዳንት ሲሪል ራማፎዛ በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ገለፃ አድርገዋል፡፡ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ህብረት ያላትን ከፍተኛ ቦታ መናሻ በማድረግ ነው ፕሬዘዳንቷ ለህብረቱ ሊቀመንበርና ለደቡብ አፍሪካ ፕሬዘዳንት በትግራይ ክልል እየተካሄደ ያለውን ህግ የማስከበር ዘመቻ በተመለከተ ማብራርያ የሰጧቸው ተብሏል።
ሁለቱ ፕሬዘዳንቶች ከዚህ ቀደም ይህንኑ ጉዳይ በተመለከተ የስልክ ውይይት አድርገው የነበረ ሲሆን ገፅ ለገፅ የተደረገው ውይይትም ነባራዊ እውነታውን ይበልጥ ለማስረዳት እድል የፈጠረ እንደነበር ተገልጿል።የደቡብ አፍሪካው ፕሬዘዳንት ሲል ራማፎዛ በፕሬዘዳንቷ ከተደረገላቸው ገለፃ በኋላ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እንደሚከታተሉት ማስታወቃቸውን ኢ.ቢ.ሲ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
ህዳር ሲታጠን
ከ102 ዓመት በፊት በ1911 ዓም. ነበር መነሻው ከወደ አሜሪካ እንደሆነ የሚነገርለት የኢንፍሉዌንዛ ቫይረስ የሚሊዮኖችን ህይወት በመቅጠፍ አለምን ያቃወሰው፡፡
ሳይንሳዊ መጠሪያው H1N1 የተባለው ቫይረስ ስፓኒሽ ፍሉ የሚል ተቀፅላ ስም ተሰጥቶታል፡፡ በሀገራችን በኢትዮጵያ ደግሞ የገባበት ወቅት እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት በቀናት ውስጥ ብቻ የቀጠፈው በህዳር ወር ነበርና የህዳር በሽታ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ሳል እና ከፍተኛ ትኩሳት ይዞ የመጣውን ይህን ወረርሽ ለማጥፋትም ህዳር 12 ቀን 1911 ዓም ሀገሬው ከየቤቱ ቆሻሻ እያወጣ እንዲያቃጥል በአዋጅ ተነገረ፡፡
ምንም እንኳን ቆሻሻን ማቃጠል ለአየር ንበርት አሉታዊ አስተዋፅዎ ያለው ቢሆንም በጊዜው ወረርሽኙን ያጠፋው ህዳር መታጠኑ ነው ተብሎ ስለሚታመን ዛሬም በአዲስ አበባ እና አንዳንድ የክልል አካባቢዎች ከመቶ አመታት በኋላ ህዳር 12 ቆሻሻ ይቃጠላል፤ ህዳር ይታጠናል፡፡
Via @addiszeybe
@YeneTube @FikerAssefa
ከ102 ዓመት በፊት በ1911 ዓም. ነበር መነሻው ከወደ አሜሪካ እንደሆነ የሚነገርለት የኢንፍሉዌንዛ ቫይረስ የሚሊዮኖችን ህይወት በመቅጠፍ አለምን ያቃወሰው፡፡
ሳይንሳዊ መጠሪያው H1N1 የተባለው ቫይረስ ስፓኒሽ ፍሉ የሚል ተቀፅላ ስም ተሰጥቶታል፡፡ በሀገራችን በኢትዮጵያ ደግሞ የገባበት ወቅት እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት በቀናት ውስጥ ብቻ የቀጠፈው በህዳር ወር ነበርና የህዳር በሽታ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ሳል እና ከፍተኛ ትኩሳት ይዞ የመጣውን ይህን ወረርሽ ለማጥፋትም ህዳር 12 ቀን 1911 ዓም ሀገሬው ከየቤቱ ቆሻሻ እያወጣ እንዲያቃጥል በአዋጅ ተነገረ፡፡
ምንም እንኳን ቆሻሻን ማቃጠል ለአየር ንበርት አሉታዊ አስተዋፅዎ ያለው ቢሆንም በጊዜው ወረርሽኙን ያጠፋው ህዳር መታጠኑ ነው ተብሎ ስለሚታመን ዛሬም በአዲስ አበባ እና አንዳንድ የክልል አካባቢዎች ከመቶ አመታት በኋላ ህዳር 12 ቆሻሻ ይቃጠላል፤ ህዳር ይታጠናል፡፡
Via @addiszeybe
@YeneTube @FikerAssefa
#ሰበር_ዜና
የመከላከያ ሰራዊት አዲግራትን ከሕወሓት ጁንታ ነፃ ወጣች።
በአሁን ሰዓት ወደ መቐለ እያመራ መሆኑ ታውቋል።
Via:- የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ
@Yenetube @Fikerassefa
የመከላከያ ሰራዊት አዲግራትን ከሕወሓት ጁንታ ነፃ ወጣች።
በአሁን ሰዓት ወደ መቐለ እያመራ መሆኑ ታውቋል።
Via:- የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ
@Yenetube @Fikerassefa
ጠ/ሚ አብይ በትግራይ ክልል እየተካሄደ ስለሚገኘው ኦፐሬሽን፣ ስለ ሰብዓዊ ድጋፎች፣ የክልሉን ነዋሪዎች ደህንነት ስለማስጠበቅ ያስተላለፉት መልዕክት:
<<ሕግ ማስከበር ተልዕኮው የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ባለፉት ጥቂት ቀናት ያስመዘገበው ድል የሚደነቅ ነው። ሠራዊታችን ትናንት ምሽት በአዲግራት ዙሪያ ያሉትን አካባቢዎች ከተቆጣጠረ በኋላ፣ ዛሬ ደግሞ አዲግራትን ከሕወሓት ኃይል ሙሉ በሙሉ ነፃ አውጥቷል።
የፌደራል መንግሥት በተቆጣጠራቸው ከተማዎችና አካባቢዎች የሚገኙ ዜጎች፣ በጸጥታ ኃይሎች ጥበቃ እየተደረገላቸው ወደ ዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸው መመለስ ጀምረዋል። ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር በመሆን፣ ሰብአዊና ማኅበራዊ ፍላጎቶች የሚሟሉበትን መንገድ እናመቻቻለን።
የሰብአዊ ድጋፍ ክንውኖችን ለመከታተል በፌደራል መንግሥት የተዋቀረው ከፍተኛ ኮሚቴ፣ ተመጣጣኝ እና ወቅታዊ ድጋፍ ለማቅረብ የሚያስችል መረጃን እንዲያሰባስቡ ተጨባጭ ሁኔታውን የሚያጣሩ ልዑካንን ወደ ስፍራው ልኳል። በተጨማሪም፣ ይህ ኮሚቴ ባለፉት ቀናት መኖሪያቸውን ጥለው የተሰደዱትን ዜጎች ሁሉ ወደ ቀያቸው ለመመለስ እና ለማቋቋም ከባለ ድርሻ አካላት ጋር መሥራቱን ይቀጥላል።
የፌደራል መንግሥት ለትግራይ ሕዝብ አጠቃላይ ደኅንነት እና ጤንነት ከፍተኛ ዋጋ የሚሰጥ ስለ ሆነ፣ በትግራይ ክልል መረጋጋት እንዲሰፍን እና ዜጎቻችን ከጉዳት እና እጦት ነፃ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ሁሉ እናደርጋለን።>>
@YeneTube @FikerAssefa
<<ሕግ ማስከበር ተልዕኮው የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ባለፉት ጥቂት ቀናት ያስመዘገበው ድል የሚደነቅ ነው። ሠራዊታችን ትናንት ምሽት በአዲግራት ዙሪያ ያሉትን አካባቢዎች ከተቆጣጠረ በኋላ፣ ዛሬ ደግሞ አዲግራትን ከሕወሓት ኃይል ሙሉ በሙሉ ነፃ አውጥቷል።
የፌደራል መንግሥት በተቆጣጠራቸው ከተማዎችና አካባቢዎች የሚገኙ ዜጎች፣ በጸጥታ ኃይሎች ጥበቃ እየተደረገላቸው ወደ ዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸው መመለስ ጀምረዋል። ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር በመሆን፣ ሰብአዊና ማኅበራዊ ፍላጎቶች የሚሟሉበትን መንገድ እናመቻቻለን።
የሰብአዊ ድጋፍ ክንውኖችን ለመከታተል በፌደራል መንግሥት የተዋቀረው ከፍተኛ ኮሚቴ፣ ተመጣጣኝ እና ወቅታዊ ድጋፍ ለማቅረብ የሚያስችል መረጃን እንዲያሰባስቡ ተጨባጭ ሁኔታውን የሚያጣሩ ልዑካንን ወደ ስፍራው ልኳል። በተጨማሪም፣ ይህ ኮሚቴ ባለፉት ቀናት መኖሪያቸውን ጥለው የተሰደዱትን ዜጎች ሁሉ ወደ ቀያቸው ለመመለስ እና ለማቋቋም ከባለ ድርሻ አካላት ጋር መሥራቱን ይቀጥላል።
የፌደራል መንግሥት ለትግራይ ሕዝብ አጠቃላይ ደኅንነት እና ጤንነት ከፍተኛ ዋጋ የሚሰጥ ስለ ሆነ፣ በትግራይ ክልል መረጋጋት እንዲሰፍን እና ዜጎቻችን ከጉዳት እና እጦት ነፃ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ሁሉ እናደርጋለን።>>
@YeneTube @FikerAssefa