የቲቦር ናዢ የኢትዮጵያ ጉብኝት
የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚንስትር ቲቦር ናዢ ኢትዮጵያን ጨምሮ 5 የአፍሪካ አገራትን ሊጎበኙ ነው፡፡
ረዳት ሚንስትሩ ከጥር 6 እስከ 20/2012 በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ሱዳን የሥራ ጉብኝት እንደሚያደርጉ ነው የተገለጸው፡፡
በሁለት ሳምንት ቆይታቸውም ከየአገራቱ ከፍተኛ አመራሮችና ዓለም ዐቀፍ የዋሽንግተን አጋር ተቋማት ኃላፊዎች ጋር ይመክራሉ ተብሏል፡፡
ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ማጠናከር፣ አካባቢያዊ ፀጥታን ማጎልበት፣ ሙስናን መዋጋት እና የንግድና የመዋዕለ ነዋይ ፍሰትን ማበረታታት የታቦር ናዢ ጉብኝት ዓላማ መሆናቸውን የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ገልጿል፡፡
ምንጭ:- አሀዱ ቴሌቪዥን
@YeneTube @Fikerassefa
የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚንስትር ቲቦር ናዢ ኢትዮጵያን ጨምሮ 5 የአፍሪካ አገራትን ሊጎበኙ ነው፡፡
ረዳት ሚንስትሩ ከጥር 6 እስከ 20/2012 በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ሱዳን የሥራ ጉብኝት እንደሚያደርጉ ነው የተገለጸው፡፡
በሁለት ሳምንት ቆይታቸውም ከየአገራቱ ከፍተኛ አመራሮችና ዓለም ዐቀፍ የዋሽንግተን አጋር ተቋማት ኃላፊዎች ጋር ይመክራሉ ተብሏል፡፡
ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ማጠናከር፣ አካባቢያዊ ፀጥታን ማጎልበት፣ ሙስናን መዋጋት እና የንግድና የመዋዕለ ነዋይ ፍሰትን ማበረታታት የታቦር ናዢ ጉብኝት ዓላማ መሆናቸውን የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ገልጿል፡፡
ምንጭ:- አሀዱ ቴሌቪዥን
@YeneTube @Fikerassefa
የትግራይ ቲቪ ጋዜጠኞች አሶሳ ላይ መታሰር እና የክልልሉ መልስ!
የትግራይ ቲቪ የአዲስ አበባ ቢሮ አስተባባሪ አቶ አክሊሉ ደባልቀው በስልክ ከነገረኝ:
"የትግራይ ቲቪ ጋዜጠኛ የሆነው ዳዊት ከበደ እና የካሜራ ባለሙያው በሀይሉ ውቤ ትናንት ምሽት በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ሶስት ሰአት ገደማ ታስረዋል። ከቅዳሜ ጀምሮ የተለያዩ ቀረፃዎችን ሲያካሂዱ ቆይተው ትናንት እስካሁን ምክንያቱ ምን እንደሆነ ባልታወቀ ምክንያት ታስረዋል። እዛ ሆነው የሰሩት እና በቲቪ የተላለፈ ፕሮግራም እንኳን አልነበረም።"
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቃል አቀባይ አቶ መለሰ በየነ የሰጠኝ መልስ:
"እኔ ለስራ ሌላ ቦታ ነኝ ነገር ግን ስልክ በመደወል ለመረዳት እንደቻልኩት ጋዜጠኞቹ የነበረንን አሰራር ተከትለው አልመጡም። ይህ ማለት ወደ ክልሉ ለዘገባ እንደሚመጡ ለክልሉ ኮሚኒኬሽን አላሳወቁም። ምን መስራት እንደሚፈልጉ ነግረውን፣ እኛም ባለሙያ እና አስፈላጊም ከሆነ የፀጥታ አካላት መድበን መሆን ነበረበት። ለምሳሌ እኔ እንደ ክልሉ ኮሚኒኬሽን ሀላፊ ስለመምጣታቸው የማውቀው ነገር የለም። ታሰሩ ሲባል እንደሌላው ሰው ነው የሰማሁት። አሁን ግን የታሰሩበት ምክንያት ምን እንደሆነ በትክክል አጣርተን እናሳውቃለን።"
ምንጭ:- ኤልያስ መሰረት
@YeneTube @Fikeeassefa
የትግራይ ቲቪ የአዲስ አበባ ቢሮ አስተባባሪ አቶ አክሊሉ ደባልቀው በስልክ ከነገረኝ:
"የትግራይ ቲቪ ጋዜጠኛ የሆነው ዳዊት ከበደ እና የካሜራ ባለሙያው በሀይሉ ውቤ ትናንት ምሽት በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ሶስት ሰአት ገደማ ታስረዋል። ከቅዳሜ ጀምሮ የተለያዩ ቀረፃዎችን ሲያካሂዱ ቆይተው ትናንት እስካሁን ምክንያቱ ምን እንደሆነ ባልታወቀ ምክንያት ታስረዋል። እዛ ሆነው የሰሩት እና በቲቪ የተላለፈ ፕሮግራም እንኳን አልነበረም።"
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቃል አቀባይ አቶ መለሰ በየነ የሰጠኝ መልስ:
"እኔ ለስራ ሌላ ቦታ ነኝ ነገር ግን ስልክ በመደወል ለመረዳት እንደቻልኩት ጋዜጠኞቹ የነበረንን አሰራር ተከትለው አልመጡም። ይህ ማለት ወደ ክልሉ ለዘገባ እንደሚመጡ ለክልሉ ኮሚኒኬሽን አላሳወቁም። ምን መስራት እንደሚፈልጉ ነግረውን፣ እኛም ባለሙያ እና አስፈላጊም ከሆነ የፀጥታ አካላት መድበን መሆን ነበረበት። ለምሳሌ እኔ እንደ ክልሉ ኮሚኒኬሽን ሀላፊ ስለመምጣታቸው የማውቀው ነገር የለም። ታሰሩ ሲባል እንደሌላው ሰው ነው የሰማሁት። አሁን ግን የታሰሩበት ምክንያት ምን እንደሆነ በትክክል አጣርተን እናሳውቃለን።"
ምንጭ:- ኤልያስ መሰረት
@YeneTube @Fikeeassefa
ግብፅ ከአሜሪካ ባደረገችው የተናጠል ውይይት ታላቁ የኅዳሴ ግድብ ውኃ የሚሞላበትና የሚተዳደርበት ሕግጋት እና አሰራር ምን መሆን እንዳለበት አገራቸው ማስረዳቷን የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አሕመድ ሐፌዝ ገልጸዋል።
Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ አዲሱ የመሬት ልኬታ/ካዳስተር/ በተካሄደባቸው አካባቢዎች የእርሻ መሬት ግብር ክፍያ የተቀየረና የተጨመረ ተደርጎ የሚነሳው ስህተት መሆኑን ገለፀ፡፡
የሰሜን ሸዋ ዞን ገጠር መሬት አጠቃቀምና አስተዳደር መምሪያና የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ በጋራ በመሆን የአርሶ አደሩ የገጠር መሬት ይዞታ አዲስ የመሬት ልኬት /ካዳስተር/ከተሰራ በኋላ የገጠር መሬት መጠቀሚያና የእርሻ ስራ ግብር ላይ ያለውን ሁኔታ በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ንጉሴ እንደገለፁት ፤የገጠር መሬት መጠቀሚያና የእርሻ ስራ ስራ ገቢ ግብር በክልሉ ምክር ቤት አዋጅ ህዳር 2001 ዓ.ም በጸደቀው መሰረት በአርሶ አደሩ መሬት ልክ እንዲከፍል ተደርጎ እየተሰራበት ቆይቷል፡፡
የአርሶ አደሮች የገጠር መሬት ይዞታ የግብር ክፍያ በምግብ ዋስትና የተያዙና ያልተያዙት በስተቀር ልዩነት እንደሌለው ገልጸው ፤በጥማድ 30 እና 40 ብር እንዲከፍሉ ሲደረግ ቆይቷል፤ አሁንም ይህ አሰራር እንደቀጠለ ያለና ያልተቀየረ ሲሆን ነገር ግን በአሁኑ ሰዓት በአንዳንድ አካባቢዎች ከግንዛቤ ማነስ ሊሆን በሚችል የአርሶ አደሩ የመሬት መጠቀሚያ ግብር የተቀየረና የተጨመረ ተደርጎ የሚነሳው ስህተትና ልዩነት አለመደረጉን ገልፀዋል፡፡
ምንጭ: የሰሜን ሸዋ ዞን ኮሚኒኬሽን መምሪያ
@YeneTube @FikerAssefa
የሰሜን ሸዋ ዞን ገጠር መሬት አጠቃቀምና አስተዳደር መምሪያና የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ በጋራ በመሆን የአርሶ አደሩ የገጠር መሬት ይዞታ አዲስ የመሬት ልኬት /ካዳስተር/ከተሰራ በኋላ የገጠር መሬት መጠቀሚያና የእርሻ ስራ ግብር ላይ ያለውን ሁኔታ በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ንጉሴ እንደገለፁት ፤የገጠር መሬት መጠቀሚያና የእርሻ ስራ ስራ ገቢ ግብር በክልሉ ምክር ቤት አዋጅ ህዳር 2001 ዓ.ም በጸደቀው መሰረት በአርሶ አደሩ መሬት ልክ እንዲከፍል ተደርጎ እየተሰራበት ቆይቷል፡፡
የአርሶ አደሮች የገጠር መሬት ይዞታ የግብር ክፍያ በምግብ ዋስትና የተያዙና ያልተያዙት በስተቀር ልዩነት እንደሌለው ገልጸው ፤በጥማድ 30 እና 40 ብር እንዲከፍሉ ሲደረግ ቆይቷል፤ አሁንም ይህ አሰራር እንደቀጠለ ያለና ያልተቀየረ ሲሆን ነገር ግን በአሁኑ ሰዓት በአንዳንድ አካባቢዎች ከግንዛቤ ማነስ ሊሆን በሚችል የአርሶ አደሩ የመሬት መጠቀሚያ ግብር የተቀየረና የተጨመረ ተደርጎ የሚነሳው ስህተትና ልዩነት አለመደረጉን ገልፀዋል፡፡
ምንጭ: የሰሜን ሸዋ ዞን ኮሚኒኬሽን መምሪያ
@YeneTube @FikerAssefa
የቤኒሻንጉል ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ‹‹ቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ›› የተሰኘ አዲስ ፓርቲ ለመመሥረት በዝግጅት ላይ የነበሩ 10 ግለሰቦች ላይ የእስር ማዘዣ በማውጣት ሰብሳቢውን ጨምሮ አራት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አዋለ። የፓርቲዉ ምክትል ሰብሳቢ ጌታሁን መርጋ፣ የሕግ ባለሙያ የሆኑት ጌታቸዉ ወድሻ፣ የድርጅት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ጉዮ ፈረደን (ዶ/ር) ሐሙስ ታኅሳስ 30/2012 መታሰራቸውን የቦሮ ፓርቲ የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ ዮሐንስ ተሰማ ተናግረዋል።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
"ጋዜጠኞቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ደብዳቤ ይዘው ስላልተገኙ ነው" የአሶሳ ፖሊስ
ዋና ኢንስፔክተር እስማኤል፤ ሁለቱ ጋዜጠኞች የፖለቲካ ፓርቲዎች ውይይትን ለመዘገብ ከኤጀንሲው አዲስ አበባ ቅርንጫፍ መላካቸውን እንደነገሯቸው ጠቅሰው፤ ጋዜጠኞቹ ወደ አሶሳ ሲመጡ ደብዳቤ ባለመያዛቸው እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ስለ ሁለቱ ጋዜጠኞች ወደ ክልሉ መምጣት የሚያውቀው ነገር ባለመኖሩ መታሰራቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ዋና ኢንስፔክተር እስማኤል፤ ሁለቱ ጋዜጠኞች የፖለቲካ ፓርቲዎች ውይይትን ለመዘገብ ከኤጀንሲው አዲስ አበባ ቅርንጫፍ መላካቸውን እንደነገሯቸው ጠቅሰው፤ ጋዜጠኞቹ ወደ አሶሳ ሲመጡ ደብዳቤ ባለመያዛቸው እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ስለ ሁለቱ ጋዜጠኞች ወደ ክልሉ መምጣት የሚያውቀው ነገር ባለመኖሩ መታሰራቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮ-ቴሌኮም ንብረት የሆኑ በርካታ የስልክ ገመዶችን ከነ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገፀ፡፡
በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ እንዳስታወቀው ጥር 15 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ መርካቶ ጋዝ ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ለበርካታ ኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች አገልግሎት የሚሰጡ እና ከመሬት ውስጥ ተቆፍረው የወጡ የስልክ ገመዶችን አከማችተው የተገኙ 2 ተጠርታሪዎች በፖሊስ አባላት ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
በተመሳሳይ በክ/ከተማው መርካቶ ኢትዮጵያ ዳቦ ቤት ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ አንድ ተጠርጣሪ በመሬት ውስጥ የተቀበሩ ንብረትነቱ የኢትዮ ቴሌኮም የሆኑ የስልክ ገመዶችን ቆፍሮ እያወጣና እየቆረጠ ሰርቆ ለመውሰድ ሲሞክር በፖሊስ አጋዥ ሃይሎች እጅ ከፈንጅ ሊያዝ መቻሉን የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ወንጀሉን ሲፈፅሙ የነበረው በሌሊቱ ክፍለ ጊዜ መሆኑን ያስታወሰው ፖሊስ መምሪያው በአሁኑ ወቅት ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡የመሰረተ ልማት አውታሮች የህብረተሰቡን የዕለት ተዕለት መረጃ ግንኙነት ያቀላሉ፡ ለሀገራች የኢኮኖሚ እድገት ከፍተኛ ሚና ያላቸው የህዝብ ሀብት ስለሆኑ ፖሊስ ወንጀሉን ለመከላከል የሚያደርገው ጥረት ህብረተሰቡ በነቃ ተሳትፎ እንዲያግዝ ኮሚሽኑ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
Via Addis Ababa Police Commission
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ እንዳስታወቀው ጥር 15 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ መርካቶ ጋዝ ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ለበርካታ ኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች አገልግሎት የሚሰጡ እና ከመሬት ውስጥ ተቆፍረው የወጡ የስልክ ገመዶችን አከማችተው የተገኙ 2 ተጠርታሪዎች በፖሊስ አባላት ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
በተመሳሳይ በክ/ከተማው መርካቶ ኢትዮጵያ ዳቦ ቤት ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ አንድ ተጠርጣሪ በመሬት ውስጥ የተቀበሩ ንብረትነቱ የኢትዮ ቴሌኮም የሆኑ የስልክ ገመዶችን ቆፍሮ እያወጣና እየቆረጠ ሰርቆ ለመውሰድ ሲሞክር በፖሊስ አጋዥ ሃይሎች እጅ ከፈንጅ ሊያዝ መቻሉን የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ወንጀሉን ሲፈፅሙ የነበረው በሌሊቱ ክፍለ ጊዜ መሆኑን ያስታወሰው ፖሊስ መምሪያው በአሁኑ ወቅት ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡የመሰረተ ልማት አውታሮች የህብረተሰቡን የዕለት ተዕለት መረጃ ግንኙነት ያቀላሉ፡ ለሀገራች የኢኮኖሚ እድገት ከፍተኛ ሚና ያላቸው የህዝብ ሀብት ስለሆኑ ፖሊስ ወንጀሉን ለመከላከል የሚያደርገው ጥረት ህብረተሰቡ በነቃ ተሳትፎ እንዲያግዝ ኮሚሽኑ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
Via Addis Ababa Police Commission
@YeneTube @FikerAssefa
ለፌዴራል መንግስት ከተመደበው 240,179,459,024 ብር ላይ ለሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ (ለሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር፣ ለተጠሪ ተቋማትና ለ45ቱ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት) 20.15% ድርሻ ይይዛል፡፡
Photo:የአጠቃላይ በጀቱ ክፍፍል
Via MoSHE
@YeneTube @FikerAssefa
Photo:የአጠቃላይ በጀቱ ክፍፍል
Via MoSHE
@YeneTube @FikerAssefa
ሰርግዎን በቅርቡ ለመሰረግ አስበዋል?
እንግድያውስ የዲኮሩን ስራ በእኛ ላይ ይጣሉት
💥LEAD DECOR
በባህላዊ እና ዘመናዊ መልኩ ዝግጅትዎን እናስውባለን::
➡️ለሠርግ
➡️ለመልስ
➡️ለልደት
➡️ለስብሰባ አዳራሽ
እንዲሁም
ለልዩ ልዩ ዝግጅቶች
0912672317, 0920315163 ደውለው ያነጋግሩን
ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት ቻናላችንን ይቀላቀሉ⬇️
https://tttttt.me/LeadDecor
እንግድያውስ የዲኮሩን ስራ በእኛ ላይ ይጣሉት
💥LEAD DECOR
በባህላዊ እና ዘመናዊ መልኩ ዝግጅትዎን እናስውባለን::
➡️ለሠርግ
➡️ለመልስ
➡️ለልደት
➡️ለስብሰባ አዳራሽ
እንዲሁም
ለልዩ ልዩ ዝግጅቶች
0912672317, 0920315163 ደውለው ያነጋግሩን
ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት ቻናላችንን ይቀላቀሉ⬇️
https://tttttt.me/LeadDecor
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የበረሃ አንበጣ የኢትዮጵያ ደቡባዊ አካባቢዎች ደርሷል
ለወራት ሰሜን ኢትዮጲያን ሲያስጨንቅ የከረመው የበረሃ አንበጣ አሁን ፊቱን ወደ ደቡብ አካባቢ ያዞረ ይመስላል። የደቡብ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዳንኤል ዳምጠዉ በክልሉ የአንበጣ መንጋ በስፋት መከሰቱን ለዶቼ ቨለ (DW) አረጋግጠዋል።
Via:- DW
@Yenetube @Fikerassefa
ለወራት ሰሜን ኢትዮጲያን ሲያስጨንቅ የከረመው የበረሃ አንበጣ አሁን ፊቱን ወደ ደቡብ አካባቢ ያዞረ ይመስላል። የደቡብ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዳንኤል ዳምጠዉ በክልሉ የአንበጣ መንጋ በስፋት መከሰቱን ለዶቼ ቨለ (DW) አረጋግጠዋል።
Via:- DW
@Yenetube @Fikerassefa
የትንባሆ ዋጋ አሁን ካለበት ዋጋ ሦስት ዕጥፍ ቢጨምር በትንባሆ ምክንያት የሚደርሰውን እና እየደረሰ ያለውን ጉዳት እስከ 40 በመቶ እንደሚቀንሰው የኢትዮጵያ ምግብ፣ መድኃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን አስታወቀ።
Via:- ኢትዮ ኤፍ ኤም /Addis Maleda
@YeneTube @Fikerassefa
Via:- ኢትዮ ኤፍ ኤም /Addis Maleda
@YeneTube @Fikerassefa
ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 2ሽሕ ኹለት መቶ 25 ግብር ከፋዮችን ኦዲት በማድረግ ሊሰወር የነበረ 7 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር ማስቀረት እንደተቻለ በገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ኦዲት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርሀኑ አበበ ተናገሩ።
Via:- አዲስ ማለዳ
@YeneTube @Fikerassefa
Via:- አዲስ ማለዳ
@YeneTube @Fikerassefa
የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዛሬ የበረከት ስምዖንን እና ታደሠ ካሳን 2 መከላከያ ምስክሮች መስማቱን የአማራ ብዙኻን መገናኛ ዘግቧል፡፡ በነገው ችሎት ሌሎች ምስክሮች ይቀርባሉ፡፡ ለምስክርነት የተጠሩት ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ደመቀ መኮንን፣ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ገዱ አንዳርጋቸው እና የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለ ማርያም መቼ እንደሚቀርቡ አልታወቀም፡፡
Via:- wazema
@YeneTube @Fikerassefa
Via:- wazema
@YeneTube @Fikerassefa
Forwarded from YeneTube
ሁሉንም ሰብስቦ በአንድ ላይ የያዘ የግብይት ድረገፅ
በድረ ገፁ ላይ ማንኛውም ግለሰብ ወይም ድርጅት አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታ በማሟላት ዕቃዎቹን ወይም አገልግሎቱን መሸጥ ይችላል።
ከ2700 በላይ ዕቃዎችና አገልግሎቶች
@SebsibieEthiopia
www.sebsibie.com
0953707070
በድረ ገፁ ላይ ማንኛውም ግለሰብ ወይም ድርጅት አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታ በማሟላት ዕቃዎቹን ወይም አገልግሎቱን መሸጥ ይችላል።
ከ2700 በላይ ዕቃዎችና አገልግሎቶች
@SebsibieEthiopia
www.sebsibie.com
0953707070
በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል የተፈጠረው ስምምነት በሰላም እጦት ለተቸገሩት እፎይታን የሰጠ ጉዳይ በመሆኑ ከዚህ በኋላ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ በኩል ክፍፍል ሊኖር አይገባም ሲሉ የቫቲካኑ ጳጳስ ፍራንሲስ ተናገሩ። ጳጳሱ በቫቲካን የሚገኘው የኢትዮጵያ ካቶሊክ ኮሌጅ 100ኛ ዓመት ምስረታ በዓል ላይ ተገኝተዋል።
Via:- ኢትዮ ኤፍ ኤም
@YeneTube @Fikerassefa
Via:- ኢትዮ ኤፍ ኤም
@YeneTube @Fikerassefa
ሐና ዩሐንስ የጋብቻ ቀለበት በድብቅ አደረገች።
የዘመን ድራማ ተዋንያኗ እና የእንተዋወቃለን የቴቪ ፕሮግራም አዘጋጇ ሐና ዩሃንስ ባሳለፍነው ሳምንት በድብቅ የጋብቻ ቀለበት እንዳረገች ኢትዮፒካሊን ዘግቧል። እንደ ኢትዮፒካሊክ ዘገባ ከሆነ በቀለበት ስነ-ስርዓቱ ላይ ከልጇ በስተቀር የተገኝ ሰው አልነበረም።
ሐና በዘጠነኛው ለዛ ሽልማት ላይ በተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማ ምርጥ የሴት ተዋናይት ተብላ መሸለሟ ይታወሳል።
Via:- AccessAddis
@YeneTube @Fikerassefa
የዘመን ድራማ ተዋንያኗ እና የእንተዋወቃለን የቴቪ ፕሮግራም አዘጋጇ ሐና ዩሃንስ ባሳለፍነው ሳምንት በድብቅ የጋብቻ ቀለበት እንዳረገች ኢትዮፒካሊን ዘግቧል። እንደ ኢትዮፒካሊክ ዘገባ ከሆነ በቀለበት ስነ-ስርዓቱ ላይ ከልጇ በስተቀር የተገኝ ሰው አልነበረም።
ሐና በዘጠነኛው ለዛ ሽልማት ላይ በተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማ ምርጥ የሴት ተዋናይት ተብላ መሸለሟ ይታወሳል።
Via:- AccessAddis
@YeneTube @Fikerassefa
በኢትዮጵያ ከትራፊክ አደጋ ጋር በተያያዘ በየቀኑ በአማካኝ 13 ሰዎች ህይወታቸው እንደሚያለልፍ የኢፌዲሪ ትራንስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
Via:- ኢቢሲ
@YeneTube @Fikerassefa
Via:- ኢቢሲ
@YeneTube @Fikerassefa
የድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ አስራ ሰባት የአስተዳደር ሠራተኞችን በግምገማ ከስራቸው አባረረ
የዩኒቨርስቲው የዓለም አቀፍ እና ሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደቻሳ ጋንፉሬ ለዶይቸ ቬለ (DW) በስልክ እንደገለፁት ዩኒቨርስቲው የመማር ማስተማር ሥራውን እንዳያከናውን ያጋጠመውን እክል ተከትሎ እያካሄደ ባለው የሠራተኞች ግምገማ ከዲስፕሊን ግድፈት ጋር በተያያዘ አስራ ሰባት የአስተዳደር ሠራተኞች ከሥራቸው እንዲባረሩ ወስኗል።
ኃላፊው እንዳሉት በአስተዳደር ሠተኞች ላይ በተካሄደው ግምገማ አንድ ሠራተኛ ከደረጃው ዝቅ ብሎ እንዲሠራ ተወስኗል። በዩኒቨርሲቲው ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት የተጀመረው ግምገማ ቀጥሎ የአካዳሚክ ክፍሉ ሠራተኞች በመገምገም ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
የድሬደዋ ዩኒቨርስቲ ከሁለት ሳምንት በላይ ያቋረጠውን መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ ለማስጀመር ቀደም ሲል በተማሪ ማደርያ ክፍሎች፤ በመመገቢያና ሌሎች አካባቢዎች ነበሩ ያላቸውን ችግሮችን ለመፍታት እና የተቋሙን አገልግሎት ምቹ የማድረግ ሥራ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑንም አቶ ደቻሳ አስረድተዋል።
ዩኒቨርስቲው በተቋረጠው ትምህርት ሳቢያ የባከኑ የትምህርት ጊዜያትን ለማካካስ የሚቻልበት ዕቅድ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን እና በቅርብ ቀናት የተቋረጠው ትምህርት ለማስጀመር እቅድ እንዳለው አስታውቀዋል።
በዩኒቨርሲቲው በትምህርት ዓመቱ በተማሪዎች በተነሱ ግጭቶች ሳቢያ ሁለት ተማሪዎች ሕይወት ማለፉና ሌሎች ተማሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱ የሚታወስ ነው። ምክንያቱ በውል አይገለፅ እንጂ ባሳለፍነው ሳምንት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት የነበሩት ዶ/ር ያሬድ ማሞ በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስቴር በተፃፈ ደብዳቤ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርጓል።
ምንጭ:- DW
@YeneTube @Fikerassefa
የዩኒቨርስቲው የዓለም አቀፍ እና ሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደቻሳ ጋንፉሬ ለዶይቸ ቬለ (DW) በስልክ እንደገለፁት ዩኒቨርስቲው የመማር ማስተማር ሥራውን እንዳያከናውን ያጋጠመውን እክል ተከትሎ እያካሄደ ባለው የሠራተኞች ግምገማ ከዲስፕሊን ግድፈት ጋር በተያያዘ አስራ ሰባት የአስተዳደር ሠራተኞች ከሥራቸው እንዲባረሩ ወስኗል።
ኃላፊው እንዳሉት በአስተዳደር ሠተኞች ላይ በተካሄደው ግምገማ አንድ ሠራተኛ ከደረጃው ዝቅ ብሎ እንዲሠራ ተወስኗል። በዩኒቨርሲቲው ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት የተጀመረው ግምገማ ቀጥሎ የአካዳሚክ ክፍሉ ሠራተኞች በመገምገም ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
የድሬደዋ ዩኒቨርስቲ ከሁለት ሳምንት በላይ ያቋረጠውን መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ ለማስጀመር ቀደም ሲል በተማሪ ማደርያ ክፍሎች፤ በመመገቢያና ሌሎች አካባቢዎች ነበሩ ያላቸውን ችግሮችን ለመፍታት እና የተቋሙን አገልግሎት ምቹ የማድረግ ሥራ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑንም አቶ ደቻሳ አስረድተዋል።
ዩኒቨርስቲው በተቋረጠው ትምህርት ሳቢያ የባከኑ የትምህርት ጊዜያትን ለማካካስ የሚቻልበት ዕቅድ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን እና በቅርብ ቀናት የተቋረጠው ትምህርት ለማስጀመር እቅድ እንዳለው አስታውቀዋል።
በዩኒቨርሲቲው በትምህርት ዓመቱ በተማሪዎች በተነሱ ግጭቶች ሳቢያ ሁለት ተማሪዎች ሕይወት ማለፉና ሌሎች ተማሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱ የሚታወስ ነው። ምክንያቱ በውል አይገለፅ እንጂ ባሳለፍነው ሳምንት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት የነበሩት ዶ/ር ያሬድ ማሞ በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስቴር በተፃፈ ደብዳቤ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርጓል።
ምንጭ:- DW
@YeneTube @Fikerassefa