YeneTube
117K subscribers
31.5K photos
485 videos
79 files
3.9K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
💥ማስታወቂያ💥
School of American English

📌ቻይንኛ
📌ፈረንሳይኛ
📌ጀርመንኛ
📌ጣልያንኛ
📌አፋን ኦሮሞ
📌አረብኛ

አንቱታን ባተፈሩ መምህራን እናስተምራለን

አድራሻዎቻችን ⬇️
ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ +251919913021
ፒያሳ ፒያሳ ገበያ ማዕከል +251919913023
22 ጎላጎል ህንፃ 6ተኛ ፎቅ +251919913022


💥💥💥10% Discount 💥💥💥💥

ቅናሹን ለመጠቀም
ይህንን ፓስት screenshot አድርገው መያዝና ስመጡ ማሣየት ይኖርብዎታል

T.me/SCHOOLOFAMERICAN
ዋልታ አራት የተቋሙን ሰራተኞች ከስራ አገደ!!

በድርጅታችን ዋልታ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽ ኮርፖሬት የፌስቡክ ገፅ waltainfo.com በ03/04/12 ዓ.ም ከትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካዔል ጋር በተያያዘ ከተቋማችን እውቅና ውጪ ሀሰተኛ መረጃ መለቀቁ ይታወሳል፡፡

ይህንን ተከትሎም ተቋማችን ወዲያውኑ ለተፈጠረው ክስተት ይቅርታ መጠየቁ እና ጉዳዩን አጣርቶ እንደሚገልፅ አስታውቆ ነበር፡፡

በዚህም መሰረት ተቋማችን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ሲሰራ ቆይቷል፡፡

በመሆኑም ሁኔታውን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲና ፖሊስ እየመረመሩት ይገኛል፡፡

የምርመራ ውጤቱን መጨረሻ እንደምንገልፅ የተጠበቀ ሆኖ ተቋማችን ከጉዳዩ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አላቸው ብሎ በጠረጠራቸው አራት የተቋሙ ሰራተኞች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል፡፡

ዛሬ የዋልታ የስራ አመራር ቦርድና ማኔጅመንት አባላት ክስተቱ ከተፈጠረበት ዕለት ጀምሮ የተደረገውን ማጣራት መነሻ በማድረግ ውይይት ካካሄዱ በኋላ ሰራተኞቹ ላልተወሰነ ጊዜ ከስራ እንዲታገዱ ወስነዋል፡፡

በቀጣይም ከአስተዳደራዊ እርምጃ ባለፈ የፍትህ አካላት ድርጊቱን በፈፀሙት አካላት ላይ አጣርቶ በሀገሪቱ ህግ መሰረት የሚወስዱትን እርምጃ ተከታትለን ይፋ የምናደርግ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ድርጅታችን በሀገሪቱ የሚዲያ ኢንዱስትሪ ውስጥ እየፈጠረ ያለውን በጎ ተፅዕኖ በእውነትኛ መረጃ እና የህዝብን ድምፅ ባከበረ መልኩ አጠናክሮ እንደሚቀጥል እናረጋግጣለን!!

Via ዋልታ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ኮርፖሬት
@YeneTube @FikerAssefa
ደም ሳይቃቡ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል - ጠ/ሚ ዐቢይ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው ዕለት በሚሊኒየም አዳራሽ በተካሄደው የአማራ እና የኦሮሞ ባለሃብቶች ኮሚቴ በተዘጋጀው የሰላም ኮንፈረስ ላይ ንግግር አድርገዋል።
በዚህ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደዚህ አይነት መድረኮች እንዲዘጋጁ ድጋፍ ላደረጉ ምሁራን፣ አባ ገዳዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ባለሀብቶች ምስጋና አቅርበዋል።እንዲሁም በሀገሪቱ የሰላም አየር እንዲመጣ እና ሰዎች ሀሳባቸውን በነፃነት ማንሸራሸር እንዲችሉ ድጋፍ ያበረከቱ ቄሮዎችና ፋኖዎችን አመስግነዋል።

የአማራ እና የኦሮሞ ህዝቦች በርካታ ቁጥር ያላቸው ህዝቦች መሆናቸውን የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ በጋራ ሲሆኑና ሲተባበሩ ለውጥ ማምጣት እንደሚችሉ እና በተቃራኒው ሲለያዩ የሚለውጡት ነገር እንደማይኖር ገልፀዋል።ሁለቱ ብሄሮች በሃገሪቱ በርካታ ቁጥር ያላቸው ህዝቦች መሆናቸውን ጠቅሰው፥ መዋደድ፣ መከባበር እና መፋቀር እንደሚገባቸውም አውስተዋል።
በቀጣይነት ሁለቱም ህዝቦች በሁሉም አቅጣጫ ከሚገኙ የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች ጋር በጋራ በመሆን የተለያዩ ውይይቶችን እንደሚያዘጋጁ ተስፋ አደርጋለሁ ብለዋል።

በኢትዮጵያ ያለው ልዩነት ፀጋ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሻለና የተለያየ ነገር ያስፈልጋልም ብለዋል በንግግራቸው።
አብሮ ለመኖርም የአብሮ መኖር ጥቅምን መገንዘብ፣ የሌሎችን እሴት ማወቅ እና ሳይጠፋፉ አብሮ መኖር እንዴት ይቻላል የሚለውን መመለስ ያስፈልጋል ሲሉም ገልፀዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብሮ ሲኖር የሃሳብ ግጭት አይኖርም ማለት ሳይሆን በዚህ የሀሳብ ልዩነት መገዳደልና መጠፋፋት አያስፈልግም ማለት መሆኑንም አስረድተዋል።ወጣቶች የታገሉት፣ የደሙት እና የደከሙት ተጨማሪ ወጣት እንዳይሞት እንጅ ሊማር የሄደ በወጣበት እንዲቀር ባለመሆኑ የአማራና የኦሮሞ ወጣቶች ተቀራርበው መስራት እንደሚገባቸው አስታውሰዋል።

ዩኒርሲቲዎችን በተመለከተም ባስተላለፉት መልዕክት ዩኒቨርሲቲ የሚኬደው ለመገዳደል ሳይሆን ለመማር መሆኑን ጠቅሰው፥ እነዚህን ወጣቶች ለግጭት የሚጠቀሙ አካላት እንደማይጠፉ አንስተዋል።በአሁኑ ወቅት በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ጠንካራ ጥበቃ የማደራጀት ስራ መከናወኑን እና በጥፋተኞች ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድም ጠቅሰዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለዴሞክራሲያ ሽግግር ባደረጉት ንግግር ሰላም እንዲሰፍንና ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት ደም መቀባባት እንደማያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል።ወጣቶችም አሁን ካሉበት ቦታ በላይ እንዲያስቡ መልዕክት አስተላልፈዋል።

Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁከት የተጠረጠሩ 16 ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ማስታወቁን ኢትዮ ኤፍኤም ዘግቧል፡፡ በጥቅምቱ የኦሮሚያ ክልል ግድያ ወንጀሎች ከሚፈለጉት 337 ተጠርጣሪዎች ደሞ 250ዎቹ ተይዘዋል፡፡ ይህ የተገለጸው የዐቃቤ ሕግ ሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ ዝናቡ ቱኑ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ነው፡፡

Via Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
በደቡብ ከልል ዎላይታ ሶዶ ከተማ ሁከትና ረብሻ ይነሳል በሚል ሥጋት የከተማይቱ የወትሮ እንቅስቃሴ ዛሬ ተስተጎጉሎ ዋለ።

የከተማይቱ ነዋሪዎችና ባለስልጣናት እንዳረጋገጡት ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ የመንግስት አገልግሎት መስጪያ ተቋማት፣ የንግድ መደብሮችና መዝናኛ ተቋማት ተዘግተዉ ነዉ የዋሉት።የትራንስፖርት አገልግሎትም የለም።ፀጥታ አስከባሪዎች በዞኑ የሚንቀሳቀሱ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችን፣ የዎላይታ ዞን በክልል እንዲደራጅ የሚጠይቁ የፖለቲካ አቀንቃኞችና ተባባሪዎቻቸዉ ያሏቸዉን ሰዎች ማሰራቸዉም ተነግሯል።የእስረኞቹ ማንነት፣ ቁጥርና የታሰሩበት ስፍራ ግን በዉል አልተገለጠም።ዞኑን የሚቆጣጠረዉ ወታደራዊ ዕዝ ወይም ኮማንድ ፖስት በበኩሉ የዎላይታ ሶዶ ከተማን ጨምሮ በዞኑ በሚገኙ ወረዳዎች የተቃውሞ ሰልፎች እንዳይደረጉ፣ የሞተር ብስክሌቶች ጉዞዎችንና እንቀስቃሴዎችንም አግዷል።ሁከት ይነሳል በሚል ሥጋት እንቅስቃሴዎች ከመገደባቸዉ ባለፍ እስከ ዛሬ አመሻሽ ድረስ የአደባባይ ተቃዉሞ፣ ሁከትም ሆነ ግጭት የለም።

Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
በቀን 10/04/2012ዓ.ም በባ/ዳር ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ብዛቱ 1,702 የሆነ ህገ ወጥ ጥይት በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡

በባ/ዳር ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ምድረ ገነት ጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያ ሠራተኞች እና የፊደራል ፖሊስ አባላት በቅንጅት በጥናት ተለይቶ በነበረ ቀንደኛ ኮንትሮባንዴስት ቤት በደረሰ የህብረተሰብ ጥቆማ መሠረት በተደረገ ብርበራ /ኦፕሬሽን/በቀን 10/04/2012 ዓ.ም ብዛቱ 1288 የክላሽ ጥይት እና 414 የብሬን ጥይት በድምሩ 1702 ህገ ወጥ ጥይት በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ከጉዳዪ ጋር በተያያዘ 02 ተጠርጣሪ ተይዘው ጉዳያቸው በህግ አግባብ እየታየ ይገኛል።

Via Ministry of Revenue
@YeneTube @FikerAssefa
IMF ለኢትዮጵያ የ2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ዶላር ብድርና ድጋፍ አጸደቀ!

የአለም አቀፉ የፋይናንስ ተቋም (IMF) ስራ አስፈጻሚ ቦርድ በሶስት አመታት ተግባራዊ የሚሆን የብድርና የእርዳታ የሚውል 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ዶላር ይፋ አድርጓል።ይህም በቅርቡ በመንግስት ይፋ ለተደረገው ‘’የአገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ’’ ማስፈጸሚያ እንደሚውል ይጠበቃል።ድጋፉ ተግባራዊ ከሚሆንባቸው ዘርፎች ዋና ዋናዎቹ

1ኛ) የውጭ ምንዛሬ እጥረት ጫናን ማቃለል

2) በገቢና ወጭ ምርቶች ያለውን አለመጣጠን መቀነስ

3) የብድር ጫናን ለመቋቋም/ተጋላጭነትን ማስቀረት

4) የአገር ውስጥ የሃብት ምንጮችን የማሰባሰብ አቅምን ማጎልበት ይገኙበታል።

ድጋፉ በጥቅሉ ሲታይ በኢኮኖሚው ውስጥ ቀጣይነት ላለው እድገት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ ለማበረታታትና ለማሳደግ፣ ስራ አጥነትን ለመቀነስ፣ በዝቅተኛ የገቢ ምንጭ ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን ማዕከል ያደረገ የልማት ትልምን የመተግበሪያ ማዕቀፍ ተድርጎ ሊወሰድ ይችላል።

ምንጭ: በዋሽንግተን የኢትዮጵያ ኤምባሲ
@YeneTube @FikerAssefa
‹‹ሕዝቡ የሚፈልገውን መርጦ በሚፈልገው ፓርቲ ይመራ ዘንድ ምርጫው በሠላማዊ ሁኔታ እንዲካሄድ ነው ምንፈልገው፡፡›› የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር ተመስገን ጥሩነህ

የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር ተመስገን ጥሩነህ ከአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት ጋር ባደረጉት ቆይታ መጭው ሀገራዊ ምርጫ በሠላም እንዲካሄድ ለማድረግ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ለሠላም እየተሠራ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡ሕዝቡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የሚፈልገውን መርጦ በሚፈለገው ፓርቲ ይተዳደር ዘንድ የክልሉ መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን ነው ያስታወቁት ርዕሰ መስተዳድሩ፡፡የክልሉ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊና ሰብዓዊ መብቶች እንዲጠበቁ ሠላም አስፈላጊ መሆኑንም ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

‹‹አሁን ባለው የክልሉ ነባራዊ ሁኔታ አንፃራዊ ሠላም ሰፍኗል›› ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ከዚህ በፊት መረጋጋት ባልነበረባቸው አካባቢዎች ከሚገኙ የማኅበረሰብ ክፍሎች ጋርም በሠላም አስፈላጊነት ዙሪያ ተደጋጋሚ ውይቶች ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡ ይህን ተከትሎም በክልሉ ለማልማት ፍላጎት ያላቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ባለሀብቶች ፍላጎት እያሳዩ እንደሆነ አመላክተዋል፡፡በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጭልጋ ወረዳ ከቅማንትና አማራ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር በተደረገው ውይይት አበረታች ውጤቶች መታየቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ ከቅማንት ኮሚቴ ጋር በተደረሰው ስምምነት መሠረትም የአካባቢውን እንቅስቃሴ ሠላማዊ ማድረግ እንደተቻለ አቶ ተመስገን ጥሩነህ ጠቁመዋል፡፡

አሁን ባለው የክልሉ ነባራዊ ሁኔታ አንጻራዊ ሠላም እንደታየና ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ በየትኛውም የክልሉ አካባቢ ያለምንም ችግር መድረክ ፈጥሮ አባላቱን ማወያየት የሚችል መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ይህን ጉዳይ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ራሳቸው ምስክርነት እየሰጡበት እንደሆነም ገልጸዋል፡፡ ‹‹ከሁከትና አለመረጋጋት የሚገኝ ነገር የለም፤ ምርጫው በሠላማዊ ሁኔታ እንዲካሄድ ነው ምንፈልገው፤ በምርጫም ሆነ በሌሎች ነገሮች አሳብቦ ወደ ግጭት የምናመራ ከሆነ የነበርንበትን ችግር ማስቀጠል ነው›› ሲሉም የተጀመረው ሠላም እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የክልሉ ኢንቨስትመንት እድገት እንዲያንሠራራ፣ የሥራ እድል ፈጠራ እንዲስፋፋ የክልሉ ሕዝብ አሁን ያለውን አንጻራዊ ሠላም መጠበቅ እንደሚገባው ርዕሰ መስተዳድሩ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
በምሥራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ አካባቢ ትናንት ማምሻውን የፀጥታ መደፍረስ አጋጥሞ ነበር፤ ብሏል የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት። አሁን ላይ ሁኔታዎች ወደ መረጋጋት እየተመለሡ ነውም ብሏል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
አገልጋይ ዮናታን አክሊሉ በመልካም ወጣት ፕሮጀክት ስም የከተማ አስተዳደሩ ለጀመረው የተማሪዎች የምገባ ፕሮግራም የ10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡

አገልጋይ ዮናታን አክሊሉ የከተማ አስተዳደሩ ለጀመረው የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብር በመልካም ወጣት ፕሮጀክት ስም የአስር ሚሊዮን ብር ድጋፍ ኢ/ር ታከለ ኡማ እና የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ በተገኙበት አስረክቧል፡፡የመልካም ወጣት ፕሮጀክት የከተማ አስተዳደሩ የጀመረውን የህጻናት ምገባ በመደገፍ ለሚቀጥሉት አምስት አመታት በጠቅላላው የ 50 ሚሊዮን ብር ድጋፍ እንደሚያደርግም አገልጋይ ዮናታን አክሊሉ ተናግሯል፡፡

ኢ/ር ታከለ ኡማ በበኩላቸው አገልጋይ ዮናታን አክሊሉ ለተማሪዎች የምገባ ፕሮግራም ላደረገው ድጋፍም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ የተማሪዎች የምገባ ፕሮግራም ህግ እና ተቋማዊ ይዘት እንዲኖረው እና በዘላቂነት እንዲተገበር መወሰኑና የተማሪዎች የምገባ ኤጀንሲ መቋቋሙም ይታወሳል፡፡

Via Mayor Office
@YeneTube @FikerAssefa
በምሥራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ከተማ አስተዳደር ትናንት አመሻሽ የበሃይማኖት ተቋማት ላይ የእሳት ቃጠሎ አደጋ ደርሷል፡፡ የፀጥታ አካላትና ሕዝቡ ባደረጉት ጥረት እሳቱ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ሥር እንደዋለም ታውቋል፡፡
ከዞኑ ፖሊስ መምሪያ ያኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው አሁን ሁኔታዎች እየተረጋጉ ነው፤ ተጠርጣሪዎችንና የችግሩን መንስኤዎች የመለዬት ሥራም እየተከናወነ ነው፡፡ የጉዳት መጠኑ በውል አለመታወቁም ተመላክቷል፡፡

ምንጭ: አብመድ
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸህ ሰኢድ አሕመድ በሞጣ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ አራት መስጂዶች መቃጠላቸዉንና የሙስሊም ሱቆችና ድርጅቶች ላይ ዝርፊያ መፈጸሙን ገልጸዋል።

Via Ethiopia Live Updates
@YeneTube @FikerAssefa
ሞጣ ከተማ አስተዳደር በቤተ እምነት ተቋማት ላይ የደረሰው የቃጠሎ አደጋ በተመለከተ የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን መግለጫ ሰጥቷል፡፡

ትናንት ታኀሣሥ 10 ቀን 2012 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡20 አካባቢ በሞጣ ከተማ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የእሳት ቃጠሎ መከሰቱን ተከትሎ በሌሎችም የሃይማኖት ተቋማት ላይ የእሳት ቃጠሎ መፈጸሙን ከዞኑ ፖሊስ መምሪያ ያገኙትን መረጃ ጠቅሰው የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ማኅበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል መምሪያ ኃላፊ ጀማል መኮንን ተናግረዋል፡፡በቡድን በመሰባሰብ መስጂዶች ላይ ጥቃት እንደተፈፀመ ነው ኮማንደር ጀማል የተናገሩት፡፡በድርጊቱ በሞጣ ከተማ አስተዳደር ቀበሌ 03 የሚገኝ መስጂድ ሙሉ በሙሉ ሲቃጠል፣ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን እና ቀበሌ 05 እና 06 የሚገኙ መስጂዶች ደግሞ በከፊል እንደተቃጠሉና አንድ የገበያ ማዕከል በቃጠሎና በመሰባበር ጉዳት እንደደረሰበት ኮማንደር ጀማል መኮንን ለአማራ ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡

በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት ሪፖርት እንዳልተደረገም አመላክተዋል፡፡ ፖሊስ ችግሩን በማስቆም የማረጋጋት ሥራ እየሠራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በቀጣይ ተጠርጣሪዎችን አፈላልጎ በመያዝ እርምጃ እንደሚወሰድም አስታውቀዋል፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች ሃይማኖትንና ማንነትን መሠረት አድረገው የሚነሱ ችግሮችን ኅብረተሰቡ ከማባባስ ይልቅ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በመተባበር የማርገብና የማረጋጋት ልምድ ሊዳብር እንደሚገባ ኮማንደር ጀማል መኮንን መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
"በብልጽግና ጎዳና ላይ በምትገኘው ኢትዮጵያ የሀገራችንን የቆየ የሃይማኖቶችን የመቻቻልና አብሮ የመኖር ባህል የሚፃረሩ ጽንፈኛ አካሄዶች ቦታ የላቸውም:: እንዲህ ያሉ የፈሪ አካሄዶችን አጥብቄ አወግዛለሁ:: መላው ሰላም ወዳድ ኢትዮጵያውያንም የመከባበርና አብሮ የመኖር ጥልቅ ዕውቀታችሁን እንድታጋሩ ጥሪዬን አቀርባለሁ:: ከፋፋይ አጀንዳዎችን መረዳትና መጠየፍ የጋራ ዕድገታችንን ለማረጋገጥ ያስችላል::"

-ጠ/ሚ አብይ አህመድ
@YeneTube @FikerAssefa
140.2 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የጎሬ-ማሻ-ቴፒ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ!

በመንገዱ ጅማሮ መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የክልሉ እና የፌደራል የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል። የጎሬ-ማሻ-ቴፒ ፕሮጀክት የደቡብ ፣ የጋምቤላ እና የኦሮሚያ ክልሎችን በአቋራጭ የሚያገናኝ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱን በ4.5 ቢሊዮን ብር ለመገንባት ጨረታዉን አሸንፎ ወደ ስራ የገባዉ የደቡብ ኮሪያው ሃዮንዳይ ዴቨሎፕመንት ካምፓኒ ነው።

የፕሮጀክቱን የማማከርና የቁጥጥር ስራ ደግሞ ሱሶንግ ኢንጂነሪንግ ከሃገር በቀሉ ኔት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ጋር በጋራ ያከናውናሉ፡፡ የግንባታዉ ሙሉ ወጪ የሚሸፈነዉም በኢትዮጵያ መንግስት እና በኮሪያው ኤግዚም ባንክ ነው፡፡ የመንገዱ መገንባት ከአዲስ አበባ ተነስቶ በጅማ አድርጎ በመቱ ወደ ጋምቤላ የሚዘልቀው ዋና መንገድ እና ከአዲስ አበባ ተነስቶ በጅማ በኩል ወደ ሚዛን ቴፒ የሚሄደውን ሌላ ዋና መንገድ በአቋራጭ የሚያስተሳስር ነው።

የመንገዱ ስራ በአራት ዓመት ከስድስት ወራት ዉስጥ ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ መርሃ ግብር ተይዞለታል ። የመንገዱ የጎን ስፋት ትከሻን ጨምሮ በገጠር 10 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር ፣ በወረዳ 19 ሜትር እና በዞን ከተማ 21.5 ሜትር ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት የመንገድ ዘርፉ የግብርና ፣ የማዕድን ፣ የባህልና ቱሪዝም ፣ ንግድና ኢንዱስትሪ ፣ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፣ የብሄራዊ ሎጂስቲክስ እና ሌሎች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዘርፎችን በሚደግፍ መልኩ እንዲተገበር ለማስቻል የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም ይህ መንገድ እነዚህን ዘርፎች በሚደግፍ መልኩ ታስቦ የሚገነባ ነው፡፡

ምንጭ:ERA
@YeneTube @FikerAssefa
የእምነት ተቋማት ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ለማውገዝ ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው

የትራንስፖርት ሚኒስቴር ወ/ሪት ዳግማዊት ሞገስ

ሃይማኖትንና ብሔርን መሰረት ያደረጉ ግጭቶች ወደማያባሩ ቀውስ ውስጥ ሊከቱ እንደሚችሉ ይታወቃል። በመሆኑም በቤተክርስቲያን፣ በመስጅድ እና በተለያዩ የእምነት ተቋማት ላይ የሚደርሰውን የተቀነባበረ ሴራ በመገንዘብ ችግሩን በሰከነ መንፈስ ማክሸፍ ይገባል። አረመኔያዊ ድርጊት በመፈጸም የሚሳተፉ አካላትን ለይቶ ለህግ ማቅረብ ለነገ የማይተው ጉዳይ ነው።
@Yenetube @Fikerassefa
በሞጣ ከተማ በሀይማኖት ተቋማት ላይ የደረሰውን ጥቃት የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ(አብን) በጽኑ ያወግዛል!!

በምስራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ከተማ ትላንት አርብ ታህሳስ 10 ቀን 2012 ዓ/ም ከምሽቱ 1 ሰዓት አካባቢ በጥንታዊና ታሪካዊው ሞጣ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ላይ ለጊዜው ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ የእሳት ቃጠሎ የተነሳ ሲሆን፣ በቤተ ክርስቲያኑ ላይ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ በከተማው ነዋሪ ርብርብ እሳቱ በቁጥጥር ስር ውሏል። ይህንን ተከትሎ የተወሰኑ ወጣቶች በመስጊዶችና አንድ የንግድ ቤት ላይ የእሳት ቃጠሎ እንዲደርስ አድርገዋል። ሱቆችን የመዝረፍ ሙከራም ተካሂዷል።

አብን በሞጣ ከተማ በሁለቱም የእምነት ተቋማትና በንብረት ላይ የተፈፀመውን ጥቃት በጥብቅ ያወግዛል። ድርጊቱም በምንም አይነት መንገድ ጠንካራ ትስስር ያለውን የሞጣና አካባቢው ህዝበ ክርስቲያንና ህዝበ ሙስሊም የሚገልጽ ሳይሆን ጥቂት በስሜት የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች ድርጊት እንደሚሆን ይረዳል።

የአማራ ሕዝብ ለሺህ ዓመታት የተለያዩ ሀይማኖቶች ተከባብረው፣ ሙስሊሙ አብያተ ክርስቲያን፣ ክርስቲያኑ መስጊዶች ሲገነቡ አብሮ እየገነባ፣ በሰላም የሚኖሩበት ህዝብ ሲሆን፣ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአማራ "ክልል" በተለይ በእስልምና እምነት ተቋማት ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች መጨመራቸው አሳሳቢ ነው። የእምነት ተቋማት ላይ የሚደረግ ጥቃት የአማራን ሕዝብ እሴት የማይወክል፣ ፍፁም ህገወጥና በአስቸኳይ ሊታረም የሚገባ ተግባር ነው ብሎ ንቅናቄያችን ያምናል።

የክልሉ መንግስት በህዝባችን የእምነት፣ የትምህርትና የንግድ ተቋማት ላይ የሚደርሱ ተደጋጋሚ ጥቃቶችንም ሆነ የህዝባችን ሰላም ለማደፍረስ የሚንቀሳቀሱ ሰርጎ ገቦችን መቆጣጠር አለመቻሉ በጣም አሳዛኝና አስቸኳይ መፍትሄ የሚያሻው ነው።

መንግስት በዚህ ድርጊት የተሳተፉ አካላትን በአስቸኳይ ለህግ እንዲያቀርብ እየጠየቅን፣ የዕምነት ተቋማቱም የእነዚህን ጥቃቶች ቀስቃሾችና ተሳታፊዎችን በቀላሉ በመለየት ለህግ ማቅረብ እንዲቻል የተሻለ የደህንነት መጠበቂያ አሰራሮችን እንዲተገብሩ፣ በዘመናዊ የሲሲቲቪ ካሜራዎች ጭምር የታገዘ ጥበቃ እንዲኖራቸው አብን በዚህ አጋጣሚ ያሳስባል።

የሞጣና አካባቢው ወጣቶችም እንደትላንቱ አይነት ችግር ሲያጋጥም በስሜት ተነሳስቶ የራሳችንንና የወገኖቻችን ሀብትና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ በፍፁም ተቀባይነት የሌለውና አውዳሚ ተግባር መሆኑን መገንዘብ አለብን።

የከተማው ወጣቶችና ህዝቡም በቃጠሎው የተጎዱ ተቋማትን አስቸኳይ ርብርብ በማድረግ መልሶ እንዲገነባቸው ጥሪ እያቀረብን፤ መላው ሕዝባችንም በዚህ ዙሪያ የተለመደ ርብርቡን እንዲያደርግ ጥሪ እናቀርባለን።

አንድ አማራ ለሁሉም አማራ፣ ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ!
ታኅሳስ 11/2012ዓ.ም
@Yenetube @Fikerassefa
የ200 ሺ ሰዎች የሃብት ዝርዝር መዝገቢያለሁ ይላል - ፀረ ሙስና ኮሚሽን

- የማንኛውም ባለሥልጣን የሃብት ብዛትን ለማወቅ ምን ያስፈልጋል?

- በአካል መቅረብ፣ ‹‹ምክንያታዊ ሆኖ መጠየቅ››

ከፌዴራል እስከ ክልል፣ ከፕሬዚዳንትና ከጠቅላይ ሚኒስትር እስከ ታች ሃላፊዎች ድረስ፣ የምክር ቤት አባላትንና የመንግሥት ሰራተኞችን… በአጠቃላይ የ200 ሺህ ሰዎችን የሃብት አይነትና ብዛት የሚዘረዝር የመረጃ መጋዘን - የብዙ መቶ ሚሊዮን መረጃዎች ጥንቅር ነው፡፡ ስም፣ ዕድሜ፣ የቤተሰብ ሁኔታና አድራሻ የመሳሰሉት ነገሮችን ጨምሮ የንብረት አይነትና ብዛትን ያካትታል፡፡ የተመዘገቡ መረጃዎችን አጠናቅሮ በቅጡ እንዳሰናዳ የገለፀው የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን፣ የባለሥልጣናትን የሀብት መረጃ ለሕዝብ ከፍቻለሁ ብሏል፡፡

አላንዳች ምክንያት የሰዎችን ሀብትና የጓዳ ንብረት ለማወቅ እንኳን በተከፈተ በር በጭላንጭል አጮልቆ የማየት ሱስን ለማርካት የተዘጋጀ መረጃ አይደለም፡፡ ይልቅስ፣ ሰዎች በጥረታቸው ንብረት እንዲያፈሩ እንጅ፣ ስልጣንን ለስርቆትና ለጉቦ እንዳይጠቀሙ ለመከላከል ያግዛል ተብሎ የተዘጋጀ መረጃ ነው፡፡

የሆኖ ሆኖ፣ የባለሥልጣናትና የበታች ሃላፊዎችን የሃብት መጠን ለማወቅ የፈለገ ሰው ምን ማሟላት አለበት? ምንም ቅድመ ሁኔታ እንደ ሌለ ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡

ዜጎች ወደ ኮሚሽኑ በአካል በመቅረብ፣ ‹‹ምክንያታዊ ሆኖ በመጠየቅ፣ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ›› የባለሥልጣናትን ሃብት መመልከት እንደሚቻል የኮሚሽኑ የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ዳይሬክተር አቶ መስፍን በላይ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡
ወደፊት፣ ለሁሉም ሕዝብ፣ በያለበት ተደራሽ ለማድረግ፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ የመረጃ ጥንቅር እየተከናወነና እየተሰናዳ ነው ብለዋል - ዳይሬክተሩ፡፡

በኮሚሽኑ የተሰበሰበውና የተሰናዳው መረጃ፤ ሦስት የመንግሥት አካላትን ይመለከታል፡፡ 1ኛ፣ የሕዝብ ተመራጮች (የፌዴራል ፓርላማ፣ የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ተመራጮች)፣ 2ኛ፣ የፌዴራልና የክልል የመንግስት ተሿሚዎች፣ 3ኛ ደግሞ፣ ውሳኔ የማሳለፍ ስልጣን ያላቸው የመንግስት ተቀጣሪዎች፣ አማካሪዎችና ሠራተኞች ላይ ያተኮረ ነው የኮሚሽኑ መረጃ፡፡

በዚህ መሠረት፣ ከ2 መቶ ሺህ በላይ ባለሥልጣናት፣ የምክር ቤት አባላትና የመንግስት ሰራተኞችም ሀብት ተመዝግቦ በኮሚሽኑ የመረጃ ቋት ውስጥ እንደሚገኝ አቶ መስፍን አስታውቀዋል፡፡

Via:- Addis Admas
@Yenetube @Fikerassefa
በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ከተማ በአራት መስጊዶች ላይ ጥቃት መፈጸሙን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስታወቀ።

ምክር ቤቱ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ ሁለቱ መስጊዶች በቃጠሎ ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን እና ሌሎች ሁለቱ ላይ ደግሞ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታውቋል።

ምክር ቤቱ «እየተመረጠ እና እየተፈለገ የሙስሊሙ ሕዝብ ንብረት የሆኑ ሆቴሎች፤ መኖሪያ ቤቶች እና መደብሮች ዘረፋ፤ ውድመት እና ቃጠሎ» ደርሶባቸዋል ብሏል።

የደረሰው ጥቃት መነሻ በከተማዋ በሚገኝ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን ላይ የደረሰ ቃጠሎ ሳይሆን እንደማይቀር አንድ የሞጣ ነዋሪ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። ከቤተ እምነቶቹ ባሻገር አንድ የመገበያያ አዳራሽ ጭምር መቃጠሉን የዐይን ይማኙ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሞጣ እና በአካባቢው ተጨማሪ ጥቃት ሊፈጸም እንደሚችል ሥጋቱን ገልጾ «መንግሥት ለዜጎች ጥበቃ የማድረግ ኃላፊነቱን እንዲወጣ» ጠይቋል።

Via:- DW
@Yenetube @Fikerassefa
ዛሬ ማታ ግዮን ሆቴል ሊካሄድ የነበረው የነአብዱ ኪያር የሚሳተፉበት" የካልቸር ዊክ" የሙዚቃ ኮንሰርት ባልታወቀ ምክንያት ተሰርዟል።

Via:- Tesfay Getenet
@Yenetube @Fikerassefa