YeneTube
117K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
83ኛው የሰማዕታት ቀን በአዲስ አበባ 6 ኪሎ የሰማዕታት መታሰቢያ ሀውልት አደባባይ እየተከበረ ነው።

ዕለቱ አባት አርበኞችና የከተማዋ ነዋሪዎች በተገኙበት ነው እየተከበረ ያለው።የሀገር መከላከያና የፌደራል ፖሊስ ማርሽ ባንድ አባላት በስፍራው በመገኘት የተለያዩ ጣዕመ ዜማዎችን አሰምተዋል።ዕለቱ በ1929 ዓ.ም በወቅቱ የኢትዮጵያ አገረ ገዢ በነበረው ሮዶልፎ ግራዚያኒ በግፍ የተጨፈጨፉ ከ30 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን የሚታወሱበት ነው።

Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
አዲስ የመንግሥት ሠራተኞች ውሎ አበል ደንብ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀረበ!

የኢፌዴሪ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አዲስ የመንግሥት ሠራተኞች ውሎ አበል ደንብ አዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ማቅረቡን አስታወቀ።በኮሚሽኑ የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አለባቸው ዓለሙ፣ ረቂቅ ደንቡ ካለው ነባራዊ ሁኔታ በመነሣት በጥናት ላይ ተመሥርቶ መዘጋጀቱን አመልክተዋል።ደንቡ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ተመርምሮ ማስተካከያ ከተደረገበት በኋላ፣ ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተመርቶ ተግባር ላይ እንዲውል የሚደረግ መሆኑም ተጠቁሟል።ከሐምሌ 1 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ ስራ ላይ የዋለው የመንግስት ሠራተኞች የቀን ውሎ አበል መመሪያ እንደሚያመለክተው የመንግሥት ሠራተኛው በየትኛውም ክልል ሄዶ ቢሰራ ከፍተኛ ደመወዝ አለው የሚባለው 225 ብር የሚታሰብለት ሲሆን፤ አነስተኛ ደመወዝ ተከፋይ ነው የሚባለው ደግሞ በቀን የሚያገኘው 111 ብር ነው።

Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
ህዝብዊ የድጋፍ ሰልፍ በሀዋሳ ከተማ እንደሚደረግ ተገለጸ!

አርብ የካቲት 13/2012 ዓ.ም በሀዋሳ ከተማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡ ማግስት ጀምሮ በሀገራችን እያስመዘገቡ ያሉትን ለውጥ በመደገፍና ለውጡን ለማስቀጠል ህዝቡ ከጎናቸው የሚቆም መሆኑን ለማረጋገጥ ታላቅ ህዝባዊ የምስጋናና የድጋፍ ሰልፍ እንደሚደረግ ተገለጸ።በመሆኑም የከተማው ነዋሪዎችና የሲዳማ ህዝብ የሚያደርጉት ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ፍጽም ሰላማዊና የደመቀ እንዲሆን የዞኑና የከተማው አስተዳደር አስፈላጊውን ዝግጅት ያጠናቀቁ መሆኑን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ግንኙነት ጽህፈት ቤትን ጠቅሶ ደቡብ ቲቪ ዘግቧል።

@YeneTube @FikerAssefa
የሸገር ዳቦ ማምረቻ ፋብሪካ ግንባታ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደረሰ!

በሜድሮክ እህት ኩባንያ ‹‹ሆራይዘን ፕላንቴሽን›› እየተገነባ ያለው የሸገር ዳቦ ማምረቻ ፋብሪካ ተጠናቆ ሥራ ሊጀምር የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ እንደደረሰ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ:: በሆራይዘን ፕላንቴሽን የእቅድ ቢዝነስ ልማትና ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ አቶ ይበልጣል ሽመልስ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት ግንባታው ከተጀመረ ወራትን ያስቆጠረው የሸገር ዳቦ ማምረቻ ፋብሪካ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሷል።የመሰረት ድንጋይ ከተጣለ ጀምሮ ሥራው በጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር እየተመራ እንደነበር የተናገሩት ሥራ አስኪያጁ በቀን 18 ሰዓት በመስራት ግንባታውን ማፋጠን እንደተቻለና ጎን ለጎንም የማሽነሪዎችንና የሌሎች ግብዓቶችን ግዢ ተፈፅሞ ሀገር ውስጥ መግባታቸውን ገልጸዋል።

Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
ከ20 አመታት በፊት ከኢትዮጵያ የወጣው ታሪካዊው የዘውድ ቅርስ ወደ አገር ተመለሰ።

ኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜያት ከሀገር የወጡ በርካታ ቅርሶች እንዳሏት ይታወቃል፡፡ከነዚህ መካከል አንዱ የሆነው እና ከ20 አመታት በፊት ባልታወቀ ሁኔታ ከኢትዮጵያ የወጣዉና ከ400 ዓመታት በላይ እድሜ ያለው የኢትዮጵያ ታሪካዊ የዘውድ ቅርስ ነዉ፡፡የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳስታወቀዉ፤ቅርሱ ተሰርቆ ለ20 አመታት ያህል በኔዘርላንድ እንደነበር የተነገረ ሲሆን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴርና በሌሎችም ትብብር ቅርሱን ወደ አገር ቤት መመለስ እንደታቸለ አስታዉቋል፡፡

ለቅርሱ መመለስ እና መገኘት የትውልደ ኢትዮጵያውያን ትብብር ቅርሱ ሚና ከፍተኛ እንደነበር የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታዉቋል፡፡በዛሬዉ እለት ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ለብሔራዊ ሙዚየም የርክክብ ስነ ስርዓት መደረጉንም ሰምተናል፡፡ኢትዮጵያ በጣሊያን እና ከዚያም ቀደም በነበሩ ወራራዎች ወቅትዊና ታሪካዊ ቅርሶቿ በአዉሮፓዉያኑ እንደተበዘበዘች የዘርፉ ምሁራን ይናገራሉ፡፡በቅርቡም የአፄ ቴዎድሮስ ፀጉር ቁንድላ ከአገረ እንግሊዝ ወደ አገር መመለሱ አይዘነጋም፡፡

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ በብድር ጫና ከከፍተኛ ወደ መካከለኛ ስጋት ተሸጋግራለች ተብሏል!

ኢትዮጵያ ከውጭ አገራት የወሰደችው የብድር መጠን ከ27 ቢሊዮን ዶላር በላይ ቢሆንም፣ አገሪቱ ከብድር ጫና ከከፍተኛ ስጋት ወደ መካከለኛ ስጋት መሸጋገሯን የገንዘብ ሚኒስቴር ገለጸ።ይህም የተረጋገጠው የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም እና ዓለም ባንክ ጋር በጋራ ባከናወኑት የብድር ጫና ትንተና ላይ መሆኑን ያስታወሰው ሚኒስቴሩ ለዚህም እንደ ምክንያት ያነሳው የቻይና የንግድ አበዳሪዎች የዕዳ ክፍያ ጊዜ ሽግሽግ እንዲራዘም መደረጉን ነው።

ኢትዮጵያ በግማሽ ዓመቱ ከዓለም ባንክ እና ከሌሎች የገንዘብ ተቋማት 2ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ብድር ያገኘች ሲሆን በእርዳታ ደግሞ 13 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር አግኝታለች።ከቻይናና ከልማት አጋር መንግስታት ደግሞ 9ነጥብ3 ቢሊዮን ብር ብድር ስታገኝ 13 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር እርዳታ ማግኘቷን ሚኒስቴሩ አስታውቋል። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ በ2012 ግማሽ ዓመት ውስጥ ከ39 ነጥብ ቢሊዮን ብር ብድርና እርዳታ ማግኘቷን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡

Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
የኢንጅነር ስመኘው በቀለ የመታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ!

የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ የነበሩት የኢንጅነር ስመኘው በቀለ የመታሰቢያ ሐውልት በዛሬው ዕለት ተመረቀ፡፡በመታሰቢያ ሐውልቱ የምርቃት ሥነ-ስርዓት ላይ በኦርቶዶክስ እምነት ስርዓት መሰረት የፍትሃትና የፀሎት ሥነ - ስርዓት ተካሂዷል፡፡ከዚህ በተጨማሪም በሐውልቱ ምርቃት ሥነ-ስርዓት ላይ የተገኙ የተለያዩ ድርጅቶ፣ ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል፡፡ለምርቃት የበቃውን የኢንጅነር ስመኘውን የስርዓተ ቀብር ሐውልት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሰራው መሆኑን ተቋሙ አስታውቋል፡፡

Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
Audio
⬆️⬆️

በደቡብ እና ምዕራብ ኦሮሚያ በነበረው የፀጥታ ችግር ወደ 1,200 በሚጠጉ ቀበሌዎች በህገ-ወጦች ተዋቅሮ የነበረ አስተዳደራዊ መዋቅር ፈርሶ ህጋዊ የመንግስት መዋቅር ተዘርግቷል ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ፡፡

⬆️ዝርዝሩን ከላይ ያለውን የድምፅ ፋይል ከፍተው ያዳምጡ!

Via Sheger
@YeneTube @FikerAssefa
የcopy እና paste ፈጣሪው የኮምፕዩተር ሳይንቲስት ላሪ ቴስለር በ74 ዓመቱ አረፈ።

@YeneTube @Fikerassefa
ወይዘሮ ፍሬአለም ሽባባው የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው እንዲያገለግሉ በጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ተሾሙ።

Via Ethiopia Live Updates
@YeneTube @FikerAssefa
ስካይ ላይት ሆቴል ባለ አምስት ኮከብ ደረጃ ተሰጥቶታል

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ስካይ ላይት ሆቴል በባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከተገመገመ በኋላ ባለ አምስት ኮከብ ደረጃ ተሰጥቶታል።

የዛሬ አመት በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተመርቆ ሰራ የጀመረው በቦሌ አየር ማረፍያ ጎን የሚገኘው ሆቴል ለግንባታ 65 ሚልየን የአሜሪካ ዶላር የፈጀበት ሲሆን 373 የመኝታ ክፍሎች ሲኖሩት በአንዴ 2,000 ተሰብሳቢዎችን የሚያስተናግድ የስብሰባም አዳራሽ አለው።

Via:- Fidelpost.com
@YeneTube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የ4 መንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን የውል ስምምነት ከተቆራጭ ድርጅቶች ጋር ዛሬ ተፈራረመ።

የተፈረሙት ፕሮጀክቶች የቆሼ- ሚጦ -ወራቤ፣ የጋምቤላ-አቦቦ-ዲማሎት፣ የግሸን መገንጠያ ዲዛይንናበግንባታ እንዲሁም የጎንጂ-ቆለላ (ቆሬ-አዲስ አለም)የመንገድ ስራ ፕሮጀክቶች ናቸው።በፊርማ ስነ ስርአቱ ላይ መንገዶቹ ከሚሰሩባቸው አካባቢዎች የተወከሉ የሀገር ሽማግሌዎችና የአስተዳደር አካላት ተገኝተዋል።

Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
በረዶ ቀላቅሎ የጣለ ዝናብ ጉዳት አደረሰ፡፡

በምዕራብ ጎጃም ዞን ቋሪት ወረዳ ቋሪት ኢየሱስ ቀበሌ ዳሞት ተራራ አካባቢ በረዶ ቀላቅሎ የዘነበ ዝናብ በሰብል፣ በመጠለያ እና በእንስሳት ላይ ጉዳት አድርሷል፡፡የቋሪት ወረዳ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሠለሞን በቀለ እንደገለጹት ትናንት የካቲት 11/2012ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ገደማ በጣለው ዝናብ በሰብል፣ በመጠለያ ቤቶችና በእንስሳት ላይ ጉዳት አድርሷል ብለዋል፡፡

የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አማረ ባይለው ጉዳቱ በደረሰ በ30 ደቂቃ ልዩነት ወደ ስፍራው እንደሔዱ ገልጸው ከፍተኛ መጠን ያለው በረዶ እንደጣለ መመልከታቸውን ተናግረዋል፡፡ ከ25 እስ 30 ሄክታር በሚሸፍን መሬት ላይ በረዶ የቀላቀለው ዝናብ መዝነቡንም ነው የተናገሩት፡፡ይህም በቀሪ እርጥበት በተዘሩት ጓያ እና ሽምብራ እንዲሁም በመስኖ ሰብሎች ላይ ጉዳት አድርሷል ብለዋል፡፡ በሰው ላይ ግን ጉዳት አለመድረሱን ነው ያስታወቁት፡፡የጉዳት መጠኑን በማረጋገጥ ውሳኔ ለመስጠት መረጃ የሚያጣራ ባለሙያ መላካቸውንም አቶ አማረ ገልጸዋል፡፡

የአማራ ክልል አደጋ መከላከል፣ ምግብ ዋስትና ፕሮግራም እና ልዩ ድጋፍ የሚሹ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ወይዘሮ እታገኝ አደመ ደግሞ መረጃው እንዳልደረሳቸው ነው የተናገሩት።በወረዳው አስተዳዳሪ የሚመራ የተቋቋመ ግብረ ኃይል ስላለ ችግር ሲፈጠር የጉዳት መጠኑን በመለዬት ለክልሉ እንደሚልክም ተናግረዋል፡፡ መረጃውን መሠረት በማድረግ የክልሉን ድጋፍ የሚሻ ከሆነ ኮሚሽኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አስታውቀዋል፡፡

Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
የጣና በለስ ስኳር ፕሮጀክት 235 ሚሊዮን ብር ብድር ባለማግኘቱ ስራው እንደተስተጓጎለበት ገለጸ!

የጣና በለስ ቁጥር አንድ የስኳር ፋብሪካ ፐሮጀክት ግንባታ 70 በመቶ መድረሱን ተከትሎ 6ሺህ ሄክታር የሸንኮራ አገዳ ለማምረት ዝግጁ ቢሆንም 235 ሚሊዮን ብር ብድር ባለማግኘቱ ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ መቸገሩን ዘ ኢትዮጵያን ሄራልድ ዘገበ።የፕሮጀክቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አንተነህ አሰጌ እንደተናገሩት ከሆነም ባንኮች ብድር እንዲሰጡን የጠየቅን ቢሆንም ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።በአሁን ወቅት 13ሺሕ ሄክታር የሸንኮራ አገዳ የተተከለ ቢሆንም ለምርትነት ዝግጁ የሆነው 2ሺህ ሄክታር ብቻ መሆኑንም ጠቅሰዋል።የፋብሪካው ግንባታ በመጠናቀቅ ደረጃ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፋብሪካው ሙሉ በሙለው ወደ ትግበራ ከመግባቱ በፊት በመጪው ግንቦት ወር የሙከራ ምርቱን ለመጀምር በዝግጅት ላይ መሆኑን አንተነህ ገልጸዋል።

Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
🇹🇷#Study_in_Turkey!🇹🇷

ያለምንም ፈተና ቱርክ ሀገር ሄደው መማር ይፈልጋሉ?
90% ስኮላርሺኘ አግኝተው መማርስ?
#Sky_Education_Consultancy ይህን መልካም አጋጣሚ አመቻቸሎት!

Deadline: 22 Feb 2020

👉 Medicine & Health sciences
👉 Engineering
👉 Psychology
👉 Pharmacy
👉 Law
👉 Business Administration
👉 Computer science and IT
👉 Architecture
👉 Finance & banking.. and more

#Education_visa_Guaranteed
#Guaranteed_acceptance_letter

#ዛሬውኑ_ያናግሩን!! LIMITED SEATS
#Sky_Education_Consultancy
0977202020
ግራ አጋቢው ዘመን
አዲስ መፅሐፍ በገበያ ላይ

የወባ ትንኞችን ከመግደል ሀሳቦችን ወደ መግደል፤
ከስራ አጥነት ወደ ስራ አልባነት እያመራን ነው… ምን ይሻላል?

ግራ አጋቢው ዘመን መፅሐፍ መፍትሄ አለው፡፡

መፅሐፉ እንዴት ከጀግንነት ወደለየለት ብሔርተኝነት፣
ከኃይማኖተኝነት ደግሞ ወደ ሽብርተኝነት እያመራን እንዳለን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡ መጨረሻችንስ?

መልሱ ግራ አጋቢው ዘመን መፅሐፍ ውስጥ ይገኛል፡፡

እንኳን ወደ ግራ አጋቢው ዘመን መፅሐፍ ግራ ተጋብተው መጡ!!

የእውነት ይሄ መፅሐፍ አስተሳሰባችሁን ያሰፋዋል!!

በየመፅሀፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛል!!
ባይብል ኮድ

ስለ እያንዳንዳችን ዕጣ ፈንታ ጨምሮ በአለም ላይ ያሉ መሪዎች ስለሚገደሉበት ቦታ፣ ስለሚገድሏቸው ሰዎች ስም…

በአለም ላይ ስለተከናወኑ ነገሮችና ወደፊትም ስለሚከናወኑ ነገሮች ሁሉ በስም፣ በቀንና በቦታ ሳይቀር ከዛሬ ሶስት ሺ አመት በፊት…

በየቤታችን በሚገኘው መፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ በኮድ ተቀጧል!!

በአንድ ምሽት ሽያጭ ብቻ ሪከርድ የያዙት ባይብል ኮድ ቁጥር 1፣ ቁጥር 2 እና የመጨረሻው ቁጥር 3 ኮዶቹን እየፈቱ ያስደምሙናል፡፡

ሶስቱንም መጽሐፎች በየመፅሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ያገኟቸዋል፡፡
@teklutilahun
Forwarded from HEY Online Market
Samsung _M30s( 64GB )

Camera: 48Mp + 8Mp + 5Mp
Front : 16Mp
Ram:4GB Ram
Storage: 64GB
6000 mAh Battery (3days)

Price:9200

Contact us
0953964175
0925927457
0910695100
Forwarded from YeneTube
📌 Minoxidil የወንዶች ፀጉርና ፂም ማሳደግያ

📌 ፀጉሮት እየሳሳ አስቸግሮታል አልያም ፂም ማብቀል ይፈልጋሉ ? መፍትሔውን ይዘንሎት መተናል

ከቆዳችን ስር የሚገኘውን የፀጉር ጉጥ በማንቃት የሳሳን ፀጉር ወደ ቀድሞው የሚመልስ

📌📌 በ"FDA" እውቅናና ማረጋገጫ የተሰጠው ደግሞም በebay ፣ amazon እና በመሳሰሉት የ online መገበያያዎች ላይ "5" ★★★★★ ኮኮብ ያገኘ ነው

በቀን 2 ጊዜ ለሚጠቀሙ ሰዎች በ 1 ወር ውስጥ ውጤት የሚያሳይ

📞 0993944661
📞 0953928523
አቶ ፈንታ ደጀን የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒሰትር ዴኤታ ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተሹመዋል፡፡ አቶ ፈንታ በአማራ ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ በመሆን ሲያገለግሉ ቆይተዋል።

@YeneTube @Fikerassefa