አሳዛኝ መረጃ
ወጣቱ ምንተስኖት ሰንበቱ ይባላል።
የወልቂጤ ዩኒቨርስቲ የ2ኛ አመት ተማሪ ሲሆን በዛሬው እለት በከምባታ ዞን አዲሎ ዙሪያ ወረዳ በገመድ ተሰቅሎ ሕይወቱ ጠፍቶ ተገኝቷል።
ፖሊስ አስክሬኑ ለምርመራ ወደ ወራቤ ሆስፒታል መላኩ ታውቋል ።
@Yenetube @Fikerassefa
ወጣቱ ምንተስኖት ሰንበቱ ይባላል።
የወልቂጤ ዩኒቨርስቲ የ2ኛ አመት ተማሪ ሲሆን በዛሬው እለት በከምባታ ዞን አዲሎ ዙሪያ ወረዳ በገመድ ተሰቅሎ ሕይወቱ ጠፍቶ ተገኝቷል።
ፖሊስ አስክሬኑ ለምርመራ ወደ ወራቤ ሆስፒታል መላኩ ታውቋል ።
@Yenetube @Fikerassefa
😭47❤15
የሩሲያ ሠራዊት የዩክሬን የጦር ኢንዱስትሪ ኮምፕሌክስ ድርጅቶችና የጦር ሰው አልባ አውሮፕላን መገጣጠሚያዎች ላይ የቡድን ጥቃት መፈፀሙን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ።
@Yenetube @Fikerassefa
@Yenetube @Fikerassefa
❤7👍2🔥2
ሕንድ የዓለም ረጅሙን የባቡር ድልድይ አስመረቀች
የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የዓለማችንን ረጅሙን የባቡር ድልድይ መርቀው ከፍተዋል።
359 ሜትር የሚረዝመው እና በችናብ ወንዝ ላይ የተገነባው ይሕ ግዙፍ ድልድይ የካሽሚር ግዛትን ከተቀረው የሕንድ ክፍል በባቡር የሚያገናኝ ነው ተብሎለታል። የድልድዩ ርዝመት ከፈረንሳዩ ኤፍል ታዎር በ35 ሜትር የሚበልጥ እንደሆንም ተገልጿል።
ለግንባታው 5.1 ቢሊየን ዶላር የወጣበት ይሕ ፕሮጀክት አጠቃላይ የባቡር መስመሩ 272 ኪ.ሜ የሚረዝም ነው።
በተራራማው የካሽሚር ግዛቶች ውስጥ ያለው አስቸጋሪ የመሬት አቀማመጥ ለትራንስፖርት አገልግሎት የማይመች እና አስቸጋሪ ቢሆንም ሕንድ የሰራችው ይሕ በዓይነቱ ልዩ የሆነ ድልድይ እና የባቡር መስመር በአካባቢው ያለውን የትራንስፖርት ችግር የሚፈታ ነው ሲል የዘገበው ኢንዲፔንዳንት ነው።
@Yenetube @Fikerassefa
የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የዓለማችንን ረጅሙን የባቡር ድልድይ መርቀው ከፍተዋል።
359 ሜትር የሚረዝመው እና በችናብ ወንዝ ላይ የተገነባው ይሕ ግዙፍ ድልድይ የካሽሚር ግዛትን ከተቀረው የሕንድ ክፍል በባቡር የሚያገናኝ ነው ተብሎለታል። የድልድዩ ርዝመት ከፈረንሳዩ ኤፍል ታዎር በ35 ሜትር የሚበልጥ እንደሆንም ተገልጿል።
ለግንባታው 5.1 ቢሊየን ዶላር የወጣበት ይሕ ፕሮጀክት አጠቃላይ የባቡር መስመሩ 272 ኪ.ሜ የሚረዝም ነው።
በተራራማው የካሽሚር ግዛቶች ውስጥ ያለው አስቸጋሪ የመሬት አቀማመጥ ለትራንስፖርት አገልግሎት የማይመች እና አስቸጋሪ ቢሆንም ሕንድ የሰራችው ይሕ በዓይነቱ ልዩ የሆነ ድልድይ እና የባቡር መስመር በአካባቢው ያለውን የትራንስፖርት ችግር የሚፈታ ነው ሲል የዘገበው ኢንዲፔንዳንት ነው።
@Yenetube @Fikerassefa
❤21👍3🔥1
ፍተሻ በአዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ፖሊስ የሕግ አግባብን የተከተለ ፍተሻና ብርበራ ለማድረግ መዘጋጀቱን አስታወቀ።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ከሶስት ቀን በፊ ባወጣው መግለጫ፣ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የሕግ አግባብን የተከተለ ፍተሻና ብርበራ ለማድረግ መዘጋጀቱን አስታወቀ።
ኅብረተሰቡ ለፀጥታው ሥራ ስኬታማነት እያደረገ ያለውን ትብብር አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ያሳሰበው የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ፣ የከተማውን ሰላምና ፀጥታ ሥጋት ላይ የሚጥሉ ወንጀለኞችን አስመልክቶ ለጠቅላይ መምሪያው በደረሱ ጥቆማዎችና በጥናት በለያቸው የሰላምና ፀጥታ ሥጋቶች ላይ ዕርምጃ ለመውሰድና ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ የሚያስችል የተጠናከረ ቁጥጥርና ፍተሻ ለማድረግ መዘጋጀቱን አስታውቋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ደረሱኝ ካላቸው ጥቆማዎችና በጥናት እንደለያቸው ከገለጻቸው ከባድ ወንጀሎች መካከል "የጦር መሣሪያ ዝውውር፣ ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርና ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር ይገኙበታል"ብሏል።
@Yenetube @Fikerassefa
የአዲስ አበባ ፖሊስ የሕግ አግባብን የተከተለ ፍተሻና ብርበራ ለማድረግ መዘጋጀቱን አስታወቀ።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ከሶስት ቀን በፊ ባወጣው መግለጫ፣ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የሕግ አግባብን የተከተለ ፍተሻና ብርበራ ለማድረግ መዘጋጀቱን አስታወቀ።
ኅብረተሰቡ ለፀጥታው ሥራ ስኬታማነት እያደረገ ያለውን ትብብር አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ያሳሰበው የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ፣ የከተማውን ሰላምና ፀጥታ ሥጋት ላይ የሚጥሉ ወንጀለኞችን አስመልክቶ ለጠቅላይ መምሪያው በደረሱ ጥቆማዎችና በጥናት በለያቸው የሰላምና ፀጥታ ሥጋቶች ላይ ዕርምጃ ለመውሰድና ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ የሚያስችል የተጠናከረ ቁጥጥርና ፍተሻ ለማድረግ መዘጋጀቱን አስታውቋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ደረሱኝ ካላቸው ጥቆማዎችና በጥናት እንደለያቸው ከገለጻቸው ከባድ ወንጀሎች መካከል "የጦር መሣሪያ ዝውውር፣ ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርና ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር ይገኙበታል"ብሏል።
@Yenetube @Fikerassefa
😁16❤13👍4👎2
በዳነሰነች ወረዳ የኦሞ ወንዝ ሞልቶ ባስከተለው ጎርፍ 8,445 ሰዎች “ዳግም” ተፈናቀሉ
በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ በተከሰተ ጎርፍ 1,753 አባወራዎች ከቀያቸው መፈናቀላቸውን የአካባቢው መንግሥት አስታወቀ።
ጎርፍ የተከሰተው የኦሞ ወንዝ በመሙላቱ እና የቱርካና ሀይቅ መደበኛ የውኃ ይዞታውን በከፍተኛ ፍጥነት በመልቀቁ ነው። የወረዳው ባለሥልጣናት በአጠቃላይ 8,445 ሰዎች “ዳግም” መፈናቀላቸውን ገልጸዋል።
በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ በተከሰተ ጎርፍ 1,753 አባወራዎች ከቀያቸው መፈናቀላቸውን የአካባቢው መንግሥት አስታወቀ። በወረዳው ጎርፍ የተከሰተው “የኦሞ ወንዝ ሞልቶ መደበኛ የመፍሰሻ አቅጣጫውን ለቆ በመውጣቱ እና የቱርካና ሀይቅ መደበኛ የውኃ ይዞታውን በከፍተኛ ፍጥነት በመልቀቁ” እንደሆነ የዳሰነች ወረዳ የመንግሥት ኮምዩንኬሽን ጽህፈት ቤት ትላንት አርብ አስታውቋል።
በወረዳው በተከሰተው ጎርፍ ምክንያት በአጠቃላይ 8,445 ሰዎች “ዳግም”
መፈናቀላቸውን የዳሰነች ወረዳ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኡስማን ሰይድ መናገራቸውን መግለጫው ይጠቁማል።
ከኢትዮጵያ በኬንያ ወደሚገኘው ቱርካና ሐይቅ የሚፈሰው የኦሞ ወንዝ እየሞላ የአካባቢውን ነዋሪዎች ሲያፈናቅል የአሁኑ የመጀመሪያ አይደለም።
ከዚህ ቀደም በተከሰተ ተመሣሣይ የጎርፍ አደጋ ከቀያቸው የተፈናቀሉ ሰዎች አሁንም በሦስት ቦታዎች በጊዜያዊነት ተጠልለው እንደሚገኙ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ መናገራቸውን የክልሉ የመንግሥት ኮምዩንኬሽን ቢሮ ከትላንት በስቲያ ሐሙስ በተረጋገጠ የፌስቡክ ገጹ ያሰራጨው ጽሁፍ ይጠቁማል። ኃላፊው እንዳሉት በ2016 ክረምት የተከሰተ ተመሳሳይ የውኃ ሙሌት “የ28 የሚሆኑ ቀበሌያትን” አፈናቅሎ ነበር።
የኦሞ ወንዝ ሲሞላ የአካባቢውን ነዋሪዎች ከቀያቸው ከማፈናቀል ባሻገር የዳሰነች እና የኦሞራቴ ከተሞችን አደጋ ውስጥ ሲጥል ቆይቷል።
@Yenetube @Fikerassefa
በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ በተከሰተ ጎርፍ 1,753 አባወራዎች ከቀያቸው መፈናቀላቸውን የአካባቢው መንግሥት አስታወቀ።
ጎርፍ የተከሰተው የኦሞ ወንዝ በመሙላቱ እና የቱርካና ሀይቅ መደበኛ የውኃ ይዞታውን በከፍተኛ ፍጥነት በመልቀቁ ነው። የወረዳው ባለሥልጣናት በአጠቃላይ 8,445 ሰዎች “ዳግም” መፈናቀላቸውን ገልጸዋል።
በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ በተከሰተ ጎርፍ 1,753 አባወራዎች ከቀያቸው መፈናቀላቸውን የአካባቢው መንግሥት አስታወቀ። በወረዳው ጎርፍ የተከሰተው “የኦሞ ወንዝ ሞልቶ መደበኛ የመፍሰሻ አቅጣጫውን ለቆ በመውጣቱ እና የቱርካና ሀይቅ መደበኛ የውኃ ይዞታውን በከፍተኛ ፍጥነት በመልቀቁ” እንደሆነ የዳሰነች ወረዳ የመንግሥት ኮምዩንኬሽን ጽህፈት ቤት ትላንት አርብ አስታውቋል።
በወረዳው በተከሰተው ጎርፍ ምክንያት በአጠቃላይ 8,445 ሰዎች “ዳግም”
መፈናቀላቸውን የዳሰነች ወረዳ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኡስማን ሰይድ መናገራቸውን መግለጫው ይጠቁማል።
ከኢትዮጵያ በኬንያ ወደሚገኘው ቱርካና ሐይቅ የሚፈሰው የኦሞ ወንዝ እየሞላ የአካባቢውን ነዋሪዎች ሲያፈናቅል የአሁኑ የመጀመሪያ አይደለም።
ከዚህ ቀደም በተከሰተ ተመሣሣይ የጎርፍ አደጋ ከቀያቸው የተፈናቀሉ ሰዎች አሁንም በሦስት ቦታዎች በጊዜያዊነት ተጠልለው እንደሚገኙ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ መናገራቸውን የክልሉ የመንግሥት ኮምዩንኬሽን ቢሮ ከትላንት በስቲያ ሐሙስ በተረጋገጠ የፌስቡክ ገጹ ያሰራጨው ጽሁፍ ይጠቁማል። ኃላፊው እንዳሉት በ2016 ክረምት የተከሰተ ተመሳሳይ የውኃ ሙሌት “የ28 የሚሆኑ ቀበሌያትን” አፈናቅሎ ነበር።
የኦሞ ወንዝ ሲሞላ የአካባቢውን ነዋሪዎች ከቀያቸው ከማፈናቀል ባሻገር የዳሰነች እና የኦሞራቴ ከተሞችን አደጋ ውስጥ ሲጥል ቆይቷል።
@Yenetube @Fikerassefa
❤12😭5
በወላይታ ሶዳ ከተማ በግድያ ወንጀል ተፈርዶበት በምህረት የተለቀቀው ተከሳሽ የ8 ዓመቷ ታዳጊ ላይ በፈፀመው የአስገድዶ መድፈር ወንጀል በእስራት ተቀጣ
በወላይታ ሶዶ ከተማ አራዳ ቀበሌ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት እንዲቀጣ መወሰኑን የሶዶ ከተማ ፖሊስ አስታውቋል።
በወላይታ ሶዶ ከተማ የጉሩሞ ላዲሳ ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ተከሳሽ ኤፍሬም ጪማ የተባለ ግለሰብ የካቲት 15 ቀን 2017 ዓ.ም አመሻሽ 12፡30 አካባቢ የግል ተበዳይ የሆነችውን የ8 ዓመት ታዳጊ ጁስ እና ኮሾሮ ገዝቶ በማታለል የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈጸሙ ተገልፆል፡፡
ግለሰቡ ከዚህ በፊት በነፍስ ግድያ ወንጀል ተባባሪ ሆኖ 14 ዓመት ፅኑ እስራት የተፈረደበትና የእስር ጊዜውን ሳይጨርስ በምህረት የወጣ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
የወላይታ ሶዶ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ኤፍሬም ጪማን በ20 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበታል።
ዳጉ ጆርናል
@Yenetube @Fikerasssefa
በወላይታ ሶዶ ከተማ አራዳ ቀበሌ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት እንዲቀጣ መወሰኑን የሶዶ ከተማ ፖሊስ አስታውቋል።
በወላይታ ሶዶ ከተማ የጉሩሞ ላዲሳ ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ተከሳሽ ኤፍሬም ጪማ የተባለ ግለሰብ የካቲት 15 ቀን 2017 ዓ.ም አመሻሽ 12፡30 አካባቢ የግል ተበዳይ የሆነችውን የ8 ዓመት ታዳጊ ጁስ እና ኮሾሮ ገዝቶ በማታለል የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈጸሙ ተገልፆል፡፡
ግለሰቡ ከዚህ በፊት በነፍስ ግድያ ወንጀል ተባባሪ ሆኖ 14 ዓመት ፅኑ እስራት የተፈረደበትና የእስር ጊዜውን ሳይጨርስ በምህረት የወጣ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
የወላይታ ሶዶ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ኤፍሬም ጪማን በ20 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበታል።
ዳጉ ጆርናል
@Yenetube @Fikerasssefa
❤20😭10
‹‹ሠራተኞች ለመኖር የሚያስችላቸው ደመወዝ ተከፍሏቸው እየኖሩ ነው ማለት አይቻልም›› የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ)
በኢትዮጵያ ሠራተኞች ለመኖር የሚያስችላቸው ደመወዝ እየተከፈላቸው ነው ለማለት እንደማይቻል፣ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ገለጸ፡፡
የኢሠማኮ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ድሪብሳ ለገሠ፣ አሁን ባለው ሁኔታ በኢትዮጵያ ሠራተኞች ደመወዝ ተከፍሏቸው በመኖር ላይ ናቸው ብሎ አፍን ሞልቶ ለመናገር የሚከብድ መሆኑን ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
በአገራዊ የምክክር ኮሚሽን በተዘጋጀ የአጀንዳ መድረክ ላይ የተገኙት አቶ ድሪብሳ ከሪፖርተር ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ ‹‹የሠራተኞች የደመወዝና ሌሎች ዋና ዋና ጥያቄዎቻቸውን እስከ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድረስ ስናቀርብ ቆይተናል፤›› ብለው፣ እየታዩ ያሉ ተጨባጭ እውነታዎችን ተቀብሎ በማስተካከል በኩል መዘግየቶች በመኖራቸውና በፍጥነት ካልተፈቱ ወዳልተፈለገ ግጭት ሊያመሩ ይችላሉ የሚል ሥጋት እንዳለ ገልጸዋል፡፡
Via:- Reporter
@Yenetube @Fikerassefa
በኢትዮጵያ ሠራተኞች ለመኖር የሚያስችላቸው ደመወዝ እየተከፈላቸው ነው ለማለት እንደማይቻል፣ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ገለጸ፡፡
የኢሠማኮ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ድሪብሳ ለገሠ፣ አሁን ባለው ሁኔታ በኢትዮጵያ ሠራተኞች ደመወዝ ተከፍሏቸው በመኖር ላይ ናቸው ብሎ አፍን ሞልቶ ለመናገር የሚከብድ መሆኑን ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
በአገራዊ የምክክር ኮሚሽን በተዘጋጀ የአጀንዳ መድረክ ላይ የተገኙት አቶ ድሪብሳ ከሪፖርተር ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ ‹‹የሠራተኞች የደመወዝና ሌሎች ዋና ዋና ጥያቄዎቻቸውን እስከ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድረስ ስናቀርብ ቆይተናል፤›› ብለው፣ እየታዩ ያሉ ተጨባጭ እውነታዎችን ተቀብሎ በማስተካከል በኩል መዘግየቶች በመኖራቸውና በፍጥነት ካልተፈቱ ወዳልተፈለገ ግጭት ሊያመሩ ይችላሉ የሚል ሥጋት እንዳለ ገልጸዋል፡፡
Via:- Reporter
@Yenetube @Fikerassefa
❤57👍7😭2😁1
መንግሥት፣ በሕገ-መንግሥቱ ውስጥ መሻሻል ያለባቸው በርካታ አንቀጾች አሉ ብሎ እንደሚያምን ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባስገባው ባለ 30 ገጽ መነሻ ሃሳብ ላይ መጠቆሙን ሪፖርተር አስነብቧል።
መንግሥት፣ አንቀጾቹ "በሰፊ ውይይት"፣ "በክርክር" እና "በሙሉ መግባባት" መሻሻል እንዳለባቸው በሰነዱ ላይ መጠቆሙንም ዘገባው ጠቅሷል። ኾኖም ሕገመንግሥቱ "ሕገመንግሥታዊነት" እምብዛም ያልታየበትና እስካኹንም "በተግባር ያልተፈተነ" መኾኑን የጠቀሰው የመንግሥት ሰነድ፣ ሕገመንግሥቱን ማሻሻል አንዳንድ ችግሮች ሊያስከትል እንደሚችልም ገልጧል ተብሏል።
ከዚህ አንጻር የሕገመንግሥት ማሻሻያ ማድረግ፣ "አዲስ ሕገመንግሥት ማስተዋወቅ ተደርጎ ሊቆጠር ይችላል" በማለት መንግሥት በሰነዱ ላይ ስጋቱን እንዳሠፈረም ዘገባው አመልክቷል።
@Yenetube @Fikerassefa
መንግሥት፣ አንቀጾቹ "በሰፊ ውይይት"፣ "በክርክር" እና "በሙሉ መግባባት" መሻሻል እንዳለባቸው በሰነዱ ላይ መጠቆሙንም ዘገባው ጠቅሷል። ኾኖም ሕገመንግሥቱ "ሕገመንግሥታዊነት" እምብዛም ያልታየበትና እስካኹንም "በተግባር ያልተፈተነ" መኾኑን የጠቀሰው የመንግሥት ሰነድ፣ ሕገመንግሥቱን ማሻሻል አንዳንድ ችግሮች ሊያስከትል እንደሚችልም ገልጧል ተብሏል።
ከዚህ አንጻር የሕገመንግሥት ማሻሻያ ማድረግ፣ "አዲስ ሕገመንግሥት ማስተዋወቅ ተደርጎ ሊቆጠር ይችላል" በማለት መንግሥት በሰነዱ ላይ ስጋቱን እንዳሠፈረም ዘገባው አመልክቷል።
@Yenetube @Fikerassefa
❤27😁15👎1
የሩሲያው ቅጥረኛ ተዋጊ ቡድን በማሊ ያለውን 'ተልዕኮ አጠናቆ' ሊወጣ መሆኑን አስታወቀ!
የሩሲያው ቅጥረኛ ተዋጊ ቡድን ፣ቫግነር በማሊ ያለውን 'ተልዕኮ አጠናቆ' ከአገሪቱ ሊወጣ መሆኑን አስታወቀ።ቫግነር በምዕራባዊቷ አፍሪካዊቷ አገር ማሊ ከአውሮፓውያኑ 2021 ጀምሮ ከአገሪቱ መከላከያ ሰራዊት ጋር በመጣመር ጽንፈኞችን ለመምታት እየሰራ ነበር።
ቫግነር "ከማሊ ሕዝብ ጎን በመሆን ሽብርተኝነትን ተዋግቷል፤ በዚህም ነዋሪዎችን ለዓመታት ሲያሸብሩ የነበሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎች እና አዛዦቻቸውን ገድያለሁ" ሲል በቴሌግራም ገጹ አስታውቋል።
ቫግነር ከአገሪቱ እንደሚወጣ ያስታወቀው የማሊ ወታደሮች ከአንድ ሳምንት ባነሰ ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ የከፋ ጥቃት ከደረሰባቸው በኋላ በአገሪቱ ማዕከል ከሚገኘው ትልቅ የጦር ሰፈር መውጣታቸውን የሚገልጹ ዘገባዎች እየወጡ ባለበት ወቅት ነው።ማሊ ለአስርት ዓመታት ከእስላማዊ ታጣቂዎች ጋር ስትታገል ቆይታለች።
@YeneTube @FikerAssefa
የሩሲያው ቅጥረኛ ተዋጊ ቡድን ፣ቫግነር በማሊ ያለውን 'ተልዕኮ አጠናቆ' ከአገሪቱ ሊወጣ መሆኑን አስታወቀ።ቫግነር በምዕራባዊቷ አፍሪካዊቷ አገር ማሊ ከአውሮፓውያኑ 2021 ጀምሮ ከአገሪቱ መከላከያ ሰራዊት ጋር በመጣመር ጽንፈኞችን ለመምታት እየሰራ ነበር።
ቫግነር "ከማሊ ሕዝብ ጎን በመሆን ሽብርተኝነትን ተዋግቷል፤ በዚህም ነዋሪዎችን ለዓመታት ሲያሸብሩ የነበሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎች እና አዛዦቻቸውን ገድያለሁ" ሲል በቴሌግራም ገጹ አስታውቋል።
ቫግነር ከአገሪቱ እንደሚወጣ ያስታወቀው የማሊ ወታደሮች ከአንድ ሳምንት ባነሰ ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ የከፋ ጥቃት ከደረሰባቸው በኋላ በአገሪቱ ማዕከል ከሚገኘው ትልቅ የጦር ሰፈር መውጣታቸውን የሚገልጹ ዘገባዎች እየወጡ ባለበት ወቅት ነው።ማሊ ለአስርት ዓመታት ከእስላማዊ ታጣቂዎች ጋር ስትታገል ቆይታለች።
@YeneTube @FikerAssefa
❤24👀1
ፀረ ጦርነት ዘመቻ ዛሬ በበይነመረብ ተጀምሮል።
በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ተመልካቾች በተከታተሉት ዉይይት ላይ የሃገሪቱ የተለያዩ አቆም ያላቸዉ ፖለቲከኞች እና ትጥቅ ትግል ላይ ያሉ ሃይሎች ተሳትፈዉበታል ፡፡
በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱት የፋኖ ሃይሎችን በመወከል ዘመነ ካሴ ንግግር አድርጎል ፡፡
በኢንተርኔት መቆረጥ ምክንያት ያልተመለከታችሁ
ቀጣዩን ሊንክ በመጠቀም መመልከት ትችላላችሁ👇👇👇
https://youtu.be/gkZic7SDHv8?si=ruIgaSJRBUiBkh7x
በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ተመልካቾች በተከታተሉት ዉይይት ላይ የሃገሪቱ የተለያዩ አቆም ያላቸዉ ፖለቲከኞች እና ትጥቅ ትግል ላይ ያሉ ሃይሎች ተሳትፈዉበታል ፡፡
በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱት የፋኖ ሃይሎችን በመወከል ዘመነ ካሴ ንግግር አድርጎል ፡፡
በኢንተርኔት መቆረጥ ምክንያት ያልተመለከታችሁ
ቀጣዩን ሊንክ በመጠቀም መመልከት ትችላላችሁ👇👇👇
https://youtu.be/gkZic7SDHv8?si=ruIgaSJRBUiBkh7x
👍39❤17😁14👎8
የህክምና ጓንት እና ስሪንጅ ከውጪ ማስገባት ማቆሙን የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት አስታወቀ።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ እንደገለጹት በአገሪቱ ውስጥ ሁለት የጓንት አምራቾች ያሉ ሲሆን፣ ዘንድሮ ሙሉ በሙሉ የህክምና ጓንት በአገር ውስጥ ምርት እየተሸፈነ ነው፡፡
እንደ ጋዜጣ ፕላስ ዘገባ በሙሉ አቅሙ እያመረተ የሚገኝ አንድ ስሪንጅ ፋብሪካ በድሬዳዋ ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ፋብሪካው ምርቶቹን ለአገልግሎቱ እያቀረበ በመሆኑ ከአንድ ዓመት በፊት ጀምሮ ስሪንጅ ከውጪ ማስገባት አቁመናል ብለዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ እንደገለጹት በአገሪቱ ውስጥ ሁለት የጓንት አምራቾች ያሉ ሲሆን፣ ዘንድሮ ሙሉ በሙሉ የህክምና ጓንት በአገር ውስጥ ምርት እየተሸፈነ ነው፡፡
እንደ ጋዜጣ ፕላስ ዘገባ በሙሉ አቅሙ እያመረተ የሚገኝ አንድ ስሪንጅ ፋብሪካ በድሬዳዋ ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ፋብሪካው ምርቶቹን ለአገልግሎቱ እያቀረበ በመሆኑ ከአንድ ዓመት በፊት ጀምሮ ስሪንጅ ከውጪ ማስገባት አቁመናል ብለዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
👍32❤16🔥2😁1
ሲዳማ ቡና ሻምፒዮን ሆነ
በኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ ሲዳማ ቡና ወላይታ ድቻን 2 ለ 1 በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆኗል።
በአዲስ አበባ ስቴዲየም በተደረገው ጨዋታ ሀብታሙ ታደሰ እና የቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና አጥቂ መስፍን ታፈሰ የሲዳማ ቡናን ግቦች አስቆጥረዋል።
በዝግ ስቴዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ካርሎስ ዳምጠው የወላይታ ድቻን ብቸኛ ግብ ያስገኘ ተጫዋች ሆኗል።
ሲዳማ ቡና የኢትዮጵያ ዋንጫን ማንሳቱን ተከትሎ በታሪኩ ለመጀመርያ ጊዜ በቀጣይ አመት በካፍ ኮንፌደሬሽን ዋንጫ ኢትዮጵያን የሚወክልም ይሆናል።
ወላይታ ድቻ በ2ኛው አጋማሽ ከተደጋጋሚ ሙከራዎች ባሻገር ግብ ቢያስቆጥርም ከጨዋታ ውጭ በሚል ተሽሮበታል።
በ2010 ዓ.ም በተሳተፈበት የኮንፌደሬሽን ዋንጫ በ1ኛው ዙር ቅድመ ማጣሪያ የግብጹን ጠንካራ ክለብ ዛማሊክ በደርሶ መልስ አሸንፎ የነበረው ወላይታ ድቻ በድጋሜ በአፍሪካ መድረክ የሚሳተፍበትን ዕድል ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
የኢትዮጵያ ዋንጫ ከአራት አመታት መቋረጥ በኋላ በ2016 ዓ.ም መጀመሩም ይታወሳል።
@Yenetube @Fikerassefa
በኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ ሲዳማ ቡና ወላይታ ድቻን 2 ለ 1 በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆኗል።
በአዲስ አበባ ስቴዲየም በተደረገው ጨዋታ ሀብታሙ ታደሰ እና የቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና አጥቂ መስፍን ታፈሰ የሲዳማ ቡናን ግቦች አስቆጥረዋል።
በዝግ ስቴዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ካርሎስ ዳምጠው የወላይታ ድቻን ብቸኛ ግብ ያስገኘ ተጫዋች ሆኗል።
ሲዳማ ቡና የኢትዮጵያ ዋንጫን ማንሳቱን ተከትሎ በታሪኩ ለመጀመርያ ጊዜ በቀጣይ አመት በካፍ ኮንፌደሬሽን ዋንጫ ኢትዮጵያን የሚወክልም ይሆናል።
ወላይታ ድቻ በ2ኛው አጋማሽ ከተደጋጋሚ ሙከራዎች ባሻገር ግብ ቢያስቆጥርም ከጨዋታ ውጭ በሚል ተሽሮበታል።
በ2010 ዓ.ም በተሳተፈበት የኮንፌደሬሽን ዋንጫ በ1ኛው ዙር ቅድመ ማጣሪያ የግብጹን ጠንካራ ክለብ ዛማሊክ በደርሶ መልስ አሸንፎ የነበረው ወላይታ ድቻ በድጋሜ በአፍሪካ መድረክ የሚሳተፍበትን ዕድል ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
የኢትዮጵያ ዋንጫ ከአራት አመታት መቋረጥ በኋላ በ2016 ዓ.ም መጀመሩም ይታወሳል።
@Yenetube @Fikerassefa
❤50👎11👍1