በሰላም ተከብሯል!
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የደመራ በዓል በሰላም መከበሩን አስታወቀ።
እጅግ በርካታ ቁጥር ያለው የኃይማኖቱ ተከታዮች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ መቀመጫቸውን ኢትዮጵያ ውስጥ ያደረጉ የውጪ ሀገራት ዲፕሎማቶች እና የተለያዩ ሀገራት ጎብኝዎች የታደሙበት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በዓሉ በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል፡፡
በያዝነው ዓመት በርካታ ህዝብ የታደመባቸው ሃይማኖታዊ እና ስፖርታዊ ዝግጅቶች በሰላም መከበራቸውን ያስተወሰው ኮሚሽኑ የደመራ በዓል በሰላም እንዲከበር ህብረተሰቡ ላደረገው ቀና ትብብር ምስጋናውን አቅርቧል፡፡በነገው ዕለት የሚከበረው የመስቀል በዓልም በሰላም እንዲከበር ህብረተሰቡ የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን ማስተላለፉን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ምንጭ:ፋና
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የደመራ በዓል በሰላም መከበሩን አስታወቀ።
እጅግ በርካታ ቁጥር ያለው የኃይማኖቱ ተከታዮች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ መቀመጫቸውን ኢትዮጵያ ውስጥ ያደረጉ የውጪ ሀገራት ዲፕሎማቶች እና የተለያዩ ሀገራት ጎብኝዎች የታደሙበት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በዓሉ በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል፡፡
በያዝነው ዓመት በርካታ ህዝብ የታደመባቸው ሃይማኖታዊ እና ስፖርታዊ ዝግጅቶች በሰላም መከበራቸውን ያስተወሰው ኮሚሽኑ የደመራ በዓል በሰላም እንዲከበር ህብረተሰቡ ላደረገው ቀና ትብብር ምስጋናውን አቅርቧል፡፡በነገው ዕለት የሚከበረው የመስቀል በዓልም በሰላም እንዲከበር ህብረተሰቡ የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን ማስተላለፉን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ምንጭ:ፋና
@YeneTube @FikerAssefa
#ቢሾፍቱ (ደብረዘይት) ደመራ አልተደመረም!!
በቢሾፍቱ (በደብረ ዘይት) ከተማ የተዘጋጀው ደመራ ሳይበራ ፕሮግራሙ ተዘግቷል። መንስዔውም የቅድስት ኪዳነምህረት ካህናት ወደ ዳመራው በተደመረበት አደባባይ ቤ/ክ የምትጠቀመውን ሰንደቅ አላማ ለምን ይዛችሁ መጣቹህ በማለት በተለያዩ አካላት #ከበሩ ሊመለሱ ችለዋል።
በዚህም ምክንያት ካህናቱ በሩ ላይ ብዙ ሰዓት ከቆሙ በዋላ ሊመለሱ ችለዋል። ይህንንም የሰሙ ወጣቱ አባቶች ሣይገኙ ደመራውን አናበራም በማለት ደመራውን ሣያበሩ በጸሎት ፕሮግራሙ ሊዘጋ ችሏል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ፌደራል ፓሊስ ከሀገሪቱ ባንዲራ ውጪ ይዞ መገኘት እንደማይቻል ትላንት ያስታወቀ ሲሆን ዛሬ መልሶ የቤተክርስቲያን የራሷን አርማ እና ሎጎ መጠቀም እንደምትችል ማስታወቁ ይታወሳል።
Via:- #Mike_YeneTube
@YeneTube @Fikerassefa
በቢሾፍቱ (በደብረ ዘይት) ከተማ የተዘጋጀው ደመራ ሳይበራ ፕሮግራሙ ተዘግቷል። መንስዔውም የቅድስት ኪዳነምህረት ካህናት ወደ ዳመራው በተደመረበት አደባባይ ቤ/ክ የምትጠቀመውን ሰንደቅ አላማ ለምን ይዛችሁ መጣቹህ በማለት በተለያዩ አካላት #ከበሩ ሊመለሱ ችለዋል።
በዚህም ምክንያት ካህናቱ በሩ ላይ ብዙ ሰዓት ከቆሙ በዋላ ሊመለሱ ችለዋል። ይህንንም የሰሙ ወጣቱ አባቶች ሣይገኙ ደመራውን አናበራም በማለት ደመራውን ሣያበሩ በጸሎት ፕሮግራሙ ሊዘጋ ችሏል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ፌደራል ፓሊስ ከሀገሪቱ ባንዲራ ውጪ ይዞ መገኘት እንደማይቻል ትላንት ያስታወቀ ሲሆን ዛሬ መልሶ የቤተክርስቲያን የራሷን አርማ እና ሎጎ መጠቀም እንደምትችል ማስታወቁ ይታወሳል።
Via:- #Mike_YeneTube
@YeneTube @Fikerassefa
በዛሬው የመስቀል ደመራ በአል አከባበር ላይ 55 የበዓሉ ታዳሚዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ህዝብ ግንኙነት እና ጉዳይ አስፈፃሚ መላከ ሕይወት አባ ወልደየሱስ ሰይፉ ለቢቢሲ ገለፁ።
መላከ ህይወት አባ ወልደየሱስ እንደገለፁት 33ቱ ምእመናን በቁጥጥር ስር የዋሉት ቤተክርስትያኗ ላይ የሚሰነዘር ጥቃት እንዲቆም የሚያወግዝ ፅሁፍ ያለበት ቲሸርት ለብሰው በመገኘታቸው ነበር።ምእመናኑ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ምክንያት የሆኑት ቲሸርቶች 'የቤተክርስትያን ጉዳይ ያገባኛል'፣ የቤተክርስትያን መቃጠልና ጥቃት ይቁም' የሚሉ ፅሁፎች ያለባቸው እንደነበሩ አባ ወልደየሱስ አስረድተዋል።
አራቱ ደግሞ የሌላ ሰው ባጅ አድርገው በመገኘታቸው በቁጥጥር ሲውሉ ቀሪዎቹ 12 የሚሆኑት ደግሞ ስለት ይዘው ተገኝተዋል በሚል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ያስረዳሉ።
በቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦች የተወሰዱት ካዛንችዝ ከሚገኘው ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ እንደነበርና በኋላ እሳቸው ወደ ፖሊስ ጣቢያው ሄደው ሃላፊዎች ከነጋገሩ በኋላ 37 በዋስ መለቀቃቸውን መላከሕይወት አባ ወልደየሱስ ተናግረዋል።
ምንጭ:- ቢቢሲ አማርኛ
@YeneTube @Fikerassefa
መላከ ህይወት አባ ወልደየሱስ እንደገለፁት 33ቱ ምእመናን በቁጥጥር ስር የዋሉት ቤተክርስትያኗ ላይ የሚሰነዘር ጥቃት እንዲቆም የሚያወግዝ ፅሁፍ ያለበት ቲሸርት ለብሰው በመገኘታቸው ነበር።ምእመናኑ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ምክንያት የሆኑት ቲሸርቶች 'የቤተክርስትያን ጉዳይ ያገባኛል'፣ የቤተክርስትያን መቃጠልና ጥቃት ይቁም' የሚሉ ፅሁፎች ያለባቸው እንደነበሩ አባ ወልደየሱስ አስረድተዋል።
አራቱ ደግሞ የሌላ ሰው ባጅ አድርገው በመገኘታቸው በቁጥጥር ሲውሉ ቀሪዎቹ 12 የሚሆኑት ደግሞ ስለት ይዘው ተገኝተዋል በሚል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ያስረዳሉ።
በቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦች የተወሰዱት ካዛንችዝ ከሚገኘው ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ እንደነበርና በኋላ እሳቸው ወደ ፖሊስ ጣቢያው ሄደው ሃላፊዎች ከነጋገሩ በኋላ 37 በዋስ መለቀቃቸውን መላከሕይወት አባ ወልደየሱስ ተናግረዋል።
ምንጭ:- ቢቢሲ አማርኛ
@YeneTube @Fikerassefa
ትናንት በካታር ዶሃ በተጀመረው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፕዮና ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ለግማሽ ፍፅሜ እና ፍፃሜ አልፈዋል።
በ17ኛው የዓለም ሻምፕዮና ለኢትዮጵያ የመጀመርያ በሆነው የሴቶች 800 ሜትር የመጀመሪያ ዙር ድርቤ ወልተጂ በተወዳደረችበት ምድብ አራት 02፡02.71 ደቂቃ በመግባት አምስተኛ ሆና አጠናቃለች። ሆኖም የዓለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፕዮኗ ከተሸናፊዎች ፈጣን ሰዓት ባስመዘገበ በሚለው ህግ ነገ መስከረም 17/2012 ዓ.ም ለሚካሄደው ግማሽ ፍፃሜ አልፋለች።
በሴቶች 3000ሜ መሰናክል የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቷ መቅደስ አበበ የግሏን ፈጣን ሰዓት በማስመዝብ ከሦስት ቀናት በኋላ ለሚደረግው የፍፃሜ ውድድር አልፋለች።በወንዶች 5000ሜ ያለፈው የዓለም ሻምፕዮኑ ሙክታር ኢድሪስ፣ የዓመቱ ፈጣን ሰዓት ባለቤት ጥላሁን ሃይሌ፣ እንዲሁም ሰለሞን ባርጋ ለፍፃሜ ውድድሩ አልፈዋል። አባዲ ሃዲስ አልተሳካለትም።
Via VOA
@YeneTube @FikerAssefa
በ17ኛው የዓለም ሻምፕዮና ለኢትዮጵያ የመጀመርያ በሆነው የሴቶች 800 ሜትር የመጀመሪያ ዙር ድርቤ ወልተጂ በተወዳደረችበት ምድብ አራት 02፡02.71 ደቂቃ በመግባት አምስተኛ ሆና አጠናቃለች። ሆኖም የዓለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፕዮኗ ከተሸናፊዎች ፈጣን ሰዓት ባስመዘገበ በሚለው ህግ ነገ መስከረም 17/2012 ዓ.ም ለሚካሄደው ግማሽ ፍፃሜ አልፋለች።
በሴቶች 3000ሜ መሰናክል የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቷ መቅደስ አበበ የግሏን ፈጣን ሰዓት በማስመዝብ ከሦስት ቀናት በኋላ ለሚደረግው የፍፃሜ ውድድር አልፋለች።በወንዶች 5000ሜ ያለፈው የዓለም ሻምፕዮኑ ሙክታር ኢድሪስ፣ የዓመቱ ፈጣን ሰዓት ባለቤት ጥላሁን ሃይሌ፣ እንዲሁም ሰለሞን ባርጋ ለፍፃሜ ውድድሩ አልፈዋል። አባዲ ሃዲስ አልተሳካለትም።
Via VOA
@YeneTube @FikerAssefa
“መደበኛ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ማንኛውም ነገር ሊፈጠር ይችላል።
ከጎረቤቷ ሰባት እጅ የምታንስ አገር የሚኖራት ሁለት ምርጫ ነው። አንድም ማፈግፈግ አሊያም ለነጻነት እስከ ሞት መዋጋት። እንዋጋለን። የኑክሌር ጦር መሳሪያ የታጠቀ አገር እስከ ፍጻሜው የተዋጋ እንደሆነ ጣጣው ከድንበር ይሻገራል፣ ፍዳው ለዓለም ይተርፋል” የፓኪስታኑ ጠቅላይ ምኒስትር ኢምራን ክኻን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ሕንድን፣ ፕሬዝዳንት ናሬንድራ ሞዲን አጥብቀው በነቀፉበት ዓለምን ካስጠነቀቁበት ንግግራቸው
Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
ከጎረቤቷ ሰባት እጅ የምታንስ አገር የሚኖራት ሁለት ምርጫ ነው። አንድም ማፈግፈግ አሊያም ለነጻነት እስከ ሞት መዋጋት። እንዋጋለን። የኑክሌር ጦር መሳሪያ የታጠቀ አገር እስከ ፍጻሜው የተዋጋ እንደሆነ ጣጣው ከድንበር ይሻገራል፣ ፍዳው ለዓለም ይተርፋል” የፓኪስታኑ ጠቅላይ ምኒስትር ኢምራን ክኻን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ሕንድን፣ ፕሬዝዳንት ናሬንድራ ሞዲን አጥብቀው በነቀፉበት ዓለምን ካስጠነቀቁበት ንግግራቸው
Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
🔥1
በአፍጋኒስታን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ እየተካሄደ ነው።
የከፋ የደህንነት ስጋት ያለባት ሀገሪቱ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮችን የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱን ሰላማዊነት እንዲያስጠብቁ አሰማርታለች።ሆኖም ድምፅ መስጠት በተጀመረ በአጭር ጊዜያት ውስጥ በካንደሃር በሚገኝ የድምፅ መስጫ ጣቢያ አቅራቢያ ፍንዳታ ተከስቷል።ምርጫው ለሁለት ጊዜ ተራዝሞ ነው ዛሬ እየተካሄደ የሚገኘው። የአሁኑ ፕሬዚዳንት አሽራፍ ጋኒ እና የቀድሞ የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አብዱላህ አብዱላህ ዋነኛ ተፎካካሪዎች ናቸው።37 ሚሊየን ዜጎች ያላት አፍጋኒስታን 10 ሚሊዮኑ ድምፅ ለመስጠት ተመዝግበውባታል።ጥቃት ይደርሳል በሚል ስጋት ድምፅ መስጠት ከሚችሉ ዜጎች መካከል በምርጫው የተመዘገቡት ግማሾቹ ብቻ ናቸው።
ምንጭ፦ ቢቢሲ/Fana
@YeneTube @FikerAssefa
የከፋ የደህንነት ስጋት ያለባት ሀገሪቱ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮችን የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱን ሰላማዊነት እንዲያስጠብቁ አሰማርታለች።ሆኖም ድምፅ መስጠት በተጀመረ በአጭር ጊዜያት ውስጥ በካንደሃር በሚገኝ የድምፅ መስጫ ጣቢያ አቅራቢያ ፍንዳታ ተከስቷል።ምርጫው ለሁለት ጊዜ ተራዝሞ ነው ዛሬ እየተካሄደ የሚገኘው። የአሁኑ ፕሬዚዳንት አሽራፍ ጋኒ እና የቀድሞ የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አብዱላህ አብዱላህ ዋነኛ ተፎካካሪዎች ናቸው።37 ሚሊየን ዜጎች ያላት አፍጋኒስታን 10 ሚሊዮኑ ድምፅ ለመስጠት ተመዝግበውባታል።ጥቃት ይደርሳል በሚል ስጋት ድምፅ መስጠት ከሚችሉ ዜጎች መካከል በምርጫው የተመዘገቡት ግማሾቹ ብቻ ናቸው።
ምንጭ፦ ቢቢሲ/Fana
@YeneTube @FikerAssefa
የጤፍ ቢራ በአሜሪካ ተመረተ ሰኞ ገበያ ላይ እንደሚውል ሰምተናል።
በኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ባለቤትነት በአሜሪካ አገር የተቋቋመው ንጉስ ቢራ ኩባንያ በአሜሪካ ከተመረተ ጤፍ የተዘጋጀ ቢራ ለገበያ አቀረበ። ሰኞ መስከረም 19 ለሚጀምረው ስርጭት 19ሺ 200 ጠርሙስ የጤፍ ቢራ የተዘጋጀ መሆኑ መሆኑን አዲስ ማለዳ ከቢራ ጠማቂው የኩባንያው ቺፍ ፋይናስ ኦፊሰር መኩሪያ ንጉሴ ሰምታለች።
ኩባንያው ቢራው በሚጠመቅበት ቦታ ለተጠቃሚዎች ምርቱን በትኩሱ ለማቅረብ የሚያስችል በመዝናኛ ማዕከል (brew pub)ና የሙዚቃ ኮንሰርት አደራሽ ከፋብሪካው ጀርባ የመግንባት እቅድ እንዳለሁ ገልፀዋል።
Via:- ከማለዳ ጋዜጣ ላይ በየኔቲዩብ የተፃፈ
@YeneTube @Fikerassefa
በኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ባለቤትነት በአሜሪካ አገር የተቋቋመው ንጉስ ቢራ ኩባንያ በአሜሪካ ከተመረተ ጤፍ የተዘጋጀ ቢራ ለገበያ አቀረበ። ሰኞ መስከረም 19 ለሚጀምረው ስርጭት 19ሺ 200 ጠርሙስ የጤፍ ቢራ የተዘጋጀ መሆኑ መሆኑን አዲስ ማለዳ ከቢራ ጠማቂው የኩባንያው ቺፍ ፋይናስ ኦፊሰር መኩሪያ ንጉሴ ሰምታለች።
ኩባንያው ቢራው በሚጠመቅበት ቦታ ለተጠቃሚዎች ምርቱን በትኩሱ ለማቅረብ የሚያስችል በመዝናኛ ማዕከል (brew pub)ና የሙዚቃ ኮንሰርት አደራሽ ከፋብሪካው ጀርባ የመግንባት እቅድ እንዳለሁ ገልፀዋል።
Via:- ከማለዳ ጋዜጣ ላይ በየኔቲዩብ የተፃፈ
@YeneTube @Fikerassefa
በዶሃ የሴቶች ማራቶን 28 ሯጮች አቋርጠው ወጡ!
ትናንት እኩለ ለሊት በኳታር፣ ዶሃ በተጀመረው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የተካሄደው የማራቶን ሩጫ ላይ የተሳተፉ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ሙቀት ምክንያት ማቋረጣቸው ተሰማ። ሩጫውን በበላይነት ኬኒያዊቷ ሩት ቼፔንጌቲች ያሸነፈች ሲሆን፤ ከ68 ተወዳዳሪዎች 28ቱ በሙቀቱ ከባድነት ምክንያት አቋርጠው መውጣታቸው ተዘግቧል።
እኩለ ለሊት ላይ የተደረገውን ይህ የሴቶች የማራቶን ውድድር ካቋረጡ ተወዳዳሪዎች መካከል ኢትዮጵያዊቷ ሩቲ አጋ አንዷ ነች።የውድድሩ አዘጋጆች ከዋናው ውድድር ቀድመው የማራቶን ውድድሩ እንዲካሄድ ያደረጉት የአየር ጠባዩ ለማራቶን ምቹ ላይሆን ይችላል በሚል እንደሆነ ተነግሯል።የሴቶች ማራቶን ሲካሄድ፤ የሙቀት መጠኑ 32 ዲግሪ ሴንቲግሬድ እንደነበር የተገለፀ ሲሆን፤ ወበቁ ደግሞ ከ70 በመቶ በላይ ነበር ተብሏል።የኢትዮጵያ ማራቶን አሰልጣኝ ሀጂ አዲሎ ሮባ፤ የቶኪዮ ማራቶን አሸናፊዋ ሩቲ ነጋን ጨምሮ ሌሎች ሁለት ተወዳዳሪዎች ማቋረጣቸውን ተናግረዋል።
"በአገራችን ማራቶንን በዚህ የአየር ጠባይ መሮጥ የሚታሰብ አይደለም" ካሉ በኋላ "ምን ያህሎቹ እንደሚጨርሱ ለማየት ጓጉቻለሁ" ብለዋል።የ23 ዓመቷ ቼፔንጌቲች ሩጫውን በ2 ሰዓት ከ32 ደቂቃ ከ43 ሰከንድ በማጠናቀቅ ወርቅ ስታገኝ፤ የባህሬን ዜግነት ያላት ሯጭ ሁለተኛ፣ ናሚቢያዊቷ ሯጭ ሦስተኛ በመሆን አጠናቀዋል።ቼፔንጌቲች፤ "በእንዲህ አይነት ፈታኝ ሁኔታ ውስጥ አሸንፋለሁ ብዬ አልጠበቅኩም" በማለት ለፈረንሳዩ የዜና ወኪል ተናግራለች። የብሪታኒያ ፈጣን የማራቶን ሯጭ ቻርሎቴ ፑርዱኤ እና ሌሎች ታዋቂ ሯጮችም አቋርጠው ከወጡት መካከል ናቸው።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ትናንት እኩለ ለሊት በኳታር፣ ዶሃ በተጀመረው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የተካሄደው የማራቶን ሩጫ ላይ የተሳተፉ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ሙቀት ምክንያት ማቋረጣቸው ተሰማ። ሩጫውን በበላይነት ኬኒያዊቷ ሩት ቼፔንጌቲች ያሸነፈች ሲሆን፤ ከ68 ተወዳዳሪዎች 28ቱ በሙቀቱ ከባድነት ምክንያት አቋርጠው መውጣታቸው ተዘግቧል።
እኩለ ለሊት ላይ የተደረገውን ይህ የሴቶች የማራቶን ውድድር ካቋረጡ ተወዳዳሪዎች መካከል ኢትዮጵያዊቷ ሩቲ አጋ አንዷ ነች።የውድድሩ አዘጋጆች ከዋናው ውድድር ቀድመው የማራቶን ውድድሩ እንዲካሄድ ያደረጉት የአየር ጠባዩ ለማራቶን ምቹ ላይሆን ይችላል በሚል እንደሆነ ተነግሯል።የሴቶች ማራቶን ሲካሄድ፤ የሙቀት መጠኑ 32 ዲግሪ ሴንቲግሬድ እንደነበር የተገለፀ ሲሆን፤ ወበቁ ደግሞ ከ70 በመቶ በላይ ነበር ተብሏል።የኢትዮጵያ ማራቶን አሰልጣኝ ሀጂ አዲሎ ሮባ፤ የቶኪዮ ማራቶን አሸናፊዋ ሩቲ ነጋን ጨምሮ ሌሎች ሁለት ተወዳዳሪዎች ማቋረጣቸውን ተናግረዋል።
"በአገራችን ማራቶንን በዚህ የአየር ጠባይ መሮጥ የሚታሰብ አይደለም" ካሉ በኋላ "ምን ያህሎቹ እንደሚጨርሱ ለማየት ጓጉቻለሁ" ብለዋል።የ23 ዓመቷ ቼፔንጌቲች ሩጫውን በ2 ሰዓት ከ32 ደቂቃ ከ43 ሰከንድ በማጠናቀቅ ወርቅ ስታገኝ፤ የባህሬን ዜግነት ያላት ሯጭ ሁለተኛ፣ ናሚቢያዊቷ ሯጭ ሦስተኛ በመሆን አጠናቀዋል።ቼፔንጌቲች፤ "በእንዲህ አይነት ፈታኝ ሁኔታ ውስጥ አሸንፋለሁ ብዬ አልጠበቅኩም" በማለት ለፈረንሳዩ የዜና ወኪል ተናግራለች። የብሪታኒያ ፈጣን የማራቶን ሯጭ ቻርሎቴ ፑርዱኤ እና ሌሎች ታዋቂ ሯጮችም አቋርጠው ከወጡት መካከል ናቸው።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
በዳውሮ ዞን የአተት ምልክት መታየቱን የዞኑ ጤና ቢሮ አስታወቆ የሚከተለውን መልዕክት አስተላልፏል!
በቀን 14/01/2012 ዓ.ም ፣ በቀን 15/01/2012 ሁለት በድምሩ 3 በአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት የተጠቁ ታካሚዎች ወደ ታርጫ ሆስፒታል መግባታቸው ሪፖርት ተደርጎልናል፡፡ ሆኖም መሰል በሽታዎችን ናሙና መመርመር የሚያስችል የመመርመርያ መሳሪያ ዝግጁነት በሆስፒታሉ ባለመኖሩ በቀን 16/01/2012 ዓ.ም ከክልል ጤና ቢሮ ባስመጣነው የአፋጣኝ መመርመርያ መሳሪያ(Rapid test kit) ከታርጫ ዙሪያ ወረዳ ሽና-ጋቡራ ቀበሌ በመጣች ታካሚ ላይ የኮሌራ ባክቴሪያ ተገኝቷል በመሆኑም መላው የዳውሮ ህዝብ በተለይም የታርጫ ዙሪያ ወረዳና የታርጫ ከተማ ነዋርዎች አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንድታደርጉ እንጠቁማለን።
ምንጭ:የዞኑ ጤና ቢሮ
@YeneTube @FikerAssefa
በቀን 14/01/2012 ዓ.ም ፣ በቀን 15/01/2012 ሁለት በድምሩ 3 በአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት የተጠቁ ታካሚዎች ወደ ታርጫ ሆስፒታል መግባታቸው ሪፖርት ተደርጎልናል፡፡ ሆኖም መሰል በሽታዎችን ናሙና መመርመር የሚያስችል የመመርመርያ መሳሪያ ዝግጁነት በሆስፒታሉ ባለመኖሩ በቀን 16/01/2012 ዓ.ም ከክልል ጤና ቢሮ ባስመጣነው የአፋጣኝ መመርመርያ መሳሪያ(Rapid test kit) ከታርጫ ዙሪያ ወረዳ ሽና-ጋቡራ ቀበሌ በመጣች ታካሚ ላይ የኮሌራ ባክቴሪያ ተገኝቷል በመሆኑም መላው የዳውሮ ህዝብ በተለይም የታርጫ ዙሪያ ወረዳና የታርጫ ከተማ ነዋርዎች አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንድታደርጉ እንጠቁማለን።
ምንጭ:የዞኑ ጤና ቢሮ
@YeneTube @FikerAssefa
በኬንያ የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያን በናይሮቢ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ መድኅኒአለም ቤተ ክርስቲያን በመገኘት የመስቀል ደመራ በዓልን በድምቀት አክብረዋል። በቦታውም በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር መለስ አለም ተገኝተው አብረው አክብረዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa