YeneTube
117K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
ግብፅ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር ባላት ውዝግብ የውሃ መብቷን እንደማትተው አስታወቀች!

የግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ አል ሲሲ በአባይ ወንዝ ላይ የሚደረጉ ማናቸውንም የተናጠል እርምጃዎችን እንደሚቃወሙ በመግለጽ፣ ግብፅ የውሃ መብቷን ችላ ትላለች ብሎ የሚያስብ ማንኛውም አካል "ተሳስቷል" ሲሉ አስታውቀዋል።

ሲሲ ከዩጋንዳ አቻቸው ዩዌሪ ሙሴቬኒ ጋር በመሆን በካይሮ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ከናይል ገባር ወንዞች የሚገኘው ዓመታዊ የውሃ ፍሰት 1,600 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ሲሆን አብዛኛው በደን፣ ረግረጋማ ቦታዎች፣ በትነት እና የከርሰ ምድር ውሃ አማካኝነት ይጠፋል ብለዋል።

አክለውም “ወደ ናይል የሚደርሰው አነስተኛ መጠን ያለው ውሃ ነው፤ ግብፅና ሱዳን በድምሩ 85 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የሚጠጋ ውሃ ይደርሳቸዋል ይህም ከጠቅላላው 4 በመቶው ብቻ ነው” ብለዋል።

የግብፁ መሪ ሀገራቸው አማራጭ የውሃ ሀብት እንደሌላት እና የምታገኘው የዝናብ መጠንም አነስተኛ መሆኑን ጠቅሰው ለግብፅ ይህንን የውሃ ድርሻ መተው “ሕይወቷን እንደመተው ይቆጠራል” ሲሉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

ግብፅ የናይል ወንዝ ለእህት ሀገራት በግብርና፣ በኤሌክትሪክ ምርት ወይም በአጠቃላይ ልማት ላይ የሚኖረውን ጥቅም እንደምትቀበል የገለጹት አል ሲሲ “ይህ ግን ለግብፅ የሚደርሰውን የውሃ መጠን መቀነስ የለበትም” ብለዋል።

ፕሬዝዳንቱ የናይል ውሃ ጉዳይን ከግብፅ ጋር ያልተገናኙ ዓላማዎችን በሀገሪቱ ላይ ለማራመድ የታሰበ ሰፊ ግፊት የመድረግ ዘመቻ አካል አድርጎ አቅርቦታል።

Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
28👎18😁9
በኢትዮጵያ "የዘፈቀደ ግድያዎች" እና "ኢ-ሰብአዊ ቅጣቶች" ቀጥለዋል
-የአሜሪካ መንግስት

የኢትዮጵያ መንግሥት ኃይሎች እና ታጣቂዎች በዜጎች ላይ "ከህግ ውጪ የሆኑ ግድያዎችን" መፈጸማቸውን የሚያሳዩ "ታማኝ መረጃዎች" መኖራቸውን የአሜሪካ መንግሥት ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ትግበራ ሪፖርት አመለከተ።ሪፖርቱ፤ መንግስት በጸጥታ ኦፕሬሽኖች ወቅት "ስቅይት" መፈጸሙን እና በባለስልጣናት ላይ "ተጠያቂነት" ማስፈን አለመቻሉን መረጃዎች እንደሚያመለክቱም ገልጿል።

በዜጎች ላይ ተፈጽመዋል በሚል ከጠቀሱት የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች መካከል የግሰለቦች "ስወራ"፣ "ስቅይት" እና "ኢሰብአዊ" ቅጣቶችን ይገኙበታል።የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ200 በላይ ሀገራትን እና ግዛቶችን በተመለከተ በየዓመቱ የሚያወጣው ይህ ሪፖርት ይፋ የተደረገው ማክሰኞ ነሐሴ 6/2017 ዓ.ም. ነው።

ሪፖርቱ፤ በአውሮፓውያኑ 2024 የነበረውን የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ የሚዳስስ ነው። የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይህንን ሪፖርት የሚያጠናቅረው እንደ የሰብአዊ መብት ተቋማት ሪፖርቶች እና መገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች ያሉ "ታማኝ" የመረጃ ምንጮች በመጠቀም ነው።ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት ውስጥ በአማራ፣ ኦሮሚያ እና ትግራይ ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ውስጥ "በርካታ ከህግ እና ከፍርድ ውጪ የሆኑ ግድያዎች" መፈጸማቸውን ሪፖርቱ ያስረዳል።

በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች እነዚህ ግድያዎች የተፈጸሙት "በግጭት አውድ" ውስጥ መሆኑን መረጃዎች እንደሚያመለክቱም ጠቅሷል።በዋንኛነት በአማራ ክልል ተጥሎ የነበረውን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የዚህ አዋጅ ተግባራዊነት ቢያበቃም "በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች [የሚፈጸሙ] በደሎች ቀጥለዋል" ብሏል። ሪፖርቱ፤ በሁለቱ ክልሎች "የተስፋፋ ህገ ወጥ የንጹሃን እና ባለስልጣናት ግድያ" መስተዋሉን የገለጸ ሲሆን "የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት እና የአማራ ፋኖ ታጣቂዎችም" እነዚህን ድርጊቶች ከፈጸሙት መካከል መሆናቸውን አስረድቷል።

በትግራይ ክልልም "የንጹሃንን ግድያን ጨምሮ ከህግ ውጪ ግድያዎች" መስተዋሉን ያሰፈረው ሪፖርቱ እነዚህ ድርጊቶች "በኤርትራ መከላከያ ሠራዊት እና የክልሉ ታጣቂዎች" የተፈጸሙ መሆናቸውን መረጃዎች እንደሚያመለክቱ ገልጿል።በተጨማሪም በምዕራብ ትግራይ "የተስፋፋ የንጹሃን ግድያ፣ የጅምላ ግዳጅ መፈናቀል፣ የዘር ማጽዳት፣ መድፈር" መፈጸማቸውን ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱ ጠቅሷል። ሪፖርቱ፤ መረጃዎችን በመጥቀስ "የአማራ ታጣቂዎች እና ግንኙነት ያላቸው ቡድኖችን" ተጠያቂ አድርጓል።

የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ተቋማት እና የመገናኛ ብዙሃን መረጃዎችን በመጥቀስም፤ መንግሥት በሚያከናውናቸው "የጸጥታ ኦፕሬሽኖች" ወቅት "ስቅይት ውስጥ ተሳትፏል" ሲል ከስሷል።ተመሳሳይ ምንጮች በመጥቀስም "የዘፈቀደ ወይም ህገወጥ ግድያ፣ ስወራ፣ ስቅይት ወይም የጭካኔ ተግባር፣ ኢሰብአዊ ወይም አዋራጅ አያያዞች ወይም ቅጣቶች" መፈጸማቸውን በሪፖርቱ አስፍሯል።

ሪፖርቱ፤ "ስቅይት በመፈጸም የሚከሰሱ የመንግሥት አካላትን ተጠያቂ ለማድረግ አለመቻሉን" መረጃዎች እንደሚያሳዩ በመጥቀስም ወቅሷል። መንግሥት የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የፈጸሙ "ባለስልጣናትን ለመለየት እና ለመቅጣት የወሰደው እርምጃ የተገደበ" እንደሆነም በሪፖርቱ ተካትቷል።መንግሥት "ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ያሉ የተወሰኑ ባለስልጣናት እንደተከሰሱ" መግለጹን ያስታወሰው ሪፖርቱ፤ እነዚህ እርምጃዎች በተመለከተ ያለው ዝርዝር መረጃ ትንሽ መሆኑን አስፍሯል።

[ቢቢሲ]
@YeneTube @FikerAssefa
33👍14🔥2😭1
👍3
YeneTube
Photo
የ1 ዓመት ከ8 ወር እድሜ ያለውን ሕጻን በማገት ሁለት ሚሊዮን ብር የጠየቁ አራት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ!

በአዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው አፍሪካ ሕብረት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ፤ የአንድ ዓመት ከስምንት ወር እድሜ ያለውን ሕጻን በማገት ሁለት ሚሊዮን ብር የጠየቁ እና በወንጀሉ ተባብረዋል የተባሉ አራት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ፋኑኤል ብርሃነ የተባለን የ1 ዓመት ከ8 ወር ዕድሜ ያለውን ሕጻን ሐምሌ 30 ቀን 20017 ዓ.ም በግምት ከምሽቱ 1 ሰዓት ከ40 ገደማ ከመኖሪያ ቤቱ በሥውር በመውሰድ ወደ ወላጅ አባቱ ስልክ መደወላቸው ተገልጿል፡፡ለአባቱ ሕጻኑን እንዳገቱት በመግለፅ እና ሁለት ሚሊዮን ብር በአካውንት ገቢ እንዲያደርጉ በመጠየቅ በቤተሰብ ላይ ጭንቀትና ድንጋጤን ፈጥረዋል፡፡

አቶ ብርሃነ ገ/ፃዲቅ የተባሉት የሕጻኑ ወላጅ አባትም ስለ ሁኔታው በአቅራቢያቸው ለሚገኝ ፖሊስ በወቅቱ አሳውቀዋል።የሕጻኑ መጥፋት ሪፖርት የደረሰው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የቄራ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የምርመራ እና የክትትል ክፍሉ ተቀናጅተው በተደረገ ከፍተኛ ጥረት፤ ካህሳይ ተክላይ የተባለውን እና ከሕጻኑ ወላጅ አባት ጋር ዝምድና ያለውን ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ፖሊስ ገልጿል፡፡

የወንጀሉ አቀነባባሪ ነው ተብሎ ተጠርጥሮ በተያዘው በካህሳይ ተክላይ ላይ በተከናወነ ምርመራ የማስፋት ሥራ በሕጻኑ እገታ ከሚገኝ ገንዘብ የጥቅም ተካፋይ ለመሆን በመስማማት፤ ወንጀሉን የተባበሩ ፊሊሞን ገ/ማርያም፣ ተክሊት ህሉፍ እና ምህረት ዕድሉ የተባሉ ተጨማሪ ሦስት ተጠርጣሪዎችም በቁጥጥር ሥር መዋላቸውም ተነግሯል፡፡

እነዚህ ተጠርጣሪዎች የተያዙት ወንጀሉ በተፈፀመ በማግሥቱ ሳሪስ አካባቢ በሚገኘው ማራኪ በተባለ ሆቴል ውስጥ አልጋ ክፍል በመከራየት ሕጻኑን ይዘው በተሸሸጉበት ወቅት ፖሊስ ባደረገው ክትትል ነው ተብሏል፡፡ በአጠቃላይ በወንጀሉ የተጠረጠሩት አራት ግለሰቦች በአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝም ፖሊስ አስታውቋል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
52🔥1😭1
Forwarded from YeneTube
ናቲ  ስፒች ላንጉጅ ቴራፒ ኪሊኒክ
Nati Speech language therapy clinic

ከእርስዎ ወይም ከቤተሰብዎ ከንግግር ጋር በተያያዘ ችግር ያለበት ሰው ያውቃሉ?

እንግዲያውስ ናቲ የንግግር የቋንቋ ሕክምና እና ማማከር ክሊኒክ ለእርስዎ የሚሆን መፍትሔ ይዞልዎት መጥቷል ከንግግር ከቋንቋ እንዲሁም ከተግባቦት ጋር በተያያዘ ህክምና ወይም ስልጠና ከፈለጉ ወደ ናቲ የንግግርና የቋንቋ ሕክምና እና ማማከር ክሊኒክ ይምጡ ወይንም ይደውሉ እፎይ የሚሉበትን ምላሽ ያገኛሉ

“አለመናገር ጨዋነት አይደለም እክል እንጂ”

👉አድራሻ፡ መገናኛ ሾላ አባይ ባንክ የካ ሚካኤል ቅርንጫፍ ያለበት ህንጻ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 205
ከመምጣትዎ በፊት ደውለው ቀጠሮ ያስይዙ

☎️ስልክ፡- 09- 08- 78- 26 -52  


  👉በተጨማሪም በነዚህ አማራጮች ያገኙናል
👉የቴሌግራም ገጽ ፡- https://tttttt.me/Nslt19

 👉የቲክቶክ ገጽ፡-https://vm.tiktok.com/ZM69FtgrR/
👉  የፌስቡክ ገጽ፡-https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
👉በ YouTube ገፅ:-https://youtube.com/@natigetnet1989?si=_81wKG_5Ev45AZvY

👂👂በነፃ

የከንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ ህክምና  በየትኛውም ክልል ለሚኖሩ በነፃ
9
Forwarded from YeneTube
በሩን ይክፈቱ ችግረወን
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋት የግል አልሚዎች እንዲሳተፉ የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ መገባቱ ተገለጸ

በዘርፉ ያለውን የኃይል ስብጥር ለማሳደግና የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋት የግል አልሚዎች እንዲሳተፉ የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ መገባቱን የኢትዮጲያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል፡፡

በየዓመቱ የሀገሪቱ የኃይል ፍላጎት በአስር በመቶ እያደገ መሆኑን ያነሱት የተቋሙ የትራንስሚሽን እና ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዷለም ሲዓን፤ ከታሪፍ ማሻሽያው ጎን ለጎን የግል አልሚዎች እንዲሳተፉ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ይሁን እንጂ በሀገሪቱ ያለው ዝቅተኛ የኤሌክትሪክ የታሪፍ ምጣኔ የግል አልሚዎችን የሚያበረታታ ባለመሆኑ እስከ አሁን የሚፈለገው ውጤት አለመገኘቱ ተገልጿል፡፡

ከአሁን ቀደም ተቋሙ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወስዶት የነበረውና በተቋሙ የፋይናንስ ቁመና ላይ ከፍተኛ ጫና ፈጥሮ የቆየውን ብድር መንግሥት ወደ ራሱ መውሰዱም ተነስቷል፡፡

ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ተቋሙ የመክፈል አቅሙንና ገቢውን ያገናዘበ ብድር ከባንኩ በመውሰድ ፕሮጀክቶችን በራሱ አቅም ለማስፈፀም እየሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡

@Yenetube @Fikerassefa
12
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይና ጋር የነበረውን የንግድ እገዳ ለተጨማሪ 90 ቀናት አራዘሙ

ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ፕላትፎርማቸው ላይ የእገዳውን ማራዘሚያ የሚያዝዘውን የስራ አስፈፃሚ ትዕዛዝ መፈረማቸውን የገለፁ ሲሆን "የስምምነቱ ሌሎች አካላት በሙሉ እንደነበሩ ይቀጥላሉ" ብለዋል። የቻይና ንግድ ሚኒስቴር በበ
ኩሉ ቀረጥ የማቆም ውሳኔው መራዘሙን በተመሳሳይ ጊዜ አስታውቋል።

ማስታወቂያው ከዚህ ቀደም የተሰጠው ጊዜ ከማብቃቱ ጥቂት ሰዓታት በፊት ነው የወጣው።

ይህ ባይሆን ኖሮ ዩናይትድ ስቴትስ በቻይና ምርቶች ላይ ቀድሞውንም ከፍ ያለውን 30% ቀረጥ ልታሳድግ ትችል ነበር፣ ቻይናም በበኩሏ ዩናይትድ ስቴትስ ወደ ቻይና የምትልካቸውን ምርቶች ላይ አፀፋዊ ቀረጥ በመጨመር ምላሽ ልትሰጥ ትችል ነበር ተብሏል።

ይህ እረፍት ሁለቱ ሀገራት ልዩነቶቻቸውን እንዲፈቱ ጊዜ የሚሰጥ ሲሆን ምናልባትም በዚህ አመት መጨረሻ ላይ ትራምፕ እና የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ መካከል ለሚደረግ ጉባኤ መንገድ ሊከፍት ይችላል።

ትራምፕ ሚያዝያ ወር ላይ ቀረጥ መጣል ከጀመሩ በኋላ ቻይና ለአንዳንድ የአሜሪካ ኩባንያዎች የሚውሉ ድርብ ጥቅም ያላቸውን እቃዎች ወደ ውጭ መላክን የገደበች ሲሆን ሌሎችን ደግሞ ወደ ቻይና እንዳይገቡ ወይም ኢንቨስት እንዳያደርጉ ከልክላለች።

በግንቦት ወር በጄኔቫ በተደረገ ስብሰባ ወደ ኋላ ለማፈግፈግ እና መነጋገራቸውን ለመቀጠል ተስማምተዋል፡ የአሜሪካ ቀረጥ ወደ 30 በመቶ ከፍ ያለ ሲሆን የቻይና ደግሞ ወደ 10 በመቶ ዝቅ ብሏል። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ድርድሮች ቀጥለዋል ሲል የዘገበው አፍሪካ ኒውስ ነው።

@Yenetube @Fikerassefa
20👎4😁1👀1
በአፋር ክልል 2 ነጥብ 8 ሚሊየን ዓመት ዕድሜ ያለው የሰው ቅሪተ አካል ተገኘ!

በአፋር ክልል "ሌዲ ገራሩ" በተባለው የጥናት ቦታ 2.8 ሚሊዮን ዓመት ዕድሜ ያለው የአዲስ የአውስትራሎፒቴከስ እና የሆሞ ዝርያዎች ቅሪተ አካላት ተገኘ።የአሪዞና ስቴት ዩኒቨርስቲ የሳይንቲስቶች እና የተመራማሪዎች ቡድን 13 ጥርሶችን በማግኘት በሰው ልጅ ዝግመተ ለውጥ ሂደት ያልተጠናውን ጊዜ ለመረዳት የሚረዱ መረጃዎች መሰብሰባቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።

ጥርሶቹ የተገኙት ከዚህ በፊት የሰው ልጅ ቅሪተ አካል በተገኘበት አከባቢ ሲሆን የቅሪተ አካል አጥንቶቹ ሙሉ ስላልሆኑ በእነዚህ 13 ጥርሶች የተወከሉት የአውስትራሎፒቲከስ እና የሆሞ ዝርያዎች ስያሜ ገና እንዳልተሰጣቸው ተገልጿል።

በኔቫዳ ዩኒቨርሲቲ የፓሊዮአንትሮፖሎጂስት እና ረቡዕ ዕለት በኔቸር ዕትም ላይ የወጣው የምርምር ስራ መሪ የሆኑት ብራያን ቪልሞር “ይህ የሰው ልጅ የዝግመተ ለውጥ ታሪክ ቀስ በቀስ እየተለዋወጠ የመጣ የአንድ ዝርያ ታሪክ ብቻ አለመሆኑን ያረጋግጣል” ብለዋል።

ቪልሞር አክለውም “ይልቁንም የሰው ልጅ የዝግመተ ለውጥ ሂደት ልክ እንደሌሎች ህይወት ያላቸው ነገሮች ነው፤ በተለያዩ ጊዜያት ብዙ ዝርያዎች ያሉት እና አብዛኛዎቹም በተመሳሳይ ጊዜ ይኖሩ ነበር” ብለዋል።

Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
😁2928👎5👍2🔥1
ኢትዮጵያ የተቀበሩ ፀረ ሰው ፈንጂዎችን ለማስወገድ የጊዜ ገደቡ ለአራተኛ ጊዜ እንዲራዘምላት ጥያቄ አቀረበች!

 በጄኔቫ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ጽሕፈት ቤት፣ በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች በጦርነት ወቅት ተቀብረው የቀሩ የፀረ ሰው ፈንጂ ቅሪቶችን ለማስወገድ የተቀመጠው የጊዜ ገደብ ለአራተኛ ጊዜ እንዲራዘም ጥያቄ አቀረበ፡፡

እ.ኤ.አ. በ2004 ኢትዮጵያ ያፀደቀችውና የኦታዋ ስምምነት በመባል የሚታወቀውን እ.ኤ.አ. በ1997 የፀደቀውን የፀረ ሰው ፈንጂዎች ጥቅም፣ ምርት፣ ግብይትና ክምችትን ለማስወገድና ለማገድ የወጣ ስምምነት መፈረሟ ይታወሳል፡፡

ኢትዮጵያ በስምምነቱ አንቀጽ 5 መሠረት በየትኛውም የአገሪቱ አካባቢዎች ያሉ ፀረ ሰው ፈንጂዎችን ማስወገድ፣ ወይም መወገዳቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ዕርምጃዎችን የመውሰድ ግዴታ እንዳለባት ተደንግጓል፡፡

https://ethiopianreporter.com/144396/

@YeneTube @FikerAssefa
19👍4
ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለ2017 ሀገራዊ የመጅሊስ ምርጫ ከ13 ሚሊዮን በላይ ሙስሊሞች ምዝገባ ማድረጋቸውን አስታወቀ!

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የ2017 ምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ሀገራዊ የመጅሊስ ምርጫ ምዝገባ ለማጠናቀቅ እና የምርጫ ኩነቶች ዝግጅትን በተመለከተ በዛሬው ዕለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

በመግለጫውም ምርጫውን በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ ላለፉት አምስት ወራት የቅድመ ዝግጅት ሲደረግ እንደነበረና በተለያዩ ክልሎች በሚገኙ በኡለማዎች፣ በምሁራን፣ በወጣቶች፣ በሴቶች እና በሥራ ማህበረሰቦች፤ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበረ የምርጫ አስፈጻሚ ቦርዱ ሰብሳቢ ዶ/ር አብዱልአዚዝ ኢብራሂም ገልጸዋል።

በአጠቃላይ ለምርጫው ይመዘገባል ተብሎ የተጠበቀው በተለይም ዕድሜው ከ18 በላይ የሆነ እንዲሁም በዕድሜ በመለየት እና ወቅቱ ክረምት ከመሆን እና ማህበረሰቡ በምርጫ ዙሪያ ያለውን ሁኔታ መረዳት እጥረትን ጨምሮ ከ8 እስከ 10 ሚሊዮን ሕዝብ እንደነበረ አንስተዋል።

ነገር ግን በ2017 በሚካሄደው የመጅሊስ ምርጫ በአጠቃላይ 13 ሚሊዮን 151 ሺሕ 889 ሕዝብ ተመዝግቦ፤ ለምርጫ ራሱን ዝግጁ ማድረጉን ሰብሳቢው ለአሐዱ ተናግረዋል።በዚህም መሠረት ከትግራይ ክልል ውጪ በሁሉም ክልሎች ላይ ምርጫው እንደሚካሄድ ገልጸው፤ የትግራይ ክልል ምርጫ ባለው የሰላም አለመረጋጋት ምክንያት በክልሉና በክልሉ የምርጫ ቦርድ ጥያቄ መሠረት ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን አስታውቀዋል።

ከ60 ሺሕ በላይ መስጅዶችን ለምዝገባ ሲጠቀሙባቸው እንደነበረ ገልጸው፤ ከእነዚህ ውስጥ 49 ሺሕ 92 መስጂዶች ምርጫ እንደሚከናወንባቸው ገልጸዋል።ምርጫው በግልጸኝነት፣ በፍትሐዊነት፣ በአካታችነትና በአሳታፊነት ለማሳካት ስፊ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት ቴክኖሎጂን ጭምር በመጠቀም ሲሰራበት ስለመቆየቱ ተናግረዋል።

ምርጫውን ለማስፈጸም ከተቋቋመው የምርጫ አስፈጻሚ አካላት እንደየእርከናቸው በአጠቃላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ 155 ሺሕ 101 ያህል ሰዎች በተለያየ ጊዜ በተለያዩ ደረጃ ስልጠና መውሰዳቸውንም አክለዋል።"ፍትሐዊነትን ከማስፈን አንፃርም በመቶዎች ከሚቆጠሩ አቤቱታ አቅራቢዎች ጋር ውይይቶች ተደርገው መቀራረብና መረዳዳት ተችሏል" ብለዋል።

በመሆኑም "ምርጫው ነገ ነሐሴ 9 ቀን 2017 ከጁምአ ሰላት በኋላ በመላ ሀገሪቱ ተጀምሮ እንደየ አካባቢው ሁኔታ እስከ እሁድ ነሐሴ 11 ቀን 2017 ድረስ የመስጂድ ደረጃ ምርጫ ይካሄዳል" ብለዋል።

ከዚያ በመቀጠልም የወረዳ ምክር ቤት፣ የዞን ምክር ቤት፣ የየክልል ምክር ቤቶች እና የፌደራል መጅሊስ ምክር ቤት ከነሐሴ 11 2017 ጀምሮ እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2017 ባሉት ጊዜያት ውስጥ እንደየ ክልሉ ተጨባጭ ሁኔታ ተካሄዶ፤ ነሐሴ 30 ቀን 2017 እንደሚጠናቀቅ አስታውቀዋል።

መላው ሙስሊም ማህበረሰብ ቀደም ሲል በምዝገባ ያሳየውን ፍቃደኝነት እና ተነሳሽነት አሁንም የምርጫ ግብ የሆነውን መሪዎቹን መምረጥ፣ ሁሉም በነቂስ ወጥቶ እንደየ ማህበረሰብ ክፍሉ ዑለማዕ፣ ምሁሩ፣ ወጣቱ፣ ሴቱ እና የሥራ ማህበረሰብ በየ መስጂዱ ወጥቶ መሪዎቹን እንዲመርጥ የምርጫ አስፈጻሚ ቦርዱ ሰብሳቢ ዶ/ር አብዱልአዚዝ ኢብራሂም ጥሪ አስተላልፈዋል።

Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
31👎10👍2🔥1
በቲክቶክ ስሙ ዳልቻ በመባል የሚይታወቀው ሰው በህግ ቁጥጥር ውስጥ መዋሉ ታውቋል ::
@Yenetube @Fikerassefa
👍114😁2711👎4
Forwarded from YeneTube
በሩን ይክፈቱ ችግረወን
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
3
የአሜሪካ ሴናተር ቴድ ክሩዝ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለሶማሊላንድ እውቅና እንዲሰጡ ያቀረቡትን ጥሪ የሶማሊላንድ ባለስልጣናት እና ታዋቂ ግለሰቦች አደነቁ!

የሶማሊላንድ ባለስልጣናት እና ታዋቂ ግለሰቦች የአሜሪካ ሴናተር ቴድ ክሩዝ ለፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለሶማሊላንድ እንደ እውቅና እንዲሰጡ ያቀረቡትን ጥሪ በደስታ ተቀብለዋል። ጥሪውም ለብዙ አስርት አመታት ሲታገሉለት ለነበረው እውቅና ትልቅ ድጋፍ እንደሆነ ገልጸዋል።

የሴኔቱ የአፍሪካ እና ግሎባል ጤና ፖሊሲ ንዑስ ኮሚቴ ሊቀመንበር የሆኑት ሴናተር ቴድ ክሩዝ ለፕሬዝዳንት ትራምፕ በጻፉት ደብዳቤ፣ ሶማሊላንድን “ለአሜሪካ ወሳኝ የደህንነት እና የዲፕሎማሲ አጋር” በማለት ያሞካሹ ሲሆን፣ “እውቅና እንዲሰጣትም” አሳስበዋል።

በደብዳቤያቸው፣ ሶማሊላንድ በቀይ ባህር ዳርቻ ላይ ያላትን ስትራቴጂያዊ አቀማመጥ፣ ጠንካራ የጦር ሃይል እና ለፀረ-ሽብርተኝነትና ፀረ-ወንበዴ ዘመቻዎች ያበረከተችውን አስተዋጽኦ ጠቅሰዋል። በተጨማሪም “ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ እና ከመሳሰሉ ተቀናቃኞች ከፍተኛ ጫና ቢደርስባትም” ሶማሊላንድ “ከአሜሪካ ጋር የጠበቀ ግንኙነት ለመፍጠር ቁርጠኛ መሆኗን” ገልጸዋል።

የሴናተር ክሩዝ ደብዳቤ የቀረበው የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን መሀመድ አብዲላሂ ኢሮ ወደ አሜሪካ ሊያደርጉት ባቀዱት ጉዞ ዋዜማ ላይ ነው። በዚህ ሳምንት፣ ሚኒስትሩ አብዲራህማን ለሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን እንደገለጹት፣ ፕሬዝዳንቱ ወደ አሜሪካ በቅርብ ቀናት ውስጥ ይፋዊ ጉዞ ያደርጋሉ።

Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
13🔥1😁1
የሲኖትራክ ተሸከርካሪ የጥራት ጉድለት ሳይሻሻል ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ ታግዷል - የጉምሩክ ኮሚሽን

የሲኖትራክ ተሽከርካሪ ያለበትን የጥራት እና የቴክኒክ ችግር እስኪያሻሽል ድረስ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መታገዱን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታውቋል።

የጥራት ጉድለቱ በየጊዜው የሰው ሕይወት ብሎም ንብረት እንዲጠፋ ምክንያት በመሆኑ፤ አምራች ድርጅቱ ማሻሻያ እስከሚያደርግ ድረስ ተሸከርካሪው ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መከልከሉን ነው የኮሚሽኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ዘሪሁን አሰፋ ለኢቢሲ ዶትስትሪም የተናገሩት።

ክልከላው ከግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ መደረጉንም ገልፀዋል።በዚህም ከተጠቀሰው ዕለት ጀምሮ ምንም ዓይነት የማስገቢያ ፈቃድ እንዳልተሰጠ አረጋግጠዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
👍3113😁10