YeneTube
118K subscribers
31.5K photos
485 videos
79 files
3.88K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
MasterCard Foundation አዲስ አበባ ላይ ቢሮውን ሊከፍት እንደሆነ ተሰምቷል ።ለዚህም የሚረዳውን ስምምነት ባለፈው አርብ እንደተፈረመ ከስራ ፈጠራ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

@YeneTube @FikerAssefa
የፍትህ ቀን ማጠቃለያ ፕሮግራም ነገ ይካሄዳል።

“የህግ ተገዢ ነኝ!” በሚል መሪ ቃል ሲከበር የቆየውን የፍትህ ወር ማጠናቀቂያ እና ጳጉሜን 5 ቀን 2011 ዓ.ም የሚከበረውን “የፍትህ ቀን” ምክንያት በማድረግ የፌዴራል የፍትህ አካላት በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበሩ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡በመሆኑም ከዝግጅቶቹ መካከል አንዱ ጳጉሜን 5 ቀን 2011 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ የሚኖረው ማጠቃለያ ፕሮግራም ከ15ሺህ ተሳታፊ በላይ የሚሳተፉበት ዝግጅት ከሰዓት ከ8፡00 ሰዓት ጀምሮ የሚከናዉን ይሆናል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
በቡሪኪናፋሶ በተፈጸሙ ሁለት ጥቃቶች በትንሹ የ29 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

በቡሪኪናፋሶ ሰሜን ሳንማተንኛ ግዛት ተሳፋሪዎችን እና እቃ ጭኖ ሲጎዝ የነበረ ተሸካርካሪ ላይ በትናንትናው ዕለት በተፈጸመ የቦምብ ጥቃት በትንሹ 15 ንጹሃን ዜጎች ሕይወት ሲያለፍ ስድስት ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡በተመሳሳይ ሰዓት በዚሁ አካባቢ 50 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሌሎች 14 ሰዎች በታጠቁ ሃይሎች መገዳለቸው ነው የተነገረው፡፡

ምንጭ፡- ሲጂ ቲ ኤን አፍሪካ/FANA
@YeneTube @FikerAssefa
ሪክ ማቻር ወደ ጁባ አቀኑ!

የቀድሞው የደቡብ ሱዳን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ሪክ ማቻር ከፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ጋር ሊወያዩ ነው።ማቻር ከሳልቫ ኪር ጋር ለሚያደርጉት ውይይትም ዛሬ ወደ ጁባ አቅንተዋል ነው የተባለው።ለሁለት ቀናት በሚኖራቸው ቆይታም ሳልቫ ኪርን ጨምሮ ከሌሎች ተቀናቃኝ ሃይሎች ጋር በተደረሰው የሰላም ስምምነት ተፈጻሚነት ዙሪያ ይወያያሉ ተብሏል።

ምንጭ:Fana
@YeneTube @FikerAssefa
⬆️⬆️⬆️

በ17ኛው የዶሃ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ኢትዮጵያን የሚወክለው የመጨረሻ አትሌቲክስ ቡድን ዝርዝር።

@YeneTube @FikerAssefa
የባህር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ በመጪው መስከረም መጨረሻ ወደ ስራ ይገባል።በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በባህር ዳር ከተማ የሚገኘው የባህር ዳር ቁጥር አንድ ኢንዱስትሪ ፓርክ በመጪው መስከረም መጨረሻ 2012 ወደ ስራ እንደሚገባ ተገለፀ።

@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሚያ ኢንዱስትሪያል ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በወለጋ ዞን የአግሮ ኢንዱስተሪያል ፓርክ ሊገነባ ነው፡፡

አግሮ ኢንዱስትሪያል ፓርኩን ለማስገንባት የቦታ መረጣ እና የአዋጭነት ጥናት ለማከናወን በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ኢንዱስትሪያል ፓርኩ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የግብርናውን ዘርፍ ግብዓቶችን በማቅረብ የሚያግዝ ሲሆን በግብርና ምርቶች ላይ ዕሴት በመጨመር በምግብ ራስን ለመቻል እንዲሁም ለኢኮኖሚያዊ እድገት ትልቅ ሚና እንደሚኖራችው ይጠበቃል፡፡ በተጨማሪም ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል እንደሚፈጥር ይጠበቃል ሲል አስታውቋል፡፡

Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ነባርና አዲስ የመደበኛ ተማሪዎች በሙሉ⬇️

1⃣የነባር የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ምዝገባ ጊዜ መስከረም 5 እና 6 ሲሆን

2⃣የሌሎች ነባር ተማሪዎች መስከረም 21 እስከ 22

3⃣እንዲሁም አዲስ ወደ ዋቻሞ የተመደባችሁ ጥቅምት 28 እና 29 መሆኑን እንገልፃለል።

#ሬጅስተራር
@YeneTube @Fikerassefa
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ነባር ተማሪዎች መግቢያ #መስከረም 20 - 21 መሆኑ አውቃችሁ ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።

የተማሪዎች ህብረት
@YeneTube @Fikerassefa
የእውቅና ፈቃድ (እድሳት) ሪፖርት ባልወጣለት ተቋም መመዝገብ ክልክል መሆኑን ኤጀንሲው አስታወቀ


የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ የ201 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የእውቅና ፈቃድ ሙሉ መረጃ ይፋ አድርጓል፡፡

መረጃው በ2012 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመዝግበው መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች የሚያገለግል ነው፡፡

ይህ ወቅታዊ መረጃ እስከ 2011 ዓ.ም መጨረሻ ያለውን የሚያካትት ሲሆን በሂደት ላይ ያሉትን ተከታትሎ እንደሚያሳውቅ ኤጀንሲው ገልጿል፡፡

ይደርሳል በሚል የእውቅና ፈቃድ ወይም የእውቅና ፈቃድ እድሳት ሪፖርት ባልወጣለት የትምህርት ተቋም ቀድሞ መመዝገብ ክልክል መሆኑንም ኤጀንሲው አስታውቋል፡፡


የተቋማቱን የእውቅና ፈቃድ ሙሉ መረጃ ለመመልከት ተከታዩን ሊንክ ይጫኑ

https://bit.ly/2kCBtWb
በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ አትክልት ተራ አካባቢ አንድ የ20 ዓመት ወጣት ከፖሊስ በተተኮሰ ጥይት መሞቱ ተገለጸ።

የ20 ዓመቱ ታዳጊ ወጣት ጅብሪል አህመድ በአትክልት ተራ አካባቢ የተለያዩ አትክሎትችን በመቸርቸር ስራ ህይወቱን ይመራ እንደነበር ኢትዮ ኤፍ ኤም በአካባቢው ከሚኖሩ ሰዎች አረጋግጧል።እናቱን በቅርቡ በሞት በማጣቱ ምክንያት ታናናሾቹን አንድ ወንድምና እህቱን ከዚሁ ስራ በሚያገኘው ገቢም ያስተዳደር ነበር።

ይሁንና በትናንትናው ዕለት ጧት ላይ ከአንድ ሰው ጋር ግጭት ውስጥ ይገባሉ። በሁለቱ ግገለሰቦች ምክንያት በአካባቢው የነበሩ የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊሶች እንደመጡ በወጣት ጅብሪል አህመድ ላይ ሶስት ጥይት ተኩሰው እንደገደሉት የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል።

ወጣት ጅብሪል ወዲያውኑ ወደ አቤት ሆስፒታል ቢወሰድም ህይወቱን ማትረፍ አልተቻለም።የሟች አስከሬንም ዛሬ ለአካባቢው ነዋሪዎች በመሰጠቱ ስርዓተ ቀብሩ በኮልፌ ሙስሊም መቃብር አካባቢ ተፈጽሟል።ፖሊስ ጉዳዩን በሚገባ ሳያጣራ ጥይት መተኮሱም በተለይም በስፍራው የነበሩ ሰዎችን አስቆጥቷል።

ነዋሪዎቹ እንዳሉት ፖሊስ ጉዳዩን ሳያጣራ ነው ልጁ ላይ የተኮሰበት፣ መንግስት ጉዳዩን አጣርቶ በህግ ተጠያቂ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል። በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር ፋሲካ ፋንታ በጉዳዩ ዙሪያ መልስ እንዲሰጡን ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም ምላሽ ሊሰጡን አልቻሉም።

Via :- Ethio FM
@YeneTube @Fikerassefa
Wollega University Corporate Communications

#OFFICIAL_Announcement .
Simannaan barattoota yuunivarsiitii Wallaggaa ifoomeera.
Barattoota buleeyyii fulbaana 19-20/2012
Barattoota haaraa Ful.26-27/2012 ta'uusaa akka bartan isin beeksifna.


Dates of Registration for senior and newly assigned Students has been decided the University's Senate ,accordingly :-

Registration Date for Senior Students will be from Septemeber 19 upto 20/2012 E.C .

Regsitration Date for Newly Assigned students Will be from September 26 up to 27/2012 E.C.

Further annocement will be made in the future by using different Media Outlets . Corporate Communications Directorate .

ማስታወቂያ ለወለጋ ዩኒቨርሲቲ ነባርና አዲስ ገቢ ተማሪዎች በሙሉ።

የ2012 የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ነባርና አዲስ ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት በዩኒቨርሲቲው አስተዳደር እንደሚከተለው ተወስኗል።
በዚሁ መሠረት :-

የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከመስከረም
19-20/2012 ዓ.ም እንዲሆን ተወስኗል።

የአዲስ ገቢ ተማሪዎች ምዝገባ ከመስከረም 26-27/2012 ዓ.ም እንዲሆን ተወስኗል።
@YeneTube @Fikerassefa
የኦሮሚያ አባ ገዳዎች ህብረት የ2012 የኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለአንድ የእርቅ ሳምንት አወጀ።

የእርቅ ሳምንቱ ከመስከረም 9 እስከ መስከረም 22 2012 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ መሆኑንም የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል።

@YeneTube @FikerAssefa
ትላንት ማታ ሲነድ ያደረው የአቃቂ ገበያ አሁን ላይ ያለሁ ገፅታ በፎቶ 📸 amir
@Yenetube @Fikerassefa
ከ7 ሚሊየን በላይ የኢትዮጵያ ብር እና 53 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ተያዘ።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከ7 ነጥብ 6 ሚሊየን በላይ የኢትዮጵያ ብር እና 53 ሺህ የአሜሪካ ዶላር መያዙን አስታወቀ፡፡ኮሚሽኑ ገንዘቡን የውጭ ሃገራት ገንዘቦችን በህገ ወጥ መንገድ ሲመነዝሩ ከነበሩ ግለሰቦች ላይ መያዙንም አስታውቋል።

ምንጭ: ፋና
@YeneTube @FikerAssefa
የገቢዎች ሚኒስቴርና የጉምሩክ ኮሚሽን አዲሱን አመት ምክንያት በማድረግ ከ207 ሚሊየን ብር በላይ ዋጋ ያላቸዉ ቁሳቁሶችን ለገሰ፡፡

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና የጉምሩክ ኮሚሽን በዛሬዉ ዕለት የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጣቸዉ ለሚገኙ ተፈናቃይ ወገን ተማሪዎች፤ ከአ/አ፤አዳማ፤ሃዋሳ፤ከተሞች ጎዳና ተነስተዉ በማዕከላት ለሚገኙ ወገኖች፤ጠያቂ ቤተሰብ ለሌላቸዉ የህግ ታራሚዎች፤ በበጎ አድራጎት ድርጅቶች ለሚረዱ አረጋዊን፤ ህፃናት፤ አካል ጉዳተኞችና ለነድያን፤ ለጀግኖች አርበኞች ማህበራት፤ንብረታቸዉ በእሳት አደጋ ለወደመባቸዉ የአገር መከላከያ አባላት በበጎ አድራጎት ድርጅቶቹ በኩል እንዲደርሳቸዉ ነዉ ስጦታዉን ያበረከተዉ፡፡

ስጦታዉን ለበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ያስረከቡት የገቢዎች ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ባስተላለፉት መልዕክት በ211 በጀት አመት ኮንትሮባንድንና ህገ ወጥነትን ለመከላከል ሰራተኞቻችንና የፀጥታ አካላት ህይወት ማጣትና የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸዉ አንስተዋል፡፡ 2011 ኮንትሮባንድን ከመከላከልና መቆጣጠር አንፃር የተመዘገበዉ ዉጤት የህዝብ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተሳትፎ የታየበት ነዉ ብለዋል፡፡

ዛሬ የተደረገዉ ድጋፍ ዜጎቻችን በዚሁ መንገድ መርዳት ብቻ ሳይሆን በዘላቂነት ፍትሃዊ ተጠቃሚ የሚሆኑበት ስራ በመስራት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸዉን ድርሻ ሊወጡ እንደሚገባ አንስተዋል፡፡ድጋፍ የተደረገላቸዉ አካላት በበኩላቸዉ ስነ ምግባሩ የተስተካከለ ትዉልድ ተቀርፆ ኮንትሮባንድና ህገ ወጥ ንግድ እንዲወገድ የበኩላቸዉን አስተዋፅኦ እንደሚወጡ ገልፀዋል፡፡

Via Ministry of Revenue
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
በአማራ ክልል ለ4 ሺህ 329 ታራሚዎች ይቅርታ ተደረገ ።

የአማራ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ለታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን የክልሉ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ገለጸ።የአማራ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አቶ ገረመው ገብረጻዲቅ ለአብመድ እንደገለጹት፥ የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት ዛሬ 5ኛ ዙር፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፣ 3ኛ አስቸኳይ ስብሰባውን አካሂዷል። በስብሰባውም የ2012 ዓ.ም የዘመን መለወጫን ምክንያት በማድረግ በክልሉ መንግስት ይቅርታ እንዲደረግላቸው በክልሉ ይቅርታ ቦርድ የቀረበለትን የይቅርታ ጥያቄ የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ ውሳኔ አስተላልፏል።

በዚህም የይቅርታ አሰጣጥ መስፈርቱን ያሟሉ 4 ሺህ 329 ታራሚዎች በይቅርታ እንዲፈቱ ውሳኔ ማሳለፉን ጠቅላይ ዐቃቤ ህጉ ገልጸዋል።ይቅርታ ከተደረገላቸው ውስጥ 90ዎቹ ሴቶች መሆናቸውም ታውቋል።በሌላ በኩል ቀደም ሲል ከእስር እንዲፈቱ ውሳኔ ተላልፎላቸው እያለ ሌላ ወንጀል በመፈጸማቸው የተፈረደባቸው እና ማረሚያ ቤት የገቡ አምስት ታራሚዎች ተሰጥቷቸው የነበረው ይቅርታ ተሰርዞ ቀሪ የእስራት ጊዜያቸውን እንዲፈጽሙ ተወስኗል።

ምንጭ: አብመድ
@YeneTube @FikerAssefa
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ለትምህርት ፈላጊዎች ያወጣው ማስታወቂያ!!

@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
HAPPY NEW YEAR!
RJ SHOES presents to you all the latest,variety and catchy brand shoes.
We have all kind of shoes for adults and kids with a fairly affordable price.
👉Adress:-Addis ababa(Gerji mebrat haile)
👉Phone:-+251900628132
:-+251911859997
👉We have a 2 days return policy.
👉Flexible Shoe order with Customers Desire.
👉Delivery to Regional distincts
👉We Are Trustworthy and Best suited for Customers wish.
To Join us on telegram click here👇👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAE3CCBtJE8NBy8ZShA