YeneTube
116K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.92K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
ሁሉም የአገሪቷ የየብስ ድንበሮች ከዛሬ ጀምሮ ከመድሀኒትና ከምግብ በስተቀር የሠዎች ዝውውር እንዳይከናወንባቸው ታግዷል!

ሁሉም የአገሪቷ የየብስ ድንበሮች ካዛሬ ጃምሮ ከመድሀኒትና ከምግብ በስተቀር የሠዎች ዝውውር እንዳይከናወንባቸው መታገዱን የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ አስታወቁ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ የኮሮና ቫይረስ ሥርጭትን ለመቆጠር ሲባል ድንበርሩን መዝጋት አስፈልጓል።ይሄንንን እንዲያሥፈጽምም ለአገሪቷ የጸጥታ ተቋማት ትእዛዝ ተላልፏል።እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ ድንበሩን ከመዝጋት በተጨማሪ የመንግሥት ተቋማት እንደየሥራ ባህሪያቸው ሠራተኞቻቸው ቤታቸው ሆነው እንዲሠሩ ማመቻቸት እንዳለባቸው ውሣኔ ተላልፏል።ጫት ቤት ሺሻ ቤት እና መጠጥ ቤቶች የተጨናነቀ ሠው እያሥተናገዱ ሥለሆነ ከዛሬ ጀምሮ የጸጥታ ሀይሎች ቁጥጥሩን በማጠናከር እርምጃ እንዲወስዱ ትዛዝ እንደተላለፈላቸው አስታውቀዋል።

Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
ስፔን 4517 አዲስ ተጠቂዎች የተገኘባት ሲሆን 462 አዲስ ሞት ከትናንት ጀምሮ ባለው ጊዜ ተመዝግቧል። እስካሁን በቫይረሱ የተጠቁት ቁጥር 33,089 ሲሆን የሟቾች ቁጥር ደግሞ 2182 ደርሷል ።

@YeneTube @FikerAssefa
ኡጋንዳ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የተጓዙትን እያደነች ነው!

ባሳለፈው ቅዳሜ አንድ ግለሰብ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጉዞ ኡጋንዳ ከደረሰ በኋላ የኮሮናቫይረስ ተጠቂ መሆኑ መረጋገጡን ተከትሎ የአገሪቱ ባለስልጣናት ከግለሰቡ ጋር ንክኪ ነበራቸው ያሏቸውን 84 ተጓዦች በማደን ላይ ናቸው።

Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኮቪድ19ን ስርጭት ለመግታት የሚደረግ የዝግጅት ሥራን አስመልክቶ፣ ከደህንነት ዘርፍ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል።በዓለም-አቀፍ ደረጃ ካለው የመዛመት ፍጥነት አንጻር፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ ቫይረሱ የያዛቸው ሰዎች ቁጥር ከመጨመሩ ጋር ተያይዞ፣ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች የተውጣጡ ንዑሳን ኮሚቴዎች የተመሰረቱ ሲሆን፥ ከእነዚህ አንዱ የደህንነት ንዑስ ኮሚቴው ነው። ውይይት ከተካሄደም በኋላ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሚከተሉት ዐበይት እርምጃዎች የሚተገበሩ መሆኑን ይፋ አድርገዋል፦

1. ከዛሬ መጋቢት 14 ቀን አንስቶ፣ የደህንነት ዘርፉ በቁጥር የበዛ ሰው የሚሳተፍባቸውን ስብሰባዎች የሚያስቆም እና ማሕበራዊ ርቀትን መጠበቅን የሚያስተገብር ይሆናል።

2. የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጨምሮ፣ የመንግሥት ተቋማት ማሕበራዊ ርቀትን ተፈጻሚ ማድረግ እና ስብሰባን ሲያካሂዱ ቫይረሱን የመከላከል ቅድመ ጥንቃቄዎችን ተፈጻሚ ማድረግ አለባቸው።

3. የመንግሥት ተቋማት የተቀጣሪዎቻቸውን ሁኔታ በማጣራት እንደየሁኔታው አንዳንዶች በቤታቸው ሆነው የሚሰሩበትን
መንገድ ማመቻቸት


4. የሕዝብ መጓጓዣ አገልግሎት ሰጪዎች አጨናንቆ ተሳፋሪዎችን መጫን የማይችሉ ሲሆን፥ ይህን ማድረጋቸው በትራፊክ
ፖሊስ እና በበጎ ፈቃደኞች አማካኝነት ቁጥጥር የሚደረግበት
ይሆናል።

5. ብሔራዊ የመከላከያ ሠራዊት እና ፖሊስ ውስጣዊ ቅድመዝግጀት በማካሄድ በሀገር ደረጃ የቫይረሱን ስርጭት የመከላከል ሥራን ለማስፈጸም መዘጋጀት።

6. በተጠቃሚው ማኅበረሰብ ላይ ሕገወጥ የዋጋ ጭማሪን የሚያደርጉ ተቋማት ላይ የሚወሰዱ እርምጃዎች የሚቀጥሉ ይሆናል።

7. መገናኛ ብዙሀን በትኩረት በየደረጃው ግንዛቤን የማሳደግ ሚና መጫወት ይጠበቅባቸዋል።

8. ብሔራዊ የመከላከያ ሠራዊት በድንበር አካባቢ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን በሙሉ ይገታሉ። ይህ እርምጃ ወደ ሀገሪቱ የሚገቡ ሸቀጦችና አስፈላጊ መገልገያዎችን አይጨምርም። በተጨማሪም፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ቫይረሱ በፍጥነት ቢዛመት ክልሎች ለይቶ ማቆያና ማከሚያ እንዲሁም የሕክምና ባለሙያዎቻቸውን እያዘጋጁ መሆኑን ገልጸዋል። አክለውም፣ ፌደራል መንግሥት የኮቪድ19ን የመከላከል ሥራን ለመሥራት 5 ቢሊየን ብር መመደቡን አስታውቀዋል።

ምንጭ: ፋና
@YeneTube @FikerAssefa
የአቃቂ ቃሊቲ መናኸሪያ የኮሮና ቫይረስን ስርጭትን ለመከላከል የሙቀት መመርመሪያ መሳሪያን መጠቀም ጀመረ፡፡

መናኸሪያው ተሳፋሪዎችን እና አሽከርካሪዎችን ሙቀትመለካት መጀመሩን ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ከግል ንጽሕና ጋር በተያያዘ አሽከርካሪዎች እና ተሳፋሪዎች በንጹህ ውሃ እና ሳሙና እጃቸውን እየታጠቡ ወደ መኪና የሚገቡ እንዲገቡ የተደረገ ሲሆን መኪኖችም ተሳፋሪዉ ከመግባቱ በፊት ተገቢውን የጽዳት ሥራ በኪሚካል እንደሚደረግላቸው መሆኑ ተገልጿል፡፡

-ከትራንስፖርት ሚኒስቴር
@YeneTube @FikerAssefa
ደቡብ አፍሪካ 128 አዲስ ተጠቂዎችን ያስተናገደች ሲሆን በአጠቃላይ 402 ሰዎች እስካሁን ተጠቅተዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
እራሳቸውን ለይተው የነበሩት የራይድ አሽከርካሪዎች ከኮረናነጻ መሆናቸው ተነገረ

አዲስ አበባ ውስጥ ዘመናዊ የታክሲ አገልግሎት የሚሰጠው የራይድ ሁለት አሽከርካሪዎች የኮሮናቫይረስ ጥርጣሬ አድሮባቸው እራሳቸውን ለይተው ከቆዩ በኋላ በተደረገላቸው ምርምራ ነጻ ሆኑ ሲል ድርጅቱ አስታወቀ።

የራይድ ታክሲ መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሳምራዊት ፍቅሩ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ያሳፈሩትን ሰው በመጠርጠራቸው እራሳቸውን ለይተው የቆዩት ሁለት ሾፌሮች እንደነበሩ፤ ነገር ግን ሁለቱም ተመርምረው ነጻ ሆነው መገኘታቸውን ተናግረዋል።

ራይድ አስራ አምስት ሺህ ሾፌሮችን በመያዝ አገልግሎት እንደሚሰጥ የተናገሩት ሥራ አስፈጻሚዋ፤ የኮሮናቫይረስ በአዲስ አበባ ውስጥ መገኘቱን ተከትሎ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ጨምረውም ሾፌሮች ከተሳፋሪ ጋር ስለሚኖራቸው ግንኙነት እንዲሁም የእጃቸውንና የመኪናቸውን ንጽህና በጸረ ተህዋሲያን እንዴት መጠበቅ እንዳለባቸው እንደሚያስተምሩ ጠቅሰዋል።

ከዚህ ባሻገርም የተሳፋሪዎችንም ሆነ የሾፌሮችን ጤንንት ለመጠበቅ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭምብልና ጓንት እንዲጠቀሙ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

-BBC
@Yenetube @Fikerassefa
ሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ንግድ እና መምሪያ ቤት የተላከ ⬆️

ጭፈራ ቤቶችን በተመለከተ ይህ ደብዳቤ ከደረሳችሁ ቀን ጀምሮ ቤታችሁን እንድትዘጉ የሚል ማሳሰቢያ አስተላልፏል ምክንያቱም የአለም ስጋት የሆነውን ኮሮና ቫይረስን ለመከላከ መሆኑን በደብዳቤ ላይ ተገልጷል ።

@Yenetube @Fikerassefa
የቦትስዋና ፕሬዝዳንት ኤሪክ ሞጊዚሲ ማሳሲ ለአራት ቀናት ራሳቸውን ማግለል በለይቶ ማቆያ ውስጥ ማድረግ መጀመራቸውን መንግሥት በፕሬዚዳንቱ ጽህፈት ቤት በኩል በዛሬው እለት አስታውቋል ፡፡

ራስን ማግለል ውሳኔው የመጣው ለስራ ጉዞ ወደ ጎረቤት ናሚቢያ ሄደው ከተመለሱ በኋላ ነው ፡፡ በዊንሆክ ፕሬዝዳንት ሀጌ ጂንግቦ በተደረገው ቃለ መሀላ ላይ ተገኝተዋል።

- CGTN
@YENETUBE @Fikerassefa
👍1
በአዲስ አበባ ለረዥም ጊዜ መንገድ ዳር የቆሙ ተሽከርካሪዎችን የማስነሳት ስራ ጀመረ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ለመንገድ ትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት ከሆኑ ነገሮች መካከል በየጎዳናዎቹ ላይ ያለአግባብ ለረዥም ጊዜ የሚቆሙ የንግድ ፣ በብልሽት እና በተለያዩ ምክንያቶች የሚቆሙ ተሽከርካሪዎች ተጠቃሽ ናቸው፡፡የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ ችግሩን ለመቅረፍ የሚያስችል ተግባር በመጀመሩ መንገድ ዳር የቆሙ ተሽከርካሪዎችን ከመጋቢት 3/2012 ዓ.ም ጀምሮ እያስነሳ ይገኛል፡፡

ኤጀንሲው ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን እና ከከተማዋ የሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ደንብ ማስከበር አገልግሎት ዘርፍ ጋር በመተባበር ሲሆን የተሽከርካሪዎቹ ባለቤቶች ንብረቶቻቸውን ከመንገድ ዳር እንዲያስነሱ ከአምስት እስከ ሰባት ቀን ጊዜ ማስታወቂያ ከተለጠፈ በኃላ በክሬን የማስነሰቱን ስራ እየተከናወነ ነው፡፡ከየመንገዱ ዳር በክሬን የሚነሱ ተሽከርካሪዎች ለሚቆዩበት ሶስት ቦታዎች የተዘጋጁ ሲሆን እስከ አሁን ስምንት ተሽከርካሪዎች ተነስተዋል፡፡

የተሽከርካሪ ባለቤቶቹ በሚሰጣቸው የጊዜ ገደብ ተሽከርካሪዎቻቸውን የማያስነሱ ከሆነ ተሽከርካሪዎቹ በሚነሱበት ወቅት ለሚደርስባቸው ጉዳቶች ኤጀንሲው ተጠያቂ የማይሆን ሲሆን ለክሬን ማስነሻ ኪራይ ክፍያ፣ ተሽከርካሪዎቹ ለሚቆዩበት ቦታ የፓርኪንግ እና የጥበቃ አገልግሎት ክፍያን ጨምሮ ባለንብረቶች ይከፍላሉ፡፡ በቀጣይም በከተማዋ በተለያዩ ቦታዎች በተለያዩ ምክንያቶች ለረዥም ጊዜ መንገድ ዳር ቆመው የሚገኙ ተሽከርካሪዎችን የማስነሳቱ ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ተብሏል።

ምንጭ: የከ/መ/ ፕሬስ ሴክሬተሪያት
@YeneTube @FikerAssefa
አል ኢምራን መስጂድ አስተዳደር የተወሰዱ እርምጃዎች :-

-ለሰላት መስጂድ ስንመጣ በየመሃላችን ሁለት ሰው ሊያሰግድ የሚችል ቦታ ርቀት አድርገን መቆም።

-ወደ መስጂድ ስንገባ እጃችንን በሳሙና ታጥበን መግባት።

- መስጂድ ሲመጣ ህፃናትን ይዞ አለመምጣት።

-ሰላምታ በቃላት መለዋወጥ....የመሳሰሉት
እርምጃዎች ተውስደዋል ሁላችንም ብንተገብረው መልካም ነው።

@Yeneyube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 11 አራብሳ ለሚ ኮብልስቶን ማምረቻ አከባቢ ስኳር እና ኬሚካል ከቀይ አፈር ጋር በመቀላቀል ማር ነው ብሎ ለመሸጥ ሲያዘጋጅ የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

ግለሰቡ ሙሉ መኖሪያ ግቢ ተከራይቶ ህገ - ወጥ ተግባሩን ሲፈፅም በቁጥጥር ስር ሊውል የቻለው ፖሊስ በጥርጣሬ ባደረገው ማጣራት ነው ፡፡በቦሌ አራብሳ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል መከላከል አባል ሳጅን ድንበሩ ጥላሁን እንደገለፁት ለስራ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ከፍተኛ ጭስ ከግቢው ሲወጣ ተመልክተው ሲጠይቁ እንጀራ እየጋገርን ነው የሚል ምላሽ ቢሰጣቸውም ተጠራጥረው ባደረጉት ማጣራት ህገ- ወጥ ድርጊት እየተፈፀመ መሆኑን በማረጋገጥ ለሚመለከተው የአስተዳደር አካል ሪፖርት አድርገዋል፡፡

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘም አንድ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት ይገኛል ብለዋል፡፡በቦሌ ክ/ከተማ የወረዳ 11 ንግድና ኢንዱስትሪ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ አድነው ወልዴ በበኩላቸው ግለሰቡ መርካቶን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ማር ነው ብሎ ያዘጋጀውን ባዕድ ነገር ሲሸጥ እንደቆየ ገልፀዋል፡፡

Via Addis Ababa Police Commission
@YeneTube @FikerAssefa
በጋምቤላ ኤርፖርት እስካሁን የመንገደኞች ሙቀት እየተለካ አለመሆኑ ተገለጸ።

በቀን ሁለት ጊዜ ማለትም ከአዲስ አበባ በአሶሳ አድርጎ ወደ ጋምቤላ እና ከጋምቤላ ወደ አዲስ አበባ የሚደረገው የሃገር ውስጥ በረራ እንደቀጠለ ነው፡፡ነገር ግን ተጓዦች ከጋምቤላ ተነስተው ወደ አዲስ አበባ ሊሄዱ ሲሉ እንዲሁም ከ አዲስ አበባ ወደ ጋምቤላ የሚገቡ ተጓዞች ወደ አየር ጣቢያው ሲደርሱ ምንም አይነት የሙቀት መለኪያ እየተደረገላቸው እንዳልሆነ የክልሉ ጤና ቢሮ ሃላፊ ካን ጋሏክ ተናግረዋል፡፡ምንም እንኳን ክልሉ አምስት የሙቀት መለኪያ ማሽኖች እንዲኖሩት ቢደረግም እነዚህን ማሽኖች ከ ደቡብ ሱዳን ጋን በሚዋሰኑ አምስት ጣቢያዎች እንዲከፋፈሉ መደረጉን ነግረውናል፡፡ይሁን እንጂ ይህ መሳሪያ በ ከተማው በሚገኘው ኤርፖርት ተግባራዊ ያለመደረጉ ወረርሽኙን ለመከላከል እየተሰራ ያለውን የጥንቃቄ ስራ እንደሚያጎድል ሃላፊው ገልጸዋል። በተጨማሪም መሳሪያውን ወደ ስፍራው ለማስገባት ጥረቶች ማድረጋችን መቀጠላቸውም ሃላፊው ተናግረዋል፡፡

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በኮሮናቫይረስ ስርጭት ስጋት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር-ኦነግ በአዲስ አበባ የሚገኘውን ቢሮውን መዝጋቱን አስታወቀ።

ምንጭ: ቢቢሲ
@YeneTube @FikerAssefa
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ እና አፍጋኒስታን የኮሮና ቫይረስ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ መቀነስ የሚያስችል ድጋፍ ሊያጸድቅ ነው!

የዓለም ባንክ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ40 ሃገራት የኮሮና ቫይረስ የሚያደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ መቀነስና መከላከል የሚያስችል የ1 ነጥብ 7 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።ድጋፉ ኢትዮጵያና አፍጋኒስታንን ጨምሮ በሃገራቱ የኮሮና ቫይረስ የሚያደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖና ጉዳት ለመቀነስ ያለመ ነው ተብሏል።

የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድም በዚህ ሳምንት ለኢትዮጵያ እና አፍጋኒስታን ድጋፍ ለማድረግ የቀረበውን ሰነድ ተመልከቶ እንደሚያጸድቅ ነው የሚጠበቀው።ድጋፉ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ባንኩ ለአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ በሚል ባለፈው ሳምንት ካጸደቀው 14 ቢሊየን ዶላር ለሃገራቱ የሚሰጥ መሆኑን የባንኩ ፕሬዚዳንት ዴቪድ ማልፓስ አስታውቀዋል።

ባንኩ ባለፈው ሳምንት ዓለም ላይ የኮሮና ቫይረስ የሚያስከትለውን ተፅዕኖ መቀነስና መከላከል የሚያስችል የ14 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ ማፅደቁ ይታወሳል።ከዚህ ባለፈም ባንኩ ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ትብብርና ከባንኩ የግሉ ሴክተር ዘርፍ ጋር በመሆን በ24 ሃገራት ተግባራዊ የሚደረግ የ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ፕሮጀክት ለመተግበር እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።

Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ለመቐለ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ በሙሉ!

የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ለመከላከል የሚወሰዱ ተጨማሪ እርምጃዎች⬆️⬆️⬆️⬆️

@YeneTube @FikerAssefa
የእርዳታ ጥሪ !

የእህታችንን ህይወት የጓጓችለትን ምርቃቷን ሳታይ እንዳትቀጠፍብን የተማሪነት ድርሻችንን እንወጣ።

ምርቃቷን በጉጉት የምትተብቀው ቤተልሄም ተስፋዬ ዛሬ ጥቁር አንበሳ ተኝታ እህት ወንድሞቼ ህይወቴን ታደጓት እያለች የ እርዳታ ጥሪ ታስተላልፋች። በቻልነው አቅም በየትምህርት ክፍላችን በመልቀቅ የ እህታችንን ህይወት እንታደግ።

ዛሬ ብቻ በ ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ጊቢ 12,921 ብር (አስራ ሁለት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሃያ አንድ ብር) መሰብሰብ ችሏል። ቀጣይ የታሰቡ ስራዎች በመላው ኢትዮጵያ ማስታወቂያ በመስራት የእህታችንን ህይወት እንታደጋለን።

በ አጠቃላይ ለህክምናው የሚያስፈልጋት ወጪ 50,000$ በ ሃገር ደረጃ 1,645,551 ማለትም አንድ ሚሊየን ስድስት መቶ አርባ አምስት ሺ አምስት መቶ ሃምሳ አንድ ብር ነው። በምንጠቀመው ማህበራዊ ሚዲያዎች በመልቀቅ እህታችን የደረሰባትን ህመም በማስተዋወቅ እንታደጋት።

ቤቲየ ተመርቀሽ ስትስቂ እናይሻለን እሺ እህት አለም። ለወገን ደራሽ ወገን ነው።

የንግድ ባንክ አካውንት

- 1000326460568
@Yenetube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና የሊግ ካምፓኒ ዛሬ ከሰዓት በፌዴሬሽኑ መሰብሰቢያ አዳራሽ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የዘንድሮ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ መቋረጡን ይፋ አድርገዋል፡፡

ክለቦችም ተጫዋቾችን ለመጠበቅ በዚህ ጊዜ ልምምዶችን ማቋረጥ እንዳለባቸው የእግር ኳሱ አስተዳዳሪው አካል አሳውቋል፡፡

በደብረዘይት በሚገኘው የክቡር ይድነቃቸው ተሰማ አካዳሚ ለፕሪሚየር ሊጉ ዝግጅታቸውን ሲያደርጉ የነበሩት ቅዱስ ጊዮርጊሶች በኮሮና ስጋት ምክንያት ልምምዳቸውን ከነገ ጀምሮ እንደሚያቆሙ ከክለቡ የወጡ መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡

via:- Hatric Sport
@Yenetube @Fikerassefa
በመላው ዓለም የተስፋፋውን የኮሮና ወረርሽኝ ለመግታት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ

በሀገራችን ኢትዮጵያ በገጠር፣ በከተማና በመላው ዓለም ለምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን በሙሉ!

ወቅታዊ የሰው ልጅ ሥጋት በመሆን በመላው ዓለም በፍጥነት በተስፋፋው የኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ዓለም አቀፍ ሥጋት ስለተከሰተ መንግሥታት ሀገርን ከጥፋት፣ ሕዝብን ከሞት ለመጠበቅ አዋጆችን እያወጡ ይገኛሉ፡፡

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት ለመታደግ እምነትና ቀኖናን ጠብቆ ሃይማኖታዊ መመሪያ የመስጠት ሐዋርያዊ ኃላፊነት አለባት፡፡

ስለዚህ ቋሚ ሲኖዶስ የጉዳዩን አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባት መሠረተ እምነትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ጠብቆ ለሁሉም ካህናትና ለሕዝበ እግዚአብሔር ደኅንነት ሲባል የሚከተሉትን መመሪያዎች አስተላልፏል፡-

1. በሰሙነ ሕማማት እንደምናደርገው የእርስ በርስ መሳሳም ቀርቶ ራስን ዝቅ በማድረግ፣ እጅ በመንሳት ወይም በእማሄ ሰላምታ በማቅረብ እንዲፈጸም፣

2. ወረርሽኙ በሰዎች መሰባሰብ የሚስፋፋ ስለሆነ ማናቸውም መንፈሳዊ ጉባኤያት፣ የትምህርት ክፍለ ጊዜያት፣ ወደ ገዳማትና አድባራት የሚደረጉ ጉዞዎች እና ምዕመናን የሚሳተፉባቸው ታላላቅ መርሐ ግብሮች ለጊዜው እንዲቋረጡ፣

3. ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲገባም ሆነ አሰፈላጊ በሆነበት ጊዜ ሁሉ እጆቻንን በመታጠብና ዘርዘር ብሎ በመቆም ሥርዓተ አምልኮ እንዲፈጸም፣

4. ዓመታዊ የንግሥ ክብረ በዓላት በቅዳሴና በማኅሌት ታስበው ክብረ በዓላቱ በሌላ ጊዜ እንዲከበሩ፣

5. የጉንፋን ምልክት ያለባቸው ለሌሎች እንዳያስተላልፉ በቤታቸው በጥንቃቄ ተለይተው በጸሎትና በሕክምና እንዲቆዩ፣ ከቤተ ክርስቲያን የሚያስፈልጋቸውን መንፈሳዊ አገልግሎትም በልዩ ሁኔታ እንዲያገኙ፣

6. በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ የተቋቋመው ግብረ ኃይል የተስፋ ልዑክ በመሆን እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ ተደራጅቶ ተልዕኮውን በአስቸኳይ እንዲጀምር

7. ሥርዓተ ቅዳሴን በተመለከተ፡-

• በቤተ መቅደስ ቀዳስያን በሆኑት ልዑካን ብቻ ሥርዓተ ቅዳሴው እንዲፈጸምና ሌሎች አገልጋዮች በቅድስቱ ዘርዘር ብለው በመቆም እንዲያገለግሉ፣

• በዕለቱ ለሚቆርቡ ምዕመናን ለአረጋውያን፣ ለወጣቶችና ለሕፃናት የፈረቃ ተራ በማዘጋጀት ቆራቢዎች ብቻ ወደ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ገብተው ዘርዘር ብለው በመቆም እንዲያስቀድሱ፣

• ሌሎች ምእመናን በአጸደ ቤተክርስቲያን ቢያንስ ሁለት የትልቅ ሰው እርምጃ ያህል በመራራቅ ቆመው እንዲያስቀድሱ፣

• የቅዳሴ ጠበል በየግል መጠቀሚያ ምእመናን በየቆሙበት ቦታ በጥንቃቄ እንዲሰጥ፣

• ሌሎች ከቅዳሴ ጋር የተያያዙ ዝርዝር የአፈፃፀም ጉዳዮችን ግብረ ኃይሉ አዘጋጅቶ በቅዱስ ሲኖዶስ በማጸደቅ ለአህጉረ ስብከት በሚልከው መመሪያ መሠረት ተግባራዊ እንዲደረግ፤

8. ከሥርዓተ ቅዳሴ በተጨማሪ እንደ ስብሐተ ነግሕ፣ ሰዓታት፣ ቁመተ ማኅሌት፣ ጥምቀተ ክርስትና፣ ጸሎተ ፍትሐት፣ የመሳሰሉ አገልግሎቶች ለሥርዓቱ በሚያስፈልገው ቁጥር ብቻ እና በውሱን ሊቃውንት በተራ እንዲፈፀም፣

9. ወረርሽኙ ከዓለም እንዲጠፋ ካህናት ብቻ በቤተ መቅደስ፣ በዐውደ ምኅረትና በአጸደ ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ጸሎተ እጣን በማድረስ ማዕጠንት እንዲፈጽሙ፣

10. በማኅበራዊ ግንኙነት በደስታ፣ በሐዘን፣ በእድር፣ በሥርዓተ ቀብር አፈፃፀምና በመሳሰሉት መሰባሰቦች በሽታው እንዳይሠራጭ አገልግሎቱ በውስን የሰው ቁጥር በጥንቃቄ እንዲፈፀም፤

11. ምዕመናን ራሳቸውን እየጠበቁ በቫይረሱ የተጠቁና አገግመው የወጡ ወገኖችን፣ እንዲሁም በውጭ ሀገር ዜጎች ላይ ከሃይማኖትና ከምግባር የወጣ መገለልና ጥቃት እንዳይደርስባቸው በክርስቲያናዊ ፍቅርና በኢትጵያዊ ጨዋነት እንክብካቤ እንዲደረግላቸው፣

12. ለነዳያን እና ለተቸገሩ ወገኖች አስፈላጊው ማኅበራዊ እና ቁሳዊ እገዛ በሁሉም አጥቢያዎች እንዲደረግ፣

13. ቤተ ክርስቲያንን ከማይወክሉና ቀኖናዊ ካልሆኑ አሳሳች መረጃዎች በመቆጠብ ሊቃውንት፣ ካህናት፣ መምህራን፣ ሰባክያን፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ከቅዱስ ሲኖዶስ የሚሰጡ መመሪያዎችን በየአጥቢያችሁና አስፈላጊ በሆኑ ቦታዎች ሁሉ እንድትፈጽሙ እና እንድታስፈጽሙ ተወስኗል፡፡

በአጠቃላይ በበሽታው እስካሁን ለተያዙት፣ በጊዜያዊ ማቆያ ለሚገኙት በሙሉ እግዚአብሔር አምላካችን ምህረቱን እንዲሰጥልን እንጸልያለን፤

በመላው ዓለም ዜጎቻቸውን በበሽታው ለተነጠቁ ሁሉ መጽናናቱን እንዲሰጥልን ያረፉትንም እንዲምርልን እግዚአብሔርን በጸሎት እንጠይቃለን፤

በመላው ዓለም የምትገኙ ወገኖቻችን የራሳችሁና የሌሎች ሕይወት ከወረርሽኙ እንዲጠበቅ እንዲሁም የበሽታው ሥርጭት እንዲቆም መንፈሳዊና ማኅበራዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ እያሳሰብን የተሰጡት መመሪያዎች ወረርሽኙ እስኪጠፋ ድረስ የጸኑ እንዲሆኑ በጥብቅ እናስታውቃለን፡፡

ልዑል እግዚአብሔር በቸርነቱና በይቅርታው ብዛት ዓለማችንን ከጥፋት የሰውን ልጅ ሁሉ ከመከራ ሞት ይጠብቅልን፡፡ አሜን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

መጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ.ም
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa