YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
483 videos
79 files
3.85K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
YeneTube
የፌደራል ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኤጀንሲ የ2011 የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ተቋማት #መቀበያ ነጥብ ይፋ አድርጓል። @yenetube @mycase27
ኤጀንሲው የቴክኒክና ሙያ ተቋማት መቀበያ ነጥብ #ይፋ አደረገ

የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኤጀንሲ በ2011 ወደ ቴክኒክና ሙያ ተቋማት መግቢያ ነጥብን ይፋ #አድርጓል፡፡

ኤጀንሲው ዛሬ እንዳስታወቀው በየዓመቱ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት #መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተፈታኞች መካከል የሥራ ገበያውን መሰረት በማድረግ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት መቀበያ መስፈርት ተመርኩዞ የመቁረጫ ነጥቡን ይፋ እንዳደረገ አመልክቷል፡፡

በዚህም መሰረት በ2010 የትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱት መካከል 725 ሺህ 652 የሚሆኑት ወደ ቴክኒክና ሙያ ተቋማት በመደበኛው ዘርፍ እንደሚገቡ ኤጀንሲው አመልክቷል፡፡

ከዚህም ውስጥ 230 ሺህ 828 ሴቶች ናቸው፡፡ በመምህራን ኮሌጅ እንዲሁም በፖሊስና መከላከያ ማሰልጠኛ ተቋማት የሚገቡት ቁጥር በዚህ መግለጫ አለመካተቱም ተመልክቷል፡፡

ምንጭ፡የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኤጀንሲ
@yenetube @mycase27
#የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች የመግቢያ ቀን ይፋ #አደረገ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የትምህርት ሚኒስቴር የሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች የቅበላ ጊዜ ይፋ #አድርጓል

ሚኒስቴሩ የተማሪዎች የቅበላ ጊዜ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን እና የመቀበያ ጊዜውንም ወደፊት #እንደሚያሳውቅ መግለጹ ይታወሳል።

በዚህም መሰረት የትምሀረት ሚኒስቴር በዛሬው እለት የሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች የቅበላ ጊዜ ይፋ ያደረገ ሲሆን፥ ተማሪዎች በተጠቀሱት ቀናት ብቻ በዩኒቨርስቲዎቹ በመገኘት እንዲመዘገቡና ትምህርት እንድትጀምሩ አስታውቋል።

ተማሪዎች ወደ #ተመደቡበት ተቋማት ሲሄዱም ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ ትራስ ጨርቅና የስፖርት ትጥቅ አማልተው እንዲጓዙም ጠቁሟል።

©fbc
@yenetube @mycase27