የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ነገ በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሰልፍ የለም አለ።
በማህበራዊ ሚዲያዎች ነገ ጥቅምት 2 ቀን 2012 ዓ/ም በአዲስ አበባ ከተማ ሰልፍ እንደሚደረግ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በሰልፉ ምክንያት የሚዘጉ መንገዶችን መኖራቸውን ገለፀ በሚል የኮሚሽኑን ሎጎና የኃላፊዎችን ስም በመጠቀም የተላለፈው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ነገ ጥቅምት 2 ቀን 2012 ዓ/ም ሰላማዊ ሰልፍም ሆነ ስብሰባ በመስቀል አደባባይ የሌለና ምንም የሚዘጋ መንገድ አለመኖሩን ህብረተሰቡ ተገንዝቦ መደበኛ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚችል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡መሰል ሀሰተኛና የተዛቡ መረጃዎች በህብረተሰቡ የእለት ከእለት እንስቃሴ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ የሚሳድሩ መሆኑን ኮሚሽኑ በማስታወስ ህብረተሰቡ ከተሳሳተ መረጃ ራሱን መጠበቅ እንዳለበት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
Via Addis Ababa Police Commission
@YeneTube @FikerAssefa
በማህበራዊ ሚዲያዎች ነገ ጥቅምት 2 ቀን 2012 ዓ/ም በአዲስ አበባ ከተማ ሰልፍ እንደሚደረግ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በሰልፉ ምክንያት የሚዘጉ መንገዶችን መኖራቸውን ገለፀ በሚል የኮሚሽኑን ሎጎና የኃላፊዎችን ስም በመጠቀም የተላለፈው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ነገ ጥቅምት 2 ቀን 2012 ዓ/ም ሰላማዊ ሰልፍም ሆነ ስብሰባ በመስቀል አደባባይ የሌለና ምንም የሚዘጋ መንገድ አለመኖሩን ህብረተሰቡ ተገንዝቦ መደበኛ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚችል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡መሰል ሀሰተኛና የተዛቡ መረጃዎች በህብረተሰቡ የእለት ከእለት እንስቃሴ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ የሚሳድሩ መሆኑን ኮሚሽኑ በማስታወስ ህብረተሰቡ ከተሳሳተ መረጃ ራሱን መጠበቅ እንዳለበት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
Via Addis Ababa Police Commission
@YeneTube @FikerAssefa
በሰቆጣ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ17 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡
በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ትናንት ከቀኑ 11፡30 አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ17 ሰዎች ሕይወት አልፏል፤ በርካቶችም ቆስለዋል፡፡የሰቆጣ ወረዳ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ደጀን ወዳጅ ለአብመድ እንደገለጹት ከወልደያ ወደ ሰቆጣ ይጓዝ የነበረ መለስተኛ አነስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከጭነቱ ልክ በላይ በርካታ ሰዎችን እንደጫነ አደጋው ደርሷል፡፡በወረዳው ዲብርሳይል (07) ቀበሌ ላይ በተከሰተው አደጋ 17 ሰዎች መሞታቸውን ያስታወቁት ኢንስፔክተር ደጀን ‹‹አራት እናቶች ከነልጆቻቸው፣ አንዲት እናት ከሦስት ልጆቻቸው፤ አባት ከልጆቹ ጋር ሕይወታቸው አልፏል፡፡ ባልና ሚስትም የነበሩ ሲሆን ባል ከነልጁ ሕይወቱ አልፏል፤ ሚስት ከአንድ ልጇ ጋር ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል ይገኛሉ›› ብለዋል፡፡
በአደጋው የተጎዱ ሰባት ሰዎች በተፈራ ኃይሉ ሆስፒታል ገብተው ሕክምና እንዲያገኙ መደረጉን ጠቅሰው ‹‹አሁን ላይ አንደኛዋ ጉዳቱ የከፋ በመሆኑ ወደ መቀሌ ሪፈራል ሆስፒታል ተልካለች›› ነው ያሉት፡፡ከወልደያ ወደ ሰቆጣ ከመጠን በላይ ጭኖ እንደመጣ የተገለጸው ተሽከርካሪ መጫን የነበረበት እስከ 12 ሰው ቢሆንም አሳፍሮ የነበረው ከእጥፍ በላይ 25 ሰዎችን እንደነበር አስታውቀዋል፡፡ቦታው ዳገት በመሆኑ ወደ ኋላ በመመለስ ከመስመር ወጥቶ ሦስት ሜትር ገደል ውስጥ መውደቁንም አመልክተዋል፡፡የመኪናው ሾፌር በሕይወት መኖሩንና በሕግ ጥላ ሥር እንደሚገኝ ያመለከቱት ኢንስፔክተር ደጀን ፖሊስ መታወቂያ የያዙ ሟቾችን አስከሬን ለቤተሰብ ማስረከቡን ገልጸዋል፡፡
ምንጭ: አብመድ
@YeneTube @FikerAssefa
በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ትናንት ከቀኑ 11፡30 አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ17 ሰዎች ሕይወት አልፏል፤ በርካቶችም ቆስለዋል፡፡የሰቆጣ ወረዳ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ደጀን ወዳጅ ለአብመድ እንደገለጹት ከወልደያ ወደ ሰቆጣ ይጓዝ የነበረ መለስተኛ አነስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከጭነቱ ልክ በላይ በርካታ ሰዎችን እንደጫነ አደጋው ደርሷል፡፡በወረዳው ዲብርሳይል (07) ቀበሌ ላይ በተከሰተው አደጋ 17 ሰዎች መሞታቸውን ያስታወቁት ኢንስፔክተር ደጀን ‹‹አራት እናቶች ከነልጆቻቸው፣ አንዲት እናት ከሦስት ልጆቻቸው፤ አባት ከልጆቹ ጋር ሕይወታቸው አልፏል፡፡ ባልና ሚስትም የነበሩ ሲሆን ባል ከነልጁ ሕይወቱ አልፏል፤ ሚስት ከአንድ ልጇ ጋር ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል ይገኛሉ›› ብለዋል፡፡
በአደጋው የተጎዱ ሰባት ሰዎች በተፈራ ኃይሉ ሆስፒታል ገብተው ሕክምና እንዲያገኙ መደረጉን ጠቅሰው ‹‹አሁን ላይ አንደኛዋ ጉዳቱ የከፋ በመሆኑ ወደ መቀሌ ሪፈራል ሆስፒታል ተልካለች›› ነው ያሉት፡፡ከወልደያ ወደ ሰቆጣ ከመጠን በላይ ጭኖ እንደመጣ የተገለጸው ተሽከርካሪ መጫን የነበረበት እስከ 12 ሰው ቢሆንም አሳፍሮ የነበረው ከእጥፍ በላይ 25 ሰዎችን እንደነበር አስታውቀዋል፡፡ቦታው ዳገት በመሆኑ ወደ ኋላ በመመለስ ከመስመር ወጥቶ ሦስት ሜትር ገደል ውስጥ መውደቁንም አመልክተዋል፡፡የመኪናው ሾፌር በሕይወት መኖሩንና በሕግ ጥላ ሥር እንደሚገኝ ያመለከቱት ኢንስፔክተር ደጀን ፖሊስ መታወቂያ የያዙ ሟቾችን አስከሬን ለቤተሰብ ማስረከቡን ገልጸዋል፡፡
ምንጭ: አብመድ
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የጎጃም አዲስ አበባ መንገድ አልተዘጋም ብሏል፡፡
ከትናንት ጀምሮ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ግን መንገዱ ዝግ እንደሆነ እየተነገረ ነው። የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ‹‹ወቅታዊ የፀጥታ ስጋቶችን መነሻ በማድረግ ፍተሻ እየተካሄደ ነበር፤ በዚህ ምክንያት መኪኖቹ ወረፋ ሲበዛባቸው ተመልሰዋል እንጅ መንገድ ስለመዘጋቱ መረጃ የለንም፤ እንዲዘጋም አላዘዝንም፡፡ ፍተሻውን ላለመጠበቅ የተመለሱ ካልሆኑ በስተቀር መንገድ አልተዘጋም›› ብለዋል፡፡ "ተጨማሪ ጥያቄዎችን ለማመስመለስ ብንፈልግም ስልካቸው በመዘጋቱ አልቻልንም፡፡" አብመድ
የደጀን ወረዳ አስተዳደርና ፀጥታ ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ካሳ አስፋው ዛሬ ከቀኑ 6፡30 ላይ በስልክ እንደገለጹት መንገዱ አሁንም እንደተዘጋ ነው፡፡ ‹‹ወደ ኦሮሚያ ክልል የሚመለከታቸው አካላት ስልክ ስንደውል ከትናንት ጀምሮ ‹አልተዘጋም› እያሉን ነው፤ በተጨባጭ የሚያልፉ መኪኖች ግን የሉም፡፡ ዛሬ ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልልም መኪኖች እየመጡ አይደለም፤ ድብብቆሹን ትቶ የሕዝቡን ችግር ለመፍታት ቢሠራ መልካም ነው›› ብለዋል፡፡
ወደ ኢፌዴሪ ትራንስፖርት ሚኒስቴር መረጃ ለማግኘት ጥረት ብናደርግም ያገኘኛቸው የሥራ ኃላፊ ‹‹ከአዲስ አበባ ውጭ ነኝ፤ ስለጉዳዩ በቂ መረጃ የለኝም›› በማለት ከፌዴራል ፖሊስ ይመለከታቸዋል የተባሉ ኃላፊን ስልክ ቁጥር ብቻ ሰጥተውናል፡፡ ከፌዴራል ፖሊስ የደወልንላቸው ግለሰብ ግን ‹‹ጉዳዩ እኔን አይመለከትም፤ ማንን እንደሚመለከትም አላውቅም፡፡ መንገድ ተዘጋ ሲባል እንዲሁ ነው የሰማሁት›› ብለዋል፡፡
በመንገዱ መዘጋት እየተጉላ ከሚገኙት ውስጥ ብዙዎቹ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ናቸው፡፡ ተማሪዎቹ የምዝገባ ጊዜ በማለፉ ለሚገጥማቸው ችግር ኃላፊነት የሚወስድ አካል ባለማግኘታቸው እየተቸገሩ መሆኑንም አመልክተዋል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርን ለማነጋገር ጥረት እያደረግን ነው፡፡ የሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነት ‹‹ስለጉዳዩ በቂ መረጃ አላገኘንም፤ ሁኔታውን አጣርተን ከሰዓት በኋላ የሚኖረውን ምላሽ እናሳውቃለን›› ብለዋል፡፡
Via አብመድ
@YeneTube @FikerAssefa
ከትናንት ጀምሮ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ግን መንገዱ ዝግ እንደሆነ እየተነገረ ነው። የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ‹‹ወቅታዊ የፀጥታ ስጋቶችን መነሻ በማድረግ ፍተሻ እየተካሄደ ነበር፤ በዚህ ምክንያት መኪኖቹ ወረፋ ሲበዛባቸው ተመልሰዋል እንጅ መንገድ ስለመዘጋቱ መረጃ የለንም፤ እንዲዘጋም አላዘዝንም፡፡ ፍተሻውን ላለመጠበቅ የተመለሱ ካልሆኑ በስተቀር መንገድ አልተዘጋም›› ብለዋል፡፡ "ተጨማሪ ጥያቄዎችን ለማመስመለስ ብንፈልግም ስልካቸው በመዘጋቱ አልቻልንም፡፡" አብመድ
የደጀን ወረዳ አስተዳደርና ፀጥታ ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ካሳ አስፋው ዛሬ ከቀኑ 6፡30 ላይ በስልክ እንደገለጹት መንገዱ አሁንም እንደተዘጋ ነው፡፡ ‹‹ወደ ኦሮሚያ ክልል የሚመለከታቸው አካላት ስልክ ስንደውል ከትናንት ጀምሮ ‹አልተዘጋም› እያሉን ነው፤ በተጨባጭ የሚያልፉ መኪኖች ግን የሉም፡፡ ዛሬ ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልልም መኪኖች እየመጡ አይደለም፤ ድብብቆሹን ትቶ የሕዝቡን ችግር ለመፍታት ቢሠራ መልካም ነው›› ብለዋል፡፡
ወደ ኢፌዴሪ ትራንስፖርት ሚኒስቴር መረጃ ለማግኘት ጥረት ብናደርግም ያገኘኛቸው የሥራ ኃላፊ ‹‹ከአዲስ አበባ ውጭ ነኝ፤ ስለጉዳዩ በቂ መረጃ የለኝም›› በማለት ከፌዴራል ፖሊስ ይመለከታቸዋል የተባሉ ኃላፊን ስልክ ቁጥር ብቻ ሰጥተውናል፡፡ ከፌዴራል ፖሊስ የደወልንላቸው ግለሰብ ግን ‹‹ጉዳዩ እኔን አይመለከትም፤ ማንን እንደሚመለከትም አላውቅም፡፡ መንገድ ተዘጋ ሲባል እንዲሁ ነው የሰማሁት›› ብለዋል፡፡
በመንገዱ መዘጋት እየተጉላ ከሚገኙት ውስጥ ብዙዎቹ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ናቸው፡፡ ተማሪዎቹ የምዝገባ ጊዜ በማለፉ ለሚገጥማቸው ችግር ኃላፊነት የሚወስድ አካል ባለማግኘታቸው እየተቸገሩ መሆኑንም አመልክተዋል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርን ለማነጋገር ጥረት እያደረግን ነው፡፡ የሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነት ‹‹ስለጉዳዩ በቂ መረጃ አላገኘንም፤ ሁኔታውን አጣርተን ከሰዓት በኋላ የሚኖረውን ምላሽ እናሳውቃለን›› ብለዋል፡፡
Via አብመድ
@YeneTube @FikerAssefa
ከባህር ዳር አዲስ አበባ የሚወስደው መንገድ ዛሬም አልተከፈተም።
የደጀን ወረዳ አስተዳደርና ፀጥታ ኃላፊ የሆኑት አቶ ካሳ አስፋውም በአሁኑ ሰዓት ኦሮሚያ ክልል ያለው መንገድ ስላልተከፈተ ደጀን ከተማ ላይ በርካታ መኪኖችና መንገደኞች በከተማዋ እንዳሉ ለቢቢሲ ገልፀዋል።በኦሮሚያ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን የጸጥታ ኃላፊ አቶ ለማ ሆርዶፋ በበኩላቸው ከባህር ዳር ወደ አዲስ አበባ የሚወስደው መንገድ የተዘጋበትን ምክንያት ለማጣራት አመራሮችን ወደ ሥፍራው እንደላኩ ገልፀው፤ ዛሬ ጠዋትም በጉዳዩ ላይ ተነጋግረውበት አንድም መኪና መቆም እንደማይችል አቅጣጫ አስቀምጠን መኪና በሰላማዊ መልኩ እያለፈ እንደሆነ መረጃ እንዳላቸው ነግረውናል።
ምንጭ:BBC
@YeneTube @FikerAssefa
የደጀን ወረዳ አስተዳደርና ፀጥታ ኃላፊ የሆኑት አቶ ካሳ አስፋውም በአሁኑ ሰዓት ኦሮሚያ ክልል ያለው መንገድ ስላልተከፈተ ደጀን ከተማ ላይ በርካታ መኪኖችና መንገደኞች በከተማዋ እንዳሉ ለቢቢሲ ገልፀዋል።በኦሮሚያ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን የጸጥታ ኃላፊ አቶ ለማ ሆርዶፋ በበኩላቸው ከባህር ዳር ወደ አዲስ አበባ የሚወስደው መንገድ የተዘጋበትን ምክንያት ለማጣራት አመራሮችን ወደ ሥፍራው እንደላኩ ገልፀው፤ ዛሬ ጠዋትም በጉዳዩ ላይ ተነጋግረውበት አንድም መኪና መቆም እንደማይችል አቅጣጫ አስቀምጠን መኪና በሰላማዊ መልኩ እያለፈ እንደሆነ መረጃ እንዳላቸው ነግረውናል።
ምንጭ:BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ደብረ ብርሀን በአሁኑ ሰዓት ወጣቱ ስላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል ስሞኑን በሚደረገው መገድ መዝጋት በጣም ነዋሪዎች መማረራቸውን ለየኔቲዩብ ገልፀዋል።
@YeneTube @Fikerassefa
@YeneTube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የእጩ ሰልጣኞች ምልመላንና ቅበላ ፖሊሲን በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ!
Via Elias Meseret/Ethiopian Airlines
@YeneTube @FikerAssefa
Via Elias Meseret/Ethiopian Airlines
@YeneTube @FikerAssefa
"በርካታ ወጣቶች ዛሬ ከጠዋቱ 4 ሰአት ጀምሮ ታስረዋል"--- እስክንድር ነጋ በስልክ ከነገረኝ
እስክንድር እንዳለው ዛሬ ጠዋት የመጨረሻ ቅስቀሳ እያደረጉ በነበሩበት ወቅት በተለይ መርካቶ አካባቢ በርካታ ወጣቶች ታስረዋል። "አሁን አንተን ሳወራህ ፖሊስ ጣብያዎች እየዞርኩ ልጆቹን ለማስፈታት እየሞከርኩ እያለ ነው። ቁጥራቸው ብዙ ነው፣ ስንት እንደሆነ እንኳን አላውቅም። ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሀላፊዎች ጋር ትንሽ ቆይቼ በአጠቃላይ ጉዳዮች ላይ አወራለሁ።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ነገ ጥቅምት 2 ሰላማዊ ሰልፍም ሆነ ስብሰባ በመስቀል አደባባይ የለም ብሎ ዛሬ ጠዋት አሳውቆ ነበር።
Via:- Elias Meseret
@YeneTube @Fikerassefa
እስክንድር እንዳለው ዛሬ ጠዋት የመጨረሻ ቅስቀሳ እያደረጉ በነበሩበት ወቅት በተለይ መርካቶ አካባቢ በርካታ ወጣቶች ታስረዋል። "አሁን አንተን ሳወራህ ፖሊስ ጣብያዎች እየዞርኩ ልጆቹን ለማስፈታት እየሞከርኩ እያለ ነው። ቁጥራቸው ብዙ ነው፣ ስንት እንደሆነ እንኳን አላውቅም። ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሀላፊዎች ጋር ትንሽ ቆይቼ በአጠቃላይ ጉዳዮች ላይ አወራለሁ።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ነገ ጥቅምት 2 ሰላማዊ ሰልፍም ሆነ ስብሰባ በመስቀል አደባባይ የለም ብሎ ዛሬ ጠዋት አሳውቆ ነበር።
Via:- Elias Meseret
@YeneTube @Fikerassefa
አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ አዲስ ገቢ ተማሪዎች በሁሉም መነኃርያዎች እና ኤርፓርቶች ተማሪዎችን እየተቀበለ መሆኑን የተማሪዎች ፕሬዝዳንት ናትናኤል ለየኔቲዩብ አስታውቋዋል።
@YeneTube @Fikerassefa
@YeneTube @Fikerassefa
የአዲስ አበባ ፖሊስ 'ነገ ለሚደረግ ሰልፍ በማስተባበር ላይ ናችሁ' ያላቸውን በርካታ ወጣቶች ማሰሩን ምንጮች ገለጹ።ከአስተባባሪዎቹ መካከል ናትናኤል የዓለም ዘውድ፣ ስምኦን፣ ደበላ ኩባ የተባሉ ወጣቶች ታስረዋል ሲል አስተባባሪው ገለጿል።
ምንጭ: ድሬቲውብ
@YeneTube @FikerAssefa
ምንጭ: ድሬቲውብ
@YeneTube @FikerAssefa
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ በማድረስ ኤልያስ መሠረት የ3ኛው ጣና ሽልማት አሸናፊ ሆኗል።
እንኳን ደስ አለህ ኤልያስ መሰረት ታዬ
ኤልያስን በቴሌግራም ያልተከተላችሁ በዚህ ሊንክ ታገኙታላችሁ @eliasmeseret
እንኳን ደስ አለህ ኤልያስ መሰረት ታዬ
ኤልያስን በቴሌግራም ያልተከተላችሁ በዚህ ሊንክ ታገኙታላችሁ @eliasmeseret
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ በማድረስ ኤልያስ መሠረት የ3ኛው ጣና ሽልማት አሸናፊ ሆኗል።
እንኳን ደስ አለህ ኤልያስ መሰረት ታዬ
ኤልያስን በቴሌግራም ያልተከተላችሁ በዚህ ሊንክ ታገኙታላችሁ @eliasmeseret
እንኳን ደስ አለህ ኤልያስ መሰረት ታዬ
ኤልያስን በቴሌግራም ያልተከተላችሁ በዚህ ሊንክ ታገኙታላችሁ @eliasmeseret
ፖሊስ የጥቅምት ሁለቱን ሰልፍ ስለመከልከሉ
የአዲስ አበባ ምክር ቤት ጥቅምት 2 2012 ዓ.ም የጠራውን ሰልፍ የአዲስ አበባ መስተዳድር በህጉ መሠረት በዝምታ ፍቃድ ከሰጠ በኃላ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥቅምት 1 2012 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ክልከላ አድርጎበታል።
ይህን አስመልክቶ ምክር ቤቱ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ፣ ምክር ቤቱ ቀደም ብሎ በጉዳዩ ዙሪያ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት፣ለሀገሪቱ ሰላምና ለህዝቧ ደህንነት ቅድሚያ በመስጠት ሰልፉን ሰርዟል።
የመንግስት ህገ ወጥ ክልከላ የዴሞክራሲ እና ፍትህ ቅልበሳውን አረጋግጧል። ስለዚህም፣ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደገለፀው፣ ሰላማዊ ትግሉን በሂደት ወደ ቀጣይ ምእራፍ ለማሸጋገር እንደሚገደድ በዚህ አጋጣሚ ይገልፃል።
የአዲስ አበባ ባላደራ ምክርቤት የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ ለማሳካት ሲንቀሳቀሱ የታሰሩ በርካታ ወጣቶች በአስቸኳይ እንዲፈቱ እንጠይቃለን።
በመላው ኢትዮጵያ የምትገኙ፣ እንዲሁም፣ በውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን ቀን ከሌሊት ያደረጋችሁት ልፋት ለዲሞክራሲ እና ፍትህ መምጣት የምትከፍሉት ዋጋ ቢሆንም፣ ባለ አደራ ምክር ቤቱ የላቀ ምስጋናውን እና አክብሮቱን ይገልፃል።
ፈጣሪ ህዝቧንና ኢትዮጵያን ይባርክ!
የአዲስ አበባ ባለአደራ ም/ቤት
አዲስ አበባ
@YeneTube @Fikerassefa
የአዲስ አበባ ምክር ቤት ጥቅምት 2 2012 ዓ.ም የጠራውን ሰልፍ የአዲስ አበባ መስተዳድር በህጉ መሠረት በዝምታ ፍቃድ ከሰጠ በኃላ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥቅምት 1 2012 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ክልከላ አድርጎበታል።
ይህን አስመልክቶ ምክር ቤቱ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ፣ ምክር ቤቱ ቀደም ብሎ በጉዳዩ ዙሪያ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት፣ለሀገሪቱ ሰላምና ለህዝቧ ደህንነት ቅድሚያ በመስጠት ሰልፉን ሰርዟል።
የመንግስት ህገ ወጥ ክልከላ የዴሞክራሲ እና ፍትህ ቅልበሳውን አረጋግጧል። ስለዚህም፣ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደገለፀው፣ ሰላማዊ ትግሉን በሂደት ወደ ቀጣይ ምእራፍ ለማሸጋገር እንደሚገደድ በዚህ አጋጣሚ ይገልፃል።
የአዲስ አበባ ባላደራ ምክርቤት የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ ለማሳካት ሲንቀሳቀሱ የታሰሩ በርካታ ወጣቶች በአስቸኳይ እንዲፈቱ እንጠይቃለን።
በመላው ኢትዮጵያ የምትገኙ፣ እንዲሁም፣ በውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን ቀን ከሌሊት ያደረጋችሁት ልፋት ለዲሞክራሲ እና ፍትህ መምጣት የምትከፍሉት ዋጋ ቢሆንም፣ ባለ አደራ ምክር ቤቱ የላቀ ምስጋናውን እና አክብሮቱን ይገልፃል።
ፈጣሪ ህዝቧንና ኢትዮጵያን ይባርክ!
የአዲስ አበባ ባለአደራ ም/ቤት
አዲስ አበባ
@YeneTube @Fikerassefa