YeneTube
116K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.92K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
በተለያየ መንገድ ወደ አገር ውስጥ ገብተው በሕገወጥ መንገድ በሚኖሩ የውጭ አገር ዜጎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ መሆኑን የኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ አስታወቀ።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙጅብ ጀማል በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ በተለያየ መንገድ ወደ አገር ውስጥ ገብተው ሕጋዊ ሳይሆኑ በሕገወጥ መንገድ በአገሪቱ የሚኖሩ የውጭ አገር ዜጎች ወደ ኤጀንሲው መጥተው ሕጋዊ መስመር የማይይዙ ከሆነ ለአገርና ለህዝብ ደህንነት ሲባል እርምጃ ይወሰዳል።እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ በተለያዩ ምክንያት በቪዛ ወደ አገር ውስጥ ከገቡ የውጭ አገር ዜጎች መካከል አንዳንዶቹ የቆይታ ጊዜያቸውን ያሳለፉ ሲሆን፤ አንድ የውጭ ዜጋ የቆይታ ጊዜው አልፎ ከሕግ ውጭ ከተቀመጠ ድርጊቱ በሕግ የሚያስቀጣ በመሆኑ በሕገወጥ መንገድ የሚኖሩ የውጭ አገር ዜጎችን ወደ ሕግ ሥርዓት ለማስገባት ከሰኔ 2011 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 15 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ ወደ ኤጀንሲው በመምጣት እንዲመዘገቡ በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ማስታወቂያ ሲያስተላልፍ ቆይቷል።

Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
በአጣዬና አካባቢው ግጭት ጋር ተያይዞ ክስ የተመሰረተባቸው 38 ግለሰቦች የክስ መቃወምያቸውን አቀረቡ

ከመጋቢት 24 እስከ 29 2011 ዓም በሰሜን ሸዋ ዞን እና በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኦሮምያ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ውስጥ በተለይም በከሚሴ ፣ በአጣዬ ፣ ማጀቴ ቆሬ ሜዳ እና አጎራባች ወረዳዎች በተነሳ ግጭት የበርካታ ሰዎች ህይወት ማለፉ እና ንብረት መውደሙ የሚታወስ ነው፡፡

ይህንን ተከትሎም ምርመራ ሲያደርግ የቆየው የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በ2011 ዓም ማገባደጃ ሀምሌ ወር ላይ ደሴ በሚገኘው የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍረድ ቤት በጉዳዩ ላይ ተሳትፎ አድርገዋል ያላቸውን 38 ግለሰቦች ከሷል፡፡

ሆኖም ተከሳሾች ጉዳያቸው በአዲስ አባ ማለትም በፌደራል ፍርድ ቤት እንዲታይላቸው ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት ክርክር ሲደረግበት ቆይቷል፡፡

ይህንን የመወሰን ስልጣን ያለው የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትም ጉዳያቸው በፌደራል ከፍተኛ ፍረድ ቤት እንዲታይ በወሰነው መሰረት አራቱ የክስ መዝገቦች በድጋሜ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ እና 20ኛ ወንጀል ችሎቶች ተከፍተው መተያት ጀምረዋል፡፡
አቃቤ ህግ በክሱ በድምሩ የ80 ሰው ህይወት ያለፈ ስለመሆኑ እና በርታ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ስለመኖራቸው አካቷል፡፡
በተጨማሪም 1 ቤተክርስቲያን የተቃጠለ መሆኑን እና ይህም ግምቱ ከ1.5 ሚሊዮን ብር በላይ መሆኑን ሌሎች የወደሙ የአካባቢው ንብረቶችም እንደነበሩ ጨምሮ ገልፅዋል።

በአራት መዝገብ ተከፋፍለው እና በተለያየ ቀጠሮ እየታዩ ያሉት ተከሳሾቹም በበኩላቸው በክሱ የተዘረዘረው የወንጀል ዝርዝር የተጠቀሱባቸውን የህግ ድንጋጌ የሚያሟሉ አይደሉም ሲሉ የመጀመርያ ደረጃ መቃወምያቸውን አቅርበዋል፡፡
በተጨማሪም የስነ ስርአት ህጉ በሚያዘው መሰረት የወንጀል ተሳትፎ ድረሻ ተሟልቶ አልቀረበም ሲሉ ተቃውመዋል፡፡

አቃቤ ህግ በመቃወምያዎቹ ላይ ምላሽ እንዲሰጥ ትእዛዝ የተሰጠ ሲሆን ችሎቶቹ ከየካቲት 24 ጀምሮ በመቃወምያ ክርክሩ ላይ በሚኖሩ ተከታታይ ቀጠሮዎች ብይን ለመስጠት ቀጥረዋል፡፡

Via:- Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
አንጋፋው አርቲስት ጀምበሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ!

በመድረክ ትወና ከ40 ዓመታት በላይ ያገለገሉት አንጋፋው አርቲስት ጀምበሬ በላይ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።አርቲስቱ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከ1949 እስከ 1953 ዓ.ም በቀድሞዉ የሀገር ፍቅር ማህበር በአሁኑ የሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት በመድረክ ትወና አገልግለዋል።እንዲሁም ከ1953 እስከ 1988 ዓ.ም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር በመድረክ ትወና ሲያገለግሉ ቆይተዋል።

አርቲስት ጀምበሬ ከተወኑባቸዉ ሥራዎች መካካል የአዛውንቶች ክበብ፣ ኦቴሎ፣ የከተማዉ ባላገር፣ ሐምሌት፣ የዋናው ተቆጣጣሪ፣ የእጮኛዉ ሚዜ፣ የልብ ፅጌሬዳ፣ 1 ዓመት ከ1 ቀን፣ የፌዝ ዶክተር፣ የእግር እሳት፣ የሚስጢር ዘብ እና የድል አጥቢያ ጥቂቶቹ ናቸው።
በተጨማሪም የዘመቻው ጥሪ፣ አመል አለብኝ፣ ግራ የገባው ግራ፣ ያልተከፈለው እዳ የተሰኙ የቴሌቪዥን ድራማዎች ላይ መተወናቸውን ኢዜአ ዘግቧል።አርቲስት ጀምበሬ በላይ በ1933 ዓ.ም በቀድሞው ጎጃም ክፍለ ሀገር የተወለዱ ሲሆን፣ የሁለት ሴት እና የአራት ወንድ ልጆች አባት ነበሩ።

Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከ8 ሺሕ በላይ አዲስ ተመራቂዎችን ሊቀጥር ነው!

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በከተማዋ በሚገኙ ከማእከላት እስከ ወረዳ ባሉ ክፍት የሥራ ቦታዎች 8 ሺሕ 100 አዳዲስ የዩኒቨርሲቲ ምሩቃንን በመቅጠር ሂደት ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ።በ2010 እና 2011 ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከ56 በላይ በሚሆኑ የትምህርት መስኮች የተመረቁ የአዲስ አበባ ወጣቶች እንዲወዳደሩ ጥሪ ቀርቦ፣ የበለጠ ብቁ የሆኑትን ለመለየት በተሰጠ ፈተና 8 ሺሕ 100 የተሻለ ውጤት ያላቸውን ተፈታኞች በመለየት የሥራ ቅጥር በመከናወን ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል።

Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
በጅማ ዞን ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ የሚደረገው የድጋፍ ሰልፍ ዛሬም የቀጠለ ሲሆን፣ በጅማ እና በአጋሮ ከተሞች በርካታ ህዝብ የተሳተፈባቸው የድጋፍ ሰልፎች በመደረግ ላይ ይገኛሉ።

@YeneTube @Fikerassefa
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የድጋፍ ሠልፍ እና የኦፌኮ ሕዝባዊ ስብሰባ መከልከል በጅማ

በትናንትናው (3/6/2012) ዕለት በጅማና አጋሮ ከተሞች 'ለብልጽግና እንሩጥ' በሚል መሪ ቃል በሺህዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ተሳትፈውበታል የተባለ የድጋፍ ሰልፍ ተደረገ።
የሠልፉ አላማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይን መደገፍ እንደሆነ ቢቢሲ ያነጋገራቸው ተሳታፊዎች ተናግረዋል።

https://telegra.ph/JJimma-02-13
ለተቃጠሉት የሞጣ መስጊዶች ግንባታ እና ንብረት ለወደመባቸው ዜጎች ማቋቋሚያ 209 ሚሊዮን ብር ተሰበሰበ!

ለተቃጠሉት የሞጣ መስጊዶች መልሶ ግንባታ እና ንብረት ለወደመባቸው ዜጎች ማቋቋሚያ የሚውል ከ209 ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዛሬ አስታውቋል።ከጥር 22 ቀን 2012 ጀምሮ በተካሄደው የድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ከተጠቀሰው ጥሬ ገንዘብ በተጨማሪ ከ700 ሺህ ብር በላይ በዓይነት መሰብሰቡንም ምክር ቤቱ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ጠቁሟል።ከህዝበ ሙስሊሙ ባለፈ ህዝበ ክርስቲያኑም በድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሩ መሳተፉን የገለፁት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ ለዚህም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በውጭ ሀገራት የተሰበሰበ ተጨማሪ ገንዘብ መኖሩን የጠቀሰው ምክር ቤቱ ይህም እስከ የካቲት 24 ቀን 2012 ድረስ ገቢ እንዲደረግም ምክር ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።በድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሩ 200 ሚሊዮን ብር ለማሰባሰብ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም ከእቅድ በላይ መሰብሰብ መቻሉም ተገልጿል።በዚሁ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሩ መጠናቀቁንም ምክር ቤቱ ጨምሮ አስታውቋል።

Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ወደ ተባበሩት አረብ ኢምሬቶች አቀኑ!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለሦስት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ወደ ተባበሩት አረብ ኢምሬቶች አቅንተዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተባበሩት አረብ ኢምሬቶች በሚኖራቸው ቆይታ ከመካከለኛው ምሥራቅ ከተውጣጡ 15 ሺህ ገደማ ኢትዮጵያውያን ጋር በአቡዳቢ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

ምንጭ:ETV
@YeneTube @FikerAssefa
የተወካዮች ምክር ቤት የኤክሳይዝ ታክስ ረቂቅ አዋጅን በአብላጫ ድምጽ አፀደቀ!

የተወካዮች ምክር ቤት፣ በአስቸኳይ ስብሰባውም የገቢ፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኤክሳይዝ ታክስ ረቂቅ አዋጅን በተመለከተ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ ተመልክቷል። ኤክሳይስ ታክስ ረቂቅ አዋጅ 1186/2012 በ4 ተቃውሞ እና በ7 ድምጸ ተአቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል።ቋሚ ኮሚቴው በስራ ላይ ያለው የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ለረጅም ጊዜ በስራ ላይ የቆየ በመሆኑ እና የማምረቻ ወጪን መሰረት አድርጎ የሚሰላ በመሆኑ ግልፅነት የሚጎድለው መሆኑን አንስቷል።

ይህን ለማስቀረትም አዲሱ አዋጅ በመሸጫ ዋጋ ላይ እንዲሰላ በማድረግ ለከፋይ እና አስከፋዩ ግልፅነት የሚፈጥር መሆኑን አመላክቷል።በሲጋራ ላይ የተጣለው የኤክሳይዝ ታክስ ምጣኔ በፓኬት በዋጋው 30 በመቶ እንዲሁም በፍሬ 5 ብር የነበረው በኤክሳይዝ ታክስ ማሻሻያው ተጨምሮ 8 ብር እንዲሆን መደረጉንም ተገልጿል።በረቂቅ አዋጁ የታሸገ ውሃ ላይ ተጥሎ የነበረው ኤክሳይዝ ታክስ ከ15 በመቶ ወደ 10 በመቶ ዝቅ እንዲል ተደርጓል።

ምንጭ:ኢቲቪ
@YeneTube @FikerAssefa
የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ሞገስ ታደሰ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ!

የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ተጫዋች የነበረው ሞገስ ታደሰ ባጋጠመው የጤና እክል ሕክምና ላይ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።ሞገስ ታደሰ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ከ'C' ቡድን ጀምሮ እስከ ዋናው ቡድን፣ ለሲዳማ ቡና፣ ለአዳማ ከተማ፣ ለኤሌክትሪክ እና ለወልድያ ክለቦች ተጫውቷል።በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከታዳጊ ጀምሮ እስከ ዋናው ቡድን ድረስ በመጫዋት ሀገራዊ ኃላፊነቱን ተወጥቷል።

ምንጭ፡- የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
@YeneTube @FikerAssefa
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጥላቻ ንግግርና የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የቀረበ አዋጅን በ23 ተቃውሞ፣ በሁለት ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ አፀደቀ።

@YeneTube @Fikerassefa
ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን ህጋዊ ሰውነት ለመስጠት የቀረበ ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ልዝርዝር ምርመራ ለህግ፣ ፍትህና ዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአንድ ተቃውሞ በአብላጫ ድምጽ መርቶታል።

Via HoPR
@YeneTube @FikerAssefa
#COVID-2019_update

የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር ከስድሳ ሺህ ያለፈ ሲሆን የሟቾች ቁጥር ደግሞ 1367 ደርሷል።

Via AFP
@YeneTube @FikerAssefa
የሕዳሴው ግድብ ድርድር አቅጣጫውን በመሳት ትኩረቱን የውሃ ድርሻ ክፍፍል ላይ ማድረጉን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል፡፡ ሱዳን አቋሟን ቀይራ እንደ አሜሪካ እና ዐለም ባንክ አጋርነቷን ለግብጽ እንዳደረገች ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጭ ተናግረዋል፡፡ ወደ አደራዳሪነት የተቀየሩት አሜሪካ እና ዐለም ባንክ ኢትዮጵያ ላይ ከፍተኛ ጫና እየፈጠሩ ነው፡፡

Via Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያን ከሱዳን የሚያገናኘው ዋና መንገድ ዛሬ ከቀትር በኋላ በመተማ ከተማ እና አካባቢዋ ነዋሪዎች ተዘግቶ ውሏል። መንገዱ የተዘጋው በትናንትናው ዕለት "የሱዳን ወታደሮች/ታጣቂዎች" በመቶዎች የሚቆጠሩ ከብቶችን ዘርፍ ወስደዋል ከተባለ በኋላ መሆኑን ሰምተናል።

@YeneTube @Fikerassefa
የጭልጋ ወረዳ ፍ/ቤት በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጭልጋ ወረዳ አይከል ከተማ መግቢያ አካባቢ የከባድ መኪና አሽከርካሪ እና ረዳት ላይ ዕገታ ፈጽመዋል የተባሉ ሁለት ግለሰቦች በ5 ዓመት ከ6 ወር እስራት እንዲቀጡ ወሰነ።

ምንጭ:Ethiopia Live Updates
@YeneTube @FikerAssefa
ሶማሊያ ለጋዜጠኞች እጅግ አደገኛ ሀገር ተባለች!

በሶማሊያ ሐሳብን የመግለጥ እና የፕሬስ ነጻነት ማነቆ መደረጉ ከዕለት ዕለት እየጠበቀ ነው ሲል የሰብአዊ መብቶች ተከራካሪው ዓለም አቀፉ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ስጋቱን ገለጠ። ፕሬዚደንት ሞሐመድ አብዱላሂ ፋርማጆ ሥልጣን ከያዙበት ካለፉት ሦስት ዓመታት አንስቶ ኹኔታው በሶማሊያ እጅግ መበላሸቱን ዓለም አቀፉ ድርጅት በዘገባው አትቷል።

በሶማሊያ የሚገኙ ጋዜጠኞች ከፍተኛ ጫና ይደረግባቸዋል፤ የቦንብ ጥቃት ሰለባ ይኾናሉ፣ ይደበደባሉ፣ ጥቃት እና እስር ይገጥማቸዋል ሲል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ዛሬ ተናግሯል። በሶማሊያ ኹኔታዎች ለጋዜጠኞች እጅግ አደገኛ መኾናቸው ተባብሷል ሲል ዓለም አቀፍ ድርጅቱ ስጋት እንዳደረበትም የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። ጋዜጠኞች ላይ ጥቃት የሚሰነዘረው በአልሸባብ ታጣቂዎች እንዲሁም በመንግሥት ወታደሮች መኾኑም ተገልጧል።

Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
የምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎችን አስጠነቀቀ

ከተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ውጭ የምርጫ ቅስቀሳ የሚያደርጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ አስጠነቀቀ።

የመገናኛ ብዙሃን የምርጫ ዘገባ ተደራሽነትና ሚና ላይ ቦርዱ ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር እየመከረ ነው።
በአሁኑ ወቅት ፓርቲዎች ህጉ ከሚፈቅደው ውጭ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ቅስቀሳ እያደረጉ መሆናቸውን በተመለከተ የውይይቱ ተሳታፊዎች ጥያቄ አንስተዋል።

የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ ቦርዱ በመጪዎቹ ጥቂት ቀናት ውስጥ የመጨረሻ የምርጫ ሰሌዳ በማውጣት እንደሚያሳውቅ ገልጸው፣ ከተጠቀሰው ጊዜ በኋላ ህግ የማስከበር ስራው ወደ ተግባር ይቀየራል ብለዋል፡፡

የምርጫ ሰሌዳው የመጨረሻ ቀን ከተቆረጠ በኋላ "እንደ እስከ ዛሬው ተቻችለን የምናልፈው ጉዳይ ሳይሆን እርምጃ የምንወሰድበት ነው" ሲሉም ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።

ምክክሩ በሚዲያና የመራጮች ትምህርት፣ የሚዲያ ሚና በመራጮች ትምህርት የውጭ ተሞክሮ፣ ምርጫ ቦርድና በመራጮች ትምህርት ዙሪያ ያለው ዝግጅት እንዲሁም የመገናኛ ብዙሃንና የጋዜጠኞች የምርጫ አዘጋገብ ስነ ምግባርና አሰራርን ለመደንገግ በወጣ መመሪያ ላይ እንሚያተኩር ተገልጿል።
ኢዜአ እንደዘገበው የምርጫ ቦርዱ ባወጣው ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት 'የምረጡኝ ዘመቻ' ጊዜ ከሚያዚያ 27 እስከነሐሴ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ነው።

ምንጭ፡-ዋልታ
@Yenetube @FikerAssefa
#Tepii University ላለፉት 2 ሳምንታት የመማር ማስተማር ክንውኑን አቋርጦ የቆየው የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ የካቲት 9/2012 ወደ መደበኛ ስራው እንደሚመለስ አስታወቀ።
@YeneTube @Fikerassefa
ቻይና የኮሮና ቫረስ ስርጭትን ከመቆጣጠር አንጻር ለውጥ እያሳየች አለመሆኑን የአለም ጤና ድርጅት አስታወቀ፡፡

ድርጅቱ እንዳለው የቫይረሱ ስርጭት በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ ያለው ከቻይና ውጪ ባሉ ሃገራት አይደለም፡፡ከፍተኛ ቁጥር የተመዘገበበት በጃፓን መርከብ ላይ ሲሆን 44 ጉዳዮች ተመዝግበዋል፤ይህም በቫይረሱ የተጠረጠሩትን ቁጥር ወደ 218 አሳድጎታል፡፡

የአለም ጤና ድርጅት መረጃ እንደሚያሳው በኮሮና ቫይረስ ሳቢያ የሚከሰት ሞትን መቀነስ ላይ ለውጥ የለም፡፡በሁቤይ ግዛት ብቻ እስከ ትናንት ድረስ 242 ሰዎች ሞተዋል፡፡በግዛቲቱ ከ14 ሺህ በላይ ሰዎች በወረርሽኙ መያዛቸውን ያስታወሱት በአለም የጤና ድርጅት ድንገተኛ የጤና ጉዳዮች ፕሮግራም ሃላፊ ማይክ ራዬን፤ ይህ የወረርሽኑ ስርጭት ላይ ተፈላጊ ለውጥ መምጣቱን አያመላክትም ብለዋል፡፡

ከቻይና ውጪ ሁለት ሞቶች የተመዘገቡ ሲሆን በ24 ሃገራት 447 በቫይረሱ መጠርጠራቸው ሪፖርት መደረጉንም ሃላፊው ተናግረዋል፡፡ጃፓን አንዲት የ80 አመት ዜጋዋ በቫይረሱ መሞታቸውን ትናንት አስታውቃለች፡፡አሜሪካ ደግሞ ወረርሽኑ በሰሜን ኮሪያ ሊዛመት ይችላል የሚል ስጋት እንዳላት ገልጻ፤ አለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶችና አሜሪካ እርዳታ እንዲያደርጉ እንደምታመቻች ማስታወሱን ቢቢሲን ጠቅሶ ኢትዮ ኤፍ ኤም ዘግቧል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa