ግንባታቸው የተጠናቀቁ 528 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ለሰራዊት አባላት የማስተላለፍ መርሃግብር እየተካሄደ ነው!
ግንባታቸው የተጠናቀቁ 528 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ተመዝግበው ለቆጠቡ ለኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን አባላትና ለተቋሙ የሲቪል ሰራተኞች በእጣ የማስተላለፍ መርሃግብር እየተካሄደ ነው።
ዕጣው በግዳጅ ላይ ያሉ የሰራዊት አባላት፣ በክብር የተሰናበቱ የሰራዊት አባላትን ያካተተ ነው። ሴት የሰራዊት አባላትን በልዩ ሁኔታ ተጠቃሚ ያደረገ መሆኑም ተጠቁሟል።
በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተፕራይዝ እየተገነቡ ካሉት የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል በአዲስ አበባ በሰሚት ቁጥር ሁለት ግንባታቸው የተጠናቀቁ 528 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ተመዝግበው ለቆጠቡ የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን አባላትና የተቋሙ ቋሚ የሲቪል ሰራተኞች በእጣ የማስተላለፍ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው።
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የክልል ከተሞች የመከላከያ ሰራዊት የጋራ መኖሪያ ቤቶችን እየገነባ ሲሆን በቅርቡም ግንባታቸው የተጠናቀቁ ቤቶችን ለሰራዊቱና ለቋሚ ሰራተኞች ያስተልፋል ተብሏል።
የተገነቡ ቤቶች በእጣ ለባለእድለኞች በሚተላለፍበት መርሃግብር ላይ የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስትር ዶክተር አብራሃም በላይን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕይዝ በኢትዮጵያ ካሉ ታላላቅ የግንባታ ኩባንያዎች አንዱ ሲሆን የኢንፎርሜሽን ደህንነት ዋና መስሪያ ቤት፣ የመከላከያ ዋና መስሪያ ቤት ህንጻን ጨምሮ በርካታ አገራዊ ፕሮጀክቶችን ገንብቷል።
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
ግንባታቸው የተጠናቀቁ 528 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ተመዝግበው ለቆጠቡ ለኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን አባላትና ለተቋሙ የሲቪል ሰራተኞች በእጣ የማስተላለፍ መርሃግብር እየተካሄደ ነው።
ዕጣው በግዳጅ ላይ ያሉ የሰራዊት አባላት፣ በክብር የተሰናበቱ የሰራዊት አባላትን ያካተተ ነው። ሴት የሰራዊት አባላትን በልዩ ሁኔታ ተጠቃሚ ያደረገ መሆኑም ተጠቁሟል።
በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተፕራይዝ እየተገነቡ ካሉት የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል በአዲስ አበባ በሰሚት ቁጥር ሁለት ግንባታቸው የተጠናቀቁ 528 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ተመዝግበው ለቆጠቡ የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን አባላትና የተቋሙ ቋሚ የሲቪል ሰራተኞች በእጣ የማስተላለፍ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው።
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የክልል ከተሞች የመከላከያ ሰራዊት የጋራ መኖሪያ ቤቶችን እየገነባ ሲሆን በቅርቡም ግንባታቸው የተጠናቀቁ ቤቶችን ለሰራዊቱና ለቋሚ ሰራተኞች ያስተልፋል ተብሏል።
የተገነቡ ቤቶች በእጣ ለባለእድለኞች በሚተላለፍበት መርሃግብር ላይ የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስትር ዶክተር አብራሃም በላይን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕይዝ በኢትዮጵያ ካሉ ታላላቅ የግንባታ ኩባንያዎች አንዱ ሲሆን የኢንፎርሜሽን ደህንነት ዋና መስሪያ ቤት፣ የመከላከያ ዋና መስሪያ ቤት ህንጻን ጨምሮ በርካታ አገራዊ ፕሮጀክቶችን ገንብቷል።
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
የገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት 10 ወራት 282 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን ገለጸ፡፡
የገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት አስር ወራት 360 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ 282 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተነገረ፡፡
ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥም 168 ነጥብ 7 ቢሊየን ብሩ ከአገር ውስጥ ገቢ ታክስ የተገኘ ሲሆን፥ 113 ነጥብ 8 ቢሊየን ብሩ ደግሞ ከወጪ ንግድ ቀረጥና ታክስ የተገኘ ገቢ መሆኑን የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው ጠቁመዋል፡፡
በዚህም የእቅዱን 93 ነጥብ 1 በመቶ ማሳካት መቻሉን ነው አቶ ላቀ በሪፖርታቸው ያመላከቱት፡፡
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት እያካሄደ በሚገኘው 8ኛ መደበኛ ጉባዔ የገቢዎች ሚኒስቴርን እና የተጠሪ ተቋማቱን የ2014 በጀት ዓመት የ10 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እያዳመጠ ነው፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት አስር ወራት 360 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ 282 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተነገረ፡፡
ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥም 168 ነጥብ 7 ቢሊየን ብሩ ከአገር ውስጥ ገቢ ታክስ የተገኘ ሲሆን፥ 113 ነጥብ 8 ቢሊየን ብሩ ደግሞ ከወጪ ንግድ ቀረጥና ታክስ የተገኘ ገቢ መሆኑን የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው ጠቁመዋል፡፡
በዚህም የእቅዱን 93 ነጥብ 1 በመቶ ማሳካት መቻሉን ነው አቶ ላቀ በሪፖርታቸው ያመላከቱት፡፡
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት እያካሄደ በሚገኘው 8ኛ መደበኛ ጉባዔ የገቢዎች ሚኒስቴርን እና የተጠሪ ተቋማቱን የ2014 በጀት ዓመት የ10 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እያዳመጠ ነው፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ኢሰመኮ ከሕግ አግባብ ውጪ በእስር ላይ የሚገኙ የኦነግ አባላት በአፋጣኝ ከእስር እንዲለቀቁ ጠየቀ!
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አመራሮች ለተራዘመ ጊዜ ከሕግ አግባብ ውጭ ታስረው የሚገኙ በመሆኑ በአፋጣኝ ከእስር ሊለቀቁ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጠየቀ፡፡የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) አመራሮቹ ከእስር ከመለቀቅም ባለፈ ለደረሰባችው ጉዳት ሊካሱ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
የፍርድ ቤትና የዐቃቤ ሕግ ውሳኔዎች በተደጋጋሚ እየተጣሰ፣ እስረኞቹ ከሕግ ውጪ ለተራዘመ እስር መዳረጋቸው ስልጣንን ያለአግባብ መጠቀም መሆኑንም ነው ኮሚሽሩ የገለጹት፡፡የኦሮሚያ ክልል መንግሥት አፋጣኝ ማጣራት አካሂዶ ተገቢውን እርምጃ ሊወሰድበት እንደሚገባም ኮሚሽነሩ ማሳሰባቸውን ከተቋሙ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ኢሰመኮ በተለያዩ ፖሊስ መምሪያዎች በእስር ላይ ያሉ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አባሎች የእስር ሁኔታን በተመለከተ ክትትል ማድረጉን ገልጿል፡፡
ኢሰመኮ፤ ከመጋቢት 1 እስከ 10 ቀን 2014 ዓ.ም በቡራዩ ፣ በገላንና በሰበታ ፖሊስ መምሪያዎች በመሄድ እስረኞችን፣ የፖሊስ መምሪያ ኃላፊዎችን፣ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽንን እና የኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ተወካዮችን በማነጋገር ምርመራ መደረጉንም አስታውቋል።
ሙሉ ዜናውን ለማንበብ: https://am.al-ain.com/article/ehrc-urges-government-to-release-members-of-olf
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አመራሮች ለተራዘመ ጊዜ ከሕግ አግባብ ውጭ ታስረው የሚገኙ በመሆኑ በአፋጣኝ ከእስር ሊለቀቁ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጠየቀ፡፡የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) አመራሮቹ ከእስር ከመለቀቅም ባለፈ ለደረሰባችው ጉዳት ሊካሱ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
የፍርድ ቤትና የዐቃቤ ሕግ ውሳኔዎች በተደጋጋሚ እየተጣሰ፣ እስረኞቹ ከሕግ ውጪ ለተራዘመ እስር መዳረጋቸው ስልጣንን ያለአግባብ መጠቀም መሆኑንም ነው ኮሚሽሩ የገለጹት፡፡የኦሮሚያ ክልል መንግሥት አፋጣኝ ማጣራት አካሂዶ ተገቢውን እርምጃ ሊወሰድበት እንደሚገባም ኮሚሽነሩ ማሳሰባቸውን ከተቋሙ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ኢሰመኮ በተለያዩ ፖሊስ መምሪያዎች በእስር ላይ ያሉ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አባሎች የእስር ሁኔታን በተመለከተ ክትትል ማድረጉን ገልጿል፡፡
ኢሰመኮ፤ ከመጋቢት 1 እስከ 10 ቀን 2014 ዓ.ም በቡራዩ ፣ በገላንና በሰበታ ፖሊስ መምሪያዎች በመሄድ እስረኞችን፣ የፖሊስ መምሪያ ኃላፊዎችን፣ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽንን እና የኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ተወካዮችን በማነጋገር ምርመራ መደረጉንም አስታውቋል።
ሙሉ ዜናውን ለማንበብ: https://am.al-ain.com/article/ehrc-urges-government-to-release-members-of-olf
@YeneTube @FikerAssefa
ኦዴሳ
ፑቲን ኦዴሳ ከተማን ሳይቆጣጠር የዩክሬይን ዘመቻው ስኬታማ ሊሆንለት አይችልም። ኦዴሳን ከተቆጣጠረ ግን በአውሮፓ ትልልቅ ጂኦፖለቲካዊ ለውጦች ይጠበቃሉ። ለምን? ኦዴሳ ይህን ያህል ጥቅሟ ምንድነው?? ይህን አጭር ቪዲዮ ተከታተሉ
https://youtu.be/sW0rM_nr8Uo
ፑቲን ኦዴሳ ከተማን ሳይቆጣጠር የዩክሬይን ዘመቻው ስኬታማ ሊሆንለት አይችልም። ኦዴሳን ከተቆጣጠረ ግን በአውሮፓ ትልልቅ ጂኦፖለቲካዊ ለውጦች ይጠበቃሉ። ለምን? ኦዴሳ ይህን ያህል ጥቅሟ ምንድነው?? ይህን አጭር ቪዲዮ ተከታተሉ
https://youtu.be/sW0rM_nr8Uo
YouTube
ኦዴሳ፣ የፑቲን ቁጭት
#Sheger_Mekoya #ሸገር_መቆያ #Sheger_FM_Mekoya
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት አቅርቦትን ለማሳደግ የሚያስችል ውይይት ከሪል እስቴት አልሚዎች ጋር አደረገ።
የከተማ አስተዳደሩ ከግሉ ዘርፍ ጋር በጋራ በመተባበር ከተማውን ለማልማት በሚያስችለው መንገድ ዙርያ በዛሬው እለት ውይይት አካሂዷል፡፡
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ት ያስሚን ዉሀቢረቢ የከተማ አስተዳደሩ ያዘጋጃቸውን አማራጭ የቤት ልማት ሞዳሊቶችን ለውይይት መነሻ ይሆን ዘንድ ለሪል እስቴት አልሚ ድርጅቶች ተወክለው ለመጡ ተሰብሳቢዎች አቅርበው ውይይት ተካሂዶበታል፡፡
ከንቲባ አዳነች በውይይቱ ወቅት እንደተናገሩት ከሪል እስቴት አልሚዎች ጋር በመተባበር ፣የሚችሉ ነዋሪዎችን የቤት ባለቤት ለማድረግና ሌሎችም በአቅማቸው ልክ ቤቶቹ ተገንብተው በተመጣጣኝ ዋጋ ተከራይተው የሚኖሩበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ከተማ አስተዳደሩ ከሚመለከታቸው ሁሉ ጋር የላቀ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ አስታወቀዋል፡፡
ባለሀብቶች የልማት አጋር እንደመሆናችሁ መጠን የተዘጋጁ ሞዳሊቲዎችን በዝርዝር በመመልከት ለተግባራዊነቱ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በቅንጅት ለመስራት እንቅስቃሴ ልታደርጉ ይገባል ብለዋል
አያይዘውም የከተማ አስተዳደሩ ፤የነዋሪዎችን የቤት ፍላጎት በሂደት ለመቅረፍ አምስት የቤት ግንባታ ሞዳሊቲዎችን በዝርዝር አዘጋጅቶ ለተግባራዊነቱ የሚጠበቅበትን ሁሉ ለማድረግ አጋርነታችሁን እየተጠባበቀ የሚገኝ በመሆኑ እናንተም በነፍስ ወከፍ በአጭር ግዜ ግንባታ ለማጠናቀቅ የሚያስችሉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማምጣት የየድርሻችሁን አሻራ ለማኖርና የታሪክ ተከፋይ ለመሆን ልትሰወስኑ ይገባል ሲሉ አጽንዖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም የውጭ አገር አልሚዎችን የአዋጭነት ደረጃን በመፈተሽ እንዲሳተፉ ለማድረግ ይሰራልም ብለዋል ከንቲባዋ
የቤት አቅርቦትን በሚፈለገው መልኩ ተደራሽ ለማድረግ በዓመት 200,000 ሺና ከዚያ በላይ ቤቶችን መገንባት ያስፈልጋል ያሉት በምክትል ከንቲባ መዓረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ት ያስሚን አሁን ያለው ወቅታዊ ፍላጎት ከፍተኛ በመሆኑ አልሚዎች ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በጋራ የተዘረጉ ሞዳሊትዎችን መሠረት በማድረግ ልትሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡
የግሉ ዘርፉ በተለይ የቤት ልማትን በሚመለከት የፌደራል መንግስትና ከተማ አስተዳደሩ የጀመሩትን በርካታ የማክሮ ኢኮኖሚ የለውጥ ስራዎች መሠረት በማድረግ በሽርክናና በሌሎችም ተስማሚ አማራጮች ዘርፉን የማነቃቃት ሥራ መስራት ከአልሚዎች ይጠበቃል ሲሉ አስታውቀዋል ኃላፊዋ
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በጋራ በቅርበት የሚሰራ ግብርሃይል በውይይቱ መጨረሻ ተቋቁሟል
በውይይቱ ማጠቃለያ ተሳታፊዎቹ የማዘጋጃ ቤትን እድሳት ተዟዙረው ጎብኝተዋል፡፡
Via:- አ/አ ኮምኒኬሽን
@Yenetube @Fikerassefa
የከተማ አስተዳደሩ ከግሉ ዘርፍ ጋር በጋራ በመተባበር ከተማውን ለማልማት በሚያስችለው መንገድ ዙርያ በዛሬው እለት ውይይት አካሂዷል፡፡
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ት ያስሚን ዉሀቢረቢ የከተማ አስተዳደሩ ያዘጋጃቸውን አማራጭ የቤት ልማት ሞዳሊቶችን ለውይይት መነሻ ይሆን ዘንድ ለሪል እስቴት አልሚ ድርጅቶች ተወክለው ለመጡ ተሰብሳቢዎች አቅርበው ውይይት ተካሂዶበታል፡፡
ከንቲባ አዳነች በውይይቱ ወቅት እንደተናገሩት ከሪል እስቴት አልሚዎች ጋር በመተባበር ፣የሚችሉ ነዋሪዎችን የቤት ባለቤት ለማድረግና ሌሎችም በአቅማቸው ልክ ቤቶቹ ተገንብተው በተመጣጣኝ ዋጋ ተከራይተው የሚኖሩበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ከተማ አስተዳደሩ ከሚመለከታቸው ሁሉ ጋር የላቀ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ አስታወቀዋል፡፡
ባለሀብቶች የልማት አጋር እንደመሆናችሁ መጠን የተዘጋጁ ሞዳሊቲዎችን በዝርዝር በመመልከት ለተግባራዊነቱ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በቅንጅት ለመስራት እንቅስቃሴ ልታደርጉ ይገባል ብለዋል
አያይዘውም የከተማ አስተዳደሩ ፤የነዋሪዎችን የቤት ፍላጎት በሂደት ለመቅረፍ አምስት የቤት ግንባታ ሞዳሊቲዎችን በዝርዝር አዘጋጅቶ ለተግባራዊነቱ የሚጠበቅበትን ሁሉ ለማድረግ አጋርነታችሁን እየተጠባበቀ የሚገኝ በመሆኑ እናንተም በነፍስ ወከፍ በአጭር ግዜ ግንባታ ለማጠናቀቅ የሚያስችሉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማምጣት የየድርሻችሁን አሻራ ለማኖርና የታሪክ ተከፋይ ለመሆን ልትሰወስኑ ይገባል ሲሉ አጽንዖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም የውጭ አገር አልሚዎችን የአዋጭነት ደረጃን በመፈተሽ እንዲሳተፉ ለማድረግ ይሰራልም ብለዋል ከንቲባዋ
የቤት አቅርቦትን በሚፈለገው መልኩ ተደራሽ ለማድረግ በዓመት 200,000 ሺና ከዚያ በላይ ቤቶችን መገንባት ያስፈልጋል ያሉት በምክትል ከንቲባ መዓረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ት ያስሚን አሁን ያለው ወቅታዊ ፍላጎት ከፍተኛ በመሆኑ አልሚዎች ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በጋራ የተዘረጉ ሞዳሊትዎችን መሠረት በማድረግ ልትሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡
የግሉ ዘርፉ በተለይ የቤት ልማትን በሚመለከት የፌደራል መንግስትና ከተማ አስተዳደሩ የጀመሩትን በርካታ የማክሮ ኢኮኖሚ የለውጥ ስራዎች መሠረት በማድረግ በሽርክናና በሌሎችም ተስማሚ አማራጮች ዘርፉን የማነቃቃት ሥራ መስራት ከአልሚዎች ይጠበቃል ሲሉ አስታውቀዋል ኃላፊዋ
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በጋራ በቅርበት የሚሰራ ግብርሃይል በውይይቱ መጨረሻ ተቋቁሟል
በውይይቱ ማጠቃለያ ተሳታፊዎቹ የማዘጋጃ ቤትን እድሳት ተዟዙረው ጎብኝተዋል፡፡
Via:- አ/አ ኮምኒኬሽን
@Yenetube @Fikerassefa
ዚምቧብዌ የቀድሞው ፕሬዝዳንት መንግስቱ ሀይለማሪያምን ደብቅሻል መባሌ አግባብ አይደለም አለች፡፡
የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ፍሬድሪክ ሻቫ ” በዘር ማጥፋት ወንጀል የተከሰሱት፣ ጥፋተኛ ተብለው በ2000 በሌሉቡት የሞት ብይን የተሰጠባቸው የቀድሞ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ሀይለማሪያምን እንዱደበቁ አድርገዋል የሚሉት ሪፖረቶች ትክክል አይደለም” ሲሉ ከአሜሪካ ድምፅ ጋር በነበራችው የተናጠል ቆይታ ተናግረዋል፡፡
ይህ የዚምቧብዌ ወቅታዊ አቋም ”ትልቅ ፖሊሲ ሽፍት ነው” ሲል የገለፀው ዘገባው የቀድሞው የሀገሪቱን አቋም የማስታወቂያ ሚኒስትሩን ንግግር ጠቅሶ ፅፏል፡፡
የቀድሞው የማስታወቂያ ሚኒስትር ቲቾና ጃኮንያ ለአውሮፓዊያኑ 2009 ለአሜሪካ ድምፅ እንደነገሩት ”መንግስቱ ሀይለማሪያምን አሳልፈን አንሰጥም” ብለው ነበር፡፡
የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኮሎኔል መንግስቱ ሀይለማሪያም ከ17 ዓመት የመሪነት ዘመን በኋላ ከኢትዮጵያ የወጡት ግንቦት 13 ቀን 1983 ዓ.ም ነበር፡፡
ከሀገራቸው ከወጡ 31ኛ ዓመታቸውን የፊታችን ቅዳሜ ይደፍናሉ፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ፍሬድሪክ ሻቫ ” በዘር ማጥፋት ወንጀል የተከሰሱት፣ ጥፋተኛ ተብለው በ2000 በሌሉቡት የሞት ብይን የተሰጠባቸው የቀድሞ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ሀይለማሪያምን እንዱደበቁ አድርገዋል የሚሉት ሪፖረቶች ትክክል አይደለም” ሲሉ ከአሜሪካ ድምፅ ጋር በነበራችው የተናጠል ቆይታ ተናግረዋል፡፡
ይህ የዚምቧብዌ ወቅታዊ አቋም ”ትልቅ ፖሊሲ ሽፍት ነው” ሲል የገለፀው ዘገባው የቀድሞው የሀገሪቱን አቋም የማስታወቂያ ሚኒስትሩን ንግግር ጠቅሶ ፅፏል፡፡
የቀድሞው የማስታወቂያ ሚኒስትር ቲቾና ጃኮንያ ለአውሮፓዊያኑ 2009 ለአሜሪካ ድምፅ እንደነገሩት ”መንግስቱ ሀይለማሪያምን አሳልፈን አንሰጥም” ብለው ነበር፡፡
የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኮሎኔል መንግስቱ ሀይለማሪያም ከ17 ዓመት የመሪነት ዘመን በኋላ ከኢትዮጵያ የወጡት ግንቦት 13 ቀን 1983 ዓ.ም ነበር፡፡
ከሀገራቸው ከወጡ 31ኛ ዓመታቸውን የፊታችን ቅዳሜ ይደፍናሉ፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ ከዓለም በርካታ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ያሉባት አገር ሆነች!
ኢንተርናል ዲስፕለስመንት ሞኒተሪንግ ሴንተር የተባለው ተቋም የአውሮፓውያኑ 2021 ማብቂያ ላይ በመላው ዓለም የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ቁጥር 59.1 ሚሊዮን መድረሱን ገልጿል።እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ አፍጋኒስታን፣ ሶሪያ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ ያሉ አገራት ደግሞ በርካታ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሚገኙባቸው አገራት ናቸው።በዓለም ላይ በርካታ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሚገኙት ከሰሃራ በታች ባሉ አገራት ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ብቻ የተመዘገበው 5 ሚሊዮን የተፈናቃይ ሕዝብ ቁጥር በአንድ አገር የተመዘገበ ትልቁ አሃዝ ሆኗል ብሏል ድርጅቱ።
በትግራይ ክልል ተቀስቅሶ አጎራባች ወደሆኑት አማራ እና አፋር ክልሎች ተሸጋግሮ የነበረው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ከቀያቸው ማፈናቀሉ ይታወቃል።ይህንን ጦርነት ተከትሎ በትግራይ፣ በአማራ እና በአፋር ክልሎች የተናቀሉ ሰዎች ቁጥር በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መሆናቸውን የተባበሩት መንግሥታት ገልጾ ነበር።ከሰሃራ በታች ባሉ አገራት ከግጭት ጋር ተያይዞ የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር 11.6 ሚሊዮን ሕዝብ ሲሆን ከተፈጥሮ አደጋ ጋር በተያያዘ ደግሞ 2.6 ሚሊዮን ሕዝብ ቀየውን ጥሎ ለመሰደድ ተገዷል።
ዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ ኮንጎ፣አፍጋኒስታን እና ሚያንማር እአአ 2021 ላይ ከፍተኛ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮችን በመመዝገባቸውን የአገር ውስጥ ተፈናቃዮችን ቁጥርን የሚከታተለው ማዕከል ገልጿል።ምንም እንኳ በመካከለኛው ምሥራቅ እና በሰሜን አፍሪካ በሚገኙ አገራት የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ቁጥር በ10 ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ቢቀንስም፤ አሁንም በቀጠናው ተፈናቅለው የሚገኙ ሰዎች ቁጥር አሳሳቢ ነው ተብሏል።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ኢንተርናል ዲስፕለስመንት ሞኒተሪንግ ሴንተር የተባለው ተቋም የአውሮፓውያኑ 2021 ማብቂያ ላይ በመላው ዓለም የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ቁጥር 59.1 ሚሊዮን መድረሱን ገልጿል።እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ አፍጋኒስታን፣ ሶሪያ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ ያሉ አገራት ደግሞ በርካታ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሚገኙባቸው አገራት ናቸው።በዓለም ላይ በርካታ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሚገኙት ከሰሃራ በታች ባሉ አገራት ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ብቻ የተመዘገበው 5 ሚሊዮን የተፈናቃይ ሕዝብ ቁጥር በአንድ አገር የተመዘገበ ትልቁ አሃዝ ሆኗል ብሏል ድርጅቱ።
በትግራይ ክልል ተቀስቅሶ አጎራባች ወደሆኑት አማራ እና አፋር ክልሎች ተሸጋግሮ የነበረው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ከቀያቸው ማፈናቀሉ ይታወቃል።ይህንን ጦርነት ተከትሎ በትግራይ፣ በአማራ እና በአፋር ክልሎች የተናቀሉ ሰዎች ቁጥር በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መሆናቸውን የተባበሩት መንግሥታት ገልጾ ነበር።ከሰሃራ በታች ባሉ አገራት ከግጭት ጋር ተያይዞ የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር 11.6 ሚሊዮን ሕዝብ ሲሆን ከተፈጥሮ አደጋ ጋር በተያያዘ ደግሞ 2.6 ሚሊዮን ሕዝብ ቀየውን ጥሎ ለመሰደድ ተገዷል።
ዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ ኮንጎ፣አፍጋኒስታን እና ሚያንማር እአአ 2021 ላይ ከፍተኛ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮችን በመመዝገባቸውን የአገር ውስጥ ተፈናቃዮችን ቁጥርን የሚከታተለው ማዕከል ገልጿል።ምንም እንኳ በመካከለኛው ምሥራቅ እና በሰሜን አፍሪካ በሚገኙ አገራት የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ቁጥር በ10 ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ቢቀንስም፤ አሁንም በቀጠናው ተፈናቅለው የሚገኙ ሰዎች ቁጥር አሳሳቢ ነው ተብሏል።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
ለቤትዎ ለቢሮዎ እንዲሁም ለድርጅትዎ ይተለያየ ውበት ያላቸውን የፍይበር ግላስ የአበባ መትከያ ከፈለጉ እኛ አለን የድርጅትዎን እርማም መትከያው ላይ እናትምሎታለን
👋👋እንዲሁም ይሄን አዋጭ ቢዝነስ
ለመጀመር ካሰቡ ሙሉ ስልጠና እንሰጣለን ይደውሉልን
https://tttttt.me/+xvCuMwxhK19kODg0
☝️☝️☝️Join our group
Phone number:0987414243
0913676664
👋👋እንዲሁም ይሄን አዋጭ ቢዝነስ
ለመጀመር ካሰቡ ሙሉ ስልጠና እንሰጣለን ይደውሉልን
https://tttttt.me/+xvCuMwxhK19kODg0
☝️☝️☝️Join our group
Phone number:0987414243
0913676664
የብሄራዊ ደኅንነትና መረጃ አገልግሎት ሠራተኞች የማናቸውም ፖለቲካ ፓርቲ አባላት እንዳይሆኑ የሚያዝ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡን ዋዜማ ዘግባለች።
የሚንስትሮች ምክር ቤት መጋቢት ላይ የመራው ረቂቅ አዋጅ፣ የብሄራዊ ደኅንነትና መረጃ ተቋምን እንደገና ለማዋቀር የቀረበ ነው። ረቂቅ አዋጁ የተቋሙ ሠራተኞች በማንኛውም የፖለቲካ ቅስቀሳ እና ገቢ በሚያስገኝ ሌላ ተጨማሪ የሥራ መስክ እንዳይሰማሩ ጭምር ይከለክላል። የተቋሙ ሠራተኞች ከሥራው ባህሪ ጋር የሚመጣጠን በቂ ደመወዝ እና ጥቅማጥቅም እንዲከፈላቸው ለመንግሥት ጥያቄ እንደሚቀርብ የሚገልጠው ረቂቁ፣ የሠራተኛ ምልመላ፣ ቅጥር፣ ሙያዊ ስነ ምግባርና የስንብት ደንቦችን ጭምር አካቷል።
@YeneTube @FikerAssefa
የሚንስትሮች ምክር ቤት መጋቢት ላይ የመራው ረቂቅ አዋጅ፣ የብሄራዊ ደኅንነትና መረጃ ተቋምን እንደገና ለማዋቀር የቀረበ ነው። ረቂቅ አዋጁ የተቋሙ ሠራተኞች በማንኛውም የፖለቲካ ቅስቀሳ እና ገቢ በሚያስገኝ ሌላ ተጨማሪ የሥራ መስክ እንዳይሰማሩ ጭምር ይከለክላል። የተቋሙ ሠራተኞች ከሥራው ባህሪ ጋር የሚመጣጠን በቂ ደመወዝ እና ጥቅማጥቅም እንዲከፈላቸው ለመንግሥት ጥያቄ እንደሚቀርብ የሚገልጠው ረቂቁ፣ የሠራተኛ ምልመላ፣ ቅጥር፣ ሙያዊ ስነ ምግባርና የስንብት ደንቦችን ጭምር አካቷል።
@YeneTube @FikerAssefa
ከ300 በላይ ሰብዓዊ ዕርዳታ የጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች በዚህ ሳምንት ወደ ትግራይ መግባታቸውን ከህወሓት ከፍተኛ አመራሮች አንዱ የሆኑት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ተናገሩ።
ተሽከርካሪዎቹ የንጽህና መጠበቂያን ጨምሮ ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶችን ጭምር ወደ ትግራይ ማድረሳቸውን ፕሮፌሰር ክንደያ በመቐለ ለሚገኘው የዶይቼ ቬለ ዘጋቢ ተናግረዋል።ለህወሓት ታማኝ የሆኑ የትግራይ ኃይሎች ከኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እና አጋሮቹ ጋር የሚያደርጉት ውጊያ "ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት የማቆም ውሳኔ" ተላልፎ ጋብ ያለው ባለፈው መጋቢት አጋማሽ ገደማ ነበር። ውጊያው እንደገና ሊቀሰቀስ ይችላል የሚል ሥጋት በሚሰማበት በዚህ ወቅት ወደ ትግራይ የሚደርሰው የሰብዓዊ ዕርዳታ ጭማሪ ማሳየቱን የህወሓት ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ፕሮፌሰር ክንደያ ተናግረዋል።
"ተኩስ ማቆም እንደ ስምምነት ካደረግን ጀምሮ የተወሰኑ ነገሮች መግባት ጀምረዋል። በዚህ ሳምንት ደግሞ ትንሽ ጨመር የማድረግ [አዝማሚያ̄] አለ። ከታኅሳስ ጀምሮ እስከ መጋቢት ምንም መኪና አልገባም ነበር። አሁን ደግሞ በዚህ ሳምንት ወደ 300 ከዚያ በላይም መኪኖች መጥተዋል። የምግብ ብቻ አይደለም። የንጽህና አገልግሎቶች ሌሎች ምግብ ነክ ያልሆኑ የምንላቸው የገቡበት ሁኔታ አለ። ዋናው መልዕክት የትግራይ ሕዝብ ተዘግቶ እጁን እንዲሰጥ፤ በተለያዩ ጥረቶች ተከቦ እጁን እንዲሰጥ የተደረገበት አጋጣሚ ነው አሁን ያለንበት።ግን ደግሞ አሁን ያየንው በዚህ ሳምንት ትንሽ የመጨመር ሁኔታ የሚያሳየው ይቻል ነበር ነው" ሲሉ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል።
የዓለም የምግብ ፕሮግራም ሰብዓዊ ዕርዳታ የጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ እና ወደ አፋር ክልሎች በማምራት ላይ እንደሚገኙ ባለፈው እሁድ ገልጾ ነበር።ድርጅቱ በተረጋገጠ የትዊተር ገጹ ባሰፈረው አጭር ጽሁፍ 85 ከባድ ተሽከርካሪዎች ባለፈው ግንቦት 6 ቀን 2014 መቐለ ከተማ መድረሳቸውን አስታውቋል። በሌሎች 130 ተሽከርካሪዎች ደግሞ በጉዞ ላይ ነበሩ።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
ተሽከርካሪዎቹ የንጽህና መጠበቂያን ጨምሮ ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶችን ጭምር ወደ ትግራይ ማድረሳቸውን ፕሮፌሰር ክንደያ በመቐለ ለሚገኘው የዶይቼ ቬለ ዘጋቢ ተናግረዋል።ለህወሓት ታማኝ የሆኑ የትግራይ ኃይሎች ከኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እና አጋሮቹ ጋር የሚያደርጉት ውጊያ "ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት የማቆም ውሳኔ" ተላልፎ ጋብ ያለው ባለፈው መጋቢት አጋማሽ ገደማ ነበር። ውጊያው እንደገና ሊቀሰቀስ ይችላል የሚል ሥጋት በሚሰማበት በዚህ ወቅት ወደ ትግራይ የሚደርሰው የሰብዓዊ ዕርዳታ ጭማሪ ማሳየቱን የህወሓት ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ፕሮፌሰር ክንደያ ተናግረዋል።
"ተኩስ ማቆም እንደ ስምምነት ካደረግን ጀምሮ የተወሰኑ ነገሮች መግባት ጀምረዋል። በዚህ ሳምንት ደግሞ ትንሽ ጨመር የማድረግ [አዝማሚያ̄] አለ። ከታኅሳስ ጀምሮ እስከ መጋቢት ምንም መኪና አልገባም ነበር። አሁን ደግሞ በዚህ ሳምንት ወደ 300 ከዚያ በላይም መኪኖች መጥተዋል። የምግብ ብቻ አይደለም። የንጽህና አገልግሎቶች ሌሎች ምግብ ነክ ያልሆኑ የምንላቸው የገቡበት ሁኔታ አለ። ዋናው መልዕክት የትግራይ ሕዝብ ተዘግቶ እጁን እንዲሰጥ፤ በተለያዩ ጥረቶች ተከቦ እጁን እንዲሰጥ የተደረገበት አጋጣሚ ነው አሁን ያለንበት።ግን ደግሞ አሁን ያየንው በዚህ ሳምንት ትንሽ የመጨመር ሁኔታ የሚያሳየው ይቻል ነበር ነው" ሲሉ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል።
የዓለም የምግብ ፕሮግራም ሰብዓዊ ዕርዳታ የጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ እና ወደ አፋር ክልሎች በማምራት ላይ እንደሚገኙ ባለፈው እሁድ ገልጾ ነበር።ድርጅቱ በተረጋገጠ የትዊተር ገጹ ባሰፈረው አጭር ጽሁፍ 85 ከባድ ተሽከርካሪዎች ባለፈው ግንቦት 6 ቀን 2014 መቐለ ከተማ መድረሳቸውን አስታውቋል። በሌሎች 130 ተሽከርካሪዎች ደግሞ በጉዞ ላይ ነበሩ።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
ዛሬ በኢትዮጵያ ኤፍኤስዲ ኢትዮጵያ የተሰኘ አዲስ የልማት ፋይናንስ ተቋም እንደተቋቋመ ካፒታል ዘግቧል።
አዲሱ ተቋም ለመንግሥት እና ለግሉ ፋይናንስ ዘርፍ የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፎችን የሚሰጥ ነው።ኤፍኤስዲ ኢትዮጵያን በገንዘብ የሚደግፉት የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን እና የእንግሊዙ የውጭ የጋራ ብልጽግና አገሮች የልማት ቢሮ እንደሆኑ ተገልጧል።ትናንት ገንዘብ ሚንስቴር እና ተቀማጭነቱ ኬንያ የሆነው ኤፍኤስዲ አፍሪካ በትብብር የመጀመሪያውን የኢትዮጵያ አክሲዮን ገበያ ለማቋቋም ስምምነት ላይ እንደደረሱ ይታወሳል።
@YeneTube @FikerAssefa
አዲሱ ተቋም ለመንግሥት እና ለግሉ ፋይናንስ ዘርፍ የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፎችን የሚሰጥ ነው።ኤፍኤስዲ ኢትዮጵያን በገንዘብ የሚደግፉት የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን እና የእንግሊዙ የውጭ የጋራ ብልጽግና አገሮች የልማት ቢሮ እንደሆኑ ተገልጧል።ትናንት ገንዘብ ሚንስቴር እና ተቀማጭነቱ ኬንያ የሆነው ኤፍኤስዲ አፍሪካ በትብብር የመጀመሪያውን የኢትዮጵያ አክሲዮን ገበያ ለማቋቋም ስምምነት ላይ እንደደረሱ ይታወሳል።
@YeneTube @FikerAssefa
ፈንጂ 5 ሰዎችን ገደለ!
በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ባቲ ከተማ ፈንጂ 5 ሰዎች መሞታቸውን የባቲ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ።የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሐመድ ሰኢድ ለዶይቼ ቬሌ ዛሬ እንደነገሩት በቅርቡ ከህወሓት ጋር በነበረ ጦርነት ቡድኑ ጥሎት የሄደን ፈንጂ ትናንት አግኝተው ሲነካኩ በመፈንዳቱ በአካባቢው የነበሩ ሠዎችን ጨምሮ 5 ሠዎች ህይወታቸው አልፏል።እንደ አቶ መሐመድ ሌሎች 5 ሠዎች ደግሞ በከፍተኛ ሁኔታ ቆስለው በህክምና ላይ ናቸው።ጉዳቱ የደረሰባቸው ሠዎች ከህፃናት እስከ አዋቂ ያሉ እንደሆኑም ጨምረው ተናግረዋል።ሕብረተሰቡ ማነኛውንም ብረት ነገር ሲያገኝ ለፀጥታ አካላት ማሳየት እንጂ በራስ መነካካት ጉዳት ያመጣልም ሲሉ ማስጠንቀቃቸውን ዶይቸ ቬሌ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ባቲ ከተማ ፈንጂ 5 ሰዎች መሞታቸውን የባቲ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ።የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሐመድ ሰኢድ ለዶይቼ ቬሌ ዛሬ እንደነገሩት በቅርቡ ከህወሓት ጋር በነበረ ጦርነት ቡድኑ ጥሎት የሄደን ፈንጂ ትናንት አግኝተው ሲነካኩ በመፈንዳቱ በአካባቢው የነበሩ ሠዎችን ጨምሮ 5 ሠዎች ህይወታቸው አልፏል።እንደ አቶ መሐመድ ሌሎች 5 ሠዎች ደግሞ በከፍተኛ ሁኔታ ቆስለው በህክምና ላይ ናቸው።ጉዳቱ የደረሰባቸው ሠዎች ከህፃናት እስከ አዋቂ ያሉ እንደሆኑም ጨምረው ተናግረዋል።ሕብረተሰቡ ማነኛውንም ብረት ነገር ሲያገኝ ለፀጥታ አካላት ማሳየት እንጂ በራስ መነካካት ጉዳት ያመጣልም ሲሉ ማስጠንቀቃቸውን ዶይቸ ቬሌ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
ኦዴሳ
ፑቲን ኦዴሳ ከተማን ሳይቆጣጠር የዩክሬይን ዘመቻው ስኬታማ ሊሆንለት አይችልም። ኦዴሳን ከተቆጣጠረ ግን በአውሮፓ ትልልቅ ጂኦፖለቲካዊ ለውጦች ይጠበቃሉ። ለምን? ኦዴሳ ይህን ያህል ጥቅሟ ምንድነው?? ይህን አጭር ቪዲዮ ተከታተሉ
https://youtu.be/sW0rM_nr8Uo
ፑቲን ኦዴሳ ከተማን ሳይቆጣጠር የዩክሬይን ዘመቻው ስኬታማ ሊሆንለት አይችልም። ኦዴሳን ከተቆጣጠረ ግን በአውሮፓ ትልልቅ ጂኦፖለቲካዊ ለውጦች ይጠበቃሉ። ለምን? ኦዴሳ ይህን ያህል ጥቅሟ ምንድነው?? ይህን አጭር ቪዲዮ ተከታተሉ
https://youtu.be/sW0rM_nr8Uo
YouTube
ኦዴሳ፣ የፑቲን ቁጭት
#Sheger_Mekoya #ሸገር_መቆያ #Sheger_FM_Mekoya
አሳዛኝ ዜና!
ተወዳጁ ኮሜዲያን ወንድወሰን ብርሃኑ (ዶክሌ) ባጋጠመው የልብ ህመም ምክንያት ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ሜድስታር ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው እለት ግንቦት 11, 2014 በተወለደ በ57 አመቱ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።
ዶክሌ ላለፋት ሁለት አስርተ አመታት በኮሜዲው ዘርፍ አዝናኝ፣ አስተማሪ እና ቁምነገር አዘል የኮሜዲ ስራዎችን ሲያቀርብ መቆየቱ ይታወቃል። ዶክሌ ሀገራችን ካፈራቻቸው ብርቅዬና ግንባር ቀደም ኮሜዲያኖች ውስጥ አንዱ ሲሆን ባለትዳርና የ5 ልጆች አባት ነበር።
@Yenetube @Fikerassefa
ተወዳጁ ኮሜዲያን ወንድወሰን ብርሃኑ (ዶክሌ) ባጋጠመው የልብ ህመም ምክንያት ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ሜድስታር ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው እለት ግንቦት 11, 2014 በተወለደ በ57 አመቱ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።
ዶክሌ ላለፋት ሁለት አስርተ አመታት በኮሜዲው ዘርፍ አዝናኝ፣ አስተማሪ እና ቁምነገር አዘል የኮሜዲ ስራዎችን ሲያቀርብ መቆየቱ ይታወቃል። ዶክሌ ሀገራችን ካፈራቻቸው ብርቅዬና ግንባር ቀደም ኮሜዲያኖች ውስጥ አንዱ ሲሆን ባለትዳርና የ5 ልጆች አባት ነበር።
@Yenetube @Fikerassefa
ደቡብ ሱዳን በናይል ወንዝ ላይ የመጀመሪያውን ቋሚ ድልድይ ሰራች
በደቡብ ሱዳን በናይል ወንዝ ላይ የመጀመሪያውን ቋሚ ድልድይ በትላንትናው እለት በይፋ መመረቁን ተከትሎ በደስታ የተሞላው የሀገሬው ህዝብ በድልድዩ ላይ ደስታውን ሲገልፅ ውሏል። በዋና ከተማዋ ጁባ የሚገኘውና 560 ሜትር ርዝመት ያለው የነጻነት ድልድይ የተገነባው ከጃፓን መንግስት በተገኘ እርዳታ ነው።
ግንባታው የጀመረው በ2013 ቢሆንም በእርስ በርስ ጦርነት እና በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የተነሳ ግንባታው ሲስተጓጎል ቆይቷል።አስቀድሞ የነበረው ድልድይ ሊንቀሳቀስ የሚችል በተለይ ለእግረኞች መሻገር አደገኛ ነበር።
በድልድዩ የምረቃ ስነስርዓት የኬንያ ፕሬዝዳንታዊ እጩ እና የአፍሪካ ህብረት የመሠረተ ልማት ልዑክ ራይላ ኦዲንጋ እንዲሁም የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ ኃላፊ ታናካ አኪሂኮ ተገኝተዋል። የነጻነት ድልድይ በጃፓን እና በደቡብ ሱዳን ህዝቦች መካከል የረጅም ጊዜ እና ዘላቂ ወዳጅነት ምልክት መሆኑን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር በስነስርዓቱ ላይ ተናግረዋል።
ድልድዩ በጁባ ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ ከማቃለሉም በላይ የንግድ እንቅስቃሴውን ለማፋጠን ይረዳል ተብሎ ይጠበቃል።
Via:- ዳጉ ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa
በደቡብ ሱዳን በናይል ወንዝ ላይ የመጀመሪያውን ቋሚ ድልድይ በትላንትናው እለት በይፋ መመረቁን ተከትሎ በደስታ የተሞላው የሀገሬው ህዝብ በድልድዩ ላይ ደስታውን ሲገልፅ ውሏል። በዋና ከተማዋ ጁባ የሚገኘውና 560 ሜትር ርዝመት ያለው የነጻነት ድልድይ የተገነባው ከጃፓን መንግስት በተገኘ እርዳታ ነው።
ግንባታው የጀመረው በ2013 ቢሆንም በእርስ በርስ ጦርነት እና በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የተነሳ ግንባታው ሲስተጓጎል ቆይቷል።አስቀድሞ የነበረው ድልድይ ሊንቀሳቀስ የሚችል በተለይ ለእግረኞች መሻገር አደገኛ ነበር።
በድልድዩ የምረቃ ስነስርዓት የኬንያ ፕሬዝዳንታዊ እጩ እና የአፍሪካ ህብረት የመሠረተ ልማት ልዑክ ራይላ ኦዲንጋ እንዲሁም የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ ኃላፊ ታናካ አኪሂኮ ተገኝተዋል። የነጻነት ድልድይ በጃፓን እና በደቡብ ሱዳን ህዝቦች መካከል የረጅም ጊዜ እና ዘላቂ ወዳጅነት ምልክት መሆኑን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር በስነስርዓቱ ላይ ተናግረዋል።
ድልድዩ በጁባ ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ ከማቃለሉም በላይ የንግድ እንቅስቃሴውን ለማፋጠን ይረዳል ተብሎ ይጠበቃል።
Via:- ዳጉ ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa
ሃገራቸውን እና ህዝባቸውን ያገለገሉ አካላት ላይ የሚደርስ መንግስታዊ እገታ እንዲቆም የፓርላማ የአብን አባላት አሳሰቡ!
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አባላት በሕግ ማስከበር ስም የሚነሱ የሕዝብ ጥያቄዎችንና ጠያቂዎችን የማጥፋትና ሕዝባችንን አንገት የማስደፋት እንቅስቃሴ አጥብቀን እንቃወማለን ሲሉ መግለጫ አወጡ።መንግስት በአማራ ክልል ህዝብ ላይ የሚፈፅመው ማዋከብ “የታወቀ ጠላት የሚያደርገው ዓይነት” ሲሆን ማዋከቡ በአስቸኳይ ካልቆመ ሀገርና ሕዝብ በጉጉት የሚጠብቀው የአገራዊ ምክክር ከወዲሁ እንዲጨናገፍ የሚያደርግ ውጤት እንደሚያስከትል አጥብቀን ለማሳሰብ እንወዳለን።
በፓርቲው አባላትና አመራሮች፣ በፋኖ አባላት፣ በሕጋዊ ታጣቂዎችና ወጣቶች እንዲሁም አገራቸውንና ሕዝባቸውን ያገለገሉ የጦር መኮንኖችንና የጸጥታ አመራሮች ላይ የሚፈጸመው መንግስታዊ እገታና ስወራ በአስቸኳይ እንዲቆምና በዚህ ሰበብ በማንነታቸው ብቻ የታገቱ አካላትም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቀቁ ሲሉም ጠይቀዋል።
የአብን የፓርላማ አባላት በመግለጫቸው “መንግስት ትንሹን መንግስታዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣና የህዝባችንን ደህንነት እንዲያረጋግጥ” በተደጋጋሚ ብንጠይቅም ጆሮ አልሰጠንም።በእዚህም የተነሳ የክልሉ ህዝብ ማንነትን መሰረት ላደረገ ጅምላ ጭፍጨፋ፣ መፈናቀልና ስደት ተዳርጓል ያሉት አባላቱ ኢትዮጵያ በሀገር ውስጥ መፈናቀል ከዓለም ቀዳሚ ለመሆኗ አንዱ ምክንያት ሆኗል።
ሕግ ማስከበርን ሰበብ በማድረግ የፌደራል የፀጥታ መዋቅር በሕገ መንግሥቱ ለክልልና ለፌዴራል ተለይቶ የተሰጠውን ኃላፊነት እና ሚና በደፈጠጠ መልኩ ክልሉን በሕገ-ወጥ መንገድ ለመቆጣጠር የሚያደርገውን ሙከራ እንዲያቆም እንዲሁም “የክልሉ መንግስት በፌደራል መንግስቱ ለሚፈጸመው።
[Addis Zeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አባላት በሕግ ማስከበር ስም የሚነሱ የሕዝብ ጥያቄዎችንና ጠያቂዎችን የማጥፋትና ሕዝባችንን አንገት የማስደፋት እንቅስቃሴ አጥብቀን እንቃወማለን ሲሉ መግለጫ አወጡ።መንግስት በአማራ ክልል ህዝብ ላይ የሚፈፅመው ማዋከብ “የታወቀ ጠላት የሚያደርገው ዓይነት” ሲሆን ማዋከቡ በአስቸኳይ ካልቆመ ሀገርና ሕዝብ በጉጉት የሚጠብቀው የአገራዊ ምክክር ከወዲሁ እንዲጨናገፍ የሚያደርግ ውጤት እንደሚያስከትል አጥብቀን ለማሳሰብ እንወዳለን።
በፓርቲው አባላትና አመራሮች፣ በፋኖ አባላት፣ በሕጋዊ ታጣቂዎችና ወጣቶች እንዲሁም አገራቸውንና ሕዝባቸውን ያገለገሉ የጦር መኮንኖችንና የጸጥታ አመራሮች ላይ የሚፈጸመው መንግስታዊ እገታና ስወራ በአስቸኳይ እንዲቆምና በዚህ ሰበብ በማንነታቸው ብቻ የታገቱ አካላትም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቀቁ ሲሉም ጠይቀዋል።
የአብን የፓርላማ አባላት በመግለጫቸው “መንግስት ትንሹን መንግስታዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣና የህዝባችንን ደህንነት እንዲያረጋግጥ” በተደጋጋሚ ብንጠይቅም ጆሮ አልሰጠንም።በእዚህም የተነሳ የክልሉ ህዝብ ማንነትን መሰረት ላደረገ ጅምላ ጭፍጨፋ፣ መፈናቀልና ስደት ተዳርጓል ያሉት አባላቱ ኢትዮጵያ በሀገር ውስጥ መፈናቀል ከዓለም ቀዳሚ ለመሆኗ አንዱ ምክንያት ሆኗል።
ሕግ ማስከበርን ሰበብ በማድረግ የፌደራል የፀጥታ መዋቅር በሕገ መንግሥቱ ለክልልና ለፌዴራል ተለይቶ የተሰጠውን ኃላፊነት እና ሚና በደፈጠጠ መልኩ ክልሉን በሕገ-ወጥ መንገድ ለመቆጣጠር የሚያደርገውን ሙከራ እንዲያቆም እንዲሁም “የክልሉ መንግስት በፌደራል መንግስቱ ለሚፈጸመው።
[Addis Zeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
“ሊፍት ኢትዮጵያ” የትራንስፖርት ዘርፉን ተቀላቅያለሁ ብሏል፡፡
ሊፍት ኢትዮጵያ የታክሲ አገልግሎት በመዲናችን አዲስ አበባ አሁን ካለው የሜትር ታክሲ ክፍያ ከ25 እስከ 35 በመቶ ቅናሽ በማድረግ ለማህበረሰቡ አገልግሎት እንደሚሰጥ የሊፍት ኢትዮጵያ ስራ አስኪያጅ አቶ ሙኒብ አብዱልካፉር ተናግረዋል፡፡አገልግሎቱ በመዲናዋ ያሉ አነስተኛ እና መካከልኛ ገቢ ያላቸውን የማህበረሰብ ክፍል የትራንስፖርት ፍላጎት ለሟሟላት መቋቋሙንም ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
አቶ ሙኒብ አገልግሎቱን የሚጠቀሙ ደንበኞች ክፍያውን የሚፈጽሙት በዲጂታል መሆኑ “ሊፍት ኢትዮጵያን” ለየት ያደርገዋል ብለዉናል፡፡ከዚህም በተጨማሪ አብረው መስራት የሚፈልጉ የተሸከርካሪ ባለንብረቶች፤ምንም ተቆራጭ( ኮሚሽን) የማይደረግባቸው ሲሆን፤በወር የ449 ብር ጥቅል በመሙላት ብቻ ያለገደብ መስራት እንደሚችሉ ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል፡፡
አሁን ላይ 1 ሺ 800 መኪናዎች ከሊፍት ኢትዮጵያ ጋር አብረው እየሰሩ መሆናቸውን የነገሩን አቶ ሙኒብ፤ በሚቀጥለው ወር 10 ሺ መኪናዎችን ወደ ስራ ለማስገባት ማቀዳቸውንም ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም “ሊፍት ተማሪ” የተባለ ለየት ያለ የተማሪዎች የወር ጥቅል የተዘጋጀም ሲሆን፤ተማሪዎች በጋራም ሆነ በግል በተመጣጣኝ ዋጋ የትራንስፖርት አገልግሎቱን እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡አገልግሎት ፈላጎዎች “የሊፍት ኢትዮጵያን” መተግበሪያ ከጎግል በማውረድ አልያም በ9885 በነጻ የስልክ መስመር በመደወል መጠቀም ይችላሉ ተብሏል፡፡
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
ሊፍት ኢትዮጵያ የታክሲ አገልግሎት በመዲናችን አዲስ አበባ አሁን ካለው የሜትር ታክሲ ክፍያ ከ25 እስከ 35 በመቶ ቅናሽ በማድረግ ለማህበረሰቡ አገልግሎት እንደሚሰጥ የሊፍት ኢትዮጵያ ስራ አስኪያጅ አቶ ሙኒብ አብዱልካፉር ተናግረዋል፡፡አገልግሎቱ በመዲናዋ ያሉ አነስተኛ እና መካከልኛ ገቢ ያላቸውን የማህበረሰብ ክፍል የትራንስፖርት ፍላጎት ለሟሟላት መቋቋሙንም ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
አቶ ሙኒብ አገልግሎቱን የሚጠቀሙ ደንበኞች ክፍያውን የሚፈጽሙት በዲጂታል መሆኑ “ሊፍት ኢትዮጵያን” ለየት ያደርገዋል ብለዉናል፡፡ከዚህም በተጨማሪ አብረው መስራት የሚፈልጉ የተሸከርካሪ ባለንብረቶች፤ምንም ተቆራጭ( ኮሚሽን) የማይደረግባቸው ሲሆን፤በወር የ449 ብር ጥቅል በመሙላት ብቻ ያለገደብ መስራት እንደሚችሉ ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል፡፡
አሁን ላይ 1 ሺ 800 መኪናዎች ከሊፍት ኢትዮጵያ ጋር አብረው እየሰሩ መሆናቸውን የነገሩን አቶ ሙኒብ፤ በሚቀጥለው ወር 10 ሺ መኪናዎችን ወደ ስራ ለማስገባት ማቀዳቸውንም ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም “ሊፍት ተማሪ” የተባለ ለየት ያለ የተማሪዎች የወር ጥቅል የተዘጋጀም ሲሆን፤ተማሪዎች በጋራም ሆነ በግል በተመጣጣኝ ዋጋ የትራንስፖርት አገልግሎቱን እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡አገልግሎት ፈላጎዎች “የሊፍት ኢትዮጵያን” መተግበሪያ ከጎግል በማውረድ አልያም በ9885 በነጻ የስልክ መስመር በመደወል መጠቀም ይችላሉ ተብሏል፡፡
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
መንግስት የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ተናገሩ።
የገንዘብ ሚኒስቴር ከልማት አጋር ሀገሮች አምባሳደሮችና የልማት ድርጅቶች የስራ ኃላፊዎች ጋር በሀገሪቱ የዘጠኝ ወር የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ላይ ዛሬ ውይይት አድርጓል።
ለውይይቱ መነሻ የዘጠኝ ወር የማክሮ ኢኮኖሚውን አፈፃፀም ሪፖርት የፕላንና ልማት ሚንስትሯ ዶ/ር ፍፁም አሰፋ ሲያቀርቡ እንዳሉት፣ ባላፉት ዘጠኝ ወራት ኢኮኖሚው በየዘርፉ ዕድገት በማስመዝገብ ላይ መሆኑን ጠቅሰው በተለይ በውጭ ቀጥተኛ የመዋዕለ ንዋይ ፍሰት፣ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውን ወደ ሀገር ውስጥ በሚልኩት ዶላር ረገድ ጥሩ ዕድገት አለ ብለዋል።
በአጠቃላይ በ9 ወር ውስጥ ኢኮኖሚው 6 ነጥብ 6 በመቶ አድጓል ያሉት ዶ/ር ፍፁም፤ በዚህ ጊዜ ውስጥ ለ 1 ነጥብ 4 ሚለዮን ዜጎች የስራ ዕድል እንደተፈጠረ፣ የመንግስት ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ7 ነጥብ 7 በመቶ ዕድገት እንደሳየ፤ እንዲሁም ባንኮች 1 ነጥብ 6 ትሪሊየን ብር ቁጠባ መሰብሰብ እንደቻሉ፣ በአጠቃላይ ከተሰራጨው ብድር ውስጥም 70 በመቶው ለግሉ ዘርፍ አገልግሎት ላይ እንደዋለ ተናግረዋል።
ውይይቱን የመሩት የገንዘብ ሚንስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እንዳሉት፣ ኢኮኖሚው በወጪ ንግድ፣ በውጭ ቀጥተኛ መዋዕለ ንዋይ ፍሰትና በሌሎችም መመዘኛዎች ጥሩ ደረጃ ላይ እንዳለ ተናግረው ነገር ግን ኢኮኖሚው በሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት፣ ድርቅ፣ ኮቪድ 19 እና በሩስያ ዩክሬን ግጭት ምክንያት እየተፈተነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
መንግስት ኢኮኖሚው የገጠመውን ወቅታዊ ችግር ለመፍታት ቅድሚያ ትኩረት የሚሹ እንደ ድርቅ ፣ በጦርነቱ የደረሱ ጉዳቶችን ለማገገም፣ እንዲሁም መሰረታዊ የመገልገያ ሸቀጦችና መሰል ጉዳዮችን በመለየት እየሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል።
በቀጣይም መንግስት የሀገሪቱን ዜጎች በልማት ተጠቃሚ ለማድረግ የሚደርገው ጥረት ከልማት አጋሮች አላማ ጋር ተመሳሳይ በመሆኑ ግንኙነታችንን ይበልጥ በማጠናከር ልንሰራ ይገባል ሲሉ አቶ አህመድ ሽዴ መናገራቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
የገንዘብ ሚኒስቴር ከልማት አጋር ሀገሮች አምባሳደሮችና የልማት ድርጅቶች የስራ ኃላፊዎች ጋር በሀገሪቱ የዘጠኝ ወር የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ላይ ዛሬ ውይይት አድርጓል።
ለውይይቱ መነሻ የዘጠኝ ወር የማክሮ ኢኮኖሚውን አፈፃፀም ሪፖርት የፕላንና ልማት ሚንስትሯ ዶ/ር ፍፁም አሰፋ ሲያቀርቡ እንዳሉት፣ ባላፉት ዘጠኝ ወራት ኢኮኖሚው በየዘርፉ ዕድገት በማስመዝገብ ላይ መሆኑን ጠቅሰው በተለይ በውጭ ቀጥተኛ የመዋዕለ ንዋይ ፍሰት፣ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውን ወደ ሀገር ውስጥ በሚልኩት ዶላር ረገድ ጥሩ ዕድገት አለ ብለዋል።
በአጠቃላይ በ9 ወር ውስጥ ኢኮኖሚው 6 ነጥብ 6 በመቶ አድጓል ያሉት ዶ/ር ፍፁም፤ በዚህ ጊዜ ውስጥ ለ 1 ነጥብ 4 ሚለዮን ዜጎች የስራ ዕድል እንደተፈጠረ፣ የመንግስት ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ7 ነጥብ 7 በመቶ ዕድገት እንደሳየ፤ እንዲሁም ባንኮች 1 ነጥብ 6 ትሪሊየን ብር ቁጠባ መሰብሰብ እንደቻሉ፣ በአጠቃላይ ከተሰራጨው ብድር ውስጥም 70 በመቶው ለግሉ ዘርፍ አገልግሎት ላይ እንደዋለ ተናግረዋል።
ውይይቱን የመሩት የገንዘብ ሚንስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እንዳሉት፣ ኢኮኖሚው በወጪ ንግድ፣ በውጭ ቀጥተኛ መዋዕለ ንዋይ ፍሰትና በሌሎችም መመዘኛዎች ጥሩ ደረጃ ላይ እንዳለ ተናግረው ነገር ግን ኢኮኖሚው በሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት፣ ድርቅ፣ ኮቪድ 19 እና በሩስያ ዩክሬን ግጭት ምክንያት እየተፈተነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
መንግስት ኢኮኖሚው የገጠመውን ወቅታዊ ችግር ለመፍታት ቅድሚያ ትኩረት የሚሹ እንደ ድርቅ ፣ በጦርነቱ የደረሱ ጉዳቶችን ለማገገም፣ እንዲሁም መሰረታዊ የመገልገያ ሸቀጦችና መሰል ጉዳዮችን በመለየት እየሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል።
በቀጣይም መንግስት የሀገሪቱን ዜጎች በልማት ተጠቃሚ ለማድረግ የሚደርገው ጥረት ከልማት አጋሮች አላማ ጋር ተመሳሳይ በመሆኑ ግንኙነታችንን ይበልጥ በማጠናከር ልንሰራ ይገባል ሲሉ አቶ አህመድ ሽዴ መናገራቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
ህወሓት ከአራት ሺ በላይ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ምርኮኞች ናቸው ያላቸውን እለቃለሁ ሲል መንግስት ደግሞ ከሰሞኑ መግለጫ እሰጥበታሉ አለ፡፡
በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ሽብርተና ተብሎ የተፈረጀው ህወሓት ራሱን የትግራይ ክልል መንግስት ብሎ የሚጠራው ድርጅት ከፍተኛ አመራር ለአሜሪካ ድምፅ ግንቦት 11 ቀን 2014 ዓ.ም እንደተናገሩት የጦር ምርኮኞች ናቸው ያሏቸውን ለመልቀቅ ወስኗል፡፡
አሻም ይህን ለማጣራት የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገለግሎት ሚኒስቴርን ለማነጋገር የሞከረች ቢሆንም ሚኒስትር ዲኤታዋ ሰላማዊት ካሳ ከሰሞኑ መግለጫ ይሰጥበታል ከማለት ውጪ የተብራራ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡
ከጥቁት ሳምንታት ወዲህ የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ዳግም ሊቀስቀስ ይችላል የሚል ስጋት በብዙዎች በሚነገርበት ወቅት ከህወሓት በኩል ይህ ወሳኔ መሰማቱ ያልተጠበቀ መሆኑ እየተነገረ ነው፡፡ታህሳስ 29 ቀን 2014 ዓ.ም የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች እንደሆኑ የሚነገርላቸው አቶ ስበሃት ነጋን ጨምሮ ሌሎች ”ተጠርጣሪዎች ክስ በማቋረጥ” ከእስር መለቀቃቸው ይታወሳል፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ሽብርተና ተብሎ የተፈረጀው ህወሓት ራሱን የትግራይ ክልል መንግስት ብሎ የሚጠራው ድርጅት ከፍተኛ አመራር ለአሜሪካ ድምፅ ግንቦት 11 ቀን 2014 ዓ.ም እንደተናገሩት የጦር ምርኮኞች ናቸው ያሏቸውን ለመልቀቅ ወስኗል፡፡
አሻም ይህን ለማጣራት የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገለግሎት ሚኒስቴርን ለማነጋገር የሞከረች ቢሆንም ሚኒስትር ዲኤታዋ ሰላማዊት ካሳ ከሰሞኑ መግለጫ ይሰጥበታል ከማለት ውጪ የተብራራ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡
ከጥቁት ሳምንታት ወዲህ የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ዳግም ሊቀስቀስ ይችላል የሚል ስጋት በብዙዎች በሚነገርበት ወቅት ከህወሓት በኩል ይህ ወሳኔ መሰማቱ ያልተጠበቀ መሆኑ እየተነገረ ነው፡፡ታህሳስ 29 ቀን 2014 ዓ.ም የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች እንደሆኑ የሚነገርላቸው አቶ ስበሃት ነጋን ጨምሮ ሌሎች ”ተጠርጣሪዎች ክስ በማቋረጥ” ከእስር መለቀቃቸው ይታወሳል፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
ለቤትዎ ለቢሮዎ እንዲሁም ለድርጅትዎ ይተለያየ ውበት ያላቸውን የፍይበር ግላስ የአበባ መትከያ ከፈለጉ እኛ አለን የድርጅትዎን እርማም መትከያው ላይ እናትምሎታለን
👋👋እንዲሁም ይሄን አዋጭ ቢዝነስ
ለመጀመር ካሰቡ ሙሉ ስልጠና እንሰጣለን ይደውሉልን
https://tttttt.me/+xvCuMwxhK19kODg0
☝️☝️☝️Join our group
Phone number:0987414243
0913676664
👋👋እንዲሁም ይሄን አዋጭ ቢዝነስ
ለመጀመር ካሰቡ ሙሉ ስልጠና እንሰጣለን ይደውሉልን
https://tttttt.me/+xvCuMwxhK19kODg0
☝️☝️☝️Join our group
Phone number:0987414243
0913676664