ቪዛ 50 ሺሕ ዶላር የሚያስገኝ የፊንቴክ ውድድር በኢትዮጵያ አስጀመረ!
ቪዛ በኢትዮጵያ የፋይናንስ ቴክኖሎጂ (ፊንቴክ) ፈጠራን ለማበረታታት፣ የክፍያ እና የግብይት ተግዳሮቶችን ለመፍታት እንዲሁም አዳዲስ መፍትሄዎችን ለማምጣት ያስችላል ያለውን "ቪዛ በየትኛውም ቦታ (VEI)" የተሰኘ የፊንቴክ ውድድር በይፋ አስጀምሯል፡፡
የቪዛ መካከለኛው እና የምስራቅ አውሮፓ፣ የመካከለኛው ምስራቅ እና አፍሪካ ቢሮ ፕሬዝዳንት አንድሪው ቶሬ፤ በሰኔ ወር በኢትዮጵያ ባደረጉት ጉብኝት ቪዛ የዲጂታል ክፍያዎችን ለማስፋፋት ያለውን ቁርጠኝነት አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለጽ፤ የፊንቴክ ፈጠራን ለማስፋፋት እና በሴቶች የሚመሩ አነስተኛ እና መካከለኛ ቢዝነሶችን ለማገዝ አዳዲስ ውጥኖች መያዙን ማስታወቃቸው ይታወሳል፡፡
ይህም እቅድ በአገር ውስጥ ለኹለተኛ ጊዜ የቪዛ ለኹሉም ፊንቴክ ውድድርን ለማዘጋጀት እና የቪዛን ‘ቀጣይ እሷ ናት’ የሴቶችን ማጎልበት ፕሮጀክት ማስጀመርን እንደሚያካትት ገልጸዋል።
“የ"ቪዛ በየትኛውም ቦታ" (Visa Everywhere Initiative) ለፊንቴክ እና ለሥራ ፈጣሪዎች በክፍያ እና በንግድ ዓለም ላይ ተጨባጭ እና ውጤታማ መፍትሄዎችን እንዲያስገኙ የሚያስችል መድረክ ነው" ሲሉ የቪዛ የኢትዮጵያ ቢሮ ኃላፊ ያሬድ እንዳለ ተናግረዋል።
ፊንቴክ እና ሌሎች የክፍያ ስርዓት ፈጣሪዎች፣ ሸማቾች እና ነጋዴዎች ክፍያ የሚፈጽሙበትን መንገድ በመቀየር ብዙ ሰዎች የሚፈልጉትን ገንዘብ በሚፈልጉበት ጊዜ በቀላሉ ማግኘት እንዲችሉ ማድረጉንም አስረድተዋል።
የዘንድሮው "ቪዛ በየትኛውም ቦታ (VEI)" ኢትዮጵያ የፍፃሜ ውድድር በመስከረም ወር የሚካሄድ ሲሆን፤ በድምሩ 50 ሺሕ ዶላር በተለያየ ደረጃ ለሚያሸንፉ ተወዳዳሪዎች እንደሚሰጥ ተነግሯል።
ይህም 1ኛ ደረጃ 25 ሺሕ ዶላር፣ 2ኛ ደረጃ 15 ሺሕ ዶላር እና 3ኛ ደረጃ 10 ሺሕ ዶላር ተሸላሚ ያደርጋል ተብሏል፡፡
ከገንዘብ ሽልማቶች በተጨማሪ፣ አሸናፊዎች ባንኮች፣ ነጋዴዎች፣ ቬንቸር ካፒታሊስቶች እና የመንግሥት አካላት የሚገኙበትን የቪዛን ሰፊ የአጋሮች መረብ ውስጥ የመካተት እና የመታወቅ እድል ያገኛሉ የተባለ ሲሆን፤ ዓለም አቀፍ ከሆኑ ታዋቂ ድርጅቶች እውቅና ማግኘት እንደሚችሉም ተነግሯል፡፡
የ"ቪዛ በየትኛውም ቦታ (VEI)" ውድድር በተለያዩ ዘርፎች የሚገኙ ንግዶች የሚያጋጥሟቸውን የክፍያ እና የግብይት ተግዳሮቶች በመፍታት ማህበረሰቡን የሚያግዙ እና በኹሉም ዘርፍ እና ደረጃ የሚገኙ አዳዲስ እና ትልቅ ሥራ ፈጣሪዎችን እንደሚያሳትፍ ተገልጿል፡፡
በዚህ መሰረት የቪዛ ለኹሉም ውድድር ምዝገባ የሚጠናቀቀው ነሀሴ 14 መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ተወዳዳሪዎች https://africa.visa.com/visa-everywhere/everywhere-initiative/initiative.html ሊንክን በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል፡፡በ2013 የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሽያጭ የክፍያ ስርዓት ኦፕሬተር በመሆን፤ የመጀመሪያውን "ቪዛ በየትኛውም ቦታ" ኢትዮጵያ ውድድርን አሪፍፔይ ማሸነፉ ይታወሳል።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FkerAssefa
ቪዛ በኢትዮጵያ የፋይናንስ ቴክኖሎጂ (ፊንቴክ) ፈጠራን ለማበረታታት፣ የክፍያ እና የግብይት ተግዳሮቶችን ለመፍታት እንዲሁም አዳዲስ መፍትሄዎችን ለማምጣት ያስችላል ያለውን "ቪዛ በየትኛውም ቦታ (VEI)" የተሰኘ የፊንቴክ ውድድር በይፋ አስጀምሯል፡፡
የቪዛ መካከለኛው እና የምስራቅ አውሮፓ፣ የመካከለኛው ምስራቅ እና አፍሪካ ቢሮ ፕሬዝዳንት አንድሪው ቶሬ፤ በሰኔ ወር በኢትዮጵያ ባደረጉት ጉብኝት ቪዛ የዲጂታል ክፍያዎችን ለማስፋፋት ያለውን ቁርጠኝነት አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለጽ፤ የፊንቴክ ፈጠራን ለማስፋፋት እና በሴቶች የሚመሩ አነስተኛ እና መካከለኛ ቢዝነሶችን ለማገዝ አዳዲስ ውጥኖች መያዙን ማስታወቃቸው ይታወሳል፡፡
ይህም እቅድ በአገር ውስጥ ለኹለተኛ ጊዜ የቪዛ ለኹሉም ፊንቴክ ውድድርን ለማዘጋጀት እና የቪዛን ‘ቀጣይ እሷ ናት’ የሴቶችን ማጎልበት ፕሮጀክት ማስጀመርን እንደሚያካትት ገልጸዋል።
“የ"ቪዛ በየትኛውም ቦታ" (Visa Everywhere Initiative) ለፊንቴክ እና ለሥራ ፈጣሪዎች በክፍያ እና በንግድ ዓለም ላይ ተጨባጭ እና ውጤታማ መፍትሄዎችን እንዲያስገኙ የሚያስችል መድረክ ነው" ሲሉ የቪዛ የኢትዮጵያ ቢሮ ኃላፊ ያሬድ እንዳለ ተናግረዋል።
ፊንቴክ እና ሌሎች የክፍያ ስርዓት ፈጣሪዎች፣ ሸማቾች እና ነጋዴዎች ክፍያ የሚፈጽሙበትን መንገድ በመቀየር ብዙ ሰዎች የሚፈልጉትን ገንዘብ በሚፈልጉበት ጊዜ በቀላሉ ማግኘት እንዲችሉ ማድረጉንም አስረድተዋል።
የዘንድሮው "ቪዛ በየትኛውም ቦታ (VEI)" ኢትዮጵያ የፍፃሜ ውድድር በመስከረም ወር የሚካሄድ ሲሆን፤ በድምሩ 50 ሺሕ ዶላር በተለያየ ደረጃ ለሚያሸንፉ ተወዳዳሪዎች እንደሚሰጥ ተነግሯል።
ይህም 1ኛ ደረጃ 25 ሺሕ ዶላር፣ 2ኛ ደረጃ 15 ሺሕ ዶላር እና 3ኛ ደረጃ 10 ሺሕ ዶላር ተሸላሚ ያደርጋል ተብሏል፡፡
ከገንዘብ ሽልማቶች በተጨማሪ፣ አሸናፊዎች ባንኮች፣ ነጋዴዎች፣ ቬንቸር ካፒታሊስቶች እና የመንግሥት አካላት የሚገኙበትን የቪዛን ሰፊ የአጋሮች መረብ ውስጥ የመካተት እና የመታወቅ እድል ያገኛሉ የተባለ ሲሆን፤ ዓለም አቀፍ ከሆኑ ታዋቂ ድርጅቶች እውቅና ማግኘት እንደሚችሉም ተነግሯል፡፡
የ"ቪዛ በየትኛውም ቦታ (VEI)" ውድድር በተለያዩ ዘርፎች የሚገኙ ንግዶች የሚያጋጥሟቸውን የክፍያ እና የግብይት ተግዳሮቶች በመፍታት ማህበረሰቡን የሚያግዙ እና በኹሉም ዘርፍ እና ደረጃ የሚገኙ አዳዲስ እና ትልቅ ሥራ ፈጣሪዎችን እንደሚያሳትፍ ተገልጿል፡፡
በዚህ መሰረት የቪዛ ለኹሉም ውድድር ምዝገባ የሚጠናቀቀው ነሀሴ 14 መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ተወዳዳሪዎች https://africa.visa.com/visa-everywhere/everywhere-initiative/initiative.html ሊንክን በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል፡፡በ2013 የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሽያጭ የክፍያ ስርዓት ኦፕሬተር በመሆን፤ የመጀመሪያውን "ቪዛ በየትኛውም ቦታ" ኢትዮጵያ ውድድርን አሪፍፔይ ማሸነፉ ይታወሳል።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FkerAssefa
❤2
የሩዋንዳ ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ ለሴት ልጃቸው ከፍተኛ ሹመት ሰጡ!
የሩዋንዳው ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ ሴት ልጃቸውን በቢሯቸው ውስጥ ቁልፍ ቦታ ላይ ሾመዋል። የ29 ዓመቷ አንጌ ካጋሜ የስትራቴጂ እና የፖሊሲ ምክር ቤት ሀላፊ ምክትል ስራ አስፈፃሚ ሆነው መሾሟን ፕሬዝዳንት ካጋሜ የመሩት የካቢኔ ስብሰባ ማክሰኞ እለት በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።
በመግለጫው በኢትዮጵያ፣ ሞሮኮ፣ ግብፅ እና ጊኒ አዳዲስ አምባሳደሮችን ጨምሮ ሌሎች ሹመቶችን ይፋ አድርጓል። የካጋሜ ሴት ልጅ ከ 2019 ጀምሮ በፕሬዚዳንት ቢሮ ውስጥ በከፍተኛ የፖሊሲ ተንታኝ ሆነና በመስራት ላይ ትገኛለች።
ከአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች የፖለቲካ ሳይንስ እና የአለም አቀፍ ጉዳዮች ዲግሪን አግኝታለች። ሌሎች ሁለት የፕሬዚዳንት ካጋሜ ልጆች በመንግስት ስልጣን ውስጥ ቦታ ይዘዋል።
የበኩር ልጃቸው ኢቫን ካጋሜ እ.ኤ.አ. በ2020 የሩዋንዳ ልማት ቦርድ ሰብሳቢ ተደርገው የተሾመ ሲሆን በግሉ ዘርፍ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገትን የማስመዝገብ ኃላፊነት ተሰጥቶታል። ሦስተኛው ልጃቸው ኢያን የሩዋንዳ መከላከያ ኃይል መኮንን ሲሆን ባለፈው ዓመት በፕሬዚዳንቱ ጠባቂነት ተመድበዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የሩዋንዳው ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ ሴት ልጃቸውን በቢሯቸው ውስጥ ቁልፍ ቦታ ላይ ሾመዋል። የ29 ዓመቷ አንጌ ካጋሜ የስትራቴጂ እና የፖሊሲ ምክር ቤት ሀላፊ ምክትል ስራ አስፈፃሚ ሆነው መሾሟን ፕሬዝዳንት ካጋሜ የመሩት የካቢኔ ስብሰባ ማክሰኞ እለት በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።
በመግለጫው በኢትዮጵያ፣ ሞሮኮ፣ ግብፅ እና ጊኒ አዳዲስ አምባሳደሮችን ጨምሮ ሌሎች ሹመቶችን ይፋ አድርጓል። የካጋሜ ሴት ልጅ ከ 2019 ጀምሮ በፕሬዚዳንት ቢሮ ውስጥ በከፍተኛ የፖሊሲ ተንታኝ ሆነና በመስራት ላይ ትገኛለች።
ከአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች የፖለቲካ ሳይንስ እና የአለም አቀፍ ጉዳዮች ዲግሪን አግኝታለች። ሌሎች ሁለት የፕሬዚዳንት ካጋሜ ልጆች በመንግስት ስልጣን ውስጥ ቦታ ይዘዋል።
የበኩር ልጃቸው ኢቫን ካጋሜ እ.ኤ.አ. በ2020 የሩዋንዳ ልማት ቦርድ ሰብሳቢ ተደርገው የተሾመ ሲሆን በግሉ ዘርፍ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገትን የማስመዝገብ ኃላፊነት ተሰጥቶታል። ሦስተኛው ልጃቸው ኢያን የሩዋንዳ መከላከያ ኃይል መኮንን ሲሆን ባለፈው ዓመት በፕሬዚዳንቱ ጠባቂነት ተመድበዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
በትግራይ ክልል የሚገኙ የሜቴክ ሠራተኞች ለኹለት ዓመታት ደሞዝ እንዳልተከፈላቸው ተናገሩ
በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ የሚገኘው የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ሜቴክ ሠራተኞች ለ24 ወራት ደምወዝ እንዳልተከፈላቸው እና በዚሁ ምክንያት ለከፋ ረሀብ መጋለጣቸውን ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።
ለኹለት ዓመት ደሞዝ ያልተከፈላቸው ሠራተኞች በኢንጂነሪንግ ግሩፑ ሥር ከሚገኙ ፋብሪካዎች መካከል የመቀሌ ኢንጂነሪንግ ፋብሪካ፣ ውቅሮ ኮንስትራክሽን ማሽነሪ ማምረቻ እና መገጣጠሚያ ፋብሪካ እንዲሁም መቀሌ ኢንጂን ፋብሪካ ከ440 በላይ ሠራተኞች መሆናቸው ተገልጿል።
በፋብሪካዎቹ የሚሰሩት ሠራተኞች አብዛኞቹ የቤተሰብ አስተዳዳሪ እና ሌላ የገቢ ምንጭ የሌላቸው በመሆኑ ለከፍተኛ ረሀብ እና ችግር መዳረጋቸውን ነው የገለጹት።
@Yenetube @Fikerassefa
በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ የሚገኘው የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ሜቴክ ሠራተኞች ለ24 ወራት ደምወዝ እንዳልተከፈላቸው እና በዚሁ ምክንያት ለከፋ ረሀብ መጋለጣቸውን ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።
ለኹለት ዓመት ደሞዝ ያልተከፈላቸው ሠራተኞች በኢንጂነሪንግ ግሩፑ ሥር ከሚገኙ ፋብሪካዎች መካከል የመቀሌ ኢንጂነሪንግ ፋብሪካ፣ ውቅሮ ኮንስትራክሽን ማሽነሪ ማምረቻ እና መገጣጠሚያ ፋብሪካ እንዲሁም መቀሌ ኢንጂን ፋብሪካ ከ440 በላይ ሠራተኞች መሆናቸው ተገልጿል።
በፋብሪካዎቹ የሚሰሩት ሠራተኞች አብዛኞቹ የቤተሰብ አስተዳዳሪ እና ሌላ የገቢ ምንጭ የሌላቸው በመሆኑ ለከፍተኛ ረሀብ እና ችግር መዳረጋቸውን ነው የገለጹት።
@Yenetube @Fikerassefa
በትግራይ ክልል ትላንት እና ዛሬ ለሶስት ጊዜ ያህል የመሬት መንቀጥቀጥ ያስከተለው ንዝረት መከሰቱ ተገለጸ!
በትግራይ ክልል የተለያዩ ከተሞች ትላንት ምሽት እና ዛሬ ጠዋት፤ ለሶስት ጊዜ ያህል የመሬት መንቀጥቀጥ ያስከተለው ንዝረት መከሰቱን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጂኦፊዚክስ፣ ህዋ ሳይንስ እና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። በክልሉ ዋና ከተማ መቐለ እና በሌሎች አራት ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎች ንዝረቱ በአካባቢያቸው ማጋጠሙን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል።
ይህን ንዝረት ያስከተለው የመጀመሪያው እና ዋናው የመሬት መንቀጥቀጥ ትላንት ማክሰኞ ሐምሌ 25፤ 2015 የተከሰተው፤ በኤርትራ ባህር ዳርቻ ዳህላክ ደሴት አካባቢ መሆኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሶሲሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ ፕሮፌሰር አታላይ አየለ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል። በሬክተር ስኬል 5.4 ሆኖ የተለካው ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ የተመዘገበው፤ ትላንት ምሽት ሁለት ሰዓት ከ15 ደቂቃ ላይ እንደነበር በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስር ባለ ኢንስቲትዩት የመሬት መንቀጥቀጥን የሚያጠናውን የትምህርት ክፍል የሚመሩት ፕሮፌሰር አታላይ አስረድተዋል።
የትላንቱ የመሬት መንቀጥቀጥ “መለስተኛ” (moderate) የሚባል ምድብ ውስጥ የሚወድቅ ቢሆንም “የሚናቅ” እንዳልሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ ተመራማሪ እና ባለሙያው ተናግረዋል።“ይህንን ያህል መጠን ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ አዲስ አበባ [ከተማ ውስጥ] ቢፈጠር ብዙ ህንጻዎች ይወድማሉ” ሲሉ ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት ፕሮፌሰር አታላይ አነጻጽረዋል።
[Ethiopia Insider]
@YeneTube @FikerAssefa
በትግራይ ክልል የተለያዩ ከተሞች ትላንት ምሽት እና ዛሬ ጠዋት፤ ለሶስት ጊዜ ያህል የመሬት መንቀጥቀጥ ያስከተለው ንዝረት መከሰቱን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጂኦፊዚክስ፣ ህዋ ሳይንስ እና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። በክልሉ ዋና ከተማ መቐለ እና በሌሎች አራት ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎች ንዝረቱ በአካባቢያቸው ማጋጠሙን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል።
ይህን ንዝረት ያስከተለው የመጀመሪያው እና ዋናው የመሬት መንቀጥቀጥ ትላንት ማክሰኞ ሐምሌ 25፤ 2015 የተከሰተው፤ በኤርትራ ባህር ዳርቻ ዳህላክ ደሴት አካባቢ መሆኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሶሲሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ ፕሮፌሰር አታላይ አየለ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል። በሬክተር ስኬል 5.4 ሆኖ የተለካው ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ የተመዘገበው፤ ትላንት ምሽት ሁለት ሰዓት ከ15 ደቂቃ ላይ እንደነበር በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስር ባለ ኢንስቲትዩት የመሬት መንቀጥቀጥን የሚያጠናውን የትምህርት ክፍል የሚመሩት ፕሮፌሰር አታላይ አስረድተዋል።
የትላንቱ የመሬት መንቀጥቀጥ “መለስተኛ” (moderate) የሚባል ምድብ ውስጥ የሚወድቅ ቢሆንም “የሚናቅ” እንዳልሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ ተመራማሪ እና ባለሙያው ተናግረዋል።“ይህንን ያህል መጠን ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ አዲስ አበባ [ከተማ ውስጥ] ቢፈጠር ብዙ ህንጻዎች ይወድማሉ” ሲሉ ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት ፕሮፌሰር አታላይ አነጻጽረዋል።
[Ethiopia Insider]
@YeneTube @FikerAssefa
👍2
በጋምቤላ ክልል ተጥሎ የነበረው የሰዓት ዕላፊ ገደብ ማሻሻያ ተደረገ!
የክልሉን ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ በማስመልከት በካቢኔ አባላቱ ተጥሎ የነበረው የሰዓት ገደብ አመሻሹ ላይ ባካሄዱት አስቸኳይ ስብሰባ ነዉ ዉሳኔዉን ያሳለፉት።
በክልሉ በተከሰተው የፀጥታ ችግር ምክንያት ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ላልተወሰነ ጊዜ የሚተገበር የሰዓት እላፊ ገደብ መጣሉን ብስራት ራዲዮ እና ቴቪ መዘገቡ ይታወሳል። በመሆኑም የክልሉ ካቢኔ የፀጥታ ሁኔታው እየተሻሻለ መምጣቱን በማስመልከት የሰውና ተሽከርካሪን እንቅስቃሴ የሰዓት ማሻሻያ ማድረጉን አሳዉቋል።
በዚህም መሰረት የባለ ሁለትና ባለሶስት እግር ባጃጅና ሞተር ተሽከርካሪዎች ከጠዋቱ 12:00 ስዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 12:30 እንዲሰሩ ማሻሻያ ተደርጓል።
የሰዎችን እንቅስቃሴ በሚመለከትም የካቢኔ አባላቱ ባሳለፉት ውሳኔ እስከ ምሽት 3 ሰዓት ድረስ መንቀሳቀስ እንደሚቻል ተወስኗል።በጋምቤላ ክልል በተከሰተዉ ግጭት ቁጥራቸው ከ 30 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ እና በ አራት ቀበሌዎች የሚኖሩ ሰዎች ሙሉ በሙሉ መፈናቀላቸውን ብስራት ራዲዮ እና ቴቪ መዘገቡ ይታወሳል።
@YeneTube @FikerAssefa
የክልሉን ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ በማስመልከት በካቢኔ አባላቱ ተጥሎ የነበረው የሰዓት ገደብ አመሻሹ ላይ ባካሄዱት አስቸኳይ ስብሰባ ነዉ ዉሳኔዉን ያሳለፉት።
በክልሉ በተከሰተው የፀጥታ ችግር ምክንያት ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ላልተወሰነ ጊዜ የሚተገበር የሰዓት እላፊ ገደብ መጣሉን ብስራት ራዲዮ እና ቴቪ መዘገቡ ይታወሳል። በመሆኑም የክልሉ ካቢኔ የፀጥታ ሁኔታው እየተሻሻለ መምጣቱን በማስመልከት የሰውና ተሽከርካሪን እንቅስቃሴ የሰዓት ማሻሻያ ማድረጉን አሳዉቋል።
በዚህም መሰረት የባለ ሁለትና ባለሶስት እግር ባጃጅና ሞተር ተሽከርካሪዎች ከጠዋቱ 12:00 ስዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 12:30 እንዲሰሩ ማሻሻያ ተደርጓል።
የሰዎችን እንቅስቃሴ በሚመለከትም የካቢኔ አባላቱ ባሳለፉት ውሳኔ እስከ ምሽት 3 ሰዓት ድረስ መንቀሳቀስ እንደሚቻል ተወስኗል።በጋምቤላ ክልል በተከሰተዉ ግጭት ቁጥራቸው ከ 30 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ እና በ አራት ቀበሌዎች የሚኖሩ ሰዎች ሙሉ በሙሉ መፈናቀላቸውን ብስራት ራዲዮ እና ቴቪ መዘገቡ ይታወሳል።
@YeneTube @FikerAssefa
የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በዓመቱ ውስጥ ከሩብ ሚሊዮን በላይ የዜጎችን አቤቱታ እንደተቀበለ ገለጸ!
የኢትዮጵያ የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም፣ ይፋ ባደረገው የ2015 ዓ.ም. የአፈጻጸም ሪፖርቱ፣ በዓመቱ በልዩ ልዩ ዘርፎች “ችግር ደርሶብናል፤” ያሉ፣ ከ277 ሺሕ በላይ ዜጎች፣ ለተቋሙ አቤቱታ እንዳቀረቡ አስታወቀ፡፡
የተቋሙ ዋና እንባ ጠባቂ ዶር. እንዳለ ኀይሌ፣ ስለ ሪፖርቱ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ማብራሪያ፣ ዘንድሮ በዜጎች የቀረበው የአቤቱታ ብዛት፣ ካለፉት ዓመታት ጋራ ሲነጻጸር፣ ከፍተኛ እንደኾነ ተናግረዋል፡፡
ተቋሙ፣ አቤቱታዎችን እየመረመረ ውሳኔ እንደሚሰጥ የጠቀሱት ዋና እንባ ጠባቂው፣ ውሳኔውን ባልተገበሩ የመንግሥት አስፈጻሚዎች ላይ፣ ክሥ እንደመሠረተም አመልክተዋል።
Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም፣ ይፋ ባደረገው የ2015 ዓ.ም. የአፈጻጸም ሪፖርቱ፣ በዓመቱ በልዩ ልዩ ዘርፎች “ችግር ደርሶብናል፤” ያሉ፣ ከ277 ሺሕ በላይ ዜጎች፣ ለተቋሙ አቤቱታ እንዳቀረቡ አስታወቀ፡፡
የተቋሙ ዋና እንባ ጠባቂ ዶር. እንዳለ ኀይሌ፣ ስለ ሪፖርቱ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ማብራሪያ፣ ዘንድሮ በዜጎች የቀረበው የአቤቱታ ብዛት፣ ካለፉት ዓመታት ጋራ ሲነጻጸር፣ ከፍተኛ እንደኾነ ተናግረዋል፡፡
ተቋሙ፣ አቤቱታዎችን እየመረመረ ውሳኔ እንደሚሰጥ የጠቀሱት ዋና እንባ ጠባቂው፣ ውሳኔውን ባልተገበሩ የመንግሥት አስፈጻሚዎች ላይ፣ ክሥ እንደመሠረተም አመልክተዋል።
Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል በሚገኙ በርካታ ከተሞች ‹‹ የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡን ›› የአካባቢው ነዋሪዎች ገለፁ፡፡
በክልሉ በመከላከያ ሰራዊትና ራሳቸውን ፋኖ ሲሉ በሚጠሩ ታጣቂዎች መካከል እየተካሄደ ባለው ውግያ ምክንያት ከትናንት ረቡዕ ከምሽት ሦስት ሰዓት ጀምሮ የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡን የክልሉ የተለያዩ ከተማ ነዋሪዎች ገልፀዋል፡፡
ነዋሪዎች እንደሚሉት ዛሬም ድረስ በአንድንድ አካባቢዎች ውግያው የቀጠለ ሲሆን በአንፃሩ እንደ ቆቦና ወልዲያ ባሉ ከተሞች ደግሞ አንፃራዊ ሰላም ሰፍኗል፡፡
ለአሻም አስተያየታቸውን የሰጡ ነዋሪዎች በቆቦ፣ ወልዲያ፣ ላሊበላ፣ ጎንደርና ደምበጫ ከተሞች የኢንተርኔት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ መቋረጡን ተናግረዋል፡፡የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጥን በተመለከተ ኢትዮ-ቴሌኮም ከዚህ ቀደም እንደተናገረው ‹‹ ጉዳዩ ከተቋሙ አቅም በላይ መሆኑን ›› አመልክቷል፡፡
የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ፍሬሕይወት ታምሩ በባለፈው የሰኔ ወር የተቋማቸውን የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ባቀረቡበት ወቅት ‹‹ የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጥን ›› በተመለከተ ከአባላቱ በኩል ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር፡፡
ፍሬሕይወት በወቅቱ በሰጡት ምላሽ ‹‹ የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጥን የሚመለከተው መንግስት ›› መሆኑን ጠቅሰው ‹‹ ከተቋማቸው አቅም በላይ ›› መሆኑን የሚያሳብቅ ምላሽ መሰጠታቸው ይታወሳል፡፡ ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ከመንግስት ይበሉ እንጂ የትኛው የመንግስት ተቋም እንደሆነ በወቅቱ አልገለፁም፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
በክልሉ በመከላከያ ሰራዊትና ራሳቸውን ፋኖ ሲሉ በሚጠሩ ታጣቂዎች መካከል እየተካሄደ ባለው ውግያ ምክንያት ከትናንት ረቡዕ ከምሽት ሦስት ሰዓት ጀምሮ የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡን የክልሉ የተለያዩ ከተማ ነዋሪዎች ገልፀዋል፡፡
ነዋሪዎች እንደሚሉት ዛሬም ድረስ በአንድንድ አካባቢዎች ውግያው የቀጠለ ሲሆን በአንፃሩ እንደ ቆቦና ወልዲያ ባሉ ከተሞች ደግሞ አንፃራዊ ሰላም ሰፍኗል፡፡
ለአሻም አስተያየታቸውን የሰጡ ነዋሪዎች በቆቦ፣ ወልዲያ፣ ላሊበላ፣ ጎንደርና ደምበጫ ከተሞች የኢንተርኔት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ መቋረጡን ተናግረዋል፡፡የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጥን በተመለከተ ኢትዮ-ቴሌኮም ከዚህ ቀደም እንደተናገረው ‹‹ ጉዳዩ ከተቋሙ አቅም በላይ መሆኑን ›› አመልክቷል፡፡
የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ፍሬሕይወት ታምሩ በባለፈው የሰኔ ወር የተቋማቸውን የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ባቀረቡበት ወቅት ‹‹ የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጥን ›› በተመለከተ ከአባላቱ በኩል ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር፡፡
ፍሬሕይወት በወቅቱ በሰጡት ምላሽ ‹‹ የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጥን የሚመለከተው መንግስት ›› መሆኑን ጠቅሰው ‹‹ ከተቋማቸው አቅም በላይ ›› መሆኑን የሚያሳብቅ ምላሽ መሰጠታቸው ይታወሳል፡፡ ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ከመንግስት ይበሉ እንጂ የትኛው የመንግስት ተቋም እንደሆነ በወቅቱ አልገለፁም፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
በ2015 በጀት ዓመት ለአዲስ አበባ ከተማ የመንግሥት ሠራተኞች ሁለት ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ብር የቤት ኪራይ ድጎማ መደረጉን የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ሂክማ ከይረዲን የበጀት ዓመቱን የሥራ እንቅስቃሴ አስመልክተው ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ከቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ ከሠራተኞች ጥያቄ ሲነሳ እንደነበር ጠቅሰዋል። የከተማ አስተዳደሩ አመራር ውይይት አድርጎ አቅም በፈቀደ መጠን ሁለት ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ብር የቤት ኪራይ ድጎማ መደረጉን ገልጸዋል። ይህም ሠራተኞች ያላቸውን የክፍያ ምጣኔ ታሳቢ ያደረገና እስከ አንድ ሺህ 500ብር እንደሆነ ጠቁመው፤ ይህ አሁን ያለውን መሠረታዊ የቤት ኪራይ ክፍያ ጥያቄ የሚፈታ ባይሆንም በተወሰነ ደረጃ ችግሩን ማቃለል ያስቻለ ነው ብለዋል።
ከኑሮ ውድነቱ ጋር ተያይዞ ሠራተኛው የሚያነሳቸው ጥያቄዎች እንዳሉ የገለጹት ኃላፊዋ፤ በሁሉም የመንግሥት መስሪያ ቤት ካፍቴሪያዎች ላይ የሚከፈሉ ክፍያዎችን በተወሰነ መጠን መንግሥት መደጎም መቻል እንዳለበት ታምኖ በ2015 መመሪያ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ እንደተገባ አስታውቀዋል።ይህም ሁሉንም ሠራተኛ ታሳቢ የደረገና በአንድ ሠራተኛ የ20 ብር ድጎማ እንደሆነ ገልጸዋል። በሂደቱ መንግሥት ከ20 ብሩ ድጎማ ባሻገር ለካፍቴሪያ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችንና መሰረተ ልማቶችን የማሟላት ሥራ እንደሚፈጽምም ጠቁመዋል።
ሙሉውን ለማንበብ: https://press.et/?p=106158
@YeneTube @FikerAssefa
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ሂክማ ከይረዲን የበጀት ዓመቱን የሥራ እንቅስቃሴ አስመልክተው ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ከቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ ከሠራተኞች ጥያቄ ሲነሳ እንደነበር ጠቅሰዋል። የከተማ አስተዳደሩ አመራር ውይይት አድርጎ አቅም በፈቀደ መጠን ሁለት ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ብር የቤት ኪራይ ድጎማ መደረጉን ገልጸዋል። ይህም ሠራተኞች ያላቸውን የክፍያ ምጣኔ ታሳቢ ያደረገና እስከ አንድ ሺህ 500ብር እንደሆነ ጠቁመው፤ ይህ አሁን ያለውን መሠረታዊ የቤት ኪራይ ክፍያ ጥያቄ የሚፈታ ባይሆንም በተወሰነ ደረጃ ችግሩን ማቃለል ያስቻለ ነው ብለዋል።
ከኑሮ ውድነቱ ጋር ተያይዞ ሠራተኛው የሚያነሳቸው ጥያቄዎች እንዳሉ የገለጹት ኃላፊዋ፤ በሁሉም የመንግሥት መስሪያ ቤት ካፍቴሪያዎች ላይ የሚከፈሉ ክፍያዎችን በተወሰነ መጠን መንግሥት መደጎም መቻል እንዳለበት ታምኖ በ2015 መመሪያ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ እንደተገባ አስታውቀዋል።ይህም ሁሉንም ሠራተኛ ታሳቢ የደረገና በአንድ ሠራተኛ የ20 ብር ድጎማ እንደሆነ ገልጸዋል። በሂደቱ መንግሥት ከ20 ብሩ ድጎማ ባሻገር ለካፍቴሪያ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችንና መሰረተ ልማቶችን የማሟላት ሥራ እንደሚፈጽምም ጠቁመዋል።
ሙሉውን ለማንበብ: https://press.et/?p=106158
@YeneTube @FikerAssefa
❤1
ሐሙስ ሐምሌ 27 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በተደረገ ውጊያ ወደ ላሊበላ የሚደረግ የአየር በረራ መቋረጡን የላሊበላ ኤርፖርት ሠራተኞች ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል፡፡
በተጨማሪም በጎንደር ከተማ ከትናንት ጀምሮ በመንግሥት የጸጥታ አካላትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል እየተደረገ ባለው ውጊያ ምክንያት በዛሬው ዕለት ወደ ጎንደር የሚደረግ የአየር በረራ አለመኖሩን አዲስ ማለዳ አረጋግጣለች።
ዛሬ ረፋድ ላይም በጎንደር አየር ማረፊያ አቅራቢያ የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ መሆኑን ነው መረዳት የተቻለው።
የላሊበላ አየር ማረፊያ ሠራተኞች ወደ ላሊበላ በቀን ከሚደረጉ ኹለት በረራዎች የመጀመሪያው ማክሰኞ ሐምሌ 25/2015 ጠዋት ላይ መደረጉን ገልጸው፤ “ተጨማሪ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ላሊበላ አየር ማረፊያ ሊገቡ ነው” የሚል ወሬ የሰሙ የፋኖ ታጣቂዎች ወደ ሥፍራው አቅንተው ጥበቃ ላይ ከነበሩ የፌዴራል ፖሊስ አባላት ጋር የተኩስ ልውውጥ ሲያደርጉ እንደነበር ጠቅሰዋል።
ይህን ተከትሎም በኹለተኛው በረራ ከቀኑ 6 ሰዓት ከ50 ላይ ላሊበላ ኤርፖርት ማረፍ የነበረበት የመንገደኞች አውሮፕላን ካለው የጸጥታ ስጋት አንጻር ሳያርፍ መመለሱን ገልጸዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
በተጨማሪም በጎንደር ከተማ ከትናንት ጀምሮ በመንግሥት የጸጥታ አካላትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል እየተደረገ ባለው ውጊያ ምክንያት በዛሬው ዕለት ወደ ጎንደር የሚደረግ የአየር በረራ አለመኖሩን አዲስ ማለዳ አረጋግጣለች።
ዛሬ ረፋድ ላይም በጎንደር አየር ማረፊያ አቅራቢያ የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ መሆኑን ነው መረዳት የተቻለው።
የላሊበላ አየር ማረፊያ ሠራተኞች ወደ ላሊበላ በቀን ከሚደረጉ ኹለት በረራዎች የመጀመሪያው ማክሰኞ ሐምሌ 25/2015 ጠዋት ላይ መደረጉን ገልጸው፤ “ተጨማሪ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ላሊበላ አየር ማረፊያ ሊገቡ ነው” የሚል ወሬ የሰሙ የፋኖ ታጣቂዎች ወደ ሥፍራው አቅንተው ጥበቃ ላይ ከነበሩ የፌዴራል ፖሊስ አባላት ጋር የተኩስ ልውውጥ ሲያደርጉ እንደነበር ጠቅሰዋል።
ይህን ተከትሎም በኹለተኛው በረራ ከቀኑ 6 ሰዓት ከ50 ላይ ላሊበላ ኤርፖርት ማረፍ የነበረበት የመንገደኞች አውሮፕላን ካለው የጸጥታ ስጋት አንጻር ሳያርፍ መመለሱን ገልጸዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
‹‹ መንግስት የታገቱት ያሉበትን ያሳውቀን ›› የታጋች ቤተሰቦች
‹‹ ባለፈው ሰኞ የታገቱ 62 ሰዎችን ለማስለቀቅ ከፍተኛ ጥረት እያደረግሁ ነው ›› - የፌደራል ፖሊስ
ባለፈው ሰኞ ሐምሌ 24 ቀን 2015 ዓ.ም ከባህርዳር ወደ አዲስ አበባ ለመምጣት ጉዞ የጀመረ ‹‹ ታታ ›› የሕዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪ ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች በታጣቂዎች እገታ እንደተፈፀመባቸው › አሻም ከቤተሰቦቻቸው ለመረዳት ችላለች፡፡
‹‹ ታናሽ ወንድሜ ነዉ፤ ዘመድ ለመጠየቅ ነበር ባህርዳር የመጣው፡፡ ስራዉ አዲስ አበባ አንድ የግል ት/ቤት ዉስጥ ጥበቃ ነዉ፡፡ ቤተሰቦቻችን በህይወት የሉም፡፡መንግስት ወንድሞቻችንን ያሉበትን ሁኔታ ያሣዉቀን ›› ሲል አንድ የታጋች ቤተሰብ በአሻም በኩል አቤቱታውን አሰምቷል፡፡
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ጀይላን አብዲ ‹‹ባለፈው ሰኞ የተጋቱት ሰዎች ቁጥር 65 ቢሆንም አሽከርካሪውን ጨምሮ አንድ እናት ልጇ አምልጠው አዲስ አበባ መግባታቸውን›› ለአሻም ነግረዋታል፡፡
በዚህም የታገቾች ቁጥር 63 መሆናቸውን አመልክተው ከአመለጡት ሰዎች በደረሳቸው ጥቆማ መሠረት የታገቱትን ለማስቀቅ ጥረት እያደረጉ መሆኑን ›› ገልፀዋል፡፡የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊው እንደሚሉት ‹‹ በኦሮሚያ ክልል ገብረ ጉረቻ ደብረፅጌ አከባቢ ተደጋጋሚ ዕገታ እንደሚፈፀም ›› ጠቅሰዋል፡፡ይህን ለመከላከል ሕብረተሰቡ ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቀርበዋል፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
‹‹ ባለፈው ሰኞ የታገቱ 62 ሰዎችን ለማስለቀቅ ከፍተኛ ጥረት እያደረግሁ ነው ›› - የፌደራል ፖሊስ
ባለፈው ሰኞ ሐምሌ 24 ቀን 2015 ዓ.ም ከባህርዳር ወደ አዲስ አበባ ለመምጣት ጉዞ የጀመረ ‹‹ ታታ ›› የሕዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪ ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች በታጣቂዎች እገታ እንደተፈፀመባቸው › አሻም ከቤተሰቦቻቸው ለመረዳት ችላለች፡፡
‹‹ ታናሽ ወንድሜ ነዉ፤ ዘመድ ለመጠየቅ ነበር ባህርዳር የመጣው፡፡ ስራዉ አዲስ አበባ አንድ የግል ት/ቤት ዉስጥ ጥበቃ ነዉ፡፡ ቤተሰቦቻችን በህይወት የሉም፡፡መንግስት ወንድሞቻችንን ያሉበትን ሁኔታ ያሣዉቀን ›› ሲል አንድ የታጋች ቤተሰብ በአሻም በኩል አቤቱታውን አሰምቷል፡፡
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ጀይላን አብዲ ‹‹ባለፈው ሰኞ የተጋቱት ሰዎች ቁጥር 65 ቢሆንም አሽከርካሪውን ጨምሮ አንድ እናት ልጇ አምልጠው አዲስ አበባ መግባታቸውን›› ለአሻም ነግረዋታል፡፡
በዚህም የታገቾች ቁጥር 63 መሆናቸውን አመልክተው ከአመለጡት ሰዎች በደረሳቸው ጥቆማ መሠረት የታገቱትን ለማስቀቅ ጥረት እያደረጉ መሆኑን ›› ገልፀዋል፡፡የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊው እንደሚሉት ‹‹ በኦሮሚያ ክልል ገብረ ጉረቻ ደብረፅጌ አከባቢ ተደጋጋሚ ዕገታ እንደሚፈፀም ›› ጠቅሰዋል፡፡ይህን ለመከላከል ሕብረተሰቡ ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቀርበዋል፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ እንዲተገብር የክልሉ መንግስት ጠየቀ!
በአማራ ክልል ያጋጠመውን የፀጥታ መደፍረስ በመደበኛ የህግ ማስከበር ሥርዓት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ እንዲተገብር የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጠየቀ።
በአማራ ክልል የተከሰተው የሰላም መደፍረስ በክልሉ ከፍተኛ ሰብአዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ እያደረሰ መሆኑን የክልሉ መንግስት አስታውቋል።
የተከሰተውን የፀጥታ ችግር በቁጥጥር ስር ለማዋል እስካሁን በክልሉና በፌደራል የፀጥታ ኃይሎች በኩል በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸው ይታወቃል።
ሆኖም በክልሉ ያለው የፀጥታ መደፍረስና ጥቃት በንፁሃን ዜጎች ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳት በአስቸኳይ ለማስቆም የፌደራል መንግስት ከመደበኛው የህግ ማስከበር ሥርዓት ባሻገር በኢፌዴሪ ህገ መንግስት መሰረት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ በአፋጣኝ እንዲተገበር ነው የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የጠየቀው።
ክልሉ ወደ ቀደመ መረጋጋቱ እንዲመለስ ዜጎች ሰላማቸው ተመልሶ አርሶአደሩ ወደ እርሻው ክልሉም ወደ ልማት ስራዎች ፊቱን እንዲያዞር ለማድረግ መንግስት ያለበትን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጣ ይገባልም በሚል የፌደራል መንግስትን ጠይቋል።
[Walta]
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል ያጋጠመውን የፀጥታ መደፍረስ በመደበኛ የህግ ማስከበር ሥርዓት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ እንዲተገብር የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጠየቀ።
በአማራ ክልል የተከሰተው የሰላም መደፍረስ በክልሉ ከፍተኛ ሰብአዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ እያደረሰ መሆኑን የክልሉ መንግስት አስታውቋል።
የተከሰተውን የፀጥታ ችግር በቁጥጥር ስር ለማዋል እስካሁን በክልሉና በፌደራል የፀጥታ ኃይሎች በኩል በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸው ይታወቃል።
ሆኖም በክልሉ ያለው የፀጥታ መደፍረስና ጥቃት በንፁሃን ዜጎች ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳት በአስቸኳይ ለማስቆም የፌደራል መንግስት ከመደበኛው የህግ ማስከበር ሥርዓት ባሻገር በኢፌዴሪ ህገ መንግስት መሰረት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ በአፋጣኝ እንዲተገበር ነው የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የጠየቀው።
ክልሉ ወደ ቀደመ መረጋጋቱ እንዲመለስ ዜጎች ሰላማቸው ተመልሶ አርሶአደሩ ወደ እርሻው ክልሉም ወደ ልማት ስራዎች ፊቱን እንዲያዞር ለማድረግ መንግስት ያለበትን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጣ ይገባልም በሚል የፌደራል መንግስትን ጠይቋል።
[Walta]
@YeneTube @FikerAssefa
ቅዱስ ሲኖዶስ በየትኛውም የሀገራችን ክፍል እየተደረጉ ባሉ ግጭቶች ተሳታፊ የሆኑ ወገኖቻችን ካለፈው የጦርነት ውጤት በመማር የተፈጠረውን ችግር በጥበብና በማስተዋል እንዲሁም በሰለጠነ አካሄድና በሰላማዊ መንገድ ተወያይተው እንዲፈቱ ጥሪ አቀረበ!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ወቅታዊ ሀገራዊ ሰላምን በተመለከተ አጀንዳ በመቅረጽ በጉዳዩ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ መግለጫ ሰጥቷል ፤ በመግለጫውም በአሁኑ ወቅት በሀገራችን በተለያዩ ቦታዎች እየተከሰተ ባለው የሰላም መደፍረስና የእርስ በርስ ግጭቶች ምክንያት የበርካታ ወገኖቻችን ውድ ሕይወት እያለፈ እና በርካታ የሀገርና የሕዝብ ሀብትና ንብረት እየወደመ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያናችን የተሰማትን ጥልቅ ሐዘን ትገልጻለች ብሏል።
ሰላም ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ፍጡራን መሠረታዊ ጉዳይ ነው፡፡ ሰላም ከሌለ ቀድሶ ማቁረብ፣ ነግዶ ማትረፍ፣ አርሶ ማምረት፣ ተምሮ ማስተማር ወልዶ ማሳደግ፣ ወጥቶ መግባት፣ አገር መምራትና ማስተዳደር አይቻልም ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅሉ ሰላም ሲጠፋ አብረው የሚጠፉ መልካም እሴቶቻችን ብዙ ናቸው፡፡ በቅርብ ጊዜ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረው ጦርነት የበርካታ ወገኖቻችንን ሕይወት የቀጠፈ ከመሆኑም በላይ ከሞት የተረፉት ወገኖቻችንም ለስደትና ለረሀብ የዳረገ፣ ለአካልና ለእእምሮ ስብራት ያጋለጠ ከመሆኑም በተጨማሪ በርካታ አድባራትና ገዳማትን እንዲሁም አብያተ ክርስቲያናትን ያፈረሰ እና መተኪያ የሌላቸውን ውድ ቅርሶቻችንን ያወደመ እጅግ በጣም አስከፊ ተግባር መሆኑ ይታወሳል።
በመሆኑም፡-
በሀገራችን በኢትዮጵያ የተከሰተው የእርስ በርስ ጦርነትና ግጭት ተወግዶ ሰላምና አንድነት እንዲሰፍን ከሁሉም በላይ እግዚአብሔርን በጾምና በጸሎት ልንማጸን ይገባል ሲል የገለጸ ሲሆን በሀገራችን በኢትዮጵያ አሁን ያለው የሰላም እጦትና የእርስ በርስ ግጭት ወደፊት ሊያስከትል የሚችለው ችግር ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ለአገራዊ ሰላም የበኩላቸውን ጥረት እንድታደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ መልእክቱን አስተላልፏል።
ቅዱስ ሲኖዶስ በመጨረሻም በየትኛውም የሀገራችን ክፍል እየተደረጉ ባሉ ግጭቶች ተሳታፊ የሆኑ ወገኖቻችን ካለፈው የጦርነት ውጤት በመማር የተፈጠረውን ችግር በጥበብና በማስተዋል እንዲሁም በሰለጠነ አካሄድና በሰላማዊ መንገድ ተወያይተው እንዲፈቱ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሰላም ጥሪዋን ከአደራ ጋር ታስተላልፋለች ሲል መልዕክቱን ማስተላለፉ ተገልጿል።
ሐምሌ 27 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ወቅታዊ ሀገራዊ ሰላምን በተመለከተ አጀንዳ በመቅረጽ በጉዳዩ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ መግለጫ ሰጥቷል ፤ በመግለጫውም በአሁኑ ወቅት በሀገራችን በተለያዩ ቦታዎች እየተከሰተ ባለው የሰላም መደፍረስና የእርስ በርስ ግጭቶች ምክንያት የበርካታ ወገኖቻችን ውድ ሕይወት እያለፈ እና በርካታ የሀገርና የሕዝብ ሀብትና ንብረት እየወደመ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያናችን የተሰማትን ጥልቅ ሐዘን ትገልጻለች ብሏል።
ሰላም ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ፍጡራን መሠረታዊ ጉዳይ ነው፡፡ ሰላም ከሌለ ቀድሶ ማቁረብ፣ ነግዶ ማትረፍ፣ አርሶ ማምረት፣ ተምሮ ማስተማር ወልዶ ማሳደግ፣ ወጥቶ መግባት፣ አገር መምራትና ማስተዳደር አይቻልም ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅሉ ሰላም ሲጠፋ አብረው የሚጠፉ መልካም እሴቶቻችን ብዙ ናቸው፡፡ በቅርብ ጊዜ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረው ጦርነት የበርካታ ወገኖቻችንን ሕይወት የቀጠፈ ከመሆኑም በላይ ከሞት የተረፉት ወገኖቻችንም ለስደትና ለረሀብ የዳረገ፣ ለአካልና ለእእምሮ ስብራት ያጋለጠ ከመሆኑም በተጨማሪ በርካታ አድባራትና ገዳማትን እንዲሁም አብያተ ክርስቲያናትን ያፈረሰ እና መተኪያ የሌላቸውን ውድ ቅርሶቻችንን ያወደመ እጅግ በጣም አስከፊ ተግባር መሆኑ ይታወሳል።
በመሆኑም፡-
በሀገራችን በኢትዮጵያ የተከሰተው የእርስ በርስ ጦርነትና ግጭት ተወግዶ ሰላምና አንድነት እንዲሰፍን ከሁሉም በላይ እግዚአብሔርን በጾምና በጸሎት ልንማጸን ይገባል ሲል የገለጸ ሲሆን በሀገራችን በኢትዮጵያ አሁን ያለው የሰላም እጦትና የእርስ በርስ ግጭት ወደፊት ሊያስከትል የሚችለው ችግር ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ለአገራዊ ሰላም የበኩላቸውን ጥረት እንድታደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ መልእክቱን አስተላልፏል።
ቅዱስ ሲኖዶስ በመጨረሻም በየትኛውም የሀገራችን ክፍል እየተደረጉ ባሉ ግጭቶች ተሳታፊ የሆኑ ወገኖቻችን ካለፈው የጦርነት ውጤት በመማር የተፈጠረውን ችግር በጥበብና በማስተዋል እንዲሁም በሰለጠነ አካሄድና በሰላማዊ መንገድ ተወያይተው እንዲፈቱ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሰላም ጥሪዋን ከአደራ ጋር ታስተላልፋለች ሲል መልዕክቱን ማስተላለፉ ተገልጿል።
ሐምሌ 27 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
በቅዱስ ሲኖዶሱ የተወገዙ የትግራይ ክልል አባቶች ውሳኔውን እንደሚቃወሙና ዳግም እንዲያጤነው ጠየቁ!
በትግራይ ክልል የሚገኙ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች እና ሓላፊዎች፣ በአክሱም ከተፈጸመው የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ እና ሹመት እንዲሁም፣ ‘መንበረ ሰላማ ከፍተኛ ቤተ ክህነት’ በሚል ከሚያደርጉት ክልላዊ እንቅስቃሴ ጋራ በተያያዘ፣ ትላንት፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተላለፈባቸውን ውግዘት፣ “ከንቱ ውግዘት ነው” ሲሉ እንደማይቀበሉት ገለጹ፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ሐምሌ 16 እና 23 ቀን 2015 ዓ.ም. በአክሱም የተፈጸመውን ሕገ ወጥ የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት የሰጡ እና የተቀበሉ፣ እንዲሁም ‘መንበረ ሰላማ’ በሚል በክርስቲያናዊ ትውፊት የማይታወቅ እንቅስቃሴ ያመነጩ እና ያስተባበሩ፥ አራት ሿሚ ሊቃነ ጳጳሳትን፣ ዘጠኝ ተሿሚ መነኰሳትንና ሁለት ሌሎች ግለሰቦችን፥ ከማዕርገ ክህነታቸው በመሻር፣ ከቤተ ክርስቲያን አገልግሎት እና አባልነት በመለየት ማውገዙን፣ በትላንትናው መግለጫው አስታውቋል፡፡
ለቅዱስ ሲኖዶሱ የውግዘት መግለጫ መልስ የሰጡት፣ በክልሉ የሚገኙ አባቶች፣ ውግዘቱ፥ የትግራይን ሕዝብ ያለአባት ለማስቀረት የተላለፈ እና በጦርነት ጊዜ የተፈጸመው በደል ቅጥያ ነው፤ ብለዋል።
Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
በትግራይ ክልል የሚገኙ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች እና ሓላፊዎች፣ በአክሱም ከተፈጸመው የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ እና ሹመት እንዲሁም፣ ‘መንበረ ሰላማ ከፍተኛ ቤተ ክህነት’ በሚል ከሚያደርጉት ክልላዊ እንቅስቃሴ ጋራ በተያያዘ፣ ትላንት፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተላለፈባቸውን ውግዘት፣ “ከንቱ ውግዘት ነው” ሲሉ እንደማይቀበሉት ገለጹ፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ሐምሌ 16 እና 23 ቀን 2015 ዓ.ም. በአክሱም የተፈጸመውን ሕገ ወጥ የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት የሰጡ እና የተቀበሉ፣ እንዲሁም ‘መንበረ ሰላማ’ በሚል በክርስቲያናዊ ትውፊት የማይታወቅ እንቅስቃሴ ያመነጩ እና ያስተባበሩ፥ አራት ሿሚ ሊቃነ ጳጳሳትን፣ ዘጠኝ ተሿሚ መነኰሳትንና ሁለት ሌሎች ግለሰቦችን፥ ከማዕርገ ክህነታቸው በመሻር፣ ከቤተ ክርስቲያን አገልግሎት እና አባልነት በመለየት ማውገዙን፣ በትላንትናው መግለጫው አስታውቋል፡፡
ለቅዱስ ሲኖዶሱ የውግዘት መግለጫ መልስ የሰጡት፣ በክልሉ የሚገኙ አባቶች፣ ውግዘቱ፥ የትግራይን ሕዝብ ያለአባት ለማስቀረት የተላለፈ እና በጦርነት ጊዜ የተፈጸመው በደል ቅጥያ ነው፤ ብለዋል።
Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
✅✅✅ "Do or Die..!" ✅✅✅
የተዋጣለት የሺያጪ ቻናል ፈልገዋል..!!!
ቤት ...❓
መሬት...❓
መካዝን...❓
ኢንዳስትሪ...❓
ኢንቨስትመንት...❓
ሪል ስቴት ..❓
ለትርፍ የሚሆኑ ለ 2 ..3..የሚከፈሉ ቦታዎችን ፈልገዋል ..❓❓❓
አዲስ አበባ ውስጥ የግዙፍ የግዢ እና የሽያጪ ቻናላችን ነው
..የምትወዱትን ሰው የሆነ ፍጥረት ወደ ቻናሉ ቤተሰብ በማደረግ መረጃን በቤትዎ ያስገቡ ..
መረጃን በቀላሉ እንዲያገኙ በማደረግ ሀላፊነታችሁን ተወጡ..!!!
+251937736408
https://tttttt.me/shger21
Inbox @FikreabAmanu
ለበለጠ መረጃ.. ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://tttttt.me/+U2S2JyiWsfAzNzc0
የተዋጣለት የሺያጪ ቻናል ፈልገዋል..!!!
ቤት ...❓
መሬት...❓
መካዝን...❓
ኢንዳስትሪ...❓
ኢንቨስትመንት...❓
ሪል ስቴት ..❓
ለትርፍ የሚሆኑ ለ 2 ..3..የሚከፈሉ ቦታዎችን ፈልገዋል ..❓❓❓
አዲስ አበባ ውስጥ የግዙፍ የግዢ እና የሽያጪ ቻናላችን ነው
..የምትወዱትን ሰው የሆነ ፍጥረት ወደ ቻናሉ ቤተሰብ በማደረግ መረጃን በቤትዎ ያስገቡ ..
መረጃን በቀላሉ እንዲያገኙ በማደረግ ሀላፊነታችሁን ተወጡ..!!!
+251937736408
https://tttttt.me/shger21
Inbox @FikreabAmanu
ለበለጠ መረጃ.. ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://tttttt.me/+U2S2JyiWsfAzNzc0
"ትልቅሰው ሪል እስቴት "
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
🔥🔥አስቸኳይ ክፍት የስራ ቅጥር💥💥
🔴በሁሉም ስራ ዘርፎች ሰራተኞችን በብዛት እንፈልጋለን።
🔥ቀጥታ ወደ ስራ ቦታ እንልካለን።
📞 ስልክ:- 09 78 88 18 19
09 77 64 18 19
💥ጉዳይ አስፈፃሚ/smart phone ያለው/
🔹የት/ደረጃ:10
🔹የስራ ልምድ: 0አመት ጀምሮ
🔹ደሞዝ:5000+ የቀን አበል
💥ካሸር አሰልጥኖ
🔹የት/ት ደረጃ= 12/ዲፕሎማ
🔹ልምድ= 0 አመት
🔹ደሞዝ= 5,500
💥ባርማን/ባሬስታ
🔹የት/ት ደረጃ= መፃፍ ማንበብ
🔹ልምድ= ያለው
🔹ደሞዝ=በስምምነት
💥ሪሴፕሽን ለገስት ሀውስ/ለሆቴሎች
🔹የት/ደረጃ:10ኛ- ከዚያ በላይ
🔹የስራ ልምድ: 0 አመት ጀምሮ
🔹ደሞዝ፡ 4,500
💥ቤቲንግ ቤት ካሸር (በፈረቃ)
🔹የት/ት ደረጃ= 10ኛ በላይ
🔹የስራ ልምድ=0
🔹ደሞዝ=5000
💥 ሼፍ/ዋና እና ረዳት/
🔹የት/ት ደረጃ= 10ኛ በላይ
🔹የስራ ልምድ=ያለው
🔹ደሞዝ=6000-10,000
▶ለበለጠ መረጃ
🏘አድራሻ: አ.አ 22 ጎላጎል ሲደርሱ ወደ ቦሌ በሚወስደው መንገድ ወረድ ብለው ሎተስ ህንፃ ግራውንድ ላይ ቢ.ቁ 006
👇👇https://tttttt.me/JobsAtHewan
🔴በሁሉም ስራ ዘርፎች ሰራተኞችን በብዛት እንፈልጋለን።
🔥ቀጥታ ወደ ስራ ቦታ እንልካለን።
📞 ስልክ:- 09 78 88 18 19
09 77 64 18 19
💥ጉዳይ አስፈፃሚ/smart phone ያለው/
🔹የት/ደረጃ:10
🔹የስራ ልምድ: 0አመት ጀምሮ
🔹ደሞዝ:5000+ የቀን አበል
💥ካሸር አሰልጥኖ
🔹የት/ት ደረጃ= 12/ዲፕሎማ
🔹ልምድ= 0 አመት
🔹ደሞዝ= 5,500
💥ባርማን/ባሬስታ
🔹የት/ት ደረጃ= መፃፍ ማንበብ
🔹ልምድ= ያለው
🔹ደሞዝ=በስምምነት
💥ሪሴፕሽን ለገስት ሀውስ/ለሆቴሎች
🔹የት/ደረጃ:10ኛ- ከዚያ በላይ
🔹የስራ ልምድ: 0 አመት ጀምሮ
🔹ደሞዝ፡ 4,500
💥ቤቲንግ ቤት ካሸር (በፈረቃ)
🔹የት/ት ደረጃ= 10ኛ በላይ
🔹የስራ ልምድ=0
🔹ደሞዝ=5000
💥 ሼፍ/ዋና እና ረዳት/
🔹የት/ት ደረጃ= 10ኛ በላይ
🔹የስራ ልምድ=ያለው
🔹ደሞዝ=6000-10,000
▶ለበለጠ መረጃ
🏘አድራሻ: አ.አ 22 ጎላጎል ሲደርሱ ወደ ቦሌ በሚወስደው መንገድ ወረድ ብለው ሎተስ ህንፃ ግራውንድ ላይ ቢ.ቁ 006
👇👇https://tttttt.me/JobsAtHewan
👍1