YeneTube
117K subscribers
31.5K photos
485 videos
79 files
3.9K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
ሮኬቶቹ የወደቁት ባህርዳር #በላይ_ዘለቀ አየር ማረፊያ በዳር በኩል ነው።

መጠነኛ ቃጠሎ ነበር አሁን እሳቱ ጠፍቷል። የእሳት አደጋ ሰራተኞች እና አምቡላንሶች እየተመለሱ ናቸው።

@Yenetube @Fikerassefa
ህውሀት የአክሱም ኤርፓርት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን ከFana Television ተመልክተናል።
@Yenetube @fikerassefa
YeneTube
ሮኬቶቹ የወደቁት ባህርዳር #በላይ_ዘለቀ አየር ማረፊያ በዳር በኩል ነው። መጠነኛ ቃጠሎ ነበር አሁን እሳቱ ጠፍቷል። የእሳት አደጋ ሰራተኞች እና አምቡላንሶች እየተመለሱ ናቸው። @Yenetube @Fikerassefa
ሮኬቶቹ በከተማይቱ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ መውደቃቸውንም ተገልፀ።

አንድ የከተማይቱ ነዋሪ ተከታታይ የሆኑ የሮኬቶቹን ድምጽ የሰሙት ከንጋቱ 12 ሰዓት ከ15 ገደማ እንደሆነ ተናግረዋል። የሮኬቶቹ ድምጽ ከዚህ ቀደም በለሊት ወደ ከተማይቱ ከተተኮሱት አነስ ያለ እንደነበርም ጠቅሰዋል።

የሮኬቶቹን መተኮስ በትግራይ እና አማራ ክልል ድንበር ከሚኖሩ ሰዎች በሰሙ ሶስት ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ድምጹን መስማታቸውን አስረድተዋል። ከትግራይ አዋሳኝ ቦታ አቅጣጫ ተወነጨፉ የተባሉትን ሮኪቶች አይተው የደወሉላቸው በጠለምት ወረዳ የምትገኘው የደጃች ሜዳ ከተማ ነዋሪዎች መሆናቸውንም ጠቁመዋል።

በባህር ዳር የሮኬቱን መውደቅ ከተሰማ በኋላ የእሳት አደጋ ተሽከርካሪዎች ወደ አየር ማረፊያ ጣቢያው አቅጣጫ ሲሄዱ መመልከታቸውን የከተማይቱ ነዋሪ ገልጸዋል።

(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@YeneTube @FikerAssefa
ለኤሌክትሪክ አገልግሎት ቅድመ ክፍያ የቆጣሪ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተላለፈ ማሳሰቢያ:

<<የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቅድመ ክፍያ የቆጣሪ አገልግሎት ለሚጠቀሙ ደንበኞቹ በዘመናዊ ቴክኖሎጅ የተደገፈ አገልግሎት ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እያከናወነ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ስለሆነም የዚሁ ዝግጅት አካል የሆኑ አንዳንድ ሥራዎች ለማከናወን ሲባል ዛሬ ሰኞ ህዳር 14 እና ነገ ማክሰኞ ህዳር 15 ቀን 2013 ዓ.ም በሁለም አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ካርድ መሙላትም ሆነ ሌሎች የቅድመ ክፍያ የተመለከቱ አገልግሎቶች የማይሰጡ መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡>>

[የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት]
@YeneTube @FikerAssefa
እስራኤል በኢትዮጵያ አዲስ አምባሳደር ሾመች።

አዲሱ አምባሳደር አቶ አለልኝ አድማሱ ናቸው።አቶ አለለኝ ቀድሞ የእስራኤል ፓርላማ አባል የነበሩ ሲሆን የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል።ተሿሚው አምባሳደር መች ወደ አዲስ አበባ መጥተው ሥራ እንደሚጀምሩ ግን ዘገባውን ይፋ ያደረገው ካአን ሬድዮ አልጠቀሰም።

Via Sheger FM
@YeneTube @FikerAssefa
በህዳሴ ግድቡ ድርድር መግባባት ያልተደረሰባቸው ጉዳዮች ለመሪዎች ውሳኔ እንዲቀርብ የአፍሪካ ኅብረት አሳሰበ!

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በተመለከተ በኢትዮጵያ፣ በግብፅና በሱዳን መካከል ሲደረግ በነበረው ድርድር መግባባት ያልተደረሰባቸው ጉዳዮች ለመሪዎች ውሳኔ እንዲቀርብ የአፍሪካ ኅብረት አሳሰበ፡፡የሦስቱ አገሮች ተደራዳሪዎች በዚህኛው ዙር ድርድራቸው አዲስ የድርድር አካሄድን መከተል ይገባል በሚል በሱዳንና በኢትዮጵያ ተቀባይነት ያገኘ ሐሳብ ተራምዶ የነበረ ቢሆንም፣ ይህንን ሐሳብ ግን ግብፅ ሳትቀበለው ቀርታለች፡፡ በሱዳንና በኢትዮጵያ በኩል የቀረበው አዲስ የድርድር አማራጭ፣ በአሁኑ ወቅት እያደራደረ የሚገኘው የአፍሪካ ኅብረት ሚና ማሳደግ የሚል ነው፡፡በዚሁ አማራጭ መሠረትም ከተለያዩ የአፍሪካ አገሮች ሁለት ሁለት ባለሙያዎች በድርድሩ እንዲሳተፉ ማድረግና የአፍሪካዊያንን ችግር በአፍሪካውያን የመቅረፍ መርህ ድርድሩ እንዲካሄድ የሚል ነበር፡፡

ይህንን አማራጭ ኢትዮጵያና ሱዳና ደግፈው ያቀረቡ ቢሆንም፣ በግብፅ በኩል ግን ተቃውሞ ገጥሞታል፡፡በዚህ ጉዳይ ላይ ዕልባት ለመስጠት ሐሙስ ኅዳር 10 ቀን 2013 ዓ.ም.፣ ድርድሩ በሦስቱ አገሮች የውኃ ጉዳይ ሚኒስትሮች አማካይነት በቪዲዮ ኮንፈረንስ ተካሄዶ የነበረ ቢሆንም ውጤት አልተገኘበትም፡፡‹‹የድርድሩ አካሄድ ካልተለወጠ በድርድሩ አልሳተፍም›› የሚል አቋም የሱዳን መንግሥት ተደራዳሪዎች ማራመዳቸውን፣ የኢትዮጵያ የውኃ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር ያወጣው መግለጫ ያመለክታል፡፡በዚህ ጉዳይ ላይ መፍትሔ ባለመገኘቱም የአደራዳሪነት ሚና የያዘው የአፍሪካ ኅብረት አስፈጻሚ ምክር ቤት ሦስቱ አገሮች ውይይት አድርገው፣ በሚቀጥለው ሳምንት ለሦስቱ አገሮች መሪዎች የሚቀርብ የተጨበጠ ነገር ላይ እንዲደርሱ በማሳሰብ ስብሰባው በዚያው ቀን መጠናቀቁን ለመረዳት ተችሏል፡፡

Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
ዳሞታ የቴክኖሎጂ እና ኢንቨስትመንት ባንክ በምስረታ ላይ ነው!

ዳሞታ የቴክኖሎጂና ኢንቨስትመንት ባንክ አክሲዮን ማኅበር ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የምስረታ ፈቃድ በመውሰድ በምስረታ ላይ መሆኑን አስታወቀ።በምስረታ ላይ የሚገኘው ዳሞታ ባንክ አክሲዮን ማኅበር ዓላማና ትኩረት አድርጎ የተነሳው ዘመናዊ የፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት መሆኑን ለአዲስ ማለዳ አስታውቋል። ባንኩ በትኩረት የሚሠራባቸው ዘርፎች የተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በመለየት እና አዋጭ የሥራ ፈጠራና የንግድ ሐሳብ ያላቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ አስታቋል።

ለዚህም የሥራ ፈጣሪዎች ልማትና ፋይናንስ(Entrepreneurs Developmenet and Finance) የሥራ ክፍል መቋቋም፣ ለአገር ሊጠቅሙ የሚችሉ ግለሰቦችን እና ድርጅቶችን የብድር አቅርቦት እንዳገኙ እንደሚደርግ የባንኩ ዋና ሰብሳቢ ኤሊያስ ሎሃ ለአዲስ ማለዳ አስታውቀዋል። ለዚህም ባንኩ ወደ ሥራ በሚገባበት ጊዜ የተሻለ የንግድ ሐሳብ ለሚቀርቡ ሥራ ፈጣሪዎች በዓመት ከሚገኘው ገቢ አምስት በመቶ ያክሉን በመመደብ የፋይናንስ አቅርቦት እንደሚሠራ ዋና ሰብሳቢው ጠቁመዋል።

Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
የቦሌ ክፍለ ከተማ አመራር በኮቪድ 19 ሕይወታቸው አለፈ!

የቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ኃላፊ የነበሩት ጉልላት ከበደ በ ኮቪድ 19 ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ኅዳር 14/2013 ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።

Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
ዩኤኢ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ መግባት እንደማይገባ ገለጸች!

(የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች)ዩኤኢ በግጭቱ ምክንያት ለተፈናቀሉ ሰዎች የ5 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ እሰጣለሁም ብላለች።የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በኢትዮጵያ የሕግ የበላይነት መከበር እንዳለበትና አሁን የተጀመረው ውጊያ መቆም እንዳለበት አስታውቋል፡፡

ዝርዝሩ👇👇👇

https://am.al-ain.com/article/ensuring-rule-of-law-in-ethiopia-vital-to-horn-of-stability

@YeneTube @FikerAssefa
የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ከህወሓት ጋር ግንኙነት አላቸው ያላቸውን የ4 ተጨማሪ ኩባንያዎች የባንክ ሒሳብ እንዲሁም ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረቶችን ማገዱን ለሸገር ተናገረ፡፡

ከዚህ ቀደም የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ከህወሓት ጋር ግንኙነት አላቸው ያላቸውን 34 ድርጅቶች የባንክ ሒሳብና ቋሚ ተንቀሳቃሽ ንብረት ማገዱ ይታወሳል፡፡የታገዱት ኩባንያዎች ቁጥር 38 መድረሱን ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ፍቃዱ ፀጋ ለሸገር ነግረዋል፡፡

ከ38ቱ ኩባንያዎች መካከል በስም መመሳሰል የኤፈርትን የኢሜል አድራሻ በመጠቀማቸው ከህወሓት ጋር ተዛምዶ ይኖራቸዋል በሚል ጥርጣሬ የባንክ ሒሳባቸው ታግደው ከነበሩት ኩባንያዎች ቢያንስ አንዱ ከዝርዝሩ ሊወጣ እንደሚችል አቶ ፀጋዬ ተናግረዋል፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ኩባንያዎቹ ላይ የወንጀል ምርመራ መጀመሩን ተናግረዋል፡፡እገዳው በድርጅቶቹ ውስጥ ተቀጥረው የሚያገለግሉ ሰራተኞችን ሕይወት እንዳያመሰቃቅል ለድርጅቶቹ አዲስ አስተዳደር ተሹሞላቸው ስራቸውን እንዲቀጥሉ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አቶ ፍቃዱ ተናግረዋል፡፡

Via Sheger FM
@YeneTube @FikerAssefa
አምስት የቀድሞ የወላይታ ዞን አመራሮች እና ሌሎች ሁለት ተጠርጣሪዎች ላይ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ ተመሰረተ። ከአመራሮቹ ጋር በአንድ መዝገብ የጊዜ ቀጠሮ ጉዳያቸው ሲታይ የቆዩ 13 ተጠርጣሪዎች በነጻ እንዲለቀቁ በፍርድ ቤት ተወስኖላቸዋል።

ዛሬ ክስ እንደተመሰረተባቸው ከተገለጸላቸው አመራሮች ውስጥ የቀድሞው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኩምቤ፣ ምክትላቸው ጎበዜ ጎዳና እና የዞኑ ብልጽግና ጽህፈት ቤት ኃላፊ የነበሩት አቶ ጥበቡ ዩሃንስ ይገኙበታል።

(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@YeneTube @FikerAssefa
በ1.5 ቢሊዮን ብር ካፒታል የባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪዎች መገጣጠሚያ ተመረቀ፤ በዓመት 30 ሺሕ ባለ ሦስት እግር ተሸከርካሪዎችን ይገጣጥማል

በኦሮሚያ ክልለ አዳማ ከተማ ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ መዋእለ ነዋይ የፈሰሰበት ባለ ሦስት እግር ተሸከርካሪዎችን የሚገጣጥም ፋብሪካ ወደ ሥራ መግባቱ ታወቀ፡፡ከአዲስ አበባ ከተማ 100 ኪሎ ርቀት ላይ በምትገኘዋ አዳማ ከተማ ከሦስት ዓመታት በፊት በተረከቡት 50 ሺህ ሜትር ስኩዌር ቦታ ላይ የተገነባው ፋብሪካ ሶስት የማምረቻ እና አንድ መጋዘን ያለው ሆኖ እያንዳንዳቸው በ 7 ሺሕ 500 ሜትር ስኬር ቦታ ላይ መሆናቸው ታውቋል፡፡

እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በየካቲት ወር 2015፣ የሆራ ኮርፖሬት ግሩፕ አባል የሆነው ሆራ ትሬዲንግ ከሕንድ አገር ከሚገኘው ግዙፉ 8AJAJ አውቶ ኃላፊነቱ የተወሰነ ኩባንያ ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎችን ለመገጣጠም መፈራረማቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚው አደም፡፡ኩባንያቸው በ56 ደቂቃ 23 ባለ ሦስት እግር ተሸከርካሪ መገጣጠም እንደሚችል ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ መገጣጠም እንደሚችል ምንተስኖት ተፈራ የሞተር ዘርፍ ም/ል ስራ አስፈፃሚ ተናግረዋል።

Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
በሻሸመኔ ከተማ ሁከት ለመፍጠር የሞከሩ 16 ተጠርጣሪዎች መያዙን የከተማዋ ጸጥታ ጽህፈት አስታወቀ።

በትናንትናው ዕለት በሻሸመኔ ከተማ ችግር ለመፍጠር የሞከሩ ተጠርጣሪዎች መያዛቸውን የከተማዋ ጸጥታ ጽህፈት ቤት ገልጿል።ትላንት በሻሸመኔ ከተማ መውጫ በሮችና አንዳንድ ስፍራዎች ይንቀሳቀሱ በነበሩ መኪኖች ላይ ድንጋይ በመወርወርና መንገድ በመዝጋት ጥቃት ለመፈጸም ከሞከሩ ውስጥ 16 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማዋ አስተዳደር እና የፀጥታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ስንታየሁ ጥላሁን ለኤትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡አቶ ስንታየሁ እንዳሉት ዕድሜያቸው ከ15 አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎቸን ለዚህ አይነት ተግባር ማሰማራት በእጅጉ ሞራለ ቢስነት ነው፡፡

ሃላፊው አክለውም እንዳለፈው አይነት ውድመት በከተማዋ አደርሳለሁ ብሉ ማሰብም አደገኛ ነው ብለዋል፡፡የከተማዋ አስተዳደር እንዲህ አይነት ተግባሮችን ፈጽሞ አይታገስም ያሉት አቶ ስንታየሁ እኚህ ታዳጊዎች ማን እና ለምን እንዳሰማራቸው ፖሊስ ምርመራ ላይ ይገኛል ነው ያሉት፡፡በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት ታዳጊዎች በከተማዋ ውስጥ ብጥብጥ በማስነሳት የመንግስትን ትኩረት የመበተን አቅጣጫ እንደተሰጣቸው መናገራቸውን ይናገራሉ አቶ ስንታየሁ፡፡በከተማዋ እና አጎራባች አከባቢዎች የተፈጠሩ ችግሮችን በአስቸኳይ እንዲቆጣጠሩና ዳግም እንዲህ አይነት ሙከራ እንዳይደረግ ከወዲሁ ጠንካራ ክትትል እንዲያደርጉ ትዕዛዝ መተላለፉንም ሃላፊው አብራርተዋል፡፡

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የሕወሃት ልዩ ሃይል ያፈረሳቸው ድልድዮችን በፍጥነት ገንብቶ ለአገልግሎት እንደሚያበቃ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሃብታሙ ተገኝ እንዳሉት በትግራይ ክልል እየተካሄደ ባለው ህግን የማስከበር ዘመቻ ላይ ሆን ተብለው በልዩ ሃይሉ የፈረሱ ድልድዮችን መልሶ በመገንብት ለህብረተሰቡ ጥቅም እንዲውሉ አደርጋለሁ ብሏል።እነዚህ ድልድዮችን እና መንገዶችን በጊዜያዊነት ወደ ቀድሞ አገልግሎታቸው ለመመለስ የብረት ድልድይ መዘጋጀቱን ገልጿል፡፡

አሁን ላይ በጦርነቱ ተጎድተው የማያሳልፉ መንገዶች የአስፋልትም ይሁን የጠጠር መንገዶችን እንደሚጠግኗቸውም ተናግረዋል፡፡የተጎዱ መንገዶችን በሚመለከት የተሟላ መረጃ አለን፣ የት የት ቦታ ችግር እንደገጠመ እና ያንን መልሶ ወደ ስራ ለማስገባት ዲስትሪክቶችም ዝግጁ ናቸው ፣ ችግሩ ስጋት ሆኖ እንደማይቀጥልም ኢንጅነር ሃብታሙ ገልጸዋል፡፡ኢንጅነር ሃብታሙ በፌዴራል መንግስት የሚሰሩ እንዳሉ ሁሉ በክልል መንግስትም የሚሰሩ እና የሚጠገኑ መንገዶች መኖራቸውን እና ክልሎች የሚያስፈልጋቸው ድጋፍ ካለ እናግዛቸዋለን ብለዋል ፡፡

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የሕወሓትን ተልዕኮ ተቀብለው በአዲስ አበባ የተለያዩ ጥቃቶችን ለመፈፀም እና የፀጥታ መደፍረስ እንዲከሰት አቅደው ሲንቀሳቀሱ ነበሩ የተባሉ ከ700 በላይ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የልዩ ልዩ ህገ- ወጥ ዝውውር ወንጀሎች ምርመራ ዳይሬክተር ኮማንደር ግርማ ተሰማ የቡድኑ ተልዕኮ የፀጥታ አካላትን የደንብ ልብስ በመልበስ ጭምር በአዲስ አበባም ለማስፈፀም ሲንቀሳቀሱ እና ዝግጅት ሲያደርጉ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ያስታወሱት፡፡

በተለያዩ ግለሰቦች መኖሪያ ቤት እና በልዩ ልዩ ተቋማት ውስጥ በተደረገ ፍተሻ 202 የተለያዩ የፀጥታ አካላት የደንብ አልባሳት ተይዘዋል ነው ያሉት፡፡የደንብ አልባሳቶቹ በሃይማኖት አባቶች መኖሪያ ቤቶች ጭምር መገኘታቸውን የጠቀሱት ኮማንደር ግርማ ይህ ደግሞ ህገወጡ እና ከሃዲው የህወሃት ቡድን በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ሳይቀር ሰርጎ በመግባት ግጭት ለመቀስቀስ እየተንቀሳቀሰ አንደሚገኝ የሚያሳይ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ከነገ የሚጀምር ከከባድ ተሽከርካሪዎች የከተማ ውስጥ እንቅስቃሴ ጋር ተያይዞ የሰዓት ገደብ ማስተላለፉን አስታወቀ፡፡ ኮሚሽኑ የሰዓት ገደቡን ያሳለፈው በአስተዳደሩ እየተከሰተ ካለው የትራፊክ መጨናነቅና በዚህም ሳቢያ እየተፈጠረ ያለውን የመንገዶች መዘጋትና መጉላላት ለመቀነስና ለማስቀረት አስቦ መሆኑን ነው የገለጸው፡፡ ገደቡ ከነገ ጀምሮ ከንጋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽት…
በድሬዳዋ በከባድ ተሽከርካሪዎች ላይ የተላለፈው የሰዓት ገደብ ተሻሻለ!

በድሬደዋ ከተማ ከባድ ተሽከርካሪ ከጠዋቱ 12 የሰአት እሰከ ምሽቱ 12 ሰአት ወደ ከተማ ውስጥ “መግባትም ሆነ በከተማ ውስጥ መንቀሳቀስ እንደማይቻል ገደብ መጣሉን በትናንት ዕለት መዘገባችን ይታወሳል::

ይሁን እንጂ 'አዲስ ዘይቤ' አገኘሁት እንዳለችው መረጃ ከሆነ ከተማዋ ከጎረቤት ሀገር የሚገቡ ተሸከርካሪዎች መኖራቸውን ታሳቢ በማድረግ የወጣውን የሰአት ገደብ ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡

በዚህም መሰረት ከባድ ተሽከርካሪ ጠዋት ከ1 ሰአት እስከ 3 ሰአት እንዲሁም ቀን ከ5 :30 እስከ 8:30 ወደ ከተማ መግባት የሚችሉ ሲሆን ነዳጅ የሚያጓጉዙ ከባድ ተሽከርካሪዎች በማንኛዉም ሰዓት እንደሚንቀሳቀሱ የድሬደዋ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት ዳይሬከተር ኮማንደር ገመቹ ካቻ ገልፀዋል፡፡

የሰዓት ገደብ በተላለፈ አካላ ላይ ደግሞ ተገቢው የህግ የትርምት እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን የፌደራል መንገድ ትራንስፖርት ባለስልጣን እና የከተማዉ የትራፊክ ፖሊስ ዳሪክቶሬት አስታውቋል፡፡

Via Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa
በ80 ሚሊየን ብር የተገነባ የጋሻሞ ሆስፒታል ተመረቀ!

የሶማሊ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፋ ሙሁመድ ዑመር በጀረር ዞን የተገነባውን የጋሻሞ ሆስፒታል መርቀው ከፍተዋል።ሆስፒታሉ በ80 ሚሊየን ብር የተገነባ ሲሆን፣ በዙሪያው ለሚገኙ 5 ወረዳዎች አገልግሎት እንደሚሰጥ ምክትል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ በምረቃው ወቅት ተናግረዋል።ሆስፒታሉ 60 በመቶ በሰው ኃይል እና በቁሳቁስ መደራጀቱን የገለፁት ምክትል ርእሰ መስተዳድሩ፣ በተለይ በክልሉ በወሊድ ወቅት የሚከሰት የእናቶች ሞትን ለመቀነስ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ ነው ብለዋል።

የሶማሌ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ሸርማርኬ ሸሪፍ፣ የሆስፒታሉ ተገንብቶ ለአገልግሎት ብቁ መሆን ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ያለውን የክልሉን የቤተሰብ ምጣኔ ለመሻሻል ያግዛል ብለዋል።ሆስፒታሉ በዙሪያው ለሚገኙ 800 ሺህ ለሚጠጉ የህብረተሰብ ክፍሎች አገልግሎት እንዲሰጥ ታስቦ የተገነባ ነው።አሁን ላይ በክልሉ 12 የሚጠጉ ሆስፒታሎች በ1 ቢሊየን ብር በሚጠጋ በጀት የግንባታ፣ የማስፋፊያ እና የማሻሻያ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውም ተገልጿል።

ምንጭ: የክልሉ መ/ኮ/ቢሮ
@YeneTube @FikerAssefa
289 ኢትዮጵያውያን ዜጎች በዛሬው እለት ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሃገራቸው ተመለሱ፡፡ከተመላሾቹ መካከል 90ዎቹ ህጻናት መሆናቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ ኢትዮጵያውያኑ መንግስት ከሳዑዲ ባለስልጣናት ጋር ባደረገው ትብብር ወደ ሃገራቸው የተመለሱ ናቸው፡፡

@YeneTube @FikerAssefa