የዓለም ጤና ድርጅት ኮቪድ የመጣው ከውሃን ቤተ ሙከራ ሳይሆን ከእንስሳት መሆኑን አስታወቀ!
የዓለም ጤና ድርጅት የኮሮና ቫይረስ መነሻ ከውሃን ቤተ ሙከራ ሳይሆን ከእንስሳት መሆኑን በጥናቱ አረጋገጠ፡፡የድርጅቱ ልዑክ ቻይና በመገኘት የኮሮና ቫይረስን መነሻ ሲያጠና መቆየቱ ይታወቃል፡፡የልዑክ ቡድኑ መሪ ፒተር ቤን ኢምባረክ መነሻውን ለማወቅ ተጨማሪ ስራዎች መሰራት እንዳለባቸውም ገልጸዋል፡፡ጥናቱን የድርጅቱ ልዑክ እና ቻይና የጤና ኮሚሽን በጋራ ማጥናታቸው ነው የተነገረው፡፡ውሃን በቻይና ምዕራባዊ ሁቤ አውራጃ የምትገኘ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ኮሮና ቫይረስ የተገኘባት ከተማ መሆኗ ይታወሳል፡፡ባለሙያዎች ወረርሽኙ ወደ ሰዎች ከመሰራጨቱ በፊት ከእንስሳ እንደመጣ ቢያምኑም እንዴት ሊከሰት እንደቻለ እርግጠኞች አይደሉም ተብሏል፡፡
(ኤፍ ቢ ሲ)
@YeneTube @FikerAssefa
የዓለም ጤና ድርጅት የኮሮና ቫይረስ መነሻ ከውሃን ቤተ ሙከራ ሳይሆን ከእንስሳት መሆኑን በጥናቱ አረጋገጠ፡፡የድርጅቱ ልዑክ ቻይና በመገኘት የኮሮና ቫይረስን መነሻ ሲያጠና መቆየቱ ይታወቃል፡፡የልዑክ ቡድኑ መሪ ፒተር ቤን ኢምባረክ መነሻውን ለማወቅ ተጨማሪ ስራዎች መሰራት እንዳለባቸውም ገልጸዋል፡፡ጥናቱን የድርጅቱ ልዑክ እና ቻይና የጤና ኮሚሽን በጋራ ማጥናታቸው ነው የተነገረው፡፡ውሃን በቻይና ምዕራባዊ ሁቤ አውራጃ የምትገኘ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ኮሮና ቫይረስ የተገኘባት ከተማ መሆኗ ይታወሳል፡፡ባለሙያዎች ወረርሽኙ ወደ ሰዎች ከመሰራጨቱ በፊት ከእንስሳ እንደመጣ ቢያምኑም እንዴት ሊከሰት እንደቻለ እርግጠኞች አይደሉም ተብሏል፡፡
(ኤፍ ቢ ሲ)
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ ወደ ሰሜንና ሰሜን ምዕራብ አንዳንድ ከተሞች ተቋርጦ የነበረው የአየር በረራ ተጀመረ!
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተፈጥሮ ሰሞኑን ተፈጥሮ ነበር ባለው አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ ምክንያት ተቋርጦ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል በሚገኙ አብዛኞቹ ከተሞች የአየር በረራ ማቋረጡን አስታውቆ ነበር።ነገር ግን ዛሬ እንደተሰማው ከአዲስ አበባ ባህርዳር፣ ጎንደር እና ላሊበላ የአየር በረራ ትናንት መጀመሩን አየር መንገዱና ተሳፋሪዎች ገልፀዋል፡፡
አንድ የአየር መንገዱ ባልደረባ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት ሰሞኑን ተፈጥሮ በነበረው ጭጋጋማ የአየር ሁኔታ ምክንያት ከአርብ ከሰኣት ጀምሮ ከአዲስ አበባ ባህር ዳር፣ ጎንደርና ላሊበላ ይደረጉ የነበሩ በረራዎች ተቋርጠው ቆይተዋል፡፡ይሁን እንጂ የአየር ሁኔታው የተሰተካከለ በመሆኑ እሁድ ወደ ላሊበላ በረራ መጀመሩን፣ ባህርዳርና ጎንደር ደግሞ ትናንት ሰኞ የበረራ አገልግሎት መቀጠሉን ገልፀዋል፡፡አንድ ከአዲስ አበባ ወደ ባህር ዳር ለመምጣት ሲጠባበቁ የነበሩ የአየር መንገዱ ደንበኛ ትናንት በረራ መጀመሩ ከአየር መንገዱ ተነግሯቸው በነበረው የበረራ መስተጓጎል በተፈጠረ ወረፋ በረራቸው ተዛውሮ ዛሬ ባሕር ዳር መግባታቸውን ለዶይቼ ቬለ በስልክ ተናግረዋል፡፡
የዶይቼ ቬለ ዘጋቢ እንዳረጋገጠውም ከትናንትና ጀምሮ በባህር ዳር አውሮፕላን ማረፊያ አውሮፕላኖች እየተነሱ ሲያርፉ ነበር፡፡ሆኖም ያለው የአየር ሁኔታ ሞቃታማነቱን እየጨመረ ስለሚሄድ በቅርቡ ተመሳሳይ የአየር ሁኔታ ለውጥ ሊኖር እንደሚችል በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ አጀንሲ የባህር ዳር ቅርንጫፍ የትንበያና ትንተና ቡድን አስተባባሪ አቶ ጥላሁን ውቤ የትንበያ ሪፖርቶችን ጠቅሰው ተናግረዋል፡፡
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተፈጥሮ ሰሞኑን ተፈጥሮ ነበር ባለው አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ ምክንያት ተቋርጦ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል በሚገኙ አብዛኞቹ ከተሞች የአየር በረራ ማቋረጡን አስታውቆ ነበር።ነገር ግን ዛሬ እንደተሰማው ከአዲስ አበባ ባህርዳር፣ ጎንደር እና ላሊበላ የአየር በረራ ትናንት መጀመሩን አየር መንገዱና ተሳፋሪዎች ገልፀዋል፡፡
አንድ የአየር መንገዱ ባልደረባ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት ሰሞኑን ተፈጥሮ በነበረው ጭጋጋማ የአየር ሁኔታ ምክንያት ከአርብ ከሰኣት ጀምሮ ከአዲስ አበባ ባህር ዳር፣ ጎንደርና ላሊበላ ይደረጉ የነበሩ በረራዎች ተቋርጠው ቆይተዋል፡፡ይሁን እንጂ የአየር ሁኔታው የተሰተካከለ በመሆኑ እሁድ ወደ ላሊበላ በረራ መጀመሩን፣ ባህርዳርና ጎንደር ደግሞ ትናንት ሰኞ የበረራ አገልግሎት መቀጠሉን ገልፀዋል፡፡አንድ ከአዲስ አበባ ወደ ባህር ዳር ለመምጣት ሲጠባበቁ የነበሩ የአየር መንገዱ ደንበኛ ትናንት በረራ መጀመሩ ከአየር መንገዱ ተነግሯቸው በነበረው የበረራ መስተጓጎል በተፈጠረ ወረፋ በረራቸው ተዛውሮ ዛሬ ባሕር ዳር መግባታቸውን ለዶይቼ ቬለ በስልክ ተናግረዋል፡፡
የዶይቼ ቬለ ዘጋቢ እንዳረጋገጠውም ከትናንትና ጀምሮ በባህር ዳር አውሮፕላን ማረፊያ አውሮፕላኖች እየተነሱ ሲያርፉ ነበር፡፡ሆኖም ያለው የአየር ሁኔታ ሞቃታማነቱን እየጨመረ ስለሚሄድ በቅርቡ ተመሳሳይ የአየር ሁኔታ ለውጥ ሊኖር እንደሚችል በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ አጀንሲ የባህር ዳር ቅርንጫፍ የትንበያና ትንተና ቡድን አስተባባሪ አቶ ጥላሁን ውቤ የትንበያ ሪፖርቶችን ጠቅሰው ተናግረዋል፡፡
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ቡሩንዲ ገቡ!
የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ዛሬ ቡሩንዲ መግባታቸው ተገልጿል፡፡ ፕሬዝዳንቷ ቡጁምቡራ እንደደረሱ በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩት የቀድሞው የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ፒዬሬ ንኩሩንዚዛ የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት የቀድሞው የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ንኩሩንዚዛ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ አዲስ አበባ በሚገኘው የቡሩንዲ ኤምባሲ በመገኘትም የአበባ ጉንጉን ማስቀመጣቸው ይታወሳል፡፡
ንኩሩንዚዛ በ55 ዓመታቸው በድንገተኛ የልብ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወሳል፡፡ በፈረንጆቹ 1963 የተወለዱት ንኩሩንዚዛ እ.ኤ.አ ከ2005 ጀምሮ ህይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ድረስ ቡሩንዲን መርተዋል።ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በሁለቱ ሀገረታት እና በቀጣናዊ ጉዳዮች ከቡሩንዲ መሪዎች ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
[Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ዛሬ ቡሩንዲ መግባታቸው ተገልጿል፡፡ ፕሬዝዳንቷ ቡጁምቡራ እንደደረሱ በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩት የቀድሞው የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ፒዬሬ ንኩሩንዚዛ የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት የቀድሞው የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ንኩሩንዚዛ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ አዲስ አበባ በሚገኘው የቡሩንዲ ኤምባሲ በመገኘትም የአበባ ጉንጉን ማስቀመጣቸው ይታወሳል፡፡
ንኩሩንዚዛ በ55 ዓመታቸው በድንገተኛ የልብ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወሳል፡፡ በፈረንጆቹ 1963 የተወለዱት ንኩሩንዚዛ እ.ኤ.አ ከ2005 ጀምሮ ህይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ድረስ ቡሩንዲን መርተዋል።ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በሁለቱ ሀገረታት እና በቀጣናዊ ጉዳዮች ከቡሩንዲ መሪዎች ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
[Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
በትግራይ ክልል ሕፃፅና ሽመልባ በተባሉ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የነበሩ 20,000 የሚጠጉ ኤርትራውያን ስደተኞች፣ መንግሥት ከጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ሲያከናውን በነበረው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ምክንያት ሙሉ ለሙሉ የመጠለያ ጣቢያዎቹን ለቀው እንደወጡ ተገለጿል፡፡
ዘገባው የሪፖርተር ነው ተጨማሪ ለማንበብ: http://bit.ly/3tFIX9B
@YeneTube @FikerAssefa
ዘገባው የሪፖርተር ነው ተጨማሪ ለማንበብ: http://bit.ly/3tFIX9B
@YeneTube @FikerAssefa
ጀርመን ኢትዮጵያዉያን ስደተኞችን ወደ ሃገራቸዉ መጠረዝዋን ቀጥላለች። በጀርመን ተቃዋሚ ፖለቲከኞች እና የሰብዓዊ ጉዳይ አቀንቃኞች ይህን የጀርመን መንግሥትን ርምጃ እያወገዙ ነዉ። የኮሮና ተኅዋሲ ስርጭት እጅግ ባየለበት እና ኢትዮጵያ ዉስጥ በትግራይ እና በተለያዩ ክልሎች የተለያዩ ተግዳሮት ባለበት በአሁኑ ወቅት በጀርመን የጥገኝነት ጥያቄ ያቀረቡ ኢትዮጵያዉያን ወደ ሃገራቸዉ እንዲመለሱ መደረጉ ስህተት ነዉ ሲሉ የሰብዓዊ ጉዳይ አቀንቃኞች ተናግረዋል።በጎርጎረሳዉያኑ 2020 ዓመት ብቻ ከጀርመን 20 ኢትዮጵያዉያን ወደ ሃገራቸዉ እንዲመለሱ ተደርጎአል።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተገነባው በሀገራችን የመጀመሪያው ትልቁና ዘመናዊ የእናቶችና ህፃናት ሆስፒታል ተጠናቀቀ ።
በ20,000 ካሬ ላይ ያረፈው ፣ 400 በላይ ተኝቶ መታከሚያ አልጋዎች ያሉት፣100 የልህቀት ማዕከል አገልግሎት መስጫ ክፍሎች፣በተመሳሳይ ሰአት ለ7 እናቶች የኦፕራሲዮን አገልግሎት መስጠት የሚያስችለው ዘመናዊና ወረቀት አልባ መስተንግዶ የሚሰጠው ይህ ሆስፒታል ዘመናዊ የህክምና ቁሳቁሶች ተሟልተውለታል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጤናው ዘርፍ በተለይ በወሊድ እና ተያያዥ ጉዳዮች በእናቶች እና ህጻናት የሚደርሰውን የሞት ምጣኔ ለመቀነስ በአይነቱ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነና ደረጃውን የጠበቀ የእናቶች እና ህጻናት ሆስፒታል ግንባታ ያጠናቀቀ ሲሆን በክብርት ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የካቲት 4 ቀን 2013 ዓ.ም ተመርቆ ስራ የሚጀምር ይሆናል።
ግንባታው ቀድሞ ለመለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ ተብሎ የተጀመረ ሲሆን የከተማ አስተዳደሩም ካቢኔ በከተማችን ትልቅ የአገልግሎት ችግር ያለበትን የእናቶችና ህጻናት ጤና ቅድሚያ በመስጠት ሰባት መቶ ሚሊየን ብር በመመደብ ተጨማሪ ግንባታ በማድረግ እና ነባሩን ግንባታ በማሻሻል ወደ ሆስፒታልነት እንዲቀየር አድርጓል።
[Addis Ababa city PS]
@YeneTube @FikerAssefa
በ20,000 ካሬ ላይ ያረፈው ፣ 400 በላይ ተኝቶ መታከሚያ አልጋዎች ያሉት፣100 የልህቀት ማዕከል አገልግሎት መስጫ ክፍሎች፣በተመሳሳይ ሰአት ለ7 እናቶች የኦፕራሲዮን አገልግሎት መስጠት የሚያስችለው ዘመናዊና ወረቀት አልባ መስተንግዶ የሚሰጠው ይህ ሆስፒታል ዘመናዊ የህክምና ቁሳቁሶች ተሟልተውለታል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጤናው ዘርፍ በተለይ በወሊድ እና ተያያዥ ጉዳዮች በእናቶች እና ህጻናት የሚደርሰውን የሞት ምጣኔ ለመቀነስ በአይነቱ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነና ደረጃውን የጠበቀ የእናቶች እና ህጻናት ሆስፒታል ግንባታ ያጠናቀቀ ሲሆን በክብርት ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የካቲት 4 ቀን 2013 ዓ.ም ተመርቆ ስራ የሚጀምር ይሆናል።
ግንባታው ቀድሞ ለመለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ ተብሎ የተጀመረ ሲሆን የከተማ አስተዳደሩም ካቢኔ በከተማችን ትልቅ የአገልግሎት ችግር ያለበትን የእናቶችና ህጻናት ጤና ቅድሚያ በመስጠት ሰባት መቶ ሚሊየን ብር በመመደብ ተጨማሪ ግንባታ በማድረግ እና ነባሩን ግንባታ በማሻሻል ወደ ሆስፒታልነት እንዲቀየር አድርጓል።
[Addis Ababa city PS]
@YeneTube @FikerAssefa
ግብፅ በኤርትራ የባህር ግዛት ላይ ፈቃድ ሳይኖራቸው በመገኘታቸው የተያዙት ግብፃውያን ዓሳ አጥማጆች እንደሆኑ በመጥቀስ ዜጎቿ እንዲለቀቁ የኤርትራን መንግሥት ጠየቀች።
በአምስት ጀልባዎች በመሆን በኤርትራ የባህር ክልል ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የተገኙትን ግብፃዊያን የኤርትራ የባህር ኃይል በቁጥጥር ሥር ያዋለው ባለፈው ወር መሆኑን መረጃዎች የሚያመለክቱ ሲሆን፣ ‹‹ዓሳ አጥማጆች ናቸው›› የተባሉትን ግብፃዊያን ለማስለቀቅም የግብፅ መንግሥት ኦፊሳላዊ ጥያቄ ለኤርትራ መንግሥት ማቅረቡ ተሰምቷል።
[Reporter]
@YeneTube @FikerAssefa
በአምስት ጀልባዎች በመሆን በኤርትራ የባህር ክልል ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የተገኙትን ግብፃዊያን የኤርትራ የባህር ኃይል በቁጥጥር ሥር ያዋለው ባለፈው ወር መሆኑን መረጃዎች የሚያመለክቱ ሲሆን፣ ‹‹ዓሳ አጥማጆች ናቸው›› የተባሉትን ግብፃዊያን ለማስለቀቅም የግብፅ መንግሥት ኦፊሳላዊ ጥያቄ ለኤርትራ መንግሥት ማቅረቡ ተሰምቷል።
[Reporter]
@YeneTube @FikerAssefa
ጉዳፍ ፀጋይ በሌቪን ፈረንሳይ በተካሄደ የ1500 ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር አዲስ የአለም ክብረወሰን አስመዘገበች።
አትሌቷ በፈረንጆቹ 2014 አትሌት ገንዘቤ ዲባባ በካርልስሩህ ያስመዘገበችውን ክብረወሰን በ2 ሰከንድ በማሻሻል ርቀቱን በ3:53.09 ማጠናቀቅ ችላለች።
አትሌት ለምለም ሀይሉም በዚሁ የፈረንሳይ የቤት ውስጥ ሻንፒዮና ውድድር በ3000 ሜትር 8:32,55 በመሮጥ ስታሸንፍ፣ አትሌት ሀብታም አለሙ በ800 ሜትር 2:00;86 በመሮጥ 2ኛ ሆናለች።
በዚሁ የቤት ውስጥ ውድድር በ3,000 ሜትር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1-4ኛ መውጣት ችለዋል፡፡
በዚሁ መሰረት አትሌት ጌትነት ዋለ 1ኛ፣ ሰለሞን ባረጋ 2ኛ፣ ለሜቻ ግርማ 3ኛ ፣ በሪሁ አረጋዊ 4ኛ፣ ታደሰ ወርቁ 6ኛ በመሆን ጨርሰዋል፡፡
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
አትሌቷ በፈረንጆቹ 2014 አትሌት ገንዘቤ ዲባባ በካርልስሩህ ያስመዘገበችውን ክብረወሰን በ2 ሰከንድ በማሻሻል ርቀቱን በ3:53.09 ማጠናቀቅ ችላለች።
አትሌት ለምለም ሀይሉም በዚሁ የፈረንሳይ የቤት ውስጥ ሻንፒዮና ውድድር በ3000 ሜትር 8:32,55 በመሮጥ ስታሸንፍ፣ አትሌት ሀብታም አለሙ በ800 ሜትር 2:00;86 በመሮጥ 2ኛ ሆናለች።
በዚሁ የቤት ውስጥ ውድድር በ3,000 ሜትር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1-4ኛ መውጣት ችለዋል፡፡
በዚሁ መሰረት አትሌት ጌትነት ዋለ 1ኛ፣ ሰለሞን ባረጋ 2ኛ፣ ለሜቻ ግርማ 3ኛ ፣ በሪሁ አረጋዊ 4ኛ፣ ታደሰ ወርቁ 6ኛ በመሆን ጨርሰዋል፡፡
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ለ6ኛው አገር አቀፍ ምርጫ የሚያስፈልጉ የመራጮች እና እጩ ምዝገባ ቅፆች እና ቁሳቁሳችን ከዛሬ ጀምሮ ማጓጓዝ እንደሚጀምር ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።
ለቀጣዩ ሃገራዊ ምርጫ የሚደረጉ ዝግጅቶች በአብዛኛው መጠናቀቃቸውንም ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ውብሸት አየለ በመግለጫው እንደገለፁት፣ በሀገራችን የትግራይ ክልልን ሳይጨምር 673 የምርጫ ክልሎች መቋቋማቸውን ገልዋል።በአዲስ አበባ እንዲሁም በዞን ከተማዎችና ወረዳዎችን ጨምሮ የምርጫ ቢሮዎችና ፅህፈት ቤቶች በመከፈት ላይ እንደሚገኙም አውስተዋል።
ለምርጫ አስፈጻሚዎችም ስልጠና ተሰቷል፣ ቁሳቁሶችም ተሟልተዋል ብለዋል።ለእጩዎችና ለመራጮች ምዝገባ የሚያገለግሉ ቅፆችና ቁሳቁሶች የተዘጋጁ መሆናቸውን የገለጹት ምክትል ሰብሳቢው፣ ቅፆቹና ቁሳቁሶቹ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ተዘጋጁት የምርጫ ክልሎች የማሰራጨትና የማጓጓዝ ስራው ይጀመራል ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ለቀጣዩ ሃገራዊ ምርጫ የሚደረጉ ዝግጅቶች በአብዛኛው መጠናቀቃቸውንም ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ውብሸት አየለ በመግለጫው እንደገለፁት፣ በሀገራችን የትግራይ ክልልን ሳይጨምር 673 የምርጫ ክልሎች መቋቋማቸውን ገልዋል።በአዲስ አበባ እንዲሁም በዞን ከተማዎችና ወረዳዎችን ጨምሮ የምርጫ ቢሮዎችና ፅህፈት ቤቶች በመከፈት ላይ እንደሚገኙም አውስተዋል።
ለምርጫ አስፈጻሚዎችም ስልጠና ተሰቷል፣ ቁሳቁሶችም ተሟልተዋል ብለዋል።ለእጩዎችና ለመራጮች ምዝገባ የሚያገለግሉ ቅፆችና ቁሳቁሶች የተዘጋጁ መሆናቸውን የገለጹት ምክትል ሰብሳቢው፣ ቅፆቹና ቁሳቁሶቹ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ተዘጋጁት የምርጫ ክልሎች የማሰራጨትና የማጓጓዝ ስራው ይጀመራል ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
በመቀለ ከተማ በነበረ ተቃውሞ የአንድ ሰው ህይወት አለፈ!
በመቀለ ከተማ በነበረው ተቃውሞ አንድ ግለሰብ በተተኮሰበት ጥይት ህይወቱ ማለፉን አጃንስን ፍራንስ ፕሬስ የህክምና ምንጮች ጠቅሶ ዘግቧል።በትላንትናው እለት በመቀሌ ከተማ በርካታ የንግድ ተቋማት ዝግ በማድረግ ነዋሪዎች ቁጣቸውን ገልፀዋል። መንግስት በትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ ሰላማዊ በማስመሰል ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማጋራት እየጣረ ነው ይህ ግን የሀሰት ነው ሲል ነዋሪዎች አነጋግሬአለው ያለው ዘገባው አመላክቷል።
መንግስት ተገዶ በገባበት በዚህ ግጭት በወርሃ ጥቅምት ማብቂያ የህወሃት ቡድን በሰሜን እዝ ላይ ጥቃት መሰንዘሩ አይዘነጋም።ከትግራይ ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የሚቀርቡ ወቀሳዎች በመረጃ ያልተደገፉ ናቸው ሲሉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ አቶ ለማ ተሰማ መናገራቸው ይታወሳል።
✍ዳጉ ጆርናል
@YeneTube @FikerAssefa
በመቀለ ከተማ በነበረው ተቃውሞ አንድ ግለሰብ በተተኮሰበት ጥይት ህይወቱ ማለፉን አጃንስን ፍራንስ ፕሬስ የህክምና ምንጮች ጠቅሶ ዘግቧል።በትላንትናው እለት በመቀሌ ከተማ በርካታ የንግድ ተቋማት ዝግ በማድረግ ነዋሪዎች ቁጣቸውን ገልፀዋል። መንግስት በትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ ሰላማዊ በማስመሰል ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማጋራት እየጣረ ነው ይህ ግን የሀሰት ነው ሲል ነዋሪዎች አነጋግሬአለው ያለው ዘገባው አመላክቷል።
መንግስት ተገዶ በገባበት በዚህ ግጭት በወርሃ ጥቅምት ማብቂያ የህወሃት ቡድን በሰሜን እዝ ላይ ጥቃት መሰንዘሩ አይዘነጋም።ከትግራይ ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የሚቀርቡ ወቀሳዎች በመረጃ ያልተደገፉ ናቸው ሲሉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ አቶ ለማ ተሰማ መናገራቸው ይታወሳል።
✍ዳጉ ጆርናል
@YeneTube @FikerAssefa
በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ለአቶ ጃዋር መሀመድ አራት የሞባይል ሲም ካርድ ሊያቀብል ሲል በቁጥጥር ስር ውሏል የተባለው ግለሰብ ዋስትና ተፈቀደለት፡፡
ተጠርጣሪ ሀምዛ ጀማል አንድ በOMN ድርጅት ስም እና 3 በግለሰብ ስም የወጡ ሲም ካርዶችን ለአቶ ጃዋር መሀመድ ሊያቀብል ሲል በማረሚያ ቤቱ የጥበቃ አባላት በቁጥጥር ስር ውሏል ተብሎ ከአንድ ወር በላይ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራ ሲደረግበትና ለአራት ጊዜ ፍርድ ቤት ሲቀርብ ቆይቷል።
በምርመራው መርማሪ ፖሊስ ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ምስክር ቃል መቀበሉን ከኢትዮ ቴሌኮም ሲም ካርዱ በማን ሰም ስለመውጣቱ ማስረጃ መሰብሰቡን ገልጾ ነበር፡፡
ምርመራ መዝገቡን አቃቤ ህግ እየተመለከተው መሆኑን እንዲሁም ተጨማሪ ምስክር ለመቀበል ተጨማሪ የምርመራ ቀናትን ጠይቆ የነበረ ሲሆን የተጠርጣሪ ጠበቃ በቂ ጊዜ ተሰጥቷል ተጨማሪ ጊዜ መጠየቁ አግባብ አደለም ሲል ተቃውሞ ተከራክሮ ነበር፡፡
የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት መርማሪ ያቀረበው የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ ተጨማሪ ጊዜ ለመስጠት አሳማኝ ምክንያት አይደለም ሲል አልተቀበለውም፡፡
እስካሁን የተከናወኑ የምርመራ ቀናት በቂ ናቸው ሲል ተጠርጣሪው የ30 ሺህ ብር ዋስ አስይዞ ከእስር እንዲፈታ ዋስትና ፈቅዷል፡፡
ምንጭ፦ ኤፍ ቢ ሲ
@YeneTube @FikerAssefa
ተጠርጣሪ ሀምዛ ጀማል አንድ በOMN ድርጅት ስም እና 3 በግለሰብ ስም የወጡ ሲም ካርዶችን ለአቶ ጃዋር መሀመድ ሊያቀብል ሲል በማረሚያ ቤቱ የጥበቃ አባላት በቁጥጥር ስር ውሏል ተብሎ ከአንድ ወር በላይ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራ ሲደረግበትና ለአራት ጊዜ ፍርድ ቤት ሲቀርብ ቆይቷል።
በምርመራው መርማሪ ፖሊስ ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ምስክር ቃል መቀበሉን ከኢትዮ ቴሌኮም ሲም ካርዱ በማን ሰም ስለመውጣቱ ማስረጃ መሰብሰቡን ገልጾ ነበር፡፡
ምርመራ መዝገቡን አቃቤ ህግ እየተመለከተው መሆኑን እንዲሁም ተጨማሪ ምስክር ለመቀበል ተጨማሪ የምርመራ ቀናትን ጠይቆ የነበረ ሲሆን የተጠርጣሪ ጠበቃ በቂ ጊዜ ተሰጥቷል ተጨማሪ ጊዜ መጠየቁ አግባብ አደለም ሲል ተቃውሞ ተከራክሮ ነበር፡፡
የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት መርማሪ ያቀረበው የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ ተጨማሪ ጊዜ ለመስጠት አሳማኝ ምክንያት አይደለም ሲል አልተቀበለውም፡፡
እስካሁን የተከናወኑ የምርመራ ቀናት በቂ ናቸው ሲል ተጠርጣሪው የ30 ሺህ ብር ዋስ አስይዞ ከእስር እንዲፈታ ዋስትና ፈቅዷል፡፡
ምንጭ፦ ኤፍ ቢ ሲ
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ክልል እርዳታ ለመስጠት የሚያስችለውን አንድ እርምጃ ወደፊት ተራምዷል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጀት አደነቀ፡፡
ላለፉት ተከታታይ ሳምንታት የድርጅቱ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ፊሊፖ ግራንዲን ጨምሮ የተለያዩ አካላት በትግራይ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረግ አስቻይ መንገዶች አልተመቻቹም፤ የእርዳታ ሰጪ ተቋማትና ሰራተኞቻቸው ወደስፍራው እንዳያቀኑ ተከልከለዋል በሚል መንግስትን ሲወቅሱ ሰንበተዋል፡፡ምንም እንኳን መንግስት ወቀሳውን ውድቅ እንዳደረገው ቢቀጥልም የመንግስታቱ ድርጅት ግን ለመጀመሪያ ጊዜ 25 የበጎ አድራጊ ሰራተኞችን ያቀፈ ቡድን ድጋፍ እንዲያደርግ የኢትዮጵያ መንግስት የይለፍ አረንጓዴ መብራት እንዳሳየ አስታውቋል፡፡
[አሐዱ ራዲዮ 94.3]
@YeneTube @FikerAssefa
ላለፉት ተከታታይ ሳምንታት የድርጅቱ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ፊሊፖ ግራንዲን ጨምሮ የተለያዩ አካላት በትግራይ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረግ አስቻይ መንገዶች አልተመቻቹም፤ የእርዳታ ሰጪ ተቋማትና ሰራተኞቻቸው ወደስፍራው እንዳያቀኑ ተከልከለዋል በሚል መንግስትን ሲወቅሱ ሰንበተዋል፡፡ምንም እንኳን መንግስት ወቀሳውን ውድቅ እንዳደረገው ቢቀጥልም የመንግስታቱ ድርጅት ግን ለመጀመሪያ ጊዜ 25 የበጎ አድራጊ ሰራተኞችን ያቀፈ ቡድን ድጋፍ እንዲያደርግ የኢትዮጵያ መንግስት የይለፍ አረንጓዴ መብራት እንዳሳየ አስታውቋል፡፡
[አሐዱ ራዲዮ 94.3]
@YeneTube @FikerAssefa
ዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተለያዩ አገራት የሚገኙ ዲፕሎማቶች ስለ አገራቸዉ ጥቅም የተሻለ ስራ የሰሩትን እና ያልሰሩትን ሊገመግም ነው፡፡
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከአለም አቀፉ ማህበረሰብ እየገጠማት ያለዉን የተዛባ አመለካከት ለማስረዳት ሁሉም ድፕሎማቶች ስለ አገራቸዉ ብሄራዊ ጥቅም በትኩረት እንዲሰሩም አሳስቧል፡፡
የተወሰኑ ድፕሎማቶች በአለም አቀፍ መገናኛዎች ጭምር በመቅርብ በኢትዮጵያ ስላለዉ ሁኔታ እንዲሁም ስለ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እያስረዱ ቢሆንም አብዛኞቹ ግን ብዙ የቤት ሥራ ይጠብቃቸዋልም ተብሏል፡፡
የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስለ አገራቸዉ ብሄራዊ ጥቅም የተሸለ አፈፃፀም የሰሩና ያልሰሩ ዲፕሎማቶችን በቁጥር ጭምር በመያዝ እንደሚገመግምም ኢትዮ ኤፍ ኤም ከሚኒስቴሩ ያገኘዉ መረጃ ያመለክታል፡፡
ኢትዮጵያን ወክለዉ በተለያዩ አገራት የሚገኙ የዲፕሎማት ማህበረሰቦች ባገኙት አጋጣሚ በአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን እና በማህበራዊ ሚዲያዎችም ጭምር የአለም አቀፉ ማህበረሰብ ስለ ኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ግንዛቤ እንዲኖረዉ በትኩረት እንዲሰሩም ጥሪ ተደርጓል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም በተለያዩ አገራት የሚኖሩ የዲያስፖራ ማህበረሰብ እና ምሁራን የአገሪቱን ብሄራዊ ጥቅም በማስጠበቅ ረገድ ብዙ ስራዎችን ሊሰሩ ይገባል ተብሏል፡፡
በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል በነበረዉ የህግ ማስከበር ሂደት ጋር ተያይዞ የአለም አቀፉ ማህበረሰብ የተዛቡ መረጃዎችን እንደያዘ ያስታወቀዉ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እዉነታዉን ለማስረዳት ሁሉም ዜጋ የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አስተላልፏል፡፡
ከህዳሴ ግድብ እና ከኢትዮ ሱዳን የድንበር ዉዝግብ ጋር ተያይዞም ዲፕሎማቶች፤ ምሁራን፤ ዲስፖራዎች፤ እና የአገር ዉስጥ ሚዲያዎች ጭምር ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ስለ አገራቸዉ ተጨባጭ ሁኔታ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ማስረዳት አለባቸዉ ተብሏል፡፡
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከአለም አቀፉ ማህበረሰብ እየገጠማት ያለዉን የተዛባ አመለካከት ለማስረዳት ሁሉም ድፕሎማቶች ስለ አገራቸዉ ብሄራዊ ጥቅም በትኩረት እንዲሰሩም አሳስቧል፡፡
የተወሰኑ ድፕሎማቶች በአለም አቀፍ መገናኛዎች ጭምር በመቅርብ በኢትዮጵያ ስላለዉ ሁኔታ እንዲሁም ስለ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እያስረዱ ቢሆንም አብዛኞቹ ግን ብዙ የቤት ሥራ ይጠብቃቸዋልም ተብሏል፡፡
የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስለ አገራቸዉ ብሄራዊ ጥቅም የተሸለ አፈፃፀም የሰሩና ያልሰሩ ዲፕሎማቶችን በቁጥር ጭምር በመያዝ እንደሚገመግምም ኢትዮ ኤፍ ኤም ከሚኒስቴሩ ያገኘዉ መረጃ ያመለክታል፡፡
ኢትዮጵያን ወክለዉ በተለያዩ አገራት የሚገኙ የዲፕሎማት ማህበረሰቦች ባገኙት አጋጣሚ በአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን እና በማህበራዊ ሚዲያዎችም ጭምር የአለም አቀፉ ማህበረሰብ ስለ ኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ግንዛቤ እንዲኖረዉ በትኩረት እንዲሰሩም ጥሪ ተደርጓል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም በተለያዩ አገራት የሚኖሩ የዲያስፖራ ማህበረሰብ እና ምሁራን የአገሪቱን ብሄራዊ ጥቅም በማስጠበቅ ረገድ ብዙ ስራዎችን ሊሰሩ ይገባል ተብሏል፡፡
በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል በነበረዉ የህግ ማስከበር ሂደት ጋር ተያይዞ የአለም አቀፉ ማህበረሰብ የተዛቡ መረጃዎችን እንደያዘ ያስታወቀዉ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እዉነታዉን ለማስረዳት ሁሉም ዜጋ የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አስተላልፏል፡፡
ከህዳሴ ግድብ እና ከኢትዮ ሱዳን የድንበር ዉዝግብ ጋር ተያይዞም ዲፕሎማቶች፤ ምሁራን፤ ዲስፖራዎች፤ እና የአገር ዉስጥ ሚዲያዎች ጭምር ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ስለ አገራቸዉ ተጨባጭ ሁኔታ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ማስረዳት አለባቸዉ ተብሏል፡፡
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ባለስልጣን በአንድ ሳምንት ዉስጥ የትራንሰፖርት ታሪፍ ማሰተካከያ አጥንቶ እንደሚገልጽ አስታወቀ፡፡
ባለስልጣኑ ህጋዉ የታሪፍ ማስተካከያ አስከሚያሳዉቅም ዋጋ የሚጨምሩ አሽከርካሪዎች ላይ ህጋዊ እርማጃ እወስዳለዉ ብሏል፡፡ባለፉት ሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ የትራንስፖርት እጥረት ተስተዉሏል፡፡እንዳንድ አሽከርካሪዎችም በራሳቸዉ ፍቃድ የነዳጅ ጭማሪ ስላለ በማለትም ዋጋ እየጨመሩም ናቸዉ፡፡የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ባለስልጣን በሁለት ቀናት የተፈጠረዉን የትራንስፖርት እጥረት መስተዋሉንም የባለስልጣኑ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ በድሉ ሌሊሳ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ባለስልጣኑ ህጋዉ የታሪፍ ማስተካከያ አስከሚያሳዉቅም ዋጋ የሚጨምሩ አሽከርካሪዎች ላይ ህጋዊ እርማጃ እወስዳለዉ ብሏል፡፡ባለፉት ሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ የትራንስፖርት እጥረት ተስተዉሏል፡፡እንዳንድ አሽከርካሪዎችም በራሳቸዉ ፍቃድ የነዳጅ ጭማሪ ስላለ በማለትም ዋጋ እየጨመሩም ናቸዉ፡፡የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ባለስልጣን በሁለት ቀናት የተፈጠረዉን የትራንስፖርት እጥረት መስተዋሉንም የባለስልጣኑ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ በድሉ ሌሊሳ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ብልጽግና ፓርቲ በመተከል ዞን ለደረሰው ግድያና ውድመት ይቅርታ ጠየቀ።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ጉባኤ ባለ ዘጠኝ ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል።ጉባኤው በአሶሳ ከተማ በክልሉ ወቅታዊ የፖለቲካና የሠላም ሁኔታ ላይ ለሶስት ቀናት ሲካሄድ ቆይቷል፡፡በዚህም በክልሉ መተከል ዞን በደረሰው አሳዛኝና ዘግናኝ ማንነት ተኮር ግድያና ውድመት ፓርቲው ይቅርታ ጠይቋል፡፡
የግል ፍላጎታቸውን ለማሳካት ‘ብልፅግና አሀዳዊ ነው’ በሚል የሀሰት ትርክት ከሁለት ቦታ በመርገጥ ህዝብን ሲበድሉ የነበሩ አመራሮች መኖራቸውም ተገምግሟል፡፡በቀጣይ የህግ የበላይነትን በማስከበር በወንጀል የተሳተፉ የስራ ኃላፊዎችም ተጠያቂ እንደሚሆኑም ተጠቁሟል።የፓርቲውን እሴትና መርህ በማክበር የዜጎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራም በአቋም መግለጫው ማሳወቁን ከኢዜአ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ጉባኤ ባለ ዘጠኝ ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል።ጉባኤው በአሶሳ ከተማ በክልሉ ወቅታዊ የፖለቲካና የሠላም ሁኔታ ላይ ለሶስት ቀናት ሲካሄድ ቆይቷል፡፡በዚህም በክልሉ መተከል ዞን በደረሰው አሳዛኝና ዘግናኝ ማንነት ተኮር ግድያና ውድመት ፓርቲው ይቅርታ ጠይቋል፡፡
የግል ፍላጎታቸውን ለማሳካት ‘ብልፅግና አሀዳዊ ነው’ በሚል የሀሰት ትርክት ከሁለት ቦታ በመርገጥ ህዝብን ሲበድሉ የነበሩ አመራሮች መኖራቸውም ተገምግሟል፡፡በቀጣይ የህግ የበላይነትን በማስከበር በወንጀል የተሳተፉ የስራ ኃላፊዎችም ተጠያቂ እንደሚሆኑም ተጠቁሟል።የፓርቲውን እሴትና መርህ በማክበር የዜጎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራም በአቋም መግለጫው ማሳወቁን ከኢዜአ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
የአፋር ክልል ህዝብና መንግስት ግምቱ ዘጠኝ ሚሊዮን ብር ግምት ያለው የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ በትግራይ ክልል በመገኘት አስረከበ።
ድጋፉን የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኤለማ አቡበከርን ጨምሮ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች በመቀሌ ተገኝተው ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አስረክበዋል።
የምግብ ቁሳቁሱ ሩዝ፣ የፉርኖ ዱቄት፣ ስኳርና ቴምር ሲሆን አጠቃላይ ብዛቱ 2ሺህ700 ኩንታል መሆኑ ተገልጿል።
የአፋር ክልል ላደረገው ድጋፍ በትግራይ ህዝብ ስም ምስጋና ያቀረቡት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ፤ “የአፋር ህዝብ የትግራይ ህዝብ ወንድም መሆኑን አሳይቷል” ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
አቶ ኤለማ አቡበከር በበኩላቸው ክልላቸው ለትግራይ ያለውን አጋርነት አጠናክሮ እንደሚቀጥል በማረጋገጥ ድጋፉ ቀጣይነት እንደሚኖረው ገልጸዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ድጋፉን የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኤለማ አቡበከርን ጨምሮ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች በመቀሌ ተገኝተው ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አስረክበዋል።
የምግብ ቁሳቁሱ ሩዝ፣ የፉርኖ ዱቄት፣ ስኳርና ቴምር ሲሆን አጠቃላይ ብዛቱ 2ሺህ700 ኩንታል መሆኑ ተገልጿል።
የአፋር ክልል ላደረገው ድጋፍ በትግራይ ህዝብ ስም ምስጋና ያቀረቡት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ፤ “የአፋር ህዝብ የትግራይ ህዝብ ወንድም መሆኑን አሳይቷል” ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
አቶ ኤለማ አቡበከር በበኩላቸው ክልላቸው ለትግራይ ያለውን አጋርነት አጠናክሮ እንደሚቀጥል በማረጋገጥ ድጋፉ ቀጣይነት እንደሚኖረው ገልጸዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አፈ ጉባኤና የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ታደለ ተረፈ ከኃላፊነት ተነሱ!
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ብልፅግና ፓርቲ የክልሉን ዋና አፈ ጉባኤና የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ታደለ ተረፈ ከኃላፊነት አነሳ።ፓርቲው የግል ፍላጎታቸውን ለማሳካት “ብልፅግና አሀዳዊ ነው በሚል የሀሰት ትርክት ሁለት ቦታ በመርገጥ” ህዝብን ሲበድሉ የነበሩ አመራሮች መኖራቸውን ገምግሟል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የብልጽግና ፓርቲ በመተከል ዞን ለተፈጸመው ግድያ እና ሌሎች ጉዳቶች ይቅርታ መጠየቁ ይታወሳል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ብልፅግና ፓርቲ የክልሉን ዋና አፈ ጉባኤና የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ታደለ ተረፈ ከኃላፊነት አነሳ።ፓርቲው የግል ፍላጎታቸውን ለማሳካት “ብልፅግና አሀዳዊ ነው በሚል የሀሰት ትርክት ሁለት ቦታ በመርገጥ” ህዝብን ሲበድሉ የነበሩ አመራሮች መኖራቸውን ገምግሟል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የብልጽግና ፓርቲ በመተከል ዞን ለተፈጸመው ግድያ እና ሌሎች ጉዳቶች ይቅርታ መጠየቁ ይታወሳል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ መስተዳድሮች የዕጩዎች ምዝገባ ቀንን ይፋ አደረገ፡፡
ቦርዱ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላ፣ በኦሮሚያ እና በሃረሪ ክልላዊ መንግስታት የሚወዳደሩ እጩዎች የሚመዘገቡበትን ቀንም ይፋ አድርጓል፡፡
በመሆኑም በሁለቱ ከተማ መስተዳድሮች እና ቀደም ሲል በተጠቀሱት ክልሎች የሚገኙ እጩዎች ምዝገባ ከየካቲት 8 እስከ የካቲት 21 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት እስከ ቀኑ 11፡30 እንደሚከናወን ቦርዱ አስታውቋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ቦርዱ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላ፣ በኦሮሚያ እና በሃረሪ ክልላዊ መንግስታት የሚወዳደሩ እጩዎች የሚመዘገቡበትን ቀንም ይፋ አድርጓል፡፡
በመሆኑም በሁለቱ ከተማ መስተዳድሮች እና ቀደም ሲል በተጠቀሱት ክልሎች የሚገኙ እጩዎች ምዝገባ ከየካቲት 8 እስከ የካቲት 21 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት እስከ ቀኑ 11፡30 እንደሚከናወን ቦርዱ አስታውቋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የትግራይ ክልል 80 በመቶው ለዕርዳታ ተደራሽ አይደለም በማለት የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ፕሬዝዳንት አበራ ቶላ ዛሬ ለጋዜጠኞች መናገራቸውን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል፡፡ ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ 10 ሺዎች በርሃብ ሊሞቱ እንደሚችሉ ያስጠነቀቀው ማኅበሩ፣ እስካሁን ዕርዳታ እየደረሰ ያለው ከመቀሌ በስተሰሜን እና ደቡብ በዋና ዋና መንገዶች አቅራቢያ ብቻ ነው ብሏል፡፡ በክልሉ 3.8 ሚሊዮን ሰዎች ዕርዳታ ፈላጊዎች አሉ የሚል ግምት እንዳለውም አስታውቋል፡፡
✍Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
✍Wazema
@YeneTube @FikerAssefa