ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲን ከምዝገባ ከመሰረዙ በፊት እስከ አምስት ዓመት ማገድ የሚያስችል አዋጅ ማሻሻያ በምክር ቤቱ ፀደቀ!
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲን ከምዝገባ ከመሰረዙ በፊት እስከ አምስት ዓመት ማገድ የሚያስችል የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነምግባር አዋጅን ዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው በ2ኛ አስቸኳይ ስብሰባው አፀደቀ።
የታገደ የፖለቲካ ፓርቲ እገዳው ፀንቶ በሚቆይበት ጊዜያት ከማንኛውንም አይነት የፖለቲካ እንቅስቃሴ፣ በየትኛውም ደረጃ በሚደረግ ምርጫ ላይ እንዲሁም በጋራ ምክር ቤቱ ውስጥ መሳተፍ ይከለክላል። ከመንግስት ከሚሰጥ ደጋፍ ተጠቃሚም አይሆንም።
በጸደቀው አዋጅ ዙሪያ አስተያየታቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ የሰጡ የወላይታ ዲሞክራሲያዊ ግንባር አመራሩ ጎበዜ ጎኣ “ምርጫ ቦርድ አሻሻሎ ባስጸደቀው ህግ ገዢው ፓርቲ ብቻውን ቢወዳደር እንጂ ሌላው ሰው የሚወዳደርበት ምንም አይነት ሜዳ የለም” ብለዋል። “ፓርቲዎችን ከምርጫ ሜዳ የሚያስወጣ ነው” ሲሉም ተችተዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲን ከምዝገባ ከመሰረዙ በፊት እስከ አምስት ዓመት ማገድ የሚያስችል የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነምግባር አዋጅን ዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው በ2ኛ አስቸኳይ ስብሰባው አፀደቀ።
የታገደ የፖለቲካ ፓርቲ እገዳው ፀንቶ በሚቆይበት ጊዜያት ከማንኛውንም አይነት የፖለቲካ እንቅስቃሴ፣ በየትኛውም ደረጃ በሚደረግ ምርጫ ላይ እንዲሁም በጋራ ምክር ቤቱ ውስጥ መሳተፍ ይከለክላል። ከመንግስት ከሚሰጥ ደጋፍ ተጠቃሚም አይሆንም።
በጸደቀው አዋጅ ዙሪያ አስተያየታቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ የሰጡ የወላይታ ዲሞክራሲያዊ ግንባር አመራሩ ጎበዜ ጎኣ “ምርጫ ቦርድ አሻሻሎ ባስጸደቀው ህግ ገዢው ፓርቲ ብቻውን ቢወዳደር እንጂ ሌላው ሰው የሚወዳደርበት ምንም አይነት ሜዳ የለም” ብለዋል። “ፓርቲዎችን ከምርጫ ሜዳ የሚያስወጣ ነው” ሲሉም ተችተዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
😁20❤8👎1