20 ዓመታት ያስቆጠረው የጥቁር አባይ ቆዳ ፋብሪካ ተዘጋ።
ባለፉት 20 ዓመታት የቆዳ ምርቶችን በማምረት ወደ ውጭ በመላክ የሚታወቀው እና በደብረብርሃን ከተማ ከቀዳሚዎቹ ፋብሪካዎች ውስጥ የሚጠቀሰው የጥቁር አባይ ቆዳ ፋብሪካ የአካባቢ ብክለት በማስከተሉ መዘጋቱ ተገለፀ፡፡የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ደስታ አንዳርጌ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል እንደገለፁት፣ ከሁለት አሥርት ዓመታት በላይ ያቋረጠው ፋብሪካ በአካባቢ ብክለት ምክንያት ከነዋሪዎች በተነሳ ተደጋጋሚ ቅሬታ እንዲዘጋ መደረጉን አረጋግጠዋል፡፡ፋብሪካው ቀደም ሲል ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል የፈጠረና በአመሰራረቱም ከቀዳሚዎቹ ውስጥ የሚጠቀስ ነበር፡፡ ይሁንና ከከተማው መስፋት ጋር ፋብሪካው ያለበት ስፍራ ዋና የመኖሪያ ማዕከል ሆኗል፡፡
ምንጭ: ኢፕድ
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፉት 20 ዓመታት የቆዳ ምርቶችን በማምረት ወደ ውጭ በመላክ የሚታወቀው እና በደብረብርሃን ከተማ ከቀዳሚዎቹ ፋብሪካዎች ውስጥ የሚጠቀሰው የጥቁር አባይ ቆዳ ፋብሪካ የአካባቢ ብክለት በማስከተሉ መዘጋቱ ተገለፀ፡፡የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ደስታ አንዳርጌ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል እንደገለፁት፣ ከሁለት አሥርት ዓመታት በላይ ያቋረጠው ፋብሪካ በአካባቢ ብክለት ምክንያት ከነዋሪዎች በተነሳ ተደጋጋሚ ቅሬታ እንዲዘጋ መደረጉን አረጋግጠዋል፡፡ፋብሪካው ቀደም ሲል ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል የፈጠረና በአመሰራረቱም ከቀዳሚዎቹ ውስጥ የሚጠቀስ ነበር፡፡ ይሁንና ከከተማው መስፋት ጋር ፋብሪካው ያለበት ስፍራ ዋና የመኖሪያ ማዕከል ሆኗል፡፡
ምንጭ: ኢፕድ
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያዊው አትሌት በዶፒንግ ምርመራ እገዳ ተጣለበት!
አሶሺዬትድ ፕሬስ ከሞናኮ እንደዘገበው - በመላው አፍሪካ ውድድሮች በ10,000 ሜትር አሸናፊ የነበረው እና ከሁለት ሳምንት በፊት ኬንያዊው አትሌት ጄፍሪ ካዎሮንሮ የግማሽ ማራቶን የዓለምን ሪከርድ በሰበረበት ውድድር በሶስተኛ ያጠናቀቀው እንዲሁም በIAAF የረጅም ርቀት አትሌቶችየደረጃ ሰንጠረዥ በ5ኛነት የሚገኘው ብርሃኑ ፀጋ አሁን እገዳ ተጥሎበታል።የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የፀረ-አበረታች ክፍል እናዳስታወቀው በEPO የታገደ እና የተከለከለ የጡንቻ እድገትን የሚጨምር ሆርሞን የዶፕተንት ምርመራ ውጤቱ ላይ በመገኘቱ አትሌት ብርሃኑ ፀጋ ከአለም አቀፍ ውድድሮች መታገዱን ዘገባው ያመለክታል።
Via Ethio Kickoff
@YeneTube @FikerAssefa
አሶሺዬትድ ፕሬስ ከሞናኮ እንደዘገበው - በመላው አፍሪካ ውድድሮች በ10,000 ሜትር አሸናፊ የነበረው እና ከሁለት ሳምንት በፊት ኬንያዊው አትሌት ጄፍሪ ካዎሮንሮ የግማሽ ማራቶን የዓለምን ሪከርድ በሰበረበት ውድድር በሶስተኛ ያጠናቀቀው እንዲሁም በIAAF የረጅም ርቀት አትሌቶችየደረጃ ሰንጠረዥ በ5ኛነት የሚገኘው ብርሃኑ ፀጋ አሁን እገዳ ተጥሎበታል።የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የፀረ-አበረታች ክፍል እናዳስታወቀው በEPO የታገደ እና የተከለከለ የጡንቻ እድገትን የሚጨምር ሆርሞን የዶፕተንት ምርመራ ውጤቱ ላይ በመገኘቱ አትሌት ብርሃኑ ፀጋ ከአለም አቀፍ ውድድሮች መታገዱን ዘገባው ያመለክታል።
Via Ethio Kickoff
@YeneTube @FikerAssefa
13 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ 200 የባቡር ፉርጎዎች እስካሁን ወደ አገር ውስጥ አልገቡም
በቻይና ሀገር የተመረቱና 13 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ ሁለት መቶ የባቡር ፉርጎዎች እስካሁን ድረስ ወደ አገር ውስጥ እንዳልገቡ የኢትዮ ጂቡቲ የባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር አስታወቀ።የአክሲዮን ማህበሩ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ጥላሁን ሰርካ ሰሞኑን ከአዲስ ዘመን ጋር በነበራቸው ቆይታ የባቡር ፉርጎዎቹን ከቻይናውያኑ ለመግዛት ሲታሰብ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማምጣት ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንደነበር ገልፀዋል።ከዚሁ የባቡር ግዢ ውስጥ ከ30 አስከ 35 በመቶ የሚሆነውን በአገር ውስጥ በማምረት ለመሸፈን በመንግሥት በኩል አቅጣጫ መያዙንም ጠቅሰዋል።
ምንጭ: አዲስ ማለዳ/ኢፕድ
@YeneTube @FikerAssefa
በቻይና ሀገር የተመረቱና 13 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ ሁለት መቶ የባቡር ፉርጎዎች እስካሁን ድረስ ወደ አገር ውስጥ እንዳልገቡ የኢትዮ ጂቡቲ የባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር አስታወቀ።የአክሲዮን ማህበሩ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ጥላሁን ሰርካ ሰሞኑን ከአዲስ ዘመን ጋር በነበራቸው ቆይታ የባቡር ፉርጎዎቹን ከቻይናውያኑ ለመግዛት ሲታሰብ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማምጣት ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንደነበር ገልፀዋል።ከዚሁ የባቡር ግዢ ውስጥ ከ30 አስከ 35 በመቶ የሚሆነውን በአገር ውስጥ በማምረት ለመሸፈን በመንግሥት በኩል አቅጣጫ መያዙንም ጠቅሰዋል።
ምንጭ: አዲስ ማለዳ/ኢፕድ
@YeneTube @FikerAssefa
የደቡብ ክልል ምክር ቤት ጉባኤ የ148 ዳኞችን ሹመት በማጽደቅ ተጠናቀቀ!
ከጥቅምት 4 እስከ 7/2012 ዓ.ም ድረስ ሲካሄድ የቆየው የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ምክር ቤት ጉባኤ የ148 ዳኞችን ሹመትና የአንድ ዳኛ ስንብት በማድረግ ተጠናቋል፡፡የዳኞችን ሹመት ለምክር ቤቱ ያቀረቡት የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት አቶ ሙሉጌታ አጎ ናቸው፡፡የፍርድ ቤቱ ፕሬዘዳንት ባቀረበት መሰረት አንድ የወረዳ ዳኞ በፈፀሙት የስነ ምግባር ግድፈትና ወንጀል የዳኞች ጉባኤ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት የዳኛውን ስንብት ከመረመረ በኋላ ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ተቀብሎ አጽድቋል፡፡
ከዳኞች ሹመት ውስጥ የሴቶች ቁጥር አነስተኛ መሆኑን የምክር ቤቱ አባላት ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት ጥያቄ የቀረበላቸው ሲሆን የሴቶች ቁጥር ሊያንስ የቻለበት ዋንኛ ምክንያት ሴቶች በህግ ትምህርት ያላቸው ተሳትፎ ማነሱ መሆኑን አንስተው ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር የሴቶች የህግ ትምህርት ተሳትፎ እንዲጨምሩ መስራት ተገቢ እንደሆነ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት አቶ ሙሉጌታ ገልጸዋል፡፡ምክር ቤት የ148 ዕጩ ዳኞችን ሹመት በሙሉ ድምጽ ካፀደቀ በኋላ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ ደምሴ ዶልቻ ዕጩ ዳኞችን ቃለ መሀላ በማስገባት የምክር ቤቱ ጉባኤ ተቋጭቷል፡፡
Via SRTA
@YeneTube @FikerAssefa
ከጥቅምት 4 እስከ 7/2012 ዓ.ም ድረስ ሲካሄድ የቆየው የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ምክር ቤት ጉባኤ የ148 ዳኞችን ሹመትና የአንድ ዳኛ ስንብት በማድረግ ተጠናቋል፡፡የዳኞችን ሹመት ለምክር ቤቱ ያቀረቡት የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት አቶ ሙሉጌታ አጎ ናቸው፡፡የፍርድ ቤቱ ፕሬዘዳንት ባቀረበት መሰረት አንድ የወረዳ ዳኞ በፈፀሙት የስነ ምግባር ግድፈትና ወንጀል የዳኞች ጉባኤ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት የዳኛውን ስንብት ከመረመረ በኋላ ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ተቀብሎ አጽድቋል፡፡
ከዳኞች ሹመት ውስጥ የሴቶች ቁጥር አነስተኛ መሆኑን የምክር ቤቱ አባላት ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት ጥያቄ የቀረበላቸው ሲሆን የሴቶች ቁጥር ሊያንስ የቻለበት ዋንኛ ምክንያት ሴቶች በህግ ትምህርት ያላቸው ተሳትፎ ማነሱ መሆኑን አንስተው ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር የሴቶች የህግ ትምህርት ተሳትፎ እንዲጨምሩ መስራት ተገቢ እንደሆነ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት አቶ ሙሉጌታ ገልጸዋል፡፡ምክር ቤት የ148 ዕጩ ዳኞችን ሹመት በሙሉ ድምጽ ካፀደቀ በኋላ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ ደምሴ ዶልቻ ዕጩ ዳኞችን ቃለ መሀላ በማስገባት የምክር ቤቱ ጉባኤ ተቋጭቷል፡፡
Via SRTA
@YeneTube @FikerAssefa
የዓዲ ግራት ዩኒቨርስቲ አዲስ ገቢ ተማሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል።ሰሞኑን የዩኒቨርስቲው አመራር ከዓዲ ግራት ህዝብ ጋር አዲስ ገቢ ተማሪዎችን በደመቀ መልኩ መቀበል የሚያስችል ውይይት እና ቅድመ ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸውን ድምፂ ወያኔ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
መደመር፣ የዶክተር አብይ መጽሃፍ ዛሬ አዲስ አበባን ጨምሮ በ20 ከተሞች በምረቃ ላይ ነው፡፡በሶስት ቋንቋዎች (በአማርኛ፣ ኦሮምኛና እንግሊዝኛ) የተጻፈው መጽሃፍ በቀጣይ በውጭ ሃገራት ይመረቃል፡፡የመደመር እሳቤ የሃገራችን ቀጣይ የለውጥ ጉዞ ላይ መሻገሪያ እሳቤ ሆኖ ሃገራዊ አንድነትን፣ የዜጎች ክብርን እና ብልጽግናን የማሳት ግብ አለው ተብሏል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር በአዲስ አበባ ውይይት እያካሄደ ነው፡፡
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) በኢትዮጵያ የመጣውን ለውጥና በትግራይ ሕዝብ ላይ ያለውን የወደፊት አንድምታ እንዲሁም በለውጡ የራሱን ሚና አስመልክቶ በአዲስ አበባ ውይይት እያደረገ ነው፡፡በውይይቱ ትዴት ዓላማና ፕሮግራሙን አስመልክቶ ግንዛቤ እያስጨበጠም ነው፡፡ በአዲስ አበባ ሀገር ፍቅር ቲያትር አዳራሽ የትዴት አባላት፣ ደጋፊዎች፣ የተፎካካሪ ፓርቲዎችና የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት ውይይት ነው እየተካሄደ የሚገኘው፡፡
‹‹ካልተሰባሰበ ትልቅ ሀገር ይልቅ የተሰባሰበች ትንሽ ሀገር ቁም ነገር ትሠራለች›› ያሉት የትዴት ሊቀ መንበር አረጋዊ በርሄ (ዶክተር) አንድነት በኢትዮጵያ እንዲጠነክር በየቦታዉ የሚነሱ ጥያቄዎችን በትብብር መፍታት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡ ‹‹የትህነግ አመራር የትግራይ ሕዝብን የመልካም አስተዳደር ችግር እና ፍትሕና ዴሞክራሲ ሳያስከብር ፓርቲዉንና ሕዝቡን ‹አንድ ነው› ብሎ መናገሩ ተገቢ አይደለም፡፡ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሆኑትም ጥቂት ግለሰቦች ናቸው፤ ሕዝቡ ላይ የሚፈጥረውን ውዝግብ ማቆም አለበት፤ ይህንንም ለመታገል ትዴት የፖለቲካ ምኅዳሩ እንዲሰፋ ይሠራል›› ብለዋል ዶክተር አረጋዊ በንግግራቸው፡፡
ምንጭ: አብመድ
@YeneTube @FikerAssefa
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) በኢትዮጵያ የመጣውን ለውጥና በትግራይ ሕዝብ ላይ ያለውን የወደፊት አንድምታ እንዲሁም በለውጡ የራሱን ሚና አስመልክቶ በአዲስ አበባ ውይይት እያደረገ ነው፡፡በውይይቱ ትዴት ዓላማና ፕሮግራሙን አስመልክቶ ግንዛቤ እያስጨበጠም ነው፡፡ በአዲስ አበባ ሀገር ፍቅር ቲያትር አዳራሽ የትዴት አባላት፣ ደጋፊዎች፣ የተፎካካሪ ፓርቲዎችና የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት ውይይት ነው እየተካሄደ የሚገኘው፡፡
‹‹ካልተሰባሰበ ትልቅ ሀገር ይልቅ የተሰባሰበች ትንሽ ሀገር ቁም ነገር ትሠራለች›› ያሉት የትዴት ሊቀ መንበር አረጋዊ በርሄ (ዶክተር) አንድነት በኢትዮጵያ እንዲጠነክር በየቦታዉ የሚነሱ ጥያቄዎችን በትብብር መፍታት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡ ‹‹የትህነግ አመራር የትግራይ ሕዝብን የመልካም አስተዳደር ችግር እና ፍትሕና ዴሞክራሲ ሳያስከብር ፓርቲዉንና ሕዝቡን ‹አንድ ነው› ብሎ መናገሩ ተገቢ አይደለም፡፡ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሆኑትም ጥቂት ግለሰቦች ናቸው፤ ሕዝቡ ላይ የሚፈጥረውን ውዝግብ ማቆም አለበት፤ ይህንንም ለመታገል ትዴት የፖለቲካ ምኅዳሩ እንዲሰፋ ይሠራል›› ብለዋል ዶክተር አረጋዊ በንግግራቸው፡፡
ምንጭ: አብመድ
@YeneTube @FikerAssefa
''መደመር'' መፅሀፍ ተመረቀ!
በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተፃፈው መደመር መፅሀፍ በሚሊኒየም አዳራሽ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አርቲስቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል።በምረቃ ስነስርዐቱ ላይ የጥበብ ባለሙያዎች ከመፅሀፉ ምዕራፎች ጥቂቱን ያነበቡ ሲሆን የመፅሀፍ ዳሰሳም ቀርቧል።የእለቱ የክብር እንግዶች ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ፣ ቀዳማይ እመቤት ዝናሽ ታያቸው፣ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ እና የአዲስ አበባ ከተማ ም/ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ የተዘጋጀውን ኬክ ከቆረሱ በኋላ መፅሀፉን ለተተኪ ተማሪዎች በስጦታነት አበርክተዋል።
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተፃፈው መደመር መፅሀፍ በሚሊኒየም አዳራሽ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አርቲስቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል።በምረቃ ስነስርዐቱ ላይ የጥበብ ባለሙያዎች ከመፅሀፉ ምዕራፎች ጥቂቱን ያነበቡ ሲሆን የመፅሀፍ ዳሰሳም ቀርቧል።የእለቱ የክብር እንግዶች ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ፣ ቀዳማይ እመቤት ዝናሽ ታያቸው፣ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ እና የአዲስ አበባ ከተማ ም/ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ የተዘጋጀውን ኬክ ከቆረሱ በኋላ መፅሀፉን ለተተኪ ተማሪዎች በስጦታነት አበርክተዋል።
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
#Shot_Fired !
📌 ''ውስኪ ጠጭ ኢህአዴጎች ውሀ የሚጠጣ ህዝብ እንዳለ አትርሱ''
📌 ''በአምስት ሺህ ብር ደመወዝ ሆቴል እየተቀለባችሁ (ምንጩን ፈጣሪ ይወቀው) ዳቦ የራበውን ህዝብ ላንተ ቆሜልሀለሁ ማለት ዘበት ነው።''
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኢህአዴግን ውህደት አስመልክተው እየወጡ ያሉ የተሳሳቱ መግለጫዎችን መሠረት አድርገው ዛሬ በሚሊኒየም አዳራሽ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
📌 ''ውስኪ ጠጭ ኢህአዴጎች ውሀ የሚጠጣ ህዝብ እንዳለ አትርሱ''
📌 ''በአምስት ሺህ ብር ደመወዝ ሆቴል እየተቀለባችሁ (ምንጩን ፈጣሪ ይወቀው) ዳቦ የራበውን ህዝብ ላንተ ቆሜልሀለሁ ማለት ዘበት ነው።''
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኢህአዴግን ውህደት አስመልክተው እየወጡ ያሉ የተሳሳቱ መግለጫዎችን መሠረት አድርገው ዛሬ በሚሊኒየም አዳራሽ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
አምስተኛው የማስ ስፖርት መርሃ-ግብር እሁድ ይካሄዳል፡፡
የአበባ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ40ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ32ኛ ጊዜ “ቱሪዝም ለሥራ እድል ፈጠራና ለተሻለ ህይወት” በሚል መሪ ቃል በከተማ ደረጃ እየተከበረ ያለውን የአለም ቱሪዝም ቀን ምክንያት በማድረግ ከአዲስ አበባ ስፖርት ኮምሽን ጋር በጋራ በመሆን ከ100ሺ ሰው በላይ ተሳታፊ የሚሆንበት አምስተኛው ከተማ አቀፍ የማስ ስፖርት መርሃ-ግብር እሁድ (ጥቅምት 9 ቀን 2012 ዓ.ም) ከማለዳው 12:30 ጀምሮ በመስቀል አደባባይ ይካሄዳል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የአበባ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ40ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ32ኛ ጊዜ “ቱሪዝም ለሥራ እድል ፈጠራና ለተሻለ ህይወት” በሚል መሪ ቃል በከተማ ደረጃ እየተከበረ ያለውን የአለም ቱሪዝም ቀን ምክንያት በማድረግ ከአዲስ አበባ ስፖርት ኮምሽን ጋር በጋራ በመሆን ከ100ሺ ሰው በላይ ተሳታፊ የሚሆንበት አምስተኛው ከተማ አቀፍ የማስ ስፖርት መርሃ-ግብር እሁድ (ጥቅምት 9 ቀን 2012 ዓ.ም) ከማለዳው 12:30 ጀምሮ በመስቀል አደባባይ ይካሄዳል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ዛሬ በመቀሌ ሊካሄድ የነበረ ሠላማዊ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ!
'ህድሪ ሰብ' በተባለ ማህበር ዛሬ ቅዳሜ መቀሌ ከተማ ውስጥ ሊካሄድ ተጠርቶ የነበረው ሠላማዊ ሰልፍ ህጋዊ አይደለም ተብሎ በፖሊስ ተበተነ።ይህ ሠላማዊ ሰልፍ የተጠራው የትግራይ ክልል የከፍተኛ የትምህርት ተቋም ተማሪዎች ችግር ያጋጥማቸዋል ወደተባሉ ቦታዎች እንዲሄዱ እንዳይደረግ በክልሉ መንግሥት ላይ ግፊት ለማድረግ እንደነበረ ተነግሯል።ሠላማዊ ሰልፉን የጠራው ማህበር ሊቀ መንበር መሃሪ ዮሐንስ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ስለሰልፉ ለማሳወቅ ለመቀሌ ከተማ ከንቲባ ጸሐፊ ደብዳቤ ማስገባታቸውንና ግልባጩንም ለዞኑ ፖሊስ ለማስገባት ሙከራ ባደረጉበት ወቅት አንቀበልም መባላቸውን ተናግረዋል።
ሊቀ መንበሩ በተጨማሪ ሠላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ መንግሥት ሁኔታዎችን እንዲያመቻች ማሳወቅ እንጂ የመፍቀድና የመከልከል ህጋዊ መብት የለውም ብለዋል።ዛሬ ጠዋት ሠላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ሮማናት ተብሎ በሚጠራው የመቀሌ ከተማ አደባባይ መሰባሰብ በጀመሩበት ጊዜ ፖሊሶች ወደ ስፍራው መጥተው ሰልፉ ህጋዊ ስላልሆነ በመግለጽ እንዲያስቆሙ መታዘዛቸውን በመግለጽ ሰልፈኞቹ እንዲበተኑ ማድረጋቸውን የሰልፉ አስተባባሪዎች ተናግረዋል።አስተባባሪዎቹም ከፖሊስ ጋር ግብግብ መፍጠር ተገቢ ባለመሆኑ ሰልፉን ለማካሄድ ለሁለተኛ ጊዜ ለፖሊስ የማሳወቂያ ደብዳቤ እንደሚያስገቡ ተናግረዋል።
የመቀሌ ከተማ ምክትል ከንቲባ ስለተከለከለው ሠላማዊ ሰልፍ ተጠይቀው "ሰልፉ ሊከለከል አይገባም። ቢሆንም የጸጥታውን ሥራ በተመለከተ ማን ተጠይቆ ምን መልስ ተሰጠ? የሚሉትን ጥያቄዎች መመለስ ይገባል" ብለዋል።የሠላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ደብዳቤውን ተቀብሎ ወደሚመለከተው አካል ያላቀረበ ግለሰብ ካለ እንቀጣለን" ያሉት አቶ አቶ ብርሐነ፤ ለፖሊስ ቀርቦ ነበር የሚለው ቅሬታን ተከትሎ ፖሊስ የመከልከል መብት ስለሌለው ተቀባይነት እንደሌለው ገልጸዋል።ሠላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ተጠይቆ ሲከለከል በዚህ ሳምንት ውስጥ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን፤ ከቀናት በፊት በሴቶች ላይ የሚፈጸም ጾታዊ ጥቃትን ለማውገዝ በተመሳሳይ መቀሌ ውስጥ ሠላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ጥያቄ ቀርቦ እንደተከለከለ መዘገባችን ይታወሳል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
'ህድሪ ሰብ' በተባለ ማህበር ዛሬ ቅዳሜ መቀሌ ከተማ ውስጥ ሊካሄድ ተጠርቶ የነበረው ሠላማዊ ሰልፍ ህጋዊ አይደለም ተብሎ በፖሊስ ተበተነ።ይህ ሠላማዊ ሰልፍ የተጠራው የትግራይ ክልል የከፍተኛ የትምህርት ተቋም ተማሪዎች ችግር ያጋጥማቸዋል ወደተባሉ ቦታዎች እንዲሄዱ እንዳይደረግ በክልሉ መንግሥት ላይ ግፊት ለማድረግ እንደነበረ ተነግሯል።ሠላማዊ ሰልፉን የጠራው ማህበር ሊቀ መንበር መሃሪ ዮሐንስ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ስለሰልፉ ለማሳወቅ ለመቀሌ ከተማ ከንቲባ ጸሐፊ ደብዳቤ ማስገባታቸውንና ግልባጩንም ለዞኑ ፖሊስ ለማስገባት ሙከራ ባደረጉበት ወቅት አንቀበልም መባላቸውን ተናግረዋል።
ሊቀ መንበሩ በተጨማሪ ሠላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ መንግሥት ሁኔታዎችን እንዲያመቻች ማሳወቅ እንጂ የመፍቀድና የመከልከል ህጋዊ መብት የለውም ብለዋል።ዛሬ ጠዋት ሠላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ሮማናት ተብሎ በሚጠራው የመቀሌ ከተማ አደባባይ መሰባሰብ በጀመሩበት ጊዜ ፖሊሶች ወደ ስፍራው መጥተው ሰልፉ ህጋዊ ስላልሆነ በመግለጽ እንዲያስቆሙ መታዘዛቸውን በመግለጽ ሰልፈኞቹ እንዲበተኑ ማድረጋቸውን የሰልፉ አስተባባሪዎች ተናግረዋል።አስተባባሪዎቹም ከፖሊስ ጋር ግብግብ መፍጠር ተገቢ ባለመሆኑ ሰልፉን ለማካሄድ ለሁለተኛ ጊዜ ለፖሊስ የማሳወቂያ ደብዳቤ እንደሚያስገቡ ተናግረዋል።
የመቀሌ ከተማ ምክትል ከንቲባ ስለተከለከለው ሠላማዊ ሰልፍ ተጠይቀው "ሰልፉ ሊከለከል አይገባም። ቢሆንም የጸጥታውን ሥራ በተመለከተ ማን ተጠይቆ ምን መልስ ተሰጠ? የሚሉትን ጥያቄዎች መመለስ ይገባል" ብለዋል።የሠላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ደብዳቤውን ተቀብሎ ወደሚመለከተው አካል ያላቀረበ ግለሰብ ካለ እንቀጣለን" ያሉት አቶ አቶ ብርሐነ፤ ለፖሊስ ቀርቦ ነበር የሚለው ቅሬታን ተከትሎ ፖሊስ የመከልከል መብት ስለሌለው ተቀባይነት እንደሌለው ገልጸዋል።ሠላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ተጠይቆ ሲከለከል በዚህ ሳምንት ውስጥ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን፤ ከቀናት በፊት በሴቶች ላይ የሚፈጸም ጾታዊ ጥቃትን ለማውገዝ በተመሳሳይ መቀሌ ውስጥ ሠላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ጥያቄ ቀርቦ እንደተከለከለ መዘገባችን ይታወሳል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች ውሃ ማድረስ አለመቻሉን ባለስልጣኑ አስታወቀ!
ከትናንት ጀምሮ በውሃ ግፊት ጣቢያዎች አካባቢ ባጋጠመ የኤሌትሪክ መቋረጥ ምክንያት በአዲስ አበባ በተወሰኑ አካባቢዎች በፈረቃቸው መሰረት ውሃ ማድረስ አልቻልኩም ሲል የአዲስ አበባ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ። የኤሌትሪክ አገልግሎት መርሀ ግብሩን ሳያሳውቀን መብራት እያጠፋ በመሆኑ በሳምንት አንድ ቀን ውሃ የሚያገኙ ደንበኞቻችን ላይ ከፍተኛ ችግር እየፈጠረ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ኃላፊ ሰርካለም ጌታቸው በተለይ ለኢቲቪ ገልጸዋል።በፈረቃቸው መሰረት ውሃ ያላገኙትም በአራዳ እና ጉለሌ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ የተወሰኑ አካባቢዎች ናቸው ብለዋል።የአዲሰ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ኃላፊ አቶ በቀለ ክፍሌ በበኩላቸው፣ በአካባቢው በነበረ የኤሌክትሪክ ፕሮጀክት ስራ አደጋ በመከሰቱ ምክንያት አገልግሎቱ ሊቋርጥ መቻሉን ተናግረዋል።በዚህ ምክንያት የመብራት ኃይል በመቋረጡ በጽዮን ሆቴል አካባቢ ላለው ጉድጓድ የሚሰጠው ኃይል ሊቋረጥ ችሏል ብለዋል።ነገር ግን ችግሩን ለመቅረፍ በአሁኑ ሰዓት አፋጣኝ የጥገና ስራ እየተከናወነ ነው ሲሉ ኃላፊው አክለዋል።
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
ከትናንት ጀምሮ በውሃ ግፊት ጣቢያዎች አካባቢ ባጋጠመ የኤሌትሪክ መቋረጥ ምክንያት በአዲስ አበባ በተወሰኑ አካባቢዎች በፈረቃቸው መሰረት ውሃ ማድረስ አልቻልኩም ሲል የአዲስ አበባ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ። የኤሌትሪክ አገልግሎት መርሀ ግብሩን ሳያሳውቀን መብራት እያጠፋ በመሆኑ በሳምንት አንድ ቀን ውሃ የሚያገኙ ደንበኞቻችን ላይ ከፍተኛ ችግር እየፈጠረ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ኃላፊ ሰርካለም ጌታቸው በተለይ ለኢቲቪ ገልጸዋል።በፈረቃቸው መሰረት ውሃ ያላገኙትም በአራዳ እና ጉለሌ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ የተወሰኑ አካባቢዎች ናቸው ብለዋል።የአዲሰ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ኃላፊ አቶ በቀለ ክፍሌ በበኩላቸው፣ በአካባቢው በነበረ የኤሌክትሪክ ፕሮጀክት ስራ አደጋ በመከሰቱ ምክንያት አገልግሎቱ ሊቋርጥ መቻሉን ተናግረዋል።በዚህ ምክንያት የመብራት ኃይል በመቋረጡ በጽዮን ሆቴል አካባቢ ላለው ጉድጓድ የሚሰጠው ኃይል ሊቋረጥ ችሏል ብለዋል።ነገር ግን ችግሩን ለመቅረፍ በአሁኑ ሰዓት አፋጣኝ የጥገና ስራ እየተከናወነ ነው ሲሉ ኃላፊው አክለዋል።
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለቻን 2020 ማጣርያ የመልስ ጨዋታቸውን ከሩዋንዳ ጋር ዛሬ ያደርጋል!
ዋልያዎቹ ለስድስተኛ ጊዜ በካሜሮን አስተናጋጅነት ለሚዘጋጀው ቻን 2020 ማጣርያ ከሩዋንዳ ጋር የመልስ ጨዋታቸውን ዛሬ ከቀኑ 11 ሰዓት ጀምሮ የሚያካሂዱ ይሆናል።በመጀመሪያው ዙር ጨዋታ በሜዳው 1 ለ 0 የተሸነፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውጤቱን ቀልብሶ ወደ ቀጣይ ዙር ለማለፍ ጥረት እንደሚያደርግ ይጠበቃል።
@YeneTube @FikerAssefa
ዋልያዎቹ ለስድስተኛ ጊዜ በካሜሮን አስተናጋጅነት ለሚዘጋጀው ቻን 2020 ማጣርያ ከሩዋንዳ ጋር የመልስ ጨዋታቸውን ዛሬ ከቀኑ 11 ሰዓት ጀምሮ የሚያካሂዱ ይሆናል።በመጀመሪያው ዙር ጨዋታ በሜዳው 1 ለ 0 የተሸነፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውጤቱን ቀልብሶ ወደ ቀጣይ ዙር ለማለፍ ጥረት እንደሚያደርግ ይጠበቃል።
@YeneTube @FikerAssefa
ከቃሊቲ ማረሚያ ታራሚዎች አመለጡ!
ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ዞን አንድ ማምለጣቸውን ምንጮች ለዋዜማ ተናገሩ፡፡ በነፍስ ግድያ ጥፈተኛ ተብለው በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የነበሩት 2 ታራሚዎች አሸናፊ መለሰ ፤ሳሙኤል መካ ጥቅምት 2 ቀን 2012 ዓ. ም ከረፋዱ 3 እስከ 4 ባለው ሰአት ውስጥ ከማረሚያ ቤቱ ቅጥር ግቢ ያመለጡ ሲሆን፤ ኤፍሬም ገ/ ጊዩርጊስ የተባለ ሌላ እስረኛ ደግሞ ለህክምና ወደ ሆስፒታል ሲወሰድ ከመኪና ላይ ዘሎ ማምለጡን ምንጮች ተናግረዋል ፡፡ማረሚያ ቤቱ የሁለቱ የታራሚዎቹን ማምለጥ ማታ በቆጠራ ሰአት እንዳወቀ ምንጮች ተናግረዋል፡፡ ይህን ተከትሎ ማረሚያ ቤቱ በእስረኞች ላይ ቁጥጥሩን ማጥበቁ ትተሰምቷል።
“እንደሚያመልጡ ታውቁ ነበር” ፣ “ያያችሁት ነገር አለ” በሚል ታራሚዎች ላይ ከፍተኛ ወከባ እየደረሰ እንደሆነ የታራሚ ቤተሰቦች ተናግረዋል። እስረኞች የጣት ቀለበትና የአንገት ሀብልም እንዲያወልቁ መደረጋቸው አግባብ አይደለም ይላሉ።የእስረኞቹን እንዴት አንዳመለጡ እና አሁንስ በቁጥጥር ስር ውለዋል ወይ? ብለን ተጨማሪ ማብራሪያ ለመጠየቅ ወደ ማረሚያ ቤቶች የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ገረመው አያሌው ስልክ የደወልንላቸው ሲሆን ከጠየቅናቸው በኃላ “የማይመች ቦታ ነኝ መልሼ ልደውል” በማለት የእጅ ስልካቸውን ዘግተውታል ፣ በተደጋጋሚ ብንደውልም ሊሰራልን አልቻለም፡፡
ዘገባው የዋዜማ ሬዲዮ ነው
@YeneTube @FikerAssefa
ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ዞን አንድ ማምለጣቸውን ምንጮች ለዋዜማ ተናገሩ፡፡ በነፍስ ግድያ ጥፈተኛ ተብለው በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የነበሩት 2 ታራሚዎች አሸናፊ መለሰ ፤ሳሙኤል መካ ጥቅምት 2 ቀን 2012 ዓ. ም ከረፋዱ 3 እስከ 4 ባለው ሰአት ውስጥ ከማረሚያ ቤቱ ቅጥር ግቢ ያመለጡ ሲሆን፤ ኤፍሬም ገ/ ጊዩርጊስ የተባለ ሌላ እስረኛ ደግሞ ለህክምና ወደ ሆስፒታል ሲወሰድ ከመኪና ላይ ዘሎ ማምለጡን ምንጮች ተናግረዋል ፡፡ማረሚያ ቤቱ የሁለቱ የታራሚዎቹን ማምለጥ ማታ በቆጠራ ሰአት እንዳወቀ ምንጮች ተናግረዋል፡፡ ይህን ተከትሎ ማረሚያ ቤቱ በእስረኞች ላይ ቁጥጥሩን ማጥበቁ ትተሰምቷል።
“እንደሚያመልጡ ታውቁ ነበር” ፣ “ያያችሁት ነገር አለ” በሚል ታራሚዎች ላይ ከፍተኛ ወከባ እየደረሰ እንደሆነ የታራሚ ቤተሰቦች ተናግረዋል። እስረኞች የጣት ቀለበትና የአንገት ሀብልም እንዲያወልቁ መደረጋቸው አግባብ አይደለም ይላሉ።የእስረኞቹን እንዴት አንዳመለጡ እና አሁንስ በቁጥጥር ስር ውለዋል ወይ? ብለን ተጨማሪ ማብራሪያ ለመጠየቅ ወደ ማረሚያ ቤቶች የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ገረመው አያሌው ስልክ የደወልንላቸው ሲሆን ከጠየቅናቸው በኃላ “የማይመች ቦታ ነኝ መልሼ ልደውል” በማለት የእጅ ስልካቸውን ዘግተውታል ፣ በተደጋጋሚ ብንደውልም ሊሰራልን አልቻለም፡፡
ዘገባው የዋዜማ ሬዲዮ ነው
@YeneTube @FikerAssefa
ዋልያዎቹ ከቻን 2020 ማጣሪያ ውጪ ሆነዋል!
ዋልያዎቹ ዛሬ ከሩዋንዳ አቻቸው ጋር ያደረጉትን የመልስ ጨዋታ በአንድ አቻ ውጤት አጠናቀዋል። 2ለ1 በሆነ የደርሶ መልስ ውጤት ሩዋንዳ የቻን 2020 ተሳታፊ መሆኗን ስታረጋግጥ፤ ኢትዮጵያ ግን ማለፍ ሳትችል ቀርታለች።መስፍን ታፈሰ በ72ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ ሲመራ የነበረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በ83ኛው ደቂቃ የአቻነት ግብ ተቆጥሮበት ነው ከውድድሩ የተሰናበተው።የሩዋንዳን የአቻነት ግብ ያስቆጠረው ኧርነስት ሴጉራ ነው።
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
ዋልያዎቹ ዛሬ ከሩዋንዳ አቻቸው ጋር ያደረጉትን የመልስ ጨዋታ በአንድ አቻ ውጤት አጠናቀዋል። 2ለ1 በሆነ የደርሶ መልስ ውጤት ሩዋንዳ የቻን 2020 ተሳታፊ መሆኗን ስታረጋግጥ፤ ኢትዮጵያ ግን ማለፍ ሳትችል ቀርታለች።መስፍን ታፈሰ በ72ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ ሲመራ የነበረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በ83ኛው ደቂቃ የአቻነት ግብ ተቆጥሮበት ነው ከውድድሩ የተሰናበተው።የሩዋንዳን የአቻነት ግብ ያስቆጠረው ኧርነስት ሴጉራ ነው።
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
ኬንያውያን በልግስና ከአፍሪካ ቀዳሚ ናቸው ተብሏል!
የማያውቋቸውን የተቸገሩ ሰዎች በመርዳት፣ ለበጎ ምግባር ገንዘብ በመለገስና በበጎ ፈቃድ ስራዎች ላይ ከፍተኛ ተሳትፎ አላቸው የተባሉት ኬንያውያን፤በልግስና ከአፍሪካ የአንደኛ፣ ከአለም አገራት ደግሞ የ11ኛ ደረጃን መያዛቸውን ሰሞኑን የወጣ አንድ አለማቀፍ ጥናት አመልክቷል፡፡ቻሪቲስ ፋውንዴሽን የተባለ ተቋም በ128 የአለማችን አገራት ላይ የሰራውን ጥናት ጠቅሶ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ ከአለማችን አገራት መካከል በልግስና ቀዳሚውን ስፍራ የያዘችው አሜሪካ ስትሆን በርማና ኒውዚላንድ በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡አውስትራሊያ፣ አየርላንድ፣ ካናዳ፣ እንግሊዝ፣ ኔዘርላንድ፣ ሲሪላንካና ኢንዶኔዥያ በተቋሙ የ2019 እጅግ ለጋስ አገራት ዝርዝር ውስጥ እንደ ቅደም ተከተላቸው ከአራተኛ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ የያዙ የአለማችን አገራት መሆናቸውም ተነግሯል፡፡
በአመቱ ከአለማችን አገራት መካከል በልግስና የመጨረሻውን ደረጃ የያዘችው አገር ቻይና ስትሆን፣ ግሪክና የመን በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡ቻሪቲስ ፋውንዴሽን የተባለው ተቋም፤ ዜጎች የማያውቁትን ሰው በመርዳት፣ ለበጎ ምግባር ገንዘብ በመለገስ ወይም በበጎ ፈቃደኝነት በመሳተፍና ሌሎች መልካም ተግባራትን በመፈጸም ረገድ ያላቸውን ተሳትፎ በመገምገም፣ የአገራቱን የልግስና ደረጃ እንደሚያወጣ ዘገባው ጠቁሟል፡፡ ኢንዶኔዢያ በልግስና ከፍተኛ መሻሻል ያሳየችዋ ቀዳሚዋ የአለማችን አገር ናት ያለው የተቋሙ ሪፖርት፤ ኬንያን በሁለተኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል፡፡
Via Addis Admas
@YeneTube @FikerAssefa
የማያውቋቸውን የተቸገሩ ሰዎች በመርዳት፣ ለበጎ ምግባር ገንዘብ በመለገስና በበጎ ፈቃድ ስራዎች ላይ ከፍተኛ ተሳትፎ አላቸው የተባሉት ኬንያውያን፤በልግስና ከአፍሪካ የአንደኛ፣ ከአለም አገራት ደግሞ የ11ኛ ደረጃን መያዛቸውን ሰሞኑን የወጣ አንድ አለማቀፍ ጥናት አመልክቷል፡፡ቻሪቲስ ፋውንዴሽን የተባለ ተቋም በ128 የአለማችን አገራት ላይ የሰራውን ጥናት ጠቅሶ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ ከአለማችን አገራት መካከል በልግስና ቀዳሚውን ስፍራ የያዘችው አሜሪካ ስትሆን በርማና ኒውዚላንድ በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡አውስትራሊያ፣ አየርላንድ፣ ካናዳ፣ እንግሊዝ፣ ኔዘርላንድ፣ ሲሪላንካና ኢንዶኔዥያ በተቋሙ የ2019 እጅግ ለጋስ አገራት ዝርዝር ውስጥ እንደ ቅደም ተከተላቸው ከአራተኛ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ የያዙ የአለማችን አገራት መሆናቸውም ተነግሯል፡፡
በአመቱ ከአለማችን አገራት መካከል በልግስና የመጨረሻውን ደረጃ የያዘችው አገር ቻይና ስትሆን፣ ግሪክና የመን በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡ቻሪቲስ ፋውንዴሽን የተባለው ተቋም፤ ዜጎች የማያውቁትን ሰው በመርዳት፣ ለበጎ ምግባር ገንዘብ በመለገስ ወይም በበጎ ፈቃደኝነት በመሳተፍና ሌሎች መልካም ተግባራትን በመፈጸም ረገድ ያላቸውን ተሳትፎ በመገምገም፣ የአገራቱን የልግስና ደረጃ እንደሚያወጣ ዘገባው ጠቁሟል፡፡ ኢንዶኔዢያ በልግስና ከፍተኛ መሻሻል ያሳየችዋ ቀዳሚዋ የአለማችን አገር ናት ያለው የተቋሙ ሪፖርት፤ ኬንያን በሁለተኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል፡፡
Via Addis Admas
@YeneTube @FikerAssefa
Estimated population in 2100. (in million)
India: 1660
China: 1004
Nigeria: 752
US: 450
DR Congo: 389
Pakistan: 364
Tanzania: 299
Indonesia: 242
#Ethiopia : 242
Niger: 209
Uganda: 202
Egypt: 201
Brazil: 200
Bangladesh: 170
Philippines: 169
(United Nations)
@YeneTube @FikerAssefa
India: 1660
China: 1004
Nigeria: 752
US: 450
DR Congo: 389
Pakistan: 364
Tanzania: 299
Indonesia: 242
#Ethiopia : 242
Niger: 209
Uganda: 202
Egypt: 201
Brazil: 200
Bangladesh: 170
Philippines: 169
(United Nations)
@YeneTube @FikerAssefa