አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለቢኒያም በለጠ የክብር ዶክትሬት ሰጠ!
የመቄዶንያ የአረጋውያንና አዕምሮ ሕሙማን ማዕከል መሥራች ቢኒያም በለጠ ለባረከተው በጎ ስራ ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የክብር ዶክተሬት ዛሬ ተሰጥቶታል።
ዩኒቨርሲቲው በመደበኛ፣ በማታና በርቀት ትምህርት መርሐ ግብር ያሰለጠናቸውን 8 ሺህ 642 የቅድመ ምረቃና ድሕረ ምረቃ ተማሪዎችን በሚሊኒየም አዳራሽ እያስመረቀ ነው።
በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንን ጨምሮ ሌሎችም ተገኝተዋል።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የመቄዶንያ የአረጋውያንና አዕምሮ ሕሙማን ማዕከል መሥራች ቢኒያም በለጠ ለባረከተው በጎ ስራ ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የክብር ዶክተሬት ዛሬ ተሰጥቶታል።
ዩኒቨርሲቲው በመደበኛ፣ በማታና በርቀት ትምህርት መርሐ ግብር ያሰለጠናቸውን 8 ሺህ 642 የቅድመ ምረቃና ድሕረ ምረቃ ተማሪዎችን በሚሊኒየም አዳራሽ እያስመረቀ ነው።
በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንን ጨምሮ ሌሎችም ተገኝተዋል።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
"የወረታ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ተገደሉ ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ የተለቀቀው ሃሰተኛ መረጃ ነው"- የወረታ ከተማ አስተዳደር
በትናንትናው እለት ማለትም ሃምሌ 12/2015 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ የቀድሞ ፖሊስ አባል የነበሩና ጡረታ የወጡና በንግድ ስራ የተሰማሩት አቶ መልኬ ጤናው የተባሉ ግለሰብ ድንገተኛ ግድያን ተከትሎ የተሳሳተና ከእውነት የራቀ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያ ተሰራጭቶ ነበር።
በዚህም መሰረት የወረታ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ተገደሉ ተብሎ የተለቀቀው መረጃ ከእውነት የራቀና የተሳሳተ መረጃ መሆኑንና የወረታ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊም በአሁኑ ሰዓት በስራ ላይ ያሉና ስራቸውን እያከናወኑ ያሉ መሆኑን የወረታ ከተማ አስተዳደር በፌስቡክ ገፁ ገልጿል።አስተዳደሩ ህብረተሰቡ በሃሰተኛ መረጃ ከመደናገር እራሱን እይዲጠብቅ አሳስቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
በትናንትናው እለት ማለትም ሃምሌ 12/2015 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ የቀድሞ ፖሊስ አባል የነበሩና ጡረታ የወጡና በንግድ ስራ የተሰማሩት አቶ መልኬ ጤናው የተባሉ ግለሰብ ድንገተኛ ግድያን ተከትሎ የተሳሳተና ከእውነት የራቀ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያ ተሰራጭቶ ነበር።
በዚህም መሰረት የወረታ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ተገደሉ ተብሎ የተለቀቀው መረጃ ከእውነት የራቀና የተሳሳተ መረጃ መሆኑንና የወረታ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊም በአሁኑ ሰዓት በስራ ላይ ያሉና ስራቸውን እያከናወኑ ያሉ መሆኑን የወረታ ከተማ አስተዳደር በፌስቡክ ገፁ ገልጿል።አስተዳደሩ ህብረተሰቡ በሃሰተኛ መረጃ ከመደናገር እራሱን እይዲጠብቅ አሳስቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍2
የቀድሞው የብአዴን ከፍተኛ አመራር አቶ ታደሰ ካሳ ከእስር ተለቀቁ!
ለአራት ዓመት ተኩል በእስር ላይ የቆዩት የቀድሞው የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) ከፍተኛ አመራር አቶ ታደሰ ካሳ ዛሬ ሐሙስ ከእስር መለቀቃቸውን ጠበቃቸው ህይወት ሊላይ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። አቶ ታደሰ ከእስር የተለቀቁት፤ የፌደራል ሰበር ሰሚ ችሎት በነጻ እንዲለቀቁ ትዕዛዝ ካስተላለፈ አንድ ሳምንት በኋላ ነው።
ከጥረት ኮርፖሬት ጋር በተያያዘ በከባድ የሙስና ወንጀል ተከስሰው የተፈረደባቸው አቶ ታደሰን በተመለከተ፤ የፌደራል ሰበር ሰሚ ችሎት ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ዕለት በዋለው ችሎቱ ነበር። ችሎቱ ጉዳዩን የተመለከተው የአማራ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ2012 ዓ.ም “ጥፋተኛ ናቸው” በማለት አቶ ታደሰ ላይ ያስተላለፈውን ቅጣት በተመለከተ በቀረበለት አቤቱታ መሰረት ነው።
ደንበኛቸው እስከ ዛሬ ድረስ ሳይፈቱ የቆዩት፤ ለአንድ ዓመት ከስድስት ወራት የታሰሩበት የቃሊቲ ማረሚያ ቤት “በራሱ መልቀቅ ስለማይችል” እንደሆነ ጠበቃ ህይወት አስረድተዋል። ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ አብዛኛውን የእስር ጊዜያቸውን በባህር ዳር ማረሚያ ቤት ያሳለፉት አቶ ታደሰ፤ በህክምና ምክንያት በተዛወሩበት ቃሊቲ ማረሚያ ቤት የቆዩት “በአደራ” ነበር።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
ለአራት ዓመት ተኩል በእስር ላይ የቆዩት የቀድሞው የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) ከፍተኛ አመራር አቶ ታደሰ ካሳ ዛሬ ሐሙስ ከእስር መለቀቃቸውን ጠበቃቸው ህይወት ሊላይ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። አቶ ታደሰ ከእስር የተለቀቁት፤ የፌደራል ሰበር ሰሚ ችሎት በነጻ እንዲለቀቁ ትዕዛዝ ካስተላለፈ አንድ ሳምንት በኋላ ነው።
ከጥረት ኮርፖሬት ጋር በተያያዘ በከባድ የሙስና ወንጀል ተከስሰው የተፈረደባቸው አቶ ታደሰን በተመለከተ፤ የፌደራል ሰበር ሰሚ ችሎት ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ዕለት በዋለው ችሎቱ ነበር። ችሎቱ ጉዳዩን የተመለከተው የአማራ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ2012 ዓ.ም “ጥፋተኛ ናቸው” በማለት አቶ ታደሰ ላይ ያስተላለፈውን ቅጣት በተመለከተ በቀረበለት አቤቱታ መሰረት ነው።
ደንበኛቸው እስከ ዛሬ ድረስ ሳይፈቱ የቆዩት፤ ለአንድ ዓመት ከስድስት ወራት የታሰሩበት የቃሊቲ ማረሚያ ቤት “በራሱ መልቀቅ ስለማይችል” እንደሆነ ጠበቃ ህይወት አስረድተዋል። ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ አብዛኛውን የእስር ጊዜያቸውን በባህር ዳር ማረሚያ ቤት ያሳለፉት አቶ ታደሰ፤ በህክምና ምክንያት በተዛወሩበት ቃሊቲ ማረሚያ ቤት የቆዩት “በአደራ” ነበር።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
"የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አንድነቷ ከተናጋ የፌዴራል እና የክልል መንግስታት ተወቃሽ ይሆናሉ" ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ አብርሃም በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ችግር ዙሪያ ዛሬ ሐምሌ 13 ቀን 2015 ዓ.ም መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም በትግራይ ክልል ተካሄደ የተባለው ሕገወጥ "የኤጲስ ቆጶሳት" ምርጫ ወደ ሹመት እንዳያመራ የፌደራል እና የክልል መንግስታት እንዲያስቆሙ ጠይቀዋል።
በትግራይ የሚገኙ አህጉረ ስብከትን የሚመሩ ሊቃነ ጳጳሳት ሕገወጥ "የኤጲስ ቆጶሳት" ምርጫ ማካሄዳቸውን እና ይህ ምርጫ ወደ ሹመት እንዳያመራ የፌደራል እና የክልል መንግስታት ኃላፊነት እንዳለባቸው ነው ብፁዕነታቸው ያስታወቁት።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አንድነት መናጋት የሀገርም አንድነት መናጋት ነውና ይህ ሹመት እንዳይፈጸም ኃላፊነታቸውን ካልተወጡ በታሪክ ተወቃሽም ተከሳሽም የፌደራል እና የክልል መንግስታት መሆናቸው አይቀርም ብለዋል ብፁዕ አቡነ አብርሃም።
በትግራይ ክልል ተፈጥሮ የነበረው ችግር ሁሉንም ያሳዘነ እንደነበር እና የተፈጠረው ችግር እንዳይፈጠር ቅዱስ ሲኖዶስ ጠይቆ የነበረ ቢሆንም አለመሳካቱን በተጨማሪም ችግሩ የሚፈታው በክልሉ ያሉ የተራቡትን ፣ የፈረሱትን እና የደከሙትን በማበርታት በመስራት መሆኑን ፤ ይህን ለማድረግም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዝግጁ መሆኗም ነው የተገለጸው።
መረጃው የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል ነው!
@Yenetube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ አብርሃም በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ችግር ዙሪያ ዛሬ ሐምሌ 13 ቀን 2015 ዓ.ም መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም በትግራይ ክልል ተካሄደ የተባለው ሕገወጥ "የኤጲስ ቆጶሳት" ምርጫ ወደ ሹመት እንዳያመራ የፌደራል እና የክልል መንግስታት እንዲያስቆሙ ጠይቀዋል።
በትግራይ የሚገኙ አህጉረ ስብከትን የሚመሩ ሊቃነ ጳጳሳት ሕገወጥ "የኤጲስ ቆጶሳት" ምርጫ ማካሄዳቸውን እና ይህ ምርጫ ወደ ሹመት እንዳያመራ የፌደራል እና የክልል መንግስታት ኃላፊነት እንዳለባቸው ነው ብፁዕነታቸው ያስታወቁት።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አንድነት መናጋት የሀገርም አንድነት መናጋት ነውና ይህ ሹመት እንዳይፈጸም ኃላፊነታቸውን ካልተወጡ በታሪክ ተወቃሽም ተከሳሽም የፌደራል እና የክልል መንግስታት መሆናቸው አይቀርም ብለዋል ብፁዕ አቡነ አብርሃም።
በትግራይ ክልል ተፈጥሮ የነበረው ችግር ሁሉንም ያሳዘነ እንደነበር እና የተፈጠረው ችግር እንዳይፈጠር ቅዱስ ሲኖዶስ ጠይቆ የነበረ ቢሆንም አለመሳካቱን በተጨማሪም ችግሩ የሚፈታው በክልሉ ያሉ የተራቡትን ፣ የፈረሱትን እና የደከሙትን በማበርታት በመስራት መሆኑን ፤ ይህን ለማድረግም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዝግጁ መሆኗም ነው የተገለጸው።
መረጃው የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል ነው!
@Yenetube @Fikerassefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ ጋር ተወያዩ!
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ ጋር በስልክ ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ከፕሬዚዳንቱ ጋር በሁለትዮሽ እና በዓለም አቀፍ የጋራ ጉዳዮች ላይ ተወያይተናል ብለዋል፡፡
እንዲሁም በዩክሬን እና በሩሲያ መካከል ሰላም ማምጣት በሚቻልበት መንገድ ላይ በስልክ መወያየታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገልፀዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ ጋር በስልክ ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ከፕሬዚዳንቱ ጋር በሁለትዮሽ እና በዓለም አቀፍ የጋራ ጉዳዮች ላይ ተወያይተናል ብለዋል፡፡
እንዲሁም በዩክሬን እና በሩሲያ መካከል ሰላም ማምጣት በሚቻልበት መንገድ ላይ በስልክ መወያየታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገልፀዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
Forwarded from YeneTube
💥💥💥አስቸኳይ የስራ ቅጥር💥💥💥
✅ድርጅታችን በተዘረዘሩት የስራ ዘርፎች ሰራተኞችን በብዛት ይፈልጋል።
═••════••• •••••• •••••• •
═••════••• •••••• •••••• •••════•
🔊 የስራ መደብ: ባንክ ተላላኪና ፅዳት
☆የት/ደረጃ:- ማንበብ እና መፃፍ የምትችል
☆የስራ ልምድ:- ያላት
☆ፆታ:- ሴት
☆ደሞዝ:4,500
═••════••• •••••• •••••• •••════•
🔊 የስራ መደብ:- መምህር በሉም ረዳትናዋና
☆የት/ደረጃ:- 10/ዲግሪ/ዲፕሎማ
☆የስራ ልምድ:- ዐ አመት እና ከዛ በላይ
☆ፆታ:- ወንድ/ሴት
☆ብዛት:- 20
☆ደሞዝ:-8,700
═••════••• •••••• •••••• •••════•
🔊 የስራ መደብ: ኮንስትራክሽን/ፎርማል
☆የት/ደረጃ:# ዲፕሎማ
☆የስራ ልምድ:# 0-2 ዓመት
☆ፆታ:# ወንድ
☆ብዛት:# 7
☆ደሞዝ:-በስምምነት
═••════••• •••••• •••••• •••════•
🔊 የስራ መደብ: ኦፌስ እንጅነሪግ
☆የት/ደረጃ:# ዲግሪ
☆የስራ ልምድ:# 2አመት
☆ፆታ:# ሴት/ወንድ
☆ብዛት:# 7
═••════••• •••••• •••••• •••════•
🔊 የስራ መደብ: ተጫራች/የጨረታ ባለሙያ/
☆የት/ት ደረጃ: መፃፍ እና ማንበብ
☆የስራ ልምድ: ጨረታ ሰርቶ የሚያውቅ
☆ፆታ: ወንድ
አድራሻችን:-አ.አ 22 ጎላጎል ሲደርሱ ወደቦሌ በሚውደው መንገድ ወረድ ብለው አዋሽ ባንክ ፊትለፊት ሎተስ ህንፃ ግራውንድ ላይ ቢ/ቁ 006
ስልክ : 0991333943/0991334043
https://tttttt.me/JobsAtHewan
✅ድርጅታችን በተዘረዘሩት የስራ ዘርፎች ሰራተኞችን በብዛት ይፈልጋል።
═••════••• •••••• •••••• •
═••════••• •••••• •••••• •••════•
🔊 የስራ መደብ: ባንክ ተላላኪና ፅዳት
☆የት/ደረጃ:- ማንበብ እና መፃፍ የምትችል
☆የስራ ልምድ:- ያላት
☆ፆታ:- ሴት
☆ደሞዝ:4,500
═••════••• •••••• •••••• •••════•
🔊 የስራ መደብ:- መምህር በሉም ረዳትናዋና
☆የት/ደረጃ:- 10/ዲግሪ/ዲፕሎማ
☆የስራ ልምድ:- ዐ አመት እና ከዛ በላይ
☆ፆታ:- ወንድ/ሴት
☆ብዛት:- 20
☆ደሞዝ:-8,700
═••════••• •••••• •••••• •••════•
🔊 የስራ መደብ: ኮንስትራክሽን/ፎርማል
☆የት/ደረጃ:# ዲፕሎማ
☆የስራ ልምድ:# 0-2 ዓመት
☆ፆታ:# ወንድ
☆ብዛት:# 7
☆ደሞዝ:-በስምምነት
═••════••• •••••• •••••• •••════•
🔊 የስራ መደብ: ኦፌስ እንጅነሪግ
☆የት/ደረጃ:# ዲግሪ
☆የስራ ልምድ:# 2አመት
☆ፆታ:# ሴት/ወንድ
☆ብዛት:# 7
═••════••• •••••• •••••• •••════•
🔊 የስራ መደብ: ተጫራች/የጨረታ ባለሙያ/
☆የት/ት ደረጃ: መፃፍ እና ማንበብ
☆የስራ ልምድ: ጨረታ ሰርቶ የሚያውቅ
☆ፆታ: ወንድ
አድራሻችን:-አ.አ 22 ጎላጎል ሲደርሱ ወደቦሌ በሚውደው መንገድ ወረድ ብለው አዋሽ ባንክ ፊትለፊት ሎተስ ህንፃ ግራውንድ ላይ ቢ/ቁ 006
ስልክ : 0991333943/0991334043
https://tttttt.me/JobsAtHewan
የዐማርኛ ቋንቋን በድምፅ መተርጎም የሚያስችል ሥራ እየተሠራ ነው!
በጉግል ትርጉም መተግበሪያ(Google Translation) ላይ፣ እከከ ዛሬ በጽሑፍ ብቻ የሚገኘውን የዐማርኛ ቋንቋ፣ በድምፅም መተርጎም የሚያስችል የመተርጎሚያ ቴክኖሎጂ በመጠናቀቅ ላይ እንደኾነ ተነገረ፡፡
በኢትዮጵያ የጉግል ክላውድሶስርስ ቡድን አስተባባሪ እንደኾነ የገለጸው የቴክኖሎጂ ባለሞያ አብዲሳ ባንጫ፣ ለድምፅ ትርጉሙ አስፈላጊ የኾነው ግብአት፣ ከሦስት ወራት በፊት ተጠናቆ፣ ወደ ጉግል ቋት እንደገባ፣ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግሯል፡፡የጉግልን ይኹንታ እንዳገኘም፣ አገልግሎት ላይ እንደሚውል አስታውቋል፡፡
ለትርጉም አገልግሎቱ፣ ቀደም ሲል ሥራ ላይ ለዋሉ አራት ተጨማሪ የኢትዮጵያ ቋንቋዎችም፣ የጉግል ትርጉም መተግበሪያ አገልግሎት በመበልጸግ ላይ እንዳለ፣ አስተባባሪው አብዲሳ ባጫ ተናግሯል፡፡ይኹን እንጂ፣ እስከ ዛሬ፣ በበጎ ፈቃደኞች የሚሠሩት የትርጉም አገልግሎቶች፣ በሞያው እና በቅንጅት ስለማይሠሩ፣ የማኅበረሰቡንና የግል ባለሀብቶችን ድጋፍ ለማግኘት ጥረት እየተደረገ እንደኾነ፣ የቴክኖሎጂ ባለሞያው አብዲሳ አመልክቷል፡፡
Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
በጉግል ትርጉም መተግበሪያ(Google Translation) ላይ፣ እከከ ዛሬ በጽሑፍ ብቻ የሚገኘውን የዐማርኛ ቋንቋ፣ በድምፅም መተርጎም የሚያስችል የመተርጎሚያ ቴክኖሎጂ በመጠናቀቅ ላይ እንደኾነ ተነገረ፡፡
በኢትዮጵያ የጉግል ክላውድሶስርስ ቡድን አስተባባሪ እንደኾነ የገለጸው የቴክኖሎጂ ባለሞያ አብዲሳ ባንጫ፣ ለድምፅ ትርጉሙ አስፈላጊ የኾነው ግብአት፣ ከሦስት ወራት በፊት ተጠናቆ፣ ወደ ጉግል ቋት እንደገባ፣ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግሯል፡፡የጉግልን ይኹንታ እንዳገኘም፣ አገልግሎት ላይ እንደሚውል አስታውቋል፡፡
ለትርጉም አገልግሎቱ፣ ቀደም ሲል ሥራ ላይ ለዋሉ አራት ተጨማሪ የኢትዮጵያ ቋንቋዎችም፣ የጉግል ትርጉም መተግበሪያ አገልግሎት በመበልጸግ ላይ እንዳለ፣ አስተባባሪው አብዲሳ ባጫ ተናግሯል፡፡ይኹን እንጂ፣ እስከ ዛሬ፣ በበጎ ፈቃደኞች የሚሠሩት የትርጉም አገልግሎቶች፣ በሞያው እና በቅንጅት ስለማይሠሩ፣ የማኅበረሰቡንና የግል ባለሀብቶችን ድጋፍ ለማግኘት ጥረት እየተደረገ እንደኾነ፣ የቴክኖሎጂ ባለሞያው አብዲሳ አመልክቷል፡፡
Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
አንጋፋው አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ጫማውን ሰቀለ!
በተለያዩ ክለቦች እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ተጫዋች የነበረው ሳላዲን ሰዒድ ከእግር ኳስ ራሱን አገለለ።
በኢትዮጵያ እግር ኳስ ከታዩ ምርጥ አጥቂዎች መካከል አንዱ የሆነው ሳላዲን ሰዒድ ከስኬታማ የአስራ አምስት ዓመታት በላይ የእግር ኳስ ህይወት ቆይታ በኋላ በዛሬው ዕለት ጫማ መስቀሉን ገልጿል።
ሳላዲን ለእግር ኳስ ቤተሰቡ ያለውን ምስጋናም ማቅረቡን ሶከር ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከዚህ ቀደም ለቅዱስ ጊዮርጊስ የተጫወተ ሲሆን አምና በሲዳማ ቡና ቆይታ ማድረጉ የሚታወስ ነው፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በተለያዩ ክለቦች እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ተጫዋች የነበረው ሳላዲን ሰዒድ ከእግር ኳስ ራሱን አገለለ።
በኢትዮጵያ እግር ኳስ ከታዩ ምርጥ አጥቂዎች መካከል አንዱ የሆነው ሳላዲን ሰዒድ ከስኬታማ የአስራ አምስት ዓመታት በላይ የእግር ኳስ ህይወት ቆይታ በኋላ በዛሬው ዕለት ጫማ መስቀሉን ገልጿል።
ሳላዲን ለእግር ኳስ ቤተሰቡ ያለውን ምስጋናም ማቅረቡን ሶከር ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከዚህ ቀደም ለቅዱስ ጊዮርጊስ የተጫወተ ሲሆን አምና በሲዳማ ቡና ቆይታ ማድረጉ የሚታወስ ነው፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራ ክልል ለ2016 በጀት ዓመት 137 ቢሊዮን 408 ሚሊዮን 472 ሺህ 187 ብር ጠቅላላ በጀት አጸደቀ!
የአማራ ክልል ምክር ቤት በ2016 በጀት ዓመት ጥቅል የበጀት ጣራ አመዳደብ ላይ መክሮ የበጀት ዓመቱን የልማት ሥራዎች ማስፈጸሚያ 137 ቢሊዮን 408 ሚሊዮን 472 ሺህ 187 ብር ጠቅላላ በጀት ማፅደቁ ተገለጸ።
የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ኀላፊ ጥላሁን መሃሪ (ዶ/ር) የ2016 በጀት ዓመት የክልሉ በጀት ዋነኛ ምንጮች ከክልሉ ታክስ እና ታክስ ነክ ካልሆኑ ገቢዎች የሚሰበሰብና ከፌዴራል መንግሥት ድጋፍ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡
ከ2016 በጀት ዓመት አጠቃላይ በጀት ውስጥ 89 ቢሊዮን 279 ሚሊዮን 467 ሺህ የሚኾነው በክልሉ ከሚሰበሰብ ገቢ፣ 44 ቢሊዮን 519 ሚሊዮን 851 ሺህ 979 የሚኾነው ከፌደራል መንግሥት ጥቅል የቀመር መደበኛ ድጋፍ የሚገኝ፣ 3 ቢሊዮን 24 ሚሊየን የሚኾነው ደግሞ ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ከፌደራል መንግሥት ድጋፍ እንዲሁም 585 ሚሊዮን 153 ሺህ 208 የሚኾነው ከውጭ እርዳታ የሚገኝ መሆኑን የገንዘብ ቢሮ ኀላፊው ተናግረዋል።
በጀትቱ ከ2015 በጀት ዓመት ከተመደበው በጀት ጋር ሲነጻጸር የ42 ቢሊዮን 88 ሚሊዮን 352 ሺህ 585 ብር እድገት እንዳለው ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የተገኘው መረጃ ይጠቁማል።
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራ ክልል ምክር ቤት በ2016 በጀት ዓመት ጥቅል የበጀት ጣራ አመዳደብ ላይ መክሮ የበጀት ዓመቱን የልማት ሥራዎች ማስፈጸሚያ 137 ቢሊዮን 408 ሚሊዮን 472 ሺህ 187 ብር ጠቅላላ በጀት ማፅደቁ ተገለጸ።
የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ኀላፊ ጥላሁን መሃሪ (ዶ/ር) የ2016 በጀት ዓመት የክልሉ በጀት ዋነኛ ምንጮች ከክልሉ ታክስ እና ታክስ ነክ ካልሆኑ ገቢዎች የሚሰበሰብና ከፌዴራል መንግሥት ድጋፍ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡
ከ2016 በጀት ዓመት አጠቃላይ በጀት ውስጥ 89 ቢሊዮን 279 ሚሊዮን 467 ሺህ የሚኾነው በክልሉ ከሚሰበሰብ ገቢ፣ 44 ቢሊዮን 519 ሚሊዮን 851 ሺህ 979 የሚኾነው ከፌደራል መንግሥት ጥቅል የቀመር መደበኛ ድጋፍ የሚገኝ፣ 3 ቢሊዮን 24 ሚሊየን የሚኾነው ደግሞ ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ከፌደራል መንግሥት ድጋፍ እንዲሁም 585 ሚሊዮን 153 ሺህ 208 የሚኾነው ከውጭ እርዳታ የሚገኝ መሆኑን የገንዘብ ቢሮ ኀላፊው ተናግረዋል።
በጀትቱ ከ2015 በጀት ዓመት ከተመደበው በጀት ጋር ሲነጻጸር የ42 ቢሊዮን 88 ሚሊዮን 352 ሺህ 585 ብር እድገት እንዳለው ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የተገኘው መረጃ ይጠቁማል።
@YeneTube @FikerAssefa
❤1
‹‹ በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ ፒኖ ቀበሌ በተፈፀመ ጥቃት ምክንያት የተገደሉ ሰዎች አስክሬኖች አልተነሱም ›› - ኢሰመጉ
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ(ኢሰመጉ) ይህን ያለው ‹‹ በጋምቤላ ክልል ያለው የጎሳ ግጭት በቂ ትኩረትና ዘላቂ መፍትሔ ሊሰጠው ይገባል! ›› ሲል ሰይሞ ሐምሌ 14 ቀን 2015 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ነው፡፡
‹‹ በጋምቤላ ክልል ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየተባባሰ በመጣው ግጭት ምክንያት በርካታ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ተፈጽመዋል ›› ያለው ጉባዔው ‹‹ በክልሉ ኢታንግ ልዩ ወረዳ ግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም በሁለት ቀበሌዎች ውስጥ ባሉ የአኝዋ እና የንዌር ጎሳዎች መካከል ግጭቱ መጀመሩን ›› አስታውሷል፡፡
ግጭቱ ‹‹ እየተስፋፋ የሄደው በዋናነት ሁለቱ ጎሳዎች በሚገናኙበት ኢታንግ ልዩ ወረዳ ውስጥ ባሉ ቀበሌዎች እና በጋምቤላ ከተማ ነው ›› ብሏል፡፡
‹‹ ኑዌር እና በአኝዋ ጎሳዎች መካከል በተደጋጋሚ ጊዜ የጎሳ ግጭቶች እንደሚነሱ ›› ያስታወሰው መግለጫው ‹‹ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተወሰኑ መሻሻሎች ታይተው የነበረ ቢሆንም ይህ ግጭት ዳግም ተቀስቅሷል ›› ሲልም አመልክቷል፡፡
‹‹ ይህ የጎሳ ግጭት በጋምቤላ ክልል በተለይም በኢታንግ ልዩ ወረዳ እና በጋምቤላ ከተማ ብሔር ብሔረሰቦች ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በስፋት የነበረ በመሆኑ ምክንያት በእነዚህ አካባቢዎች በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ላይ ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ ንብረት ውድመት እና መፈናቀል ደርሷል ›› ብሏል፡፡
‹‹ በኢታንግ ልዩ ወረዳ ውስጥ በሚገኙ አራት ቀበሌዎች ውስጥ ያሉ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን እና በወረዳው ባሉ የተለያዩ ግጭቱ ከፍተኛ በነበረባቸው ቀበሌዎች ላይ በርካታ ቤቶች መቃጠላቸውን ›› ጉባዔው ከአካባቢዎቹ ካሰባሰባቸው መረጃዎች መረዳት መቻሉን ጠቅሷል፡፡
‹‹ በኢታንግ ልዩ ወረዳ ፒኖ ቀበሌ ይህ ሪፖርት እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በጥቃቱ ምክንያት የተገደሉ ሰዎች አስክሬኖች እንዳልተነሱ፣ በእዚህ የጎሳ ግጭት ላይ የተለያዩ መሳሪያዎችን የታጠቁ ሰዎች እየተሳተፉበት በመሆኑ የጉዳቱን መጠን ከፍተኛ እንዳደረገው ›› አመልክቷል፡፡
‹‹ በአኝዋ ዞን ጎግ ወረደ ፑኝዶ ወረዳ አሁን ላይ የተሻለ የጸጥታ ሁኔታ ቢኖርም በአካባቢው በተደጋጋሚ ተመሳሳይ የጎሳ ግጨቶች ስለሚነሱ ስጋቶች መኖራቸውን እንዲሁም ይህንን ግጭት ለመቆጣጠር የክልሉ መንግስት በአጠቃላይ ክልሉ ላይ ተፈጻሚ የሚሆን ሰዓት እላፊ ማወጁንና የክልሉ ፖሊስ፣ የፌደራል ፖሊስ እና የመከላከያ ሰራዊት ግጭቱን ለመቆጣጠር ጥረት እያደረጉ መሆኑን ›› ካሰባሰብኳቸው መረጃዎች ተርጅቼያለሁ ብሏል፡፡
የጉባዔው መግለጫ ሲቀጥል ‹‹ በተጨማሪም በደቡብ ሱዳን የተነሳውን የእርስ በእርስ ግጭት ተከትሎ በርካታ ቁጥር ያላቸው የደቡብ ሱዳን ስደተኞች በጋምቤላ ክልል በሚገኙ አምስት የስደተኛ መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ መስፈራቸውን ›› ጠቁሟል፡፡
‹‹ የስደተኞቹ ቁጥር መጠለያ ጣቢያዎቹ ከሚችሉት አቅም በላይ መሆኑንና የሰፈሩባቸው አካባቢዎች ውስጥ ያሉት አንዳንድ የተቀባይ ማህበረሰቦች ከስደተኞቹ ጋር ባለው የጎሳ ልዩነት ምክንያት የደህንነት ስጋት እንዳለባቸው ›› በመግለጫው አትቷል፡፡
‹‹ ይህም ጉዳይ ስደተኞቹን እና ተቀባይ ማህበረሰቦችን ባማከለ ውይይት ላይ በተመሰረተ ዘላቂ መፍትሔ ሊፈታ እንደሚገባውና ይህ ካልሆነ ግን ችግሮች ሊፈጠሩ እንደሚችሉ ›› ኢሰመጉ ከአካባቢዎቹ ካሰባሰባቸው መረጃዎች ለመረዳት መቻሉን ገልፆል፡፡
ጉባዔው በመግለጫው ማጠቃሊያ አምስት ምክረ ሃሳቦችን አስቀምጧል፡፡ በዚህም ‹‹ የጋምቤላ ክልላዊ መንግስት በክልሉ በተደጋጋሚ በአኝዋ እና በኑዌር ጎሳዎች መካከለ ለሚነሳው ግጭት ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ ›› ጠይቋል፡፡
‹‹ በጋምቤላ ክልል በተለይም ውጥረት በተስፋፋባቸው በኢታንግ ልዩ ወረዳ እና በጋምቤላ ከተማ የክልሉ መንግስት ያለውን ስጋትእንዲቆጣጠርና የሰዎችን ሰብዓዊ መብቶች የማስከበር ኃላፊነቱን እንዲወጣ ›› የጠየቀበትም በምክረ ሃሳቡ ውስጥ ተካትቷል፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ(ኢሰመጉ) ይህን ያለው ‹‹ በጋምቤላ ክልል ያለው የጎሳ ግጭት በቂ ትኩረትና ዘላቂ መፍትሔ ሊሰጠው ይገባል! ›› ሲል ሰይሞ ሐምሌ 14 ቀን 2015 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ነው፡፡
‹‹ በጋምቤላ ክልል ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየተባባሰ በመጣው ግጭት ምክንያት በርካታ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ተፈጽመዋል ›› ያለው ጉባዔው ‹‹ በክልሉ ኢታንግ ልዩ ወረዳ ግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም በሁለት ቀበሌዎች ውስጥ ባሉ የአኝዋ እና የንዌር ጎሳዎች መካከል ግጭቱ መጀመሩን ›› አስታውሷል፡፡
ግጭቱ ‹‹ እየተስፋፋ የሄደው በዋናነት ሁለቱ ጎሳዎች በሚገናኙበት ኢታንግ ልዩ ወረዳ ውስጥ ባሉ ቀበሌዎች እና በጋምቤላ ከተማ ነው ›› ብሏል፡፡
‹‹ ኑዌር እና በአኝዋ ጎሳዎች መካከል በተደጋጋሚ ጊዜ የጎሳ ግጭቶች እንደሚነሱ ›› ያስታወሰው መግለጫው ‹‹ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተወሰኑ መሻሻሎች ታይተው የነበረ ቢሆንም ይህ ግጭት ዳግም ተቀስቅሷል ›› ሲልም አመልክቷል፡፡
‹‹ ይህ የጎሳ ግጭት በጋምቤላ ክልል በተለይም በኢታንግ ልዩ ወረዳ እና በጋምቤላ ከተማ ብሔር ብሔረሰቦች ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በስፋት የነበረ በመሆኑ ምክንያት በእነዚህ አካባቢዎች በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ላይ ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ ንብረት ውድመት እና መፈናቀል ደርሷል ›› ብሏል፡፡
‹‹ በኢታንግ ልዩ ወረዳ ውስጥ በሚገኙ አራት ቀበሌዎች ውስጥ ያሉ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን እና በወረዳው ባሉ የተለያዩ ግጭቱ ከፍተኛ በነበረባቸው ቀበሌዎች ላይ በርካታ ቤቶች መቃጠላቸውን ›› ጉባዔው ከአካባቢዎቹ ካሰባሰባቸው መረጃዎች መረዳት መቻሉን ጠቅሷል፡፡
‹‹ በኢታንግ ልዩ ወረዳ ፒኖ ቀበሌ ይህ ሪፖርት እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በጥቃቱ ምክንያት የተገደሉ ሰዎች አስክሬኖች እንዳልተነሱ፣ በእዚህ የጎሳ ግጭት ላይ የተለያዩ መሳሪያዎችን የታጠቁ ሰዎች እየተሳተፉበት በመሆኑ የጉዳቱን መጠን ከፍተኛ እንዳደረገው ›› አመልክቷል፡፡
‹‹ በአኝዋ ዞን ጎግ ወረደ ፑኝዶ ወረዳ አሁን ላይ የተሻለ የጸጥታ ሁኔታ ቢኖርም በአካባቢው በተደጋጋሚ ተመሳሳይ የጎሳ ግጨቶች ስለሚነሱ ስጋቶች መኖራቸውን እንዲሁም ይህንን ግጭት ለመቆጣጠር የክልሉ መንግስት በአጠቃላይ ክልሉ ላይ ተፈጻሚ የሚሆን ሰዓት እላፊ ማወጁንና የክልሉ ፖሊስ፣ የፌደራል ፖሊስ እና የመከላከያ ሰራዊት ግጭቱን ለመቆጣጠር ጥረት እያደረጉ መሆኑን ›› ካሰባሰብኳቸው መረጃዎች ተርጅቼያለሁ ብሏል፡፡
የጉባዔው መግለጫ ሲቀጥል ‹‹ በተጨማሪም በደቡብ ሱዳን የተነሳውን የእርስ በእርስ ግጭት ተከትሎ በርካታ ቁጥር ያላቸው የደቡብ ሱዳን ስደተኞች በጋምቤላ ክልል በሚገኙ አምስት የስደተኛ መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ መስፈራቸውን ›› ጠቁሟል፡፡
‹‹ የስደተኞቹ ቁጥር መጠለያ ጣቢያዎቹ ከሚችሉት አቅም በላይ መሆኑንና የሰፈሩባቸው አካባቢዎች ውስጥ ያሉት አንዳንድ የተቀባይ ማህበረሰቦች ከስደተኞቹ ጋር ባለው የጎሳ ልዩነት ምክንያት የደህንነት ስጋት እንዳለባቸው ›› በመግለጫው አትቷል፡፡
‹‹ ይህም ጉዳይ ስደተኞቹን እና ተቀባይ ማህበረሰቦችን ባማከለ ውይይት ላይ በተመሰረተ ዘላቂ መፍትሔ ሊፈታ እንደሚገባውና ይህ ካልሆነ ግን ችግሮች ሊፈጠሩ እንደሚችሉ ›› ኢሰመጉ ከአካባቢዎቹ ካሰባሰባቸው መረጃዎች ለመረዳት መቻሉን ገልፆል፡፡
ጉባዔው በመግለጫው ማጠቃሊያ አምስት ምክረ ሃሳቦችን አስቀምጧል፡፡ በዚህም ‹‹ የጋምቤላ ክልላዊ መንግስት በክልሉ በተደጋጋሚ በአኝዋ እና በኑዌር ጎሳዎች መካከለ ለሚነሳው ግጭት ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ ›› ጠይቋል፡፡
‹‹ በጋምቤላ ክልል በተለይም ውጥረት በተስፋፋባቸው በኢታንግ ልዩ ወረዳ እና በጋምቤላ ከተማ የክልሉ መንግስት ያለውን ስጋትእንዲቆጣጠርና የሰዎችን ሰብዓዊ መብቶች የማስከበር ኃላፊነቱን እንዲወጣ ›› የጠየቀበትም በምክረ ሃሳቡ ውስጥ ተካትቷል፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሞ ዳያስፖራ ማኅበረሰብ ተወካዮች እና አምባሳደር ማይክ ሐመር ተወያዩ!
የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር፣ በዩናይትድ ስቴትስ ከትውልደ ኢትዮጵያውያን የኦሮሞ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋራ እንደተወያዩ፣ የኦሮሞ ቅርስ አመራር እና ተሟጋች ማኅበር አስታወቀ።
የኦሮሞ ዳያስፖራ ተወካዮቹ፣ የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት፣ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ጥሎት የነበረውን የርዳታ ማዕቀብ መልሶ ማንሣቱ እንዳሳዘናቸው፣ ለአምባሳደር ማይክ እንደተናገሩ፣ መግለጫው አመልክቷል።
ምክንያት ያደረጉትም፣ በኢትዮጵያ፣ አሁንም አለ ያሉትን የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች በመጥቀስ እንደኾነ፣ ማኅበሩ ገልጿል።አምባሳደር ሐመር በበኩላቸው፣ የርዳታ ማዕቀቡን የማንሣት ውሳኔ ላይ የተደረሰው፣ ከሀገር ውስጥም ኾነ ከዓለም አቀፍ አካላት በተገኘው መረጃ መሠረት፣ “በተለይም፣ ከሰላም ስምምነቱ ወዲህ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚፈጽመው የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች መቀነስ በማሳየቱ ነው፤” ማለታቸውን መግለጫው አስፍሯል።
በሽግግር ፍትሕ ሒደት ውስጥ፣ “የኦሮሚያ ድርሻ ምን ይኾናል?” የሚለውን ጉዳይ፣ ተወካዮቹ ለአምባሳደር ሐመር እንዳነሡላቸው መግለጫው አመልክቷል።በኢትዮጵያ መንግሥት እና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት መካከል ሲደረግ የነበረው ድርድር መስተጓጎሉን በተመለከተ፣ የኦሮሞ ማኅበረሰብ ተወካዮቹ ለአምባሳደር ሐመር እንዳነሡላቸውና በዚኽም የዳያስፖራውን ማኅበረሰብ ለመርዳት ያላቸውን ፍላጎት እንደገለጹላቸው፣ መግለጫው አመልክቷል።
Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር፣ በዩናይትድ ስቴትስ ከትውልደ ኢትዮጵያውያን የኦሮሞ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋራ እንደተወያዩ፣ የኦሮሞ ቅርስ አመራር እና ተሟጋች ማኅበር አስታወቀ።
የኦሮሞ ዳያስፖራ ተወካዮቹ፣ የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት፣ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ጥሎት የነበረውን የርዳታ ማዕቀብ መልሶ ማንሣቱ እንዳሳዘናቸው፣ ለአምባሳደር ማይክ እንደተናገሩ፣ መግለጫው አመልክቷል።
ምክንያት ያደረጉትም፣ በኢትዮጵያ፣ አሁንም አለ ያሉትን የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች በመጥቀስ እንደኾነ፣ ማኅበሩ ገልጿል።አምባሳደር ሐመር በበኩላቸው፣ የርዳታ ማዕቀቡን የማንሣት ውሳኔ ላይ የተደረሰው፣ ከሀገር ውስጥም ኾነ ከዓለም አቀፍ አካላት በተገኘው መረጃ መሠረት፣ “በተለይም፣ ከሰላም ስምምነቱ ወዲህ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚፈጽመው የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች መቀነስ በማሳየቱ ነው፤” ማለታቸውን መግለጫው አስፍሯል።
በሽግግር ፍትሕ ሒደት ውስጥ፣ “የኦሮሚያ ድርሻ ምን ይኾናል?” የሚለውን ጉዳይ፣ ተወካዮቹ ለአምባሳደር ሐመር እንዳነሡላቸው መግለጫው አመልክቷል።በኢትዮጵያ መንግሥት እና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት መካከል ሲደረግ የነበረው ድርድር መስተጓጎሉን በተመለከተ፣ የኦሮሞ ማኅበረሰብ ተወካዮቹ ለአምባሳደር ሐመር እንዳነሡላቸውና በዚኽም የዳያስፖራውን ማኅበረሰብ ለመርዳት ያላቸውን ፍላጎት እንደገለጹላቸው፣ መግለጫው አመልክቷል።
Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#update: የ "ቴሌግራም" መተግበሪያ ተጠቃሚዎቹ እንደሌሎቹ ማኅበራዊ ትስስር ገጾች "ስቶሪ/Story" መለጠፍ እንዲችሉ የሚያስችል ማዘመኛ ይፋ አድርጓል።
አሁን ላይ ለፕሪሚየም ተጠቃሚዎች ብቻ የተፈቀደው ይህ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ፎቶ እንዲሁም ቪዲዮ በስቶሪ እንዲያጋሩ ያስችላል።
ይህ ማዘመኛው ቴሌግራምን ከሌሎቹ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችና የመልዕክት መለዋወጫ መተግበሪያዎች ጋር ያመሳስለዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
አሁን ላይ ለፕሪሚየም ተጠቃሚዎች ብቻ የተፈቀደው ይህ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ፎቶ እንዲሁም ቪዲዮ በስቶሪ እንዲያጋሩ ያስችላል።
ይህ ማዘመኛው ቴሌግራምን ከሌሎቹ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችና የመልዕክት መለዋወጫ መተግበሪያዎች ጋር ያመሳስለዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
ባህርዳር ዩኒቨርስቲ 7637 ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው!
የባህርዳር ዩኒቨርስቲ በ79 የተለያዩ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን 7 ሺሕ 637 ተማሪዎችን እያስመረቀ ይገኛል።በዘንድሮ አመት በተጀመረው የመውጫ ፈተናም የባህርዳር ዩኒቨርስቲ 85 ነጥብ 2 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎቹ አልፈዋል፡፡
የባህርዳር ዩኒቨርስቲ እያካሄደ በሚገኘው የምረቃ መርሃ ግብሩ ለጋዜጠኛ መአዛ ብሩ እና ጌሪት ሆልትላንድ የክብር ዶክትሬት እንደሚሰጥ ታውቋል።
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር)፣ የዩኒቨርስቲው ፕሬዝደንት ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር)፣ የዩኒቨርስቲው ሴኔት አባላት፣ ተመራቂዎች እንዲሁም የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የባህርዳር ዩኒቨርስቲ በ79 የተለያዩ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን 7 ሺሕ 637 ተማሪዎችን እያስመረቀ ይገኛል።በዘንድሮ አመት በተጀመረው የመውጫ ፈተናም የባህርዳር ዩኒቨርስቲ 85 ነጥብ 2 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎቹ አልፈዋል፡፡
የባህርዳር ዩኒቨርስቲ እያካሄደ በሚገኘው የምረቃ መርሃ ግብሩ ለጋዜጠኛ መአዛ ብሩ እና ጌሪት ሆልትላንድ የክብር ዶክትሬት እንደሚሰጥ ታውቋል።
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር)፣ የዩኒቨርስቲው ፕሬዝደንት ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር)፣ የዩኒቨርስቲው ሴኔት አባላት፣ ተመራቂዎች እንዲሁም የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር "ክልሉን እንታደግ" ሲሉ ጥሪ አቀረቡ!
ባልተለመደ ሁኔታ በላለፉት ሦስት ቀናት በዝግ የተካሄደው የአማራ ክልል ምክር ቤት፤ በክልሉ ወቅታዊ የሰላምና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ ከአባላቱ ጠንካራ ጥያቄዎችን ማስተናገዱ ተሰምቷል፡፡በምክር ቤቱ ሰብሰባ ላይ ጥያቄ ያነሱት የሕዝብ ተወካዮች፤ "የአማራን ሕዝብ አንገት ለማስደፋት ቀን ከሌሊት የሚሰሩ አካላት አሉ” ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
አባላቱ ክልሉ አሁን ላይ የገጠመውን አለመረጋጋት ለመፍታት መጀመሪያ የክልሉ አስተዳደር መዋቅር ራሱን መፈተሸና ማስተካከል አለበትም ነው ያሉት።የምክር ቤቱ አባላት አክለውም፤ "ክልሉ ያሉበትን መዋቅራዊ ችግሮች ካላስተካከለና ራሱን አስተካክሎ በግልጽ ካላወጣ፣ የሕዝቡን ጥያቄ መመለስ አይቻልም" ሲሉ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡
በየአካባቢው የሚስተዋሉ ውጊያዎች የክልሉን ሕዝብ እያዳከሙ ነው ያሉት አባላቱ፤ የክልሉ መንግሥት መከላከያ ሠራዊት አስገብቶ ውጊያ እንዲደረግ መፍቀድ አልነበረበትም የሚል ትችትም አንስተዋል።ከምክር ቤት በአባላቱ ጠንካራ ጥያቄዎች የቀረቡላቸው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡትም ምላሽ፤ “ክልሉን እንታደግ” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
“ችግራችንን በራሳችን የመፍታት አቅም እንፍጠር” ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በየዞኑ ከምክር ቤት አባላት አምስት አምስት ሰው ተመርጦ የኃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራንና ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰዎች የተሳተፉበት ውይይት ያለምንም ገደብ እንዲደረግም ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳደሩ ያቀረቡት የውይይት ጥሪ በአስር ቀናት ውስጥ እንዲካሄድም ነው የጠየቁት። በውይይቱ የሚነሱ ጉዳዮች በወረዳ፣ በዞንና በክልል በየደረጃው መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጥረት እንደሚያደርጉም ጠቁመዋል፡፡አስተዳደራቸው ለሰላም አማራጭ ቅድሚያ በመሰጠት፤ በሽዋ፣ በወሎ፣ በጎጃምና በጎንደር ውይይት እንዲደረግ ዕድል መፍጠሩን አስታውሰዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳደሩ “እንታደገው” ያሉትና የሚመሩት ክልል፤ በተለይ የመከላከያ ሠራዊት በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ከተሰማራ ጊዜ ጀምሮ በውጊያ፣ መንገድ በመዝጋት፣ በሕዝብ ተቃውሞና በመሳሰሉት ሁነቶች ውስጥ እያለፈ ነው፡፡
የመከላከያ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከአማራ ክልል የሰላም እጦት ጋር በተያየዘ በቅርቡ በሰጡት አስተያየት፤ “ክልሉ ፓራላይዝድ ሆኗል” ሲሉ መደመጣቸው የሚታወስ ነው፡፡ ፊልድ ማርሻሉ የአማራ ክልል አስተዳደር ሽባ ሆኗል የሚል ይዘት ያለው አስተያየት ከሰጡ በኋላ፤ የመከላከያ ሠራዊት በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ከፋኖ ታጣቂዎች ጋር ውጊያ ውስጥ ገብቷል፡፡
በመንግሥት እና በታጣቂ ቡድኑ መካከል ያለው ግጭት፤ ገና ከጅምሩ በውይይትና በድርድር እንዲፈታ የተለያዩ የፖለቲካ ኃይሎች ጥሪ ሲያቀርቡ ቢቆዩም፣ አሁንም በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ውጊያዎች እየተካሄዱ ነው፡፡
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
ባልተለመደ ሁኔታ በላለፉት ሦስት ቀናት በዝግ የተካሄደው የአማራ ክልል ምክር ቤት፤ በክልሉ ወቅታዊ የሰላምና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ ከአባላቱ ጠንካራ ጥያቄዎችን ማስተናገዱ ተሰምቷል፡፡በምክር ቤቱ ሰብሰባ ላይ ጥያቄ ያነሱት የሕዝብ ተወካዮች፤ "የአማራን ሕዝብ አንገት ለማስደፋት ቀን ከሌሊት የሚሰሩ አካላት አሉ” ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
አባላቱ ክልሉ አሁን ላይ የገጠመውን አለመረጋጋት ለመፍታት መጀመሪያ የክልሉ አስተዳደር መዋቅር ራሱን መፈተሸና ማስተካከል አለበትም ነው ያሉት።የምክር ቤቱ አባላት አክለውም፤ "ክልሉ ያሉበትን መዋቅራዊ ችግሮች ካላስተካከለና ራሱን አስተካክሎ በግልጽ ካላወጣ፣ የሕዝቡን ጥያቄ መመለስ አይቻልም" ሲሉ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡
በየአካባቢው የሚስተዋሉ ውጊያዎች የክልሉን ሕዝብ እያዳከሙ ነው ያሉት አባላቱ፤ የክልሉ መንግሥት መከላከያ ሠራዊት አስገብቶ ውጊያ እንዲደረግ መፍቀድ አልነበረበትም የሚል ትችትም አንስተዋል።ከምክር ቤት በአባላቱ ጠንካራ ጥያቄዎች የቀረቡላቸው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡትም ምላሽ፤ “ክልሉን እንታደግ” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
“ችግራችንን በራሳችን የመፍታት አቅም እንፍጠር” ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በየዞኑ ከምክር ቤት አባላት አምስት አምስት ሰው ተመርጦ የኃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራንና ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰዎች የተሳተፉበት ውይይት ያለምንም ገደብ እንዲደረግም ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳደሩ ያቀረቡት የውይይት ጥሪ በአስር ቀናት ውስጥ እንዲካሄድም ነው የጠየቁት። በውይይቱ የሚነሱ ጉዳዮች በወረዳ፣ በዞንና በክልል በየደረጃው መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጥረት እንደሚያደርጉም ጠቁመዋል፡፡አስተዳደራቸው ለሰላም አማራጭ ቅድሚያ በመሰጠት፤ በሽዋ፣ በወሎ፣ በጎጃምና በጎንደር ውይይት እንዲደረግ ዕድል መፍጠሩን አስታውሰዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳደሩ “እንታደገው” ያሉትና የሚመሩት ክልል፤ በተለይ የመከላከያ ሠራዊት በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ከተሰማራ ጊዜ ጀምሮ በውጊያ፣ መንገድ በመዝጋት፣ በሕዝብ ተቃውሞና በመሳሰሉት ሁነቶች ውስጥ እያለፈ ነው፡፡
የመከላከያ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከአማራ ክልል የሰላም እጦት ጋር በተያየዘ በቅርቡ በሰጡት አስተያየት፤ “ክልሉ ፓራላይዝድ ሆኗል” ሲሉ መደመጣቸው የሚታወስ ነው፡፡ ፊልድ ማርሻሉ የአማራ ክልል አስተዳደር ሽባ ሆኗል የሚል ይዘት ያለው አስተያየት ከሰጡ በኋላ፤ የመከላከያ ሠራዊት በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ከፋኖ ታጣቂዎች ጋር ውጊያ ውስጥ ገብቷል፡፡
በመንግሥት እና በታጣቂ ቡድኑ መካከል ያለው ግጭት፤ ገና ከጅምሩ በውይይትና በድርድር እንዲፈታ የተለያዩ የፖለቲካ ኃይሎች ጥሪ ሲያቀርቡ ቢቆዩም፣ አሁንም በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ውጊያዎች እየተካሄዱ ነው፡፡
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ተመራቂ ተማሪና ወላጅ አባቷ ከምርቃት ሲመለሱ በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ!
በዛሬው እለት በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ከሱልልታ ከተማ አቅራቢ በምትገኘው ኮሰ በር አካባቢ ከቀኑ 11:30 በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአምስት ሰዎች ህይወት አልፏል። ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ፅጌ 16 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ ሀይሩፍ ተሽከርካሪ 65 መንገደኞችን ካሳፈረ ከህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ጋር ተጋጭቶ አደጋው ደርሷል።
በአደጋው የሀይሩፉ አሽከርካሪን ጨምሮ የአምስት ሰዎች ህይወት ማለፉን በሱልልታ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት የትራፊክ ደህንነት ቁጥጥር ዋና ሳጅን ደፋሩ ምትኩ ተናግረዋል። ከሟቾቹ መካከል የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ተመራቂ ተማሪና ወላጅ አባቷ ከምርቃት ሲመለሱ በትራፊክ አደጋው ህይወታቸው ሲያልፍ የተመራቂዋ ታናሽ ወንድም የሆነ የ 16 ዓመት ታዳጊ በአደጋው ክፉኛ ቆስሏል።
በአደጋው ህይወታቸውን ካጡ አምስት ሰዎች በተጨማሪ ሶስት ሰዎች ላይ ከባድ ስድስት ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን ቁጥጥር ዋና ሳጅን ደፋሩ ምትኩ ለብስራት ሬዲዮና ቲቪ ጨምረው ተናግረዋል።
[ዳጉ ጆርናል/ብስራት ሬዲዮ]
@YeneTube @FikerAssefa
በዛሬው እለት በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ከሱልልታ ከተማ አቅራቢ በምትገኘው ኮሰ በር አካባቢ ከቀኑ 11:30 በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአምስት ሰዎች ህይወት አልፏል። ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ፅጌ 16 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ ሀይሩፍ ተሽከርካሪ 65 መንገደኞችን ካሳፈረ ከህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ጋር ተጋጭቶ አደጋው ደርሷል።
በአደጋው የሀይሩፉ አሽከርካሪን ጨምሮ የአምስት ሰዎች ህይወት ማለፉን በሱልልታ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት የትራፊክ ደህንነት ቁጥጥር ዋና ሳጅን ደፋሩ ምትኩ ተናግረዋል። ከሟቾቹ መካከል የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ተመራቂ ተማሪና ወላጅ አባቷ ከምርቃት ሲመለሱ በትራፊክ አደጋው ህይወታቸው ሲያልፍ የተመራቂዋ ታናሽ ወንድም የሆነ የ 16 ዓመት ታዳጊ በአደጋው ክፉኛ ቆስሏል።
በአደጋው ህይወታቸውን ካጡ አምስት ሰዎች በተጨማሪ ሶስት ሰዎች ላይ ከባድ ስድስት ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን ቁጥጥር ዋና ሳጅን ደፋሩ ምትኩ ለብስራት ሬዲዮና ቲቪ ጨምረው ተናግረዋል።
[ዳጉ ጆርናል/ብስራት ሬዲዮ]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተርና ሌሎች ሁለት ም/ዳይሬክተሮች ከስልጣናቸው ተነሱ።
የኢሚግሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ብሩህተስፋ ሙልጌታን ጨምሮ ሌሎች ሁለት ም/ዳይሬክተሮች ከስልጣን መነሳታቸውን ዋዜማ ዘግባለች።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢሚግሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ብሩህተስፋ ሙልጌታን ጨምሮ ሌሎች ሁለት ም/ዳይሬክተሮች ከስልጣን መነሳታቸውን ዋዜማ ዘግባለች።
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
YeneTube
የኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተርና ሌሎች ሁለት ም/ዳይሬክተሮች ከስልጣናቸው ተነሱ። የኢሚግሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ብሩህተስፋ ሙልጌታን ጨምሮ ሌሎች ሁለት ም/ዳይሬክተሮች ከስልጣን መነሳታቸውን ዋዜማ ዘግባለች። @YeneTube @FikerAssefa
በተያያዘ ዜና ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል።
አዲሷ ተሿሚ ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት ከዚህ ቀደም የቱሪዝም ሚንስትር ዲዔታ ፣ በውጪ ጉዳይ ሚር የዲያስፖራ አገልግሎትና በውጪ ሀገር በዲፕሎማቲክ ሚስዮን ውስጥ ይሰሩ እንደነበር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
አዲሷ ተሿሚ ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት ከዚህ ቀደም የቱሪዝም ሚንስትር ዲዔታ ፣ በውጪ ጉዳይ ሚር የዲያስፖራ አገልግሎትና በውጪ ሀገር በዲፕሎማቲክ ሚስዮን ውስጥ ይሰሩ እንደነበር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
371ሺህ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ ለማቋቋም ዝግጅት እየተደረገ ነው!
371ሺህ የሚደርሱ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋም ሥራ ለመሥራት ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ ብሔራዊ ተሐድሶ ኮሚሽን ገለጸ፡፡
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በሰሜኑ ጦርነት እንዲሁም በሌሎች አካባቢዎች የፖለቲካ ዓላማቸውን በትጥቅ ለማስፈጸም ተደራጅተው ሲንቀሳቀሱ የነበሩና በአሁኑ ጊዜ ወደ ሰላማዊ ትግል ለመግባት የወሰኑ 371 ሺ የሚደርሱ የቀድሞ ተዋጊዎችን በአንድ ቦታ የማሰባሰብ እና መልሶ የማቋቋም ሥራዎችን ለመሥራት ዝግጅት እየተደረገ ነው፡፡
(ኢ ፕ ድ)
@YeneTube @FikerAssefa
371ሺህ የሚደርሱ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋም ሥራ ለመሥራት ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ ብሔራዊ ተሐድሶ ኮሚሽን ገለጸ፡፡
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በሰሜኑ ጦርነት እንዲሁም በሌሎች አካባቢዎች የፖለቲካ ዓላማቸውን በትጥቅ ለማስፈጸም ተደራጅተው ሲንቀሳቀሱ የነበሩና በአሁኑ ጊዜ ወደ ሰላማዊ ትግል ለመግባት የወሰኑ 371 ሺ የሚደርሱ የቀድሞ ተዋጊዎችን በአንድ ቦታ የማሰባሰብ እና መልሶ የማቋቋም ሥራዎችን ለመሥራት ዝግጅት እየተደረገ ነው፡፡
(ኢ ፕ ድ)
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
በ2015 በጀት ዓመት ከቡና የወጪ ንግድ ከአንድ ነጥብ ሦስት ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሳሕለማርያም ገብረመድህን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በ2015 በጀት ዓመት 360 ሺህ 144 ቶን ቡና በላይ በመላክ አንድ ነጥብ 8 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ 240 ሺህ 369 ቶን በላይ ቡና በመላክ ከአንድ ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘት ተችሏል፡፡ ይህም የዕቅዱን 67 በመቶ ማሳካት ተችሏል፡፡
በበጀት ዓመቱ የተላከው ቡና መዳረሻ ሀገራት መካከልም ሳዑዲ ዓረቢያ በመጠን 48 ሺህ 413 ነጥብ 39 ቶን ሲሆን በገቢ 224 ነጥብ 84 ሚሊዮን ዶላር፣ ጀርመን በመጠን 36 ሺህ 065 ነጥብ 71 ቶን ቡና፤ በገቢ ደግሞ 173 ነጥብ 47 ሚሊዮን ዶላር፣ አሜሪካ በመጠን 21ሺህ 020 ነጥብ 86 ቶን፣ በገቢ 150 ነጥብ 47 ሚሊዮን ዶላር ድርሻ ኖሯቸው ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃን መያዛቸውን ጠቅሰዋል፡፡
አቶ ሳሕለማርያም ወደ ውጪ ከተላከው የቡና ምርት የተገኘው ገቢ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር እጅግ መጠነኛ ቅናሽ እንዳለው ገልጸው፤ ከዓለም አቀፍ የቡና ዋጋ መቀነስ፣ ከነበሩት ሌሎች ፈታኝ ሁኔታዎች አንጻር ሲታይ በእጅጉ የሚበረታታ ውጤት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በተለይ በበጀት ዓመቱ ቡና ላኪዎች በተለያዩ ኤግዚቢሽኖች ላይ በመሳተፍ የሀገሪቱን ቡና የማስተዋወቅ ሥራ ሠርተዋል፡፡ በዚህም 141 ቡና ላኪዎችን እንዲሳተፉ በማመቻቸት 47 ሺህ 424 ቶን ቡና ከገዥዎች ጋር ኮንትራት በመግባት 76 ሚሊዮን 500 ሺህ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል፡፡
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሳሕለማርያም ገብረመድህን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በ2015 በጀት ዓመት 360 ሺህ 144 ቶን ቡና በላይ በመላክ አንድ ነጥብ 8 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ 240 ሺህ 369 ቶን በላይ ቡና በመላክ ከአንድ ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘት ተችሏል፡፡ ይህም የዕቅዱን 67 በመቶ ማሳካት ተችሏል፡፡
በበጀት ዓመቱ የተላከው ቡና መዳረሻ ሀገራት መካከልም ሳዑዲ ዓረቢያ በመጠን 48 ሺህ 413 ነጥብ 39 ቶን ሲሆን በገቢ 224 ነጥብ 84 ሚሊዮን ዶላር፣ ጀርመን በመጠን 36 ሺህ 065 ነጥብ 71 ቶን ቡና፤ በገቢ ደግሞ 173 ነጥብ 47 ሚሊዮን ዶላር፣ አሜሪካ በመጠን 21ሺህ 020 ነጥብ 86 ቶን፣ በገቢ 150 ነጥብ 47 ሚሊዮን ዶላር ድርሻ ኖሯቸው ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃን መያዛቸውን ጠቅሰዋል፡፡
አቶ ሳሕለማርያም ወደ ውጪ ከተላከው የቡና ምርት የተገኘው ገቢ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር እጅግ መጠነኛ ቅናሽ እንዳለው ገልጸው፤ ከዓለም አቀፍ የቡና ዋጋ መቀነስ፣ ከነበሩት ሌሎች ፈታኝ ሁኔታዎች አንጻር ሲታይ በእጅጉ የሚበረታታ ውጤት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በተለይ በበጀት ዓመቱ ቡና ላኪዎች በተለያዩ ኤግዚቢሽኖች ላይ በመሳተፍ የሀገሪቱን ቡና የማስተዋወቅ ሥራ ሠርተዋል፡፡ በዚህም 141 ቡና ላኪዎችን እንዲሳተፉ በማመቻቸት 47 ሺህ 424 ቶን ቡና ከገዥዎች ጋር ኮንትራት በመግባት 76 ሚሊዮን 500 ሺህ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል፡፡
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa