YeneTube
118K subscribers
31.5K photos
485 videos
79 files
3.88K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
Forwarded from YeneTube
በሩን ይክፈቱ ችግረወን
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
4
Forwarded from YeneTube
🎁ከተወዳጁ የሂል ሳይድ መንደር ውስጥ ለሽያጭ የመጨረሻ በሆነው የዲያስፓራ  ብሎክ ቁጥር 3 ላይ ከባለ አንድ  እስከ ባለ አራት መኝታ ከተጨማሪ የሰራተኛ፣ ላውንደሪ ክፍል እና የዕቃ ክፍል ያካተቱ ቤቶች

🏡በ 8% ቅድመ ክፍያ ብቻ
የቤቱን 60% ደግሞ እየኖሩበት ወይም አከራይተውት በ20 አመት ቀስ ብለው መክፈል የሚችሉት

    💎 ባለ 1 መኝታ በ 487,000 ብር
    💎ባለ 2 መኝታ በ 825,982 ሺ ብር
    💎ባለ 3 መኝታ በ 854,221 ሺ ብር
    💎ባለ 4 መኝታ በ 1,157,787 ብር  ቅድመ ክፍያ ጀምሮ

🛍️🛒ሱቆች ከ 70 ካሬ ጀምሮ ይምጡ የግሎ ያድርጉ

- ባሉት ውስን ቀናቶች ለሚመጡ ደንበኞች እስከ 3 ሚሊዮን ብር  የሚደርስ ታላቅ ቅናሽ አቅርበን እየጠበቅኖት ነው

-እንዲሁም በ ግሩፕ ሆነው ለሚመጡ ደንበኞች ዳጎስ ያለ ቅናሽ አዘጋጅተን እየጠበቅኖት ነው

ይደውሉልን
የዘመናዊ መንደራችን አካል ይሁኑ!

☎️0900025097

#telegram (@SamuelDMCRealtor)
#WhatsApp
2
Forwarded from YeneTube
የ5 ሚሊየን ቅናሽ ተደረገ 😳😳
📍አሚስኮ ሪልስቴት(AMISCO RealEstate)
ለቡ ሙዚቃ ሰፈር

👍👍ለ 5 ቤት ብቻ የተደረገ ልዩ ቅናሽ

☎️09-89-26-43-80

           🏠🏠 በካሬ 75ሺ ብር ብቻ (በከፊል ማጠናቂያ)
100% ለሚከፍል በካሬ=65ሺብር

        📌ባለ 3መኝታ 183.7ካሬ
👍ጠቅላላ = 13,777,500 ብር
👍30% ቅድመክፍያ = 4,133,250ብር
      ቀሪውን በ1&1/2ዓመት የሚከፍሉት
100%ለከፈለ =11.9ሚሊየን ብር

         📌ባለ 3መኝታ 192.69ካሬ

👍ጠቅላላ = 14,451,750 ብር
👍30% ቅድመክፍያ = 4,335,525ብር
      ቀሪውን በ1&1/2ዓመት የሚከፍሉት
100%ለከፈለ =12.5ሚሊየን ብር

ሳይቱ የሚያሟላቸው ነገሮች
👉B+G+12+terrace
👉 90% የተጠናቀቀ
👉በ6 ወር የምትረከቡት
👉 ምቹ መኖሪያ ሰፈር
👉የተሟላ እና በቂ ፓርኪንግ
👉 የጋራ አዳራሽ
👉 የደህንነት መጠበቂያ ካሜራ
👉 የከርሰ ምድር ውሃ
👉 ዋና ገንዳ
👉 የልጆች መጫወቻ
👉 ደህንነቱ የተጠበቀ የመኖሪያ መንደር
👉 የቆሻሻ ማስወገጃ
👉እሳት አደጋ ማጥፊያ
👉 ተጠባባቂ ጀነሬተር
👉 ሊፊት
👉ሰፊ ቴራስ
👉6500 ካሬ ላይ ያረፈ ጊቢ
👉ግሪን ጋርደን
👉በ100ሜ ርቀት የእምነት ተቋማት
የሚያስፈልግዎትን ሁሉ በአቅራቢያዎ የሚያገኙበት

እድሉን ለመጠቀም
☎️09-89-26-43-80

Whatsup: 09-89-26-43-80
Telegram: @fiyami11
Email:hiwottadi22@icloud.com



 
7
❗️የሩሲያ ጦር በዶኔስክ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ የሚገኘውን ስትራቴጂካዊ የቻሶቭ ያር ከተማ ነፃ አወጣ

የቻሶቭ ያር ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ በዙሪያው ያለውን አካባቢ ለብዙ ኪሎ ሜትሮች ለመቆጣጠር የሚያስችል ወሳኝ ስትራቴጂካዊ ቦታ እንደሆነ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የቻሶቭ ያር በቁጥጥር ስር መዋል ወደ ክራማቶርስ-ስላቭያንስክ ለመገስገስ መንገድ የሚከፍት እንደሆነም ተነግሯል።

@Yenetube @Fikerassefa
7🔥1
በፎቶ፡ የአንድ ጀንበር 700 ሚሊየን ችግኞች የመትከል መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት በመላው ኢትዮጵያ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

የ2017 የአርንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ዛሬ ከማለዳ ጀምሮ በመላው ኢትዮጵያ እየተካሄደ ሲሆን እስካሁን "ከ103 ሚሊየን በላይ ችግኞች መተከላቸው" ተገልጿል።

በተከላው በመርሃ-ግብሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር)  ጨምሮ 4 ነጥብ 3 ሚሊየን ሰዎች  ተሳታፊ መሆናቸውን የመንግስት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመህርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ “በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር 8 ቢሊየን ገደማ ችግኞች የሚተከሉ ሲሆን፤ ይህም ባለፉት ሰባት ዓመታት የተተከሉ ችግኞችን መጠን 48 ቢሊየን ማድረስ የሚያስችል ነው” ብለዋል፡፡

በአረንጓዴ አሻራ ዕቅዳችን 50 ቢሊየን ችግኝ መትከል ነው ሲሉም በመህርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ባደረጉት ንግግር ገልጸዋል።
24😁22🔥1
"ማኬባ" የሚል መጠሪያ ባለው አዲስ የስኳር ምርት ማሰራጫ መንገድ ስኳር ማግኘት እንዳልቻሉ ቅሬታ አቅራቢዎች ገለጹ!

የስኳር ምርት ስርጭት ላይ እያጋጠመ ያለውን ችግር ለማቃለል "ማኬባ" በሚል መጠሪያ ወጣቶችን በማደራጀት ምርቱ በተመጣጣኝ ዋጋ ለነዋሪዎች ቤት ለቤት የሚደርስበት አሰራር ሥራ ላይ መዋሉ ይታወሳል።የአዲስ አበባ ሕብረት ሥራ ኮሚሽን 'በስኳር ምርት በግብይት ወቅት የሚፈጠረውን መጨናነቅ ያስወግዳል' በሚል አዲስ የጀመረው አሰራር አስቀድሞ በተነገረለት መንገድ ስኳር ለመግዛት እንዳላስቻላቸው ቅሬታ አቅራቢዎች ለአሐዱ ተናግረዋል።

"በአዲሱ አሰራር መሰረት ስኳር ካገኘን 9 ወራት አልፈውናል" የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ የስኳር ምርቱን ቤት ለቤት እንዲያዳርሱ የተደራጁትን ወጣቶች ሲያነጋግሩም ከሥነ-ምግባር ያፈነገጠ ምላሽ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል።ከሸማቾች ማኅበር ስኳር ያገኙበት የነበረውን አሰራር እንደሚያቃልል የተነገረለት አዲሱ አሰራር፤ በምልአት ተግባራዊ አለመደረጉ ለተጨማሪ ወጪ እንደዳረጋቸውም ተናግረዋል፡፡

ስኳሩን በግዢ ማግኘት ስለሚችሉበት ሁኔታ የአካባቢያቸውን ሸማቾች ማኅበር ቅርንጫፍ ቢሮ በሚያነጋሩበት ወቅትም "እኛን አይመለከትም" የሚል ምላሽ ተሰጥቶናል ብለዋል።አሐዱም የቅሬታ አቅራቢዎችን ጥያቄ ይዞ የአዲስ አበባ ሕብረት ሥራ ኮሚሽንን ጠይቋል።

የተቋሙ ዋና ኮሚሽነር ወ/ሮ ልዕልት ግደይ "በምርት አቅርቦት ላይ የሚነሳውን ቅሬታ ለመፍታት ከንግድ ቢሮ ጋር በመተባበር ወጣቶችን በማደራጀት 'ማኬባ' በሚባል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ዘርግተናል" ብለዋል።

አሰራሩ ስኳርን ጨምሮ ዱቄት፣ ዘይት፣ መኮሮኒ እና ፓስታ መግዛት የፈለገ ሸማች በስልክ መልዕክት ጠይቆ ቤቱ ድረስ የሚመጣለት አዲስ አሰራር እንደሆነ አብራርተው፤ በንግድ ቢሮ በኩል ተመን በማውጣት ቤት ለቤት የሚያደርሱ ወጣቶችን በማደራጀት እንዲያቀርቡ መደረጉን ተናግረዋል።

በዚህም በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ 7 ክፍለ ከተሞች ተደራሽ እንደሆነ እና የቀሩትን ክፍለ ከተሞች ለማዳረስ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ "አዲሱ ስርዓት ተግባራዊ ባተደረገባቸው አካባቢዎች የስኳር ምርትን በሸማች ማኅበራት በኩል ለማዳረስ ጥረት እየተደረገ ነው" ብለዋል።

የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር አክለውም አዲሱ አሰራር ላይ ከማኅበረሰቡ ከሚያነሳቸው ቅሬታዎች መካከል ዋነኛው አገልግሎቱን ለመስጠት የሚጓዙበት 'ቤት ዝግ ነው' ብሎ መመለስ እንደሆነ ጠቅሰው፤ የተገልጋዩን ማኅበረሰብ ቅሬታ ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር ንግግር እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
21😭2
በኦሮሚያ ክልል የአንድ አመት ከስምንት ወር ህፃን "በፀጥታ ኃይሎች" መገደሉ ተገለጸ፤ የአካባቢው ባለስልጣን ህፃኑ የተገደለው 'በተኩስ ልውውጥ ነው' ብለዋል!

በኦሮሚያ ክልል ኢሉ አባ ቦር ዞን ኖጳ ወረዳ፤ የአንድ አመት ከስምንት ወር ህጻን "በፀጥታ ኃይሎች" በተቶከሰ ጥይት መገደሉን ወላጅ እናቱ ወ/ሮ ዛራ ሀሰን ለአዲስ ስታንዳርድ ተናገሩ። በአሁኑ ወቅትም በፀጥታ ችግር ምክንያት ከቀዬቸው ለመፈናቀል መገደዳቸውን ገልጸዋል።

የህፃኑ እናት ወ/ሮ ዛራ ሀሰን፤ “ልጇ የተገደለው የአባቱ እቅፍ ውስጥ እያለ” መሆኑን ገልጸዋል። “በሰዓቱ ሁላችንም ቤት ውስጥ ተቀምጠን ነበር። ልጃችንም በአባቱ እቅፍ ውስጥ ነበር፤ ከዛም በተተኮሰው ጥይት ተመታ። ልጁ ከሞተ በኋላ አባቱ አስከሬኑን ትቶ እራሱን ለማትረፍ ሮጦ አመለጠ” ብለዋል።

የኖጳ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ደጀኔ ከበደ የህፃኑን ሞት አረጋግጠው፤ ነገር ግን ህጽኑ የተገደለው "በመንግስት ኃይሎች እና በሸኔ ታጣቂዎች መካከል በተካሄደ የተኩስ ልውውጥ በመሆኑ በየትኛው ወገን ጥይት እንደተመታ አልተለየም" ብለዋል። “ታጣቂዎቹ ከዚህ ክስተት በፊት ለብዙ ቀናት የሰዎቹን ቤት እንደ መደበቂያ ሲጠቀሙበት ነበር” ሲሉም ተናግረዋል።

Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
😭3921😁1
አቢሲኒያ ባንክ ከታክስ በፊት ከ12.1 ቢሊዮን ብር በላይ ማትረፉ ታወቀ!

 የባንክ ኢንዱስትሪውን ቀድመው ከተቀላቀሉት የግል ባንኮች መካከል አንዱ የሆነው አቢሲኒያ ባንክ፣ በተጠናቀቀው የሒሳብ ዓመት ከታክስና ከሌሎች ተቀናሾች በፊት ከ12.14 ቢሊዮን ብር በላይ ማትረፉ ታወቀ፡፡

ባንኩ በ2017 የሒሳብ ዓመት ያስመዘገበው ትርፍ ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነፃፀር፣ የ208 በመቶ ዕድገት ያሳየ መሆኑን የባንኩ መረጃ ያመለክታል፡፡ በዓመቱ ውስጥ ከታክስ በፊት አገኛለሁ ብሎ በዕቅድ ከያዘው የትርፍ መጠን ጋር ሲነፃፀርም፣ አፈጻጸሙ 147 በመቶ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል፡፡

አቢሲኒያ ባንክ በሒሳብ ዓመቱ ያገኘው ትርፍ መጠን በኢንዱስትሪው ሁለተኛው ከፍተኛ የትርፍ መጠን ሲሆን፣ በ2017 የሒሳብ ዓመት ከታክስ በፊት አስመዝግቦት የነበረው የትርፍ መጠን 5.28 ቢሊዮን ብር እንደነበር ይታወሳል፡፡

Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
20👍6
የወሎ ኮምቦልቻ አውሮፕላን ማረፊያ ማስፋፊያ ግንባታ ተጠናቆ ተመረቀ!

ከ1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የወሎ ኮምቦልቻ የመንገደኞች አውሮፕላን ማስፋፊያ ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እና የኢትዮጵያ አየር መንግድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በተገኙበት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።

@YeneTube @FikerAssefa
17