የፓናማ ፖሊስ ከአንድ ኃይማኖት ጋር ግንኙነት አለው ያለውን የጅምላ መቃብር ማግኘታቸውን አስታወቀ።
ፖሊስ ምርመራ ላይ እንደሆነ ጨምሮ አስታውቋል።መርማሪዎች በሰሜን ምዕራብ የፓናማ አውራጃ ከተገኘው የጅምላ መቃብሩ የተቆፈሩ አፅሞችን እየሰበሰቡ ነው።ባለፈው ጥር አሁን የጅምላ መቃብሩ ከተገኘበት ሥፍራ ብዙም ሳይርቅ የሰባት ሰዎች አስከሬን አንድ ላይ ተቀብሮ መገኘቱ ይታወሳል።ሬሳዎቹ አንድ ሰይጣን ለማውጣት ጉልበት የተቀላቀለበት ኃይል ከሚጠቀም ኃይማኖት ጋር ግንኙነት አላቸው ተብሏል።አቃቤ ሕግ አዛኤል ቱግሪ፤ መርማሪዎች በተራራዎች መካከል 10 ሰዓት ያክል ተጉዘው የጅምላ መቃብሩን እንዳገኙት ያስረዳሉ።መቃብሩ ንጋቤ ቡግሌ የተሰኘ ሥፍራ ካለ አንድ ወንዝ አቅራቢያ ነው የተገኘው።የጅምላ መቃብሩ ከፓናማ ዋና ከተማ ፓናማ ሲቲ 350 ኪሎ ሜትር ርቆ ነው የሚገኘው።
አቃቤ ሕጉ በአሁን ወቅት የአስከሬን ቁጥርና ፆታ መለየት እጅግ አዳጋች ነው ሲሉ ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል።አፅሞቹ ተሰብስበው የሬሳ ምርመራ እንደሚደርግላቸው ታውቋል።ከቀናት በፊት ፖሊስ የኒው ላይት ኦፍ ጋድ ቤተ እምነት መሪ ነው የተባለ ሰው ወርሃ ጥር ላይ ከተገኘው መቃብር ጋር በተያያዘ ክስ በቁጥጥር ሥር አውሏል።ባለፈው ጥር የጅምላ መቃብሩ የተገኘው ሶስት ሰዎች አምልጠው በአቅራቢያው ወዳለ ሆስፒታል ሄደው ጥቆማ ከሰጡ በኋላ ነው።መቃብሩ ሲቆፈር አንዲት ነብሰ ጡር እናትና አምስት ልጆቿ እንዲሁም አንድ ታዳጊ ተገኝተዋል።ይህን ተከትሎ ፖሊስ ባካሄደው ፍተሻ በአንድ ቤተ እምነት ውስጥ አንዲት እርቃኗን ያለች ሴት፣ ገጀራዎች፣ ቢላዎች መስዋዕት የሆነ ፍየል አግኝቷል።ቤተ እምነቱ ሰይጣን ለማውጣት በሚል ኃይል የተቀላቀለበት መንገድ ይጠቀም ነበር ተብሏል።በኃይማኖቱ ቁጥጥር ሥር የነበሩ 15 ሰዎች መለቀቃቸውም በጊዜው ተዘግቦ ነበር።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ፖሊስ ምርመራ ላይ እንደሆነ ጨምሮ አስታውቋል።መርማሪዎች በሰሜን ምዕራብ የፓናማ አውራጃ ከተገኘው የጅምላ መቃብሩ የተቆፈሩ አፅሞችን እየሰበሰቡ ነው።ባለፈው ጥር አሁን የጅምላ መቃብሩ ከተገኘበት ሥፍራ ብዙም ሳይርቅ የሰባት ሰዎች አስከሬን አንድ ላይ ተቀብሮ መገኘቱ ይታወሳል።ሬሳዎቹ አንድ ሰይጣን ለማውጣት ጉልበት የተቀላቀለበት ኃይል ከሚጠቀም ኃይማኖት ጋር ግንኙነት አላቸው ተብሏል።አቃቤ ሕግ አዛኤል ቱግሪ፤ መርማሪዎች በተራራዎች መካከል 10 ሰዓት ያክል ተጉዘው የጅምላ መቃብሩን እንዳገኙት ያስረዳሉ።መቃብሩ ንጋቤ ቡግሌ የተሰኘ ሥፍራ ካለ አንድ ወንዝ አቅራቢያ ነው የተገኘው።የጅምላ መቃብሩ ከፓናማ ዋና ከተማ ፓናማ ሲቲ 350 ኪሎ ሜትር ርቆ ነው የሚገኘው።
አቃቤ ሕጉ በአሁን ወቅት የአስከሬን ቁጥርና ፆታ መለየት እጅግ አዳጋች ነው ሲሉ ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል።አፅሞቹ ተሰብስበው የሬሳ ምርመራ እንደሚደርግላቸው ታውቋል።ከቀናት በፊት ፖሊስ የኒው ላይት ኦፍ ጋድ ቤተ እምነት መሪ ነው የተባለ ሰው ወርሃ ጥር ላይ ከተገኘው መቃብር ጋር በተያያዘ ክስ በቁጥጥር ሥር አውሏል።ባለፈው ጥር የጅምላ መቃብሩ የተገኘው ሶስት ሰዎች አምልጠው በአቅራቢያው ወዳለ ሆስፒታል ሄደው ጥቆማ ከሰጡ በኋላ ነው።መቃብሩ ሲቆፈር አንዲት ነብሰ ጡር እናትና አምስት ልጆቿ እንዲሁም አንድ ታዳጊ ተገኝተዋል።ይህን ተከትሎ ፖሊስ ባካሄደው ፍተሻ በአንድ ቤተ እምነት ውስጥ አንዲት እርቃኗን ያለች ሴት፣ ገጀራዎች፣ ቢላዎች መስዋዕት የሆነ ፍየል አግኝቷል።ቤተ እምነቱ ሰይጣን ለማውጣት በሚል ኃይል የተቀላቀለበት መንገድ ይጠቀም ነበር ተብሏል።በኃይማኖቱ ቁጥጥር ሥር የነበሩ 15 ሰዎች መለቀቃቸውም በጊዜው ተዘግቦ ነበር።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
አቶ ጃዋር መሃመድና አቶ በቀለ ገርባ አንድ ላይ እንዲገናኙ ያቀረቡትን አቤቱታ ተከትሎ አፈፃፀሙን ለመመልከት በተሰጠው ቀጠሮ መሰረት ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ።
ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ተወካይም ቀርበው ትእዛዙ መፈፀሙን አብራርቷል።እነ አቶ ጃዋር መሃመድና አቶ በቀለ ገርባም ትእዛዙ መፈፀሙን ገልፀዋል።የአቶ ሀምዛ አዳነ (ቦረና) እና የአቶ ሸምሰዲን ጠሃ ጠበቃ ለችሎቱ ደንበኞቹ 30 ደቂቃ ብቻ አየር እያገኙ መሆኑን በመግለፅ፤ ከ30 ደቂቃ በላይ የፀሃይ ብርሃን እና አየር እንዲያገኙ ትእዛዝ እንዲሰጥለት ጠይቋል።
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎትም በቂ አየር እና የፀሃይ ብርሃን እንዲያገኙ ትእዛዝ ሰጥቷል።በሌላ በኩል በሰብአዊ መበት ጥሰት ወንጀል በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት በእነ ጌታቸው አሰፋ መዝገብ የተከሰሱ ከ15 በላይ ተከሳሾች ፍርድ ቤት ቀርበው የአቃቤ ህግ ምስክር እየተሰማ ይገኛል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ተወካይም ቀርበው ትእዛዙ መፈፀሙን አብራርቷል።እነ አቶ ጃዋር መሃመድና አቶ በቀለ ገርባም ትእዛዙ መፈፀሙን ገልፀዋል።የአቶ ሀምዛ አዳነ (ቦረና) እና የአቶ ሸምሰዲን ጠሃ ጠበቃ ለችሎቱ ደንበኞቹ 30 ደቂቃ ብቻ አየር እያገኙ መሆኑን በመግለፅ፤ ከ30 ደቂቃ በላይ የፀሃይ ብርሃን እና አየር እንዲያገኙ ትእዛዝ እንዲሰጥለት ጠይቋል።
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎትም በቂ አየር እና የፀሃይ ብርሃን እንዲያገኙ ትእዛዝ ሰጥቷል።በሌላ በኩል በሰብአዊ መበት ጥሰት ወንጀል በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት በእነ ጌታቸው አሰፋ መዝገብ የተከሰሱ ከ15 በላይ ተከሳሾች ፍርድ ቤት ቀርበው የአቃቤ ህግ ምስክር እየተሰማ ይገኛል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ከአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች የተሰረቁ 8 ተሽከርካሪዎችን ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ዋሉ!
በኮሚሽኑ የተደራጁ ወንጀሎች ምርመራ ዲቪዚዮን ኃላፊ ኢንስፔክተር ያሬድ አለማየሁ እንደገለፁት ከአዲስ አበባ ከተማ ተሰርቀው የተወሰዱ 8 የተለያዩ ተሽከርካሪዎችን ከአዲስ አበባ ውጪ በሚገኙ የተለያዩ የሀገራችን ከተሞች ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራ ይገኛል ብለዋል።
የተሽከርካሪ ባለንብረቶች ቸልተኝነት እና ጥንቃቄ ጉድለት በተለይም ቁልፍ ሳይነቅሉ እና የተሟላ ጥበቃ ባለበት ስፍራ ሳያቆሙ መሄድ፣ በከተማችን የተሽከርካሪ ስርቆት ከሚፈፀምባቸው ምቹ ሁኔታዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
ከዚህ በተጨማሪም በተለያዩ ጉዳዮች በጉምሩክ ተይዘው የነበሩ እና ከ35 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው 4 ተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ሰራተኞች ጋር በመመሳጠር እና ሃሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀት እንዲወጡ ከተደረጉ በኋላ በፖሊስ በተደረገ ክትትል ተሽከርካሪዎቹ ወንጀሉን ፈፅመዋል ከተባሉት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኮሚሽኑ መረጃ ያመለክታል።
[Addis Ababa Police Commission]
@YeneTube @FikerAssefa
በኮሚሽኑ የተደራጁ ወንጀሎች ምርመራ ዲቪዚዮን ኃላፊ ኢንስፔክተር ያሬድ አለማየሁ እንደገለፁት ከአዲስ አበባ ከተማ ተሰርቀው የተወሰዱ 8 የተለያዩ ተሽከርካሪዎችን ከአዲስ አበባ ውጪ በሚገኙ የተለያዩ የሀገራችን ከተሞች ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራ ይገኛል ብለዋል።
የተሽከርካሪ ባለንብረቶች ቸልተኝነት እና ጥንቃቄ ጉድለት በተለይም ቁልፍ ሳይነቅሉ እና የተሟላ ጥበቃ ባለበት ስፍራ ሳያቆሙ መሄድ፣ በከተማችን የተሽከርካሪ ስርቆት ከሚፈፀምባቸው ምቹ ሁኔታዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
ከዚህ በተጨማሪም በተለያዩ ጉዳዮች በጉምሩክ ተይዘው የነበሩ እና ከ35 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው 4 ተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ሰራተኞች ጋር በመመሳጠር እና ሃሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀት እንዲወጡ ከተደረጉ በኋላ በፖሊስ በተደረገ ክትትል ተሽከርካሪዎቹ ወንጀሉን ፈፅመዋል ከተባሉት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኮሚሽኑ መረጃ ያመለክታል።
[Addis Ababa Police Commission]
@YeneTube @FikerAssefa
በጅግጅጋ ጉምሩክ በዛሬ ዕለት ወደ ሀገር ሊገባ የነበረ 200 ሺህ ብር መያዙን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በትላንትናው ዕለት በመንግሥት ይፋ በተደረገው የብር ኖት ቅያሪ ምክንያት ከሱማሌላንድ በቶጎውጫሌ በኩል በተለያየ በህገወጥ መንገድ ወደ ውጭ የሸሸ የኢትዮጵያ 200 ሺህ ብር በአንድ ግለሰብ አማካኝነት ወደ ሀገር ሊገባ ሲል በጉምሩክ ፈታሽ አማካኝነት ከነተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር መዋሉ ነው የተገለጸው፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በትላንትናው ዕለት በመንግሥት ይፋ በተደረገው የብር ኖት ቅያሪ ምክንያት ከሱማሌላንድ በቶጎውጫሌ በኩል በተለያየ በህገወጥ መንገድ ወደ ውጭ የሸሸ የኢትዮጵያ 200 ሺህ ብር በአንድ ግለሰብ አማካኝነት ወደ ሀገር ሊገባ ሲል በጉምሩክ ፈታሽ አማካኝነት ከነተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር መዋሉ ነው የተገለጸው፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
ከሳውዲ አረቢያ የመውጫ ቪዛ አግኝተው ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ከሀገሪቱ መንግስት ጋር በመስማማት ከነሃሴ 17/2012 ጀምሮ አስፈላጊው የጉዞ ሰነድና የትብብር ደብዳቤ በመያዝ ሲሰጥ የነበረው አገልግሎት ላልተወሰነ ጊዜ በሳውዲ ኢሚግሬሽን በኩል መቋረጡን በሪያድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳውቋል። @YeneTube @FikerAssefa
በሳዑዲ እስካሁን ከታወቁት ውጭ ሌሎች በርካታ አሰቃቂ የስደተኛ ማጎሪያዎች አሉ ብሎ እንደሚገምት ቴሌግራፍ ጋዜጣ ዘግቧል፡፡
ከመካ ከተማ አቅራቢያ ባለው አል ሹማሲ ማጎሪያ ጣቢያ ብቻ 16 ሺህ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች እንደታጎሩ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ገልጧል፡፡ ሰሞኑን ወደ ሀገራቸው እየተመለሱ ያሉት ስደተኞችም፣ በሁለቱ ሀገሮች ስምምነት የመውጫ አውሮፕላን ትኬታቸውን በራሳቸው ወጭ ገዝተው ነው- ብሏል ዘገባው፡፡ ሳዑዲ ግን ይህን ስምምነት አሁን እንደሰረዘችው እና ይህም በቀጣይ ስደተኞችን መውጫ እንደሚያሳጣቸው፣ ጋዜጣው በሪያድ የኢትዮጵያ ኢምባሲን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡
[Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
ከመካ ከተማ አቅራቢያ ባለው አል ሹማሲ ማጎሪያ ጣቢያ ብቻ 16 ሺህ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች እንደታጎሩ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ገልጧል፡፡ ሰሞኑን ወደ ሀገራቸው እየተመለሱ ያሉት ስደተኞችም፣ በሁለቱ ሀገሮች ስምምነት የመውጫ አውሮፕላን ትኬታቸውን በራሳቸው ወጭ ገዝተው ነው- ብሏል ዘገባው፡፡ ሳዑዲ ግን ይህን ስምምነት አሁን እንደሰረዘችው እና ይህም በቀጣይ ስደተኞችን መውጫ እንደሚያሳጣቸው፣ ጋዜጣው በሪያድ የኢትዮጵያ ኢምባሲን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡
[Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
በመቐለ ከተማ ሦስት ወጣቶች ሞተው ተገኙ!
በመቀለ ከተማ በአይደር ክፍለ ከተማ አዲሓ ተብሎ በሚታወቀው ሰፈር አንዲት ሴትና ሁለት ወንድ ጓደኛሞች በአንድ ቤት ውስጥ ሞተው ተገኙ።ወጣቶቹ ሞተው የተገኙት በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ መሆኑን በከተማዋ የሚገኘው የአይደር ክፍለ ከተማ ፖሊስ ለቢቢሲ ገልጿል።ህይወታቸው አልፎ የተገኙት ሦስቱ ወጣቶች ርዕሶም ገብረእግዚአብሔር፣ ግርማይ ኃብተሚካኤል እና መርሃዊት ሐድጉ የተባሉት ጓደኛሞች መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን እድሜያቸው ደግሞ በ20ዎች ውስጥ እንደሆነ ተነግሯል።ሦስቱም ወጣቶች ባለፈው ቅዳሜ መስከረም ሁለት ቀን በጋራ ሲጫወቱ አምሽተው ወደ ቤታቸው እንደገቡ የተገለጸ ሲሆን፤ በማግስቱ እሁድ ከሰዓት ግን በአንደኛው ሟች ቤት ውስጥ ሞተው መገኘታቸው ታውቋል።
በአይደር ክፍለ ከተማ የወንጀል ምርመራ ክፍል ባልደረባ የሆኑት ምክትል ኢንስፔክተር ገብረማርያም የማነ እንዳሉት የወጣቶቹ ሞት መንስዔ ለማወቅ ፖሊስ መርመራ እያካሄደ እንደሆነ ለቢቢሲ ገልጸዋል።ጨምረውም እስካሁን ባገኘው መረጃ ፖሊስ ለወጣቶቹ ሞት መንስዔ ተብሎ የሚጠረጠር ፍንጭ ያገኘ ቢሆንም፤ በአይደር ሆስፒታል የአስከሬን ምርመራ ተደርጎ ውጤት እስኪመጣለት ድረስ እየጠበቀ መሆኑንም መርማሪው ጨምረው ተናግረዋል።የሟች ርዕሶም ገብረእግዚአብሔር ወንድም የሆነው ገብረ መድኅን ገብረእግዚአብሔር ለቢቢሲ እንደተናገረው ወጣቶቹ ተኝተውበት በነበረው ክፍል ውስጥ የነበረው ጄነሬተር ለሞታቸው መንስኤ ሊሆን እንደሚችል አመልክቷል።
ገብረመድኅን እንደሚለው ከሆነ ቅዳሜ ዕለት ወጣቶቹ በሚኖሩበት አካባቢ መብራት ጠፍቶ ስለነበር ጄኔሬተሩ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረ ቢሆንም ማታ ግን ተለኩሶ ስለመቆየቱ መረጃ እንደሌለው ተናግሯል።ህይወታቸው አልፎ የተገኙት ሦስቱ ወጣቶች አስከሬን ወደ አይደር ሆስፒታል ሲወሰዱ ከህልፈታቸው በፊት ከአፋቸው አረፋ ይደፍቁ እንደነበርም ጨምሮ ተናግሯል።የሶስቱ ወጣቶች ድንገተኛ ሞት ዜና በርካታ የመቀለ ከተማ ነዋሪዎችን ያስደነገጠ ሲሆን፤ ለሞታቸው ሰበብ የሆነውን ምክንያት ለማወቅ የህክምናና የፖሊስ የመርመራ ውጤት እየተጠበቀ ነው።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
በመቀለ ከተማ በአይደር ክፍለ ከተማ አዲሓ ተብሎ በሚታወቀው ሰፈር አንዲት ሴትና ሁለት ወንድ ጓደኛሞች በአንድ ቤት ውስጥ ሞተው ተገኙ።ወጣቶቹ ሞተው የተገኙት በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ መሆኑን በከተማዋ የሚገኘው የአይደር ክፍለ ከተማ ፖሊስ ለቢቢሲ ገልጿል።ህይወታቸው አልፎ የተገኙት ሦስቱ ወጣቶች ርዕሶም ገብረእግዚአብሔር፣ ግርማይ ኃብተሚካኤል እና መርሃዊት ሐድጉ የተባሉት ጓደኛሞች መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን እድሜያቸው ደግሞ በ20ዎች ውስጥ እንደሆነ ተነግሯል።ሦስቱም ወጣቶች ባለፈው ቅዳሜ መስከረም ሁለት ቀን በጋራ ሲጫወቱ አምሽተው ወደ ቤታቸው እንደገቡ የተገለጸ ሲሆን፤ በማግስቱ እሁድ ከሰዓት ግን በአንደኛው ሟች ቤት ውስጥ ሞተው መገኘታቸው ታውቋል።
በአይደር ክፍለ ከተማ የወንጀል ምርመራ ክፍል ባልደረባ የሆኑት ምክትል ኢንስፔክተር ገብረማርያም የማነ እንዳሉት የወጣቶቹ ሞት መንስዔ ለማወቅ ፖሊስ መርመራ እያካሄደ እንደሆነ ለቢቢሲ ገልጸዋል።ጨምረውም እስካሁን ባገኘው መረጃ ፖሊስ ለወጣቶቹ ሞት መንስዔ ተብሎ የሚጠረጠር ፍንጭ ያገኘ ቢሆንም፤ በአይደር ሆስፒታል የአስከሬን ምርመራ ተደርጎ ውጤት እስኪመጣለት ድረስ እየጠበቀ መሆኑንም መርማሪው ጨምረው ተናግረዋል።የሟች ርዕሶም ገብረእግዚአብሔር ወንድም የሆነው ገብረ መድኅን ገብረእግዚአብሔር ለቢቢሲ እንደተናገረው ወጣቶቹ ተኝተውበት በነበረው ክፍል ውስጥ የነበረው ጄነሬተር ለሞታቸው መንስኤ ሊሆን እንደሚችል አመልክቷል።
ገብረመድኅን እንደሚለው ከሆነ ቅዳሜ ዕለት ወጣቶቹ በሚኖሩበት አካባቢ መብራት ጠፍቶ ስለነበር ጄኔሬተሩ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረ ቢሆንም ማታ ግን ተለኩሶ ስለመቆየቱ መረጃ እንደሌለው ተናግሯል።ህይወታቸው አልፎ የተገኙት ሦስቱ ወጣቶች አስከሬን ወደ አይደር ሆስፒታል ሲወሰዱ ከህልፈታቸው በፊት ከአፋቸው አረፋ ይደፍቁ እንደነበርም ጨምሮ ተናግሯል።የሶስቱ ወጣቶች ድንገተኛ ሞት ዜና በርካታ የመቀለ ከተማ ነዋሪዎችን ያስደነገጠ ሲሆን፤ ለሞታቸው ሰበብ የሆነውን ምክንያት ለማወቅ የህክምናና የፖሊስ የመርመራ ውጤት እየተጠበቀ ነው።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የ”ሰላም”ፈራሚዎቹ ልኡካን ኋይት ሀውስ ደርሰዋል!
በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች( ዩኤኢ)፣ በእስራኤልና በባህሬን የሰላም ስምምነት የሚሳተፉት የሉእካን ቡድን አባላት አሜሪካ ኋይት ሃውስ ገብተዋል፡፡የዩኤኢ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሸክ አብዱላህ ቢን ዛይድ አልናህያን፣ የባህሬኑ አቻቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አብዱላቲፍ አል ዛያኒና የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይገኛሉ፡፡ሉእካኑ ኋይት ኃውስ ሲደርሱ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ተቀብለዋቸዋል፡፡በኋይት ሀውስ አንድ ሺ አሜሪካውያን፣ የአለም አቀፍና የአረብ ታዋቂ ሰዎች በኋይት ሃውስ ተገኝተዋል፡፡የአረብ ሀገራቱና የእስራኤል ግንኙነት እንዲታደስ እያመቻቸች ያለችው አሜሪካ ስትሆን ባለፈው ወር ዩኤኢና እስራል ታሪካዊ የተባለ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
[Al ain]
@YeneTube @FikerAssefa
በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች( ዩኤኢ)፣ በእስራኤልና በባህሬን የሰላም ስምምነት የሚሳተፉት የሉእካን ቡድን አባላት አሜሪካ ኋይት ሃውስ ገብተዋል፡፡የዩኤኢ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሸክ አብዱላህ ቢን ዛይድ አልናህያን፣ የባህሬኑ አቻቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አብዱላቲፍ አል ዛያኒና የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይገኛሉ፡፡ሉእካኑ ኋይት ኃውስ ሲደርሱ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ተቀብለዋቸዋል፡፡በኋይት ሀውስ አንድ ሺ አሜሪካውያን፣ የአለም አቀፍና የአረብ ታዋቂ ሰዎች በኋይት ሃውስ ተገኝተዋል፡፡የአረብ ሀገራቱና የእስራኤል ግንኙነት እንዲታደስ እያመቻቸች ያለችው አሜሪካ ስትሆን ባለፈው ወር ዩኤኢና እስራል ታሪካዊ የተባለ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
[Al ain]
@YeneTube @FikerAssefa
በደቡብ ክልል በኮንሶ ዞንና በአሌ ልዩ ወረዳ አዋሳኝ ድንበሮች ላይ ዳግም ባገረሸ ግጭት በትንሹ አራት ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ።
የአካባቢው ነዋሪዎች አንዳሉት ከባለፈው ዓርብ ጀምሮ ዳግም በተቀሰቀሰ ግጭት ከሞቱት ሰዎች ባሻገር የመኖርያ መንደሮች በእሳት ወድመዋል። የግጭቱ መነሻ በአሌ ልዩ ወረዳ ቀርቀርቴ ቀበሌ ውስጥ በቡድን የተሰባሰቡ ሰዎች የአንድ ሰው ሕይወት አጥፍተዋል የሚል መረጃ ከተሰራጨ በኋላ መሆኑን፤ በዚህም ምክንያት በሁለቱም ወገን በርካታ ቤቶች መቃጠላቸውን አንድ እማኝ ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል። የቀርቀርቴ ቀበሌ ነዋሪ መሆናቸውን የገለፁት የዓይን ምስክሩ እንደሚሉት ቢያንስ የአራት ሰዎች ሕይወት ጠፍቷል።በኮንሶ ዞን የካራ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ካሣሁን ገረመው በወረዳው አርካይዴና ገላቡ በተባሉት ቀበሌዎች ላይ በተፈጸመ ጥቃት ሁለት ሰዎች መሞታቸውን አረጋግጠዋል። የደቡብ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዓለማየው ባውዴም ግጭቱ ዳግም መቀስቀሱን በማረጋገጥ፤ በአሁኑ ወቅትም የፀጥታ ኃይል በመንደሮቹ በመግባት ለማረጋጋት እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
የአካባቢው ነዋሪዎች አንዳሉት ከባለፈው ዓርብ ጀምሮ ዳግም በተቀሰቀሰ ግጭት ከሞቱት ሰዎች ባሻገር የመኖርያ መንደሮች በእሳት ወድመዋል። የግጭቱ መነሻ በአሌ ልዩ ወረዳ ቀርቀርቴ ቀበሌ ውስጥ በቡድን የተሰባሰቡ ሰዎች የአንድ ሰው ሕይወት አጥፍተዋል የሚል መረጃ ከተሰራጨ በኋላ መሆኑን፤ በዚህም ምክንያት በሁለቱም ወገን በርካታ ቤቶች መቃጠላቸውን አንድ እማኝ ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል። የቀርቀርቴ ቀበሌ ነዋሪ መሆናቸውን የገለፁት የዓይን ምስክሩ እንደሚሉት ቢያንስ የአራት ሰዎች ሕይወት ጠፍቷል።በኮንሶ ዞን የካራ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ካሣሁን ገረመው በወረዳው አርካይዴና ገላቡ በተባሉት ቀበሌዎች ላይ በተፈጸመ ጥቃት ሁለት ሰዎች መሞታቸውን አረጋግጠዋል። የደቡብ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዓለማየው ባውዴም ግጭቱ ዳግም መቀስቀሱን በማረጋገጥ፤ በአሁኑ ወቅትም የፀጥታ ኃይል በመንደሮቹ በመግባት ለማረጋጋት እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ 700 ተጨማሪ ሰዎች ኮሮናቫይረስ ሲገኝባቸው፤ የ13 ሰዎች ህይወት አልፏል።
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 10,024 የላብራቶሪ ምርመራ 700 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስትር ተናግሯል፡፡ባለፋት 24 ሰዓታት የ13 ሰዎች ሕይወት አልፏል፤አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርን 1035 አድርሶታል።በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 655 ሰዎች ማገገማቸው የተነገረ ሲሆን ይህም ከበሽታው የገገሙ ሰዎችን ቁጥር 25,988 አድርሶታል፡፡በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 65,486 ደርሷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 10,024 የላብራቶሪ ምርመራ 700 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስትር ተናግሯል፡፡ባለፋት 24 ሰዓታት የ13 ሰዎች ሕይወት አልፏል፤አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርን 1035 አድርሶታል።በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 655 ሰዎች ማገገማቸው የተነገረ ሲሆን ይህም ከበሽታው የገገሙ ሰዎችን ቁጥር 25,988 አድርሶታል፡፡በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 65,486 ደርሷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ዩኤኢ እና ባህሬን ከእስራኤል ጋር ታሪካዊውን የሰላም ስምምነት በዋይት ሀውስ ተፈራረሙ!
በፍልስጤም ነፃ አውጪ ድርጅት እና እስራኤል መካከል እ.ኤ.አ. በ 1993 የኦስሎ ስምምነት ከተፈረመ ከ 26 ዓመታት በላይ ከዘለቀ ቖይታ በኋላ ዛሬ በዋይት ሃውስ በእስራኤል እና በአረብ ሀገራት መካከል የመጀመሪያው የሰላም ስምምነት ተፈርሟል፡፡በአንድ ወር ጊዜ ዉስጥ እስራኤል ከተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች እና ከባህሬን ጋር ስምምነት እንድትደርስ አሜሪካ የማደራደሩን ስራ አከናውናለች፡፡የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እና የባህሬን መንግሥት በፊርማው ሥነ-ስርዓት ላይ በቅደም ተከተል በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቻቸው ሼክ አብዱላህ ቢን ዛይድ አል ናህያን እና አብዱል ላቲፍ ቢን ራሺድ አል ዛያኒ የተወከሉ ሲሆኑ እስራኤል ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ተወክላለች፡፡
[Al ain]
@YeneTube @FikerAssefa
በፍልስጤም ነፃ አውጪ ድርጅት እና እስራኤል መካከል እ.ኤ.አ. በ 1993 የኦስሎ ስምምነት ከተፈረመ ከ 26 ዓመታት በላይ ከዘለቀ ቖይታ በኋላ ዛሬ በዋይት ሃውስ በእስራኤል እና በአረብ ሀገራት መካከል የመጀመሪያው የሰላም ስምምነት ተፈርሟል፡፡በአንድ ወር ጊዜ ዉስጥ እስራኤል ከተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች እና ከባህሬን ጋር ስምምነት እንድትደርስ አሜሪካ የማደራደሩን ስራ አከናውናለች፡፡የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እና የባህሬን መንግሥት በፊርማው ሥነ-ስርዓት ላይ በቅደም ተከተል በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቻቸው ሼክ አብዱላህ ቢን ዛይድ አል ናህያን እና አብዱል ላቲፍ ቢን ራሺድ አል ዛያኒ የተወከሉ ሲሆኑ እስራኤል ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ተወክላለች፡፡
[Al ain]
@YeneTube @FikerAssefa
በአሜሪካ 99 ሺህ ዶላር የተያዘበት ኢትዮጵያዊ ገንዘቡ ሊወረስ ይችላል ተባለ!
ባለፈው ሳምንት ለጉምሩክ ተቆጣጣሪዎች ሳያሳውቅ ወደ 99 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ከአሜሪካ ሊያስወጣ ሲል የተያዘበት ኢትዮጵያዊ ገንዘቡ ሊወረስ እንደሚችል ተገለጸ።ቢቢሲ በአሜሪካ የአገር ውስጥ ደኅንነት መስሪያ ቤት ስር ከሚገኘው የጉምሩክና የድንበር መቆጣጠሪያ ክፍል ባገኘው መረጃ መሰረት ከኢትዮጵያዊው ላይ የተያዘው ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ በመንግሥት ሊወረስ ይችላል ተብሏል።
የዛሬ ሳምንት ረቡዕ ወደ አዲስ አበባ ሊጓዝ ከነበረው መንገደኛ ላይ ዋሽንግተን በሚገኘው ደለስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአሜሪካ ጉምሩክና ድንበር ተቆጣጣሪዎች የተያዘው ገንዘብ 99 ሺህ ዶላር የሚጠጋ እንደሆነ ተነግሯል።
ቢቢሲ እንዳረጋገጠው ከግለሰቡ ላይ የተያዘው የገንዘብ መጠን 98,762 ዶላር ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ ብር ሲመነዘር ከ3.6 ሚሊዮን ብር በላይ ይሆናል።የጉምሩክ መስሪያ ቤቱ የሕዝብ ግንኙነት ሠራተኛ ስቲቭ ሳፕ ለቢቢሲ በሰጡት የጽሁፍ ምላሽ ላይ እንዳመለከቱት፣ ግለሰቡ ይዞት የነበረው ዶላር የተያዘበት ተጓዦች የያዙትን የገንዘብ መጠን እንዲያሳውቁ የሚጠይቀውን የአገሪቱን ሕግ በመተለላፍ ነው።በተጨማሪም ቢቢሲ ባገኘው መረጃ መሰረት ግለሰቡ በዚሁ ሳቢያ ያልታሰረ ሲሆን የወንጀል ክስ ስላልተመሰረተበትም ማንነቱ እንደማይገለጽ ለማወቅ ተችሏል።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፈው ሳምንት ለጉምሩክ ተቆጣጣሪዎች ሳያሳውቅ ወደ 99 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ከአሜሪካ ሊያስወጣ ሲል የተያዘበት ኢትዮጵያዊ ገንዘቡ ሊወረስ እንደሚችል ተገለጸ።ቢቢሲ በአሜሪካ የአገር ውስጥ ደኅንነት መስሪያ ቤት ስር ከሚገኘው የጉምሩክና የድንበር መቆጣጠሪያ ክፍል ባገኘው መረጃ መሰረት ከኢትዮጵያዊው ላይ የተያዘው ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ በመንግሥት ሊወረስ ይችላል ተብሏል።
የዛሬ ሳምንት ረቡዕ ወደ አዲስ አበባ ሊጓዝ ከነበረው መንገደኛ ላይ ዋሽንግተን በሚገኘው ደለስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአሜሪካ ጉምሩክና ድንበር ተቆጣጣሪዎች የተያዘው ገንዘብ 99 ሺህ ዶላር የሚጠጋ እንደሆነ ተነግሯል።
ቢቢሲ እንዳረጋገጠው ከግለሰቡ ላይ የተያዘው የገንዘብ መጠን 98,762 ዶላር ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ ብር ሲመነዘር ከ3.6 ሚሊዮን ብር በላይ ይሆናል።የጉምሩክ መስሪያ ቤቱ የሕዝብ ግንኙነት ሠራተኛ ስቲቭ ሳፕ ለቢቢሲ በሰጡት የጽሁፍ ምላሽ ላይ እንዳመለከቱት፣ ግለሰቡ ይዞት የነበረው ዶላር የተያዘበት ተጓዦች የያዙትን የገንዘብ መጠን እንዲያሳውቁ የሚጠይቀውን የአገሪቱን ሕግ በመተለላፍ ነው።በተጨማሪም ቢቢሲ ባገኘው መረጃ መሰረት ግለሰቡ በዚሁ ሳቢያ ያልታሰረ ሲሆን የወንጀል ክስ ስላልተመሰረተበትም ማንነቱ እንደማይገለጽ ለማወቅ ተችሏል።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች በኮሮናቫይረስ መያዛቸው ተጠቆመ!
በተለያዩ ሃገራት ከሚያገለግሉትና ለሥልጠና ከመጡት የኢትዮጵያ አምባሳደሮች እና ዲፕሎማቶች የተወሰኑት በኮሮናቫይረስ መያዛቸውን ታማኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምንጮች ለአሜሪካ ድምፅ አረጋግጠዋል።በቫይረሱ መያዛቸው የተነገራቸው አምባሳደሮች ቁጥር ይሄን ያህል ነው ማለት እንደማይቻል የጠቀሱት ምንጮቹ፣ የተነገራቸው በየግል በመሆኑ ድምሩን ማስቀመጥ እንደማይቻል አመልክተዋል። ቀደም ሲል ሲጠቀስ የነበረው ቁጥር ግን 12 እንደነበር ነው የጠቆሙት፤ ቆየት ብለው የወጡ ያልተረጋገጡ መረጃዎች ደግሞ 21 አድርሰውታል::ሁኔታውን ለስልጠና ከመሰባሰባቸው ጋር ማገናኘት እንደማይቻል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምንጮች አክለው ጠቅሰዋል።ከየትኛውም የሕብረተሰብ ክፍል ናሙና ሲወሰድ እንደሚሆነው ሁሉ ከአምባሳደሮቹም መካከል የተወሰኑት ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል ነው ያሉት።ከተለያየ የዓለም ክፍል መጥተው ለተሰባሰቡ ሰዎች ምርመራ ሲደረግ በቫይረሱ የተያዙ መገኘታቸው የሚጠበቅ መሆኑንም ነው ያመለከቱት።አምባሳደሮቹ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት በቢሾፍቱ ከተማ ኩሪፍቱ መዝናኛ በተካሄደው ስልጠና ለመሳተፍ መሆኑንም የቪኦኤ ዘገባ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
በተለያዩ ሃገራት ከሚያገለግሉትና ለሥልጠና ከመጡት የኢትዮጵያ አምባሳደሮች እና ዲፕሎማቶች የተወሰኑት በኮሮናቫይረስ መያዛቸውን ታማኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምንጮች ለአሜሪካ ድምፅ አረጋግጠዋል።በቫይረሱ መያዛቸው የተነገራቸው አምባሳደሮች ቁጥር ይሄን ያህል ነው ማለት እንደማይቻል የጠቀሱት ምንጮቹ፣ የተነገራቸው በየግል በመሆኑ ድምሩን ማስቀመጥ እንደማይቻል አመልክተዋል። ቀደም ሲል ሲጠቀስ የነበረው ቁጥር ግን 12 እንደነበር ነው የጠቆሙት፤ ቆየት ብለው የወጡ ያልተረጋገጡ መረጃዎች ደግሞ 21 አድርሰውታል::ሁኔታውን ለስልጠና ከመሰባሰባቸው ጋር ማገናኘት እንደማይቻል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምንጮች አክለው ጠቅሰዋል።ከየትኛውም የሕብረተሰብ ክፍል ናሙና ሲወሰድ እንደሚሆነው ሁሉ ከአምባሳደሮቹም መካከል የተወሰኑት ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል ነው ያሉት።ከተለያየ የዓለም ክፍል መጥተው ለተሰባሰቡ ሰዎች ምርመራ ሲደረግ በቫይረሱ የተያዙ መገኘታቸው የሚጠበቅ መሆኑንም ነው ያመለከቱት።አምባሳደሮቹ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት በቢሾፍቱ ከተማ ኩሪፍቱ መዝናኛ በተካሄደው ስልጠና ለመሳተፍ መሆኑንም የቪኦኤ ዘገባ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
Audio
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን በገንዘብ ለውጡ ሂደት ላይ ሊፈፀሙ የሚችሉ የመጭበርበር ሙከራዎችን ለመቆጣጠር ከዛሬ ጀምሮ የፖሊስ አባላትን ማሰማራቱን ለሸገር ተናገሯል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የፋይናንስ ደንበኞች ጥበቃ መመሪያ አወጣ!
መመሪያው የፋይናንስ ተጠቃሚዎችን ካልተገባ ችግር የሚጠብቅ ነው ይላል። መመሪያው እንደሚለው የደንበኞች እምነት በፋይናንስ አካታችነት፣ ጤናማ የገንዘብ እንቅስቃሴ፣ የዘርፉን እድገት ለማጎልበት፣ እንዲሁም የፋይናንስ ስርአቱ በስነምግባር የተረጋጋ እንዲሁም በፈጠራ እና ብቃት የታገዘ እንዱሆን አስፈላጉ በመሆኑ መመሪያው ሊወጣ ግድ ሆናል፡፡በፋይናንስ ዘርፍ የመረዳት ደረጃቸው ዝቅተኛ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ ማንኛውም ዜጋ አገልግሎ ላይ መታለል እነዳያጋጥመው ከፍተኛ ሃላፊነት ለሁሉም የፋይናንስ ተቋመት ይሰጣል አዲሱ መመሪያ፡፡በከፍተኛ የለውጥ ጉዞ ላይ የሚገኘው ብሄራዊ ባንክ ባለፉት ሁለት አመታት 47 መመሪያዎችን ያወጣ ሲሆን አብዛኞቹ አዳዲስ መሆናቸውን የባንኩ ገዥ ይናገር ደሴ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
[Capital]
@YeneTube @FikerAssefa
መመሪያው የፋይናንስ ተጠቃሚዎችን ካልተገባ ችግር የሚጠብቅ ነው ይላል። መመሪያው እንደሚለው የደንበኞች እምነት በፋይናንስ አካታችነት፣ ጤናማ የገንዘብ እንቅስቃሴ፣ የዘርፉን እድገት ለማጎልበት፣ እንዲሁም የፋይናንስ ስርአቱ በስነምግባር የተረጋጋ እንዲሁም በፈጠራ እና ብቃት የታገዘ እንዱሆን አስፈላጉ በመሆኑ መመሪያው ሊወጣ ግድ ሆናል፡፡በፋይናንስ ዘርፍ የመረዳት ደረጃቸው ዝቅተኛ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ ማንኛውም ዜጋ አገልግሎ ላይ መታለል እነዳያጋጥመው ከፍተኛ ሃላፊነት ለሁሉም የፋይናንስ ተቋመት ይሰጣል አዲሱ መመሪያ፡፡በከፍተኛ የለውጥ ጉዞ ላይ የሚገኘው ብሄራዊ ባንክ ባለፉት ሁለት አመታት 47 መመሪያዎችን ያወጣ ሲሆን አብዛኞቹ አዳዲስ መሆናቸውን የባንኩ ገዥ ይናገር ደሴ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
[Capital]
@YeneTube @FikerAssefa
ፓርላማው ለመጪው ዓርብ አስቸኳይ ስብሰባ ጠራ!
ከሰኔ 30 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ለዓመታዊ እረፍት የተበተነው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ለመጪው ዓርብ መስከረም 8 ቀን 2013 ዓ.ም. አስቸኳይ ስብሰባ ጠራ።ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው የሕዝብ ተመራጮቹ ለአስቸኳይ ስብሰባ ተጠርተዋል፡፡ የተጠራው አስቸኳይ ስብሰባም ምክር ቤቱ የኮሮና ወረርሽኝ ከተከሰተ ጀምሮ ስብሰባውን በሚያካሂድበት የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አዳራሽ እንደሚሆን ይጠቁማል።ሪፖርተር ያነጋገራቸው የምክር ቤቱ ምንጮች ለአስቸኳይ ስብሰባው ከሚቀርቡ አጀንዳዎች መካከል፣ እስካሁን እንደሚታወቀው ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) የሚያቀርቡትን የካቢኔ አባላት ሹመት መርምሮ ማፅደቅ እንደሆነ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ (ዶ/ር) ለምክር ቤቱ ከሚያቀርቧቸው ተሿሚዎች መካከል ሦስቱ በምክር ቤቱ ሳይሾሙ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጧቸው የሹመት ደብዳቤ ብቻ ቢሮ ተረክበው እያገለገሉ የሚገኙት ባለሥልጣናት ናቸው።ከእነዚህም መካከል ከጥቂት ሳምንታት በፊት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባነት ተነስተው የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሹመት ደብዳቤ የተሰጣቸው ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) ይገኙበታል።በተመሳሳይ ወቅት ከማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትርነት ተነስተው የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር እንዲሆኑ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሹመት ደብዳቤ የተሰጣቸው አቶ ሳሙኤል ሁርካቶና የመከላከያ ሚኒስትር የነበሩትን አቶ ለማ መገርሳ በመተካት የተሾሙት ቀንአ ያደታ (ዶ/ር) ናቸው።
[ሪፖርተር]
@YeneTube @FikerAssefa
ከሰኔ 30 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ለዓመታዊ እረፍት የተበተነው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ለመጪው ዓርብ መስከረም 8 ቀን 2013 ዓ.ም. አስቸኳይ ስብሰባ ጠራ።ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው የሕዝብ ተመራጮቹ ለአስቸኳይ ስብሰባ ተጠርተዋል፡፡ የተጠራው አስቸኳይ ስብሰባም ምክር ቤቱ የኮሮና ወረርሽኝ ከተከሰተ ጀምሮ ስብሰባውን በሚያካሂድበት የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አዳራሽ እንደሚሆን ይጠቁማል።ሪፖርተር ያነጋገራቸው የምክር ቤቱ ምንጮች ለአስቸኳይ ስብሰባው ከሚቀርቡ አጀንዳዎች መካከል፣ እስካሁን እንደሚታወቀው ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) የሚያቀርቡትን የካቢኔ አባላት ሹመት መርምሮ ማፅደቅ እንደሆነ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ (ዶ/ር) ለምክር ቤቱ ከሚያቀርቧቸው ተሿሚዎች መካከል ሦስቱ በምክር ቤቱ ሳይሾሙ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጧቸው የሹመት ደብዳቤ ብቻ ቢሮ ተረክበው እያገለገሉ የሚገኙት ባለሥልጣናት ናቸው።ከእነዚህም መካከል ከጥቂት ሳምንታት በፊት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባነት ተነስተው የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሹመት ደብዳቤ የተሰጣቸው ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) ይገኙበታል።በተመሳሳይ ወቅት ከማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትርነት ተነስተው የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር እንዲሆኑ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሹመት ደብዳቤ የተሰጣቸው አቶ ሳሙኤል ሁርካቶና የመከላከያ ሚኒስትር የነበሩትን አቶ ለማ መገርሳ በመተካት የተሾሙት ቀንአ ያደታ (ዶ/ር) ናቸው።
[ሪፖርተር]
@YeneTube @FikerAssefa
በሳውዲ እስር ቤቶች የሚገኙ ስደተኞች ሁኔታ አሳሳቢ ነው ሲል ዓለም አቀፉ የስደትድርጅት ገለፀ።
ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት ከጀኔቫ ትናንት ባወጣው ዘገባ በሳዑዲ አረቢያ መንግሥት ባለሥልጣናት የታሰሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ሰብዓዊ ሁኔታ እያሽቆለቆለ መምጣቱን አሳስቧል።
በቅርቡ በተሰራጨው ተንቀሳቃሽ ምስል የሰዎች መጨናነቅ ፣ለሰዎች የሚያስፈልጉ መሠረታዊ ዕቃዎች እጥረት እና የጤና እና የንፅህና አጠባበቅ ሁኔታዎችን እንዲሁም የእርዳታ ልመናዎች ድርጅቱ መመልከቱን ጠቅሷል።ስደተኞች በተለይም ለእስር የተዳረጉት ከሚያጋጥማቸው መድልዎ ፣ የውጭ ዜጎች ጥላቻ ፣ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር እና የጉልበት ብዝበዛ አደጋ በተጨማሪ ከጎርጎሪያኑ 2020 መጀመሪያ ጀምሮ በድንገት ለተከሰተው የኮቪድ -19 በሽታ ተጋላጭነታቸውም ጨምሯል ሲል አይ ኦ ኤም ገልጿል።
ስለሆነም ሀገራት ምንም ይሁን ምን በሁሉም ለህዝብ የጤና በሚሰጡ ምላሾች ስደተኞችን ማካተታቸውን እንዲያረጋግጡ ጥሪ አቅርቧል፡፡በእንደዚህ ያሉ አስቸጋሪ ሁኔታዎች የስደተኞችን ደህንነት ለማረጋገጥ የአስቸኳይ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች ሰብዓዊ እርዳታ እንዲያገኙ ድርጅቱ ተማፅኗል፡፡ይህ ድጋፍ ከመጡበት ሀገር የሚደረግን ዘላቂ የመልሶ ማቋቋምንና በፈቃደኝነት ወደ ሀገራቸው የመመለስ አማራጮችን እንደሚያጠቃልል አመልክቷል።ከዚህ በተጨማሪ ስደተኞችን በግዳጅ መመለስና በኮቪድ-19 ሰበብ በአንድ አካባቢ ማጎር እንዲገታ ዓለም አቀፉ የስደት ድርጅትና እና የተባበሩት መንግስታት የስደት ትስስር ጥሪ አቅርበዋል። ከዚህ ይልቅ ለህፃናት፣ ለቤተሰብ አባላትና ተጋላጭ ለሆኑ ስደተኞች ቅድሚያ በመስጠት ማህበረሰብን መሠረት ያደረጉ አማራጮችን እንዲጠቀሙ መክረዋል።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት ከጀኔቫ ትናንት ባወጣው ዘገባ በሳዑዲ አረቢያ መንግሥት ባለሥልጣናት የታሰሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ሰብዓዊ ሁኔታ እያሽቆለቆለ መምጣቱን አሳስቧል።
በቅርቡ በተሰራጨው ተንቀሳቃሽ ምስል የሰዎች መጨናነቅ ፣ለሰዎች የሚያስፈልጉ መሠረታዊ ዕቃዎች እጥረት እና የጤና እና የንፅህና አጠባበቅ ሁኔታዎችን እንዲሁም የእርዳታ ልመናዎች ድርጅቱ መመልከቱን ጠቅሷል።ስደተኞች በተለይም ለእስር የተዳረጉት ከሚያጋጥማቸው መድልዎ ፣ የውጭ ዜጎች ጥላቻ ፣ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር እና የጉልበት ብዝበዛ አደጋ በተጨማሪ ከጎርጎሪያኑ 2020 መጀመሪያ ጀምሮ በድንገት ለተከሰተው የኮቪድ -19 በሽታ ተጋላጭነታቸውም ጨምሯል ሲል አይ ኦ ኤም ገልጿል።
ስለሆነም ሀገራት ምንም ይሁን ምን በሁሉም ለህዝብ የጤና በሚሰጡ ምላሾች ስደተኞችን ማካተታቸውን እንዲያረጋግጡ ጥሪ አቅርቧል፡፡በእንደዚህ ያሉ አስቸጋሪ ሁኔታዎች የስደተኞችን ደህንነት ለማረጋገጥ የአስቸኳይ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች ሰብዓዊ እርዳታ እንዲያገኙ ድርጅቱ ተማፅኗል፡፡ይህ ድጋፍ ከመጡበት ሀገር የሚደረግን ዘላቂ የመልሶ ማቋቋምንና በፈቃደኝነት ወደ ሀገራቸው የመመለስ አማራጮችን እንደሚያጠቃልል አመልክቷል።ከዚህ በተጨማሪ ስደተኞችን በግዳጅ መመለስና በኮቪድ-19 ሰበብ በአንድ አካባቢ ማጎር እንዲገታ ዓለም አቀፉ የስደት ድርጅትና እና የተባበሩት መንግስታት የስደት ትስስር ጥሪ አቅርበዋል። ከዚህ ይልቅ ለህፃናት፣ ለቤተሰብ አባላትና ተጋላጭ ለሆኑ ስደተኞች ቅድሚያ በመስጠት ማህበረሰብን መሠረት ያደረጉ አማራጮችን እንዲጠቀሙ መክረዋል።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
በመተከል ዞን ከታጣቂ ሀይሎች ጥቃት እራሳቸውን ለመጠበቅ በሚል በጫካ ውስጥ ተሸሽገው የነበሩ ከ300 በላይ ዜጎች ወደ ቄያቸው ተመለሱ፡፡
በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ በታጣቂ ሀይሎች ከተሰነዘረው ጥቃት ሸሽተው በጫካ ውስጥ ተደብቀው የነበሩ 12 የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ ከ 310 በላይ ንፁሀን ዜጎች በፌደራልና በክልል የፀጥታ ሀይሎች በተሰራ ኦፕሬሽን ወደ ቄያቸው መመለሳቸው ተገለፀ፡፡በቅርቡ ጳጉሜ 2 ቀን 2012 ዓ.ም በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ ኤርታል ቀበሌ ላይ በታጣቂ ሀይሎች በተሰነዘረ ጥቃት የአካባቢው ሰላማዊ ሰዎችን እና በመንግስት መዋቅር ውስጥ ያሉ ባለሙያዎች ወደ ጫካ ተበታትነው እንደነበረ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል መከላከል ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ነጋ ጃራ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡
ኮሚሽነሩ እንዳሉት 12 የጤና ባለሙያዎች እና የልማት ጣቢያ ሰራተኞች በወቅቱ ከተፈጠረው ጥቃት በመሸሽ በጫካ ውስጥ እራሳቸውን ደብቀው መቆየታቸውን አንስተዋል፡፡ሆኖም በፌደራልና በክልል የፀጥታ ሀይሎች በተሰራ ኦፕሬሽን በህይወት ተገኝተው ወደ ቀበሌያቸው እንዲመለሱና ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲመሩ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡ከዚህ ባሻገር 300 የሚሆን ንፁሀን የማህበረሰብ ክፍሎች በተመሳሳይ ከጥቃቱ ሸሽተው በቀበሌው በቅርብ እርቀት ወደሚገኝ ጫካ እራሳቸውን የሸሸጉ መሆኑን ገልፀዋል ም/ል ኮሚሽነር ነጋ።እነዚህንም ዜጎች ወደ ቄያቸው መመለስ መቻላቸውን እና ሰላማዊ ህይወታቸውን እንዲመሩ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡ታጣቂዎቹን የመደምሰስ ስራው በመካሄድ ላይ ነው ያሉት ኮሚሽነር ነጋ በጫካ እራሳቸውን የደበቁ ንፁሀን ዜጎችን ወደ ቄያቸው የመመለስ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል በማለት ነግረውናል፡፡
ሙሉ በሙሉ የኦፕሬሽን ስራው እንደተጠናቀቀ በተደራጀ መልኩ ትክክለኛ መረጃዎችን ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግም አስታውቀዋል።በመተከል ዞን ወንበራ ወረዳ የተፈጠረውን ተመሳሳይ ጥቃት ለመቀልበስ የፌደራልና የክልል የፀጥታ ሀይሎች ገብተው የተቀናጀ የወንጀል መከላከል ስራ ተጀምሯል ብለዋል፡፡ሙሉ የኦፕሬሽን ስራው እንደተጠናቀቀ መረጃው ለህዝብ ይፋ ይሆናል ብለዋል፡፡ በመተከል ዞን ቡለን እና ወንበራ ወረዳ ላይ የፀጥታ ችግር ከመከሰቱ በፊት በጉባ ወረዳም እነዚህ የታጠቁ ሀይሎች ገብተው በንፁሀን ዜጎች ላይ ጥቃት መሰንዘር የጀምረው እንደነበር ይታወቃል፡፡
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ በታጣቂ ሀይሎች ከተሰነዘረው ጥቃት ሸሽተው በጫካ ውስጥ ተደብቀው የነበሩ 12 የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ ከ 310 በላይ ንፁሀን ዜጎች በፌደራልና በክልል የፀጥታ ሀይሎች በተሰራ ኦፕሬሽን ወደ ቄያቸው መመለሳቸው ተገለፀ፡፡በቅርቡ ጳጉሜ 2 ቀን 2012 ዓ.ም በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ ኤርታል ቀበሌ ላይ በታጣቂ ሀይሎች በተሰነዘረ ጥቃት የአካባቢው ሰላማዊ ሰዎችን እና በመንግስት መዋቅር ውስጥ ያሉ ባለሙያዎች ወደ ጫካ ተበታትነው እንደነበረ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል መከላከል ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ነጋ ጃራ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡
ኮሚሽነሩ እንዳሉት 12 የጤና ባለሙያዎች እና የልማት ጣቢያ ሰራተኞች በወቅቱ ከተፈጠረው ጥቃት በመሸሽ በጫካ ውስጥ እራሳቸውን ደብቀው መቆየታቸውን አንስተዋል፡፡ሆኖም በፌደራልና በክልል የፀጥታ ሀይሎች በተሰራ ኦፕሬሽን በህይወት ተገኝተው ወደ ቀበሌያቸው እንዲመለሱና ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲመሩ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡ከዚህ ባሻገር 300 የሚሆን ንፁሀን የማህበረሰብ ክፍሎች በተመሳሳይ ከጥቃቱ ሸሽተው በቀበሌው በቅርብ እርቀት ወደሚገኝ ጫካ እራሳቸውን የሸሸጉ መሆኑን ገልፀዋል ም/ል ኮሚሽነር ነጋ።እነዚህንም ዜጎች ወደ ቄያቸው መመለስ መቻላቸውን እና ሰላማዊ ህይወታቸውን እንዲመሩ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡ታጣቂዎቹን የመደምሰስ ስራው በመካሄድ ላይ ነው ያሉት ኮሚሽነር ነጋ በጫካ እራሳቸውን የደበቁ ንፁሀን ዜጎችን ወደ ቄያቸው የመመለስ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል በማለት ነግረውናል፡፡
ሙሉ በሙሉ የኦፕሬሽን ስራው እንደተጠናቀቀ በተደራጀ መልኩ ትክክለኛ መረጃዎችን ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግም አስታውቀዋል።በመተከል ዞን ወንበራ ወረዳ የተፈጠረውን ተመሳሳይ ጥቃት ለመቀልበስ የፌደራልና የክልል የፀጥታ ሀይሎች ገብተው የተቀናጀ የወንጀል መከላከል ስራ ተጀምሯል ብለዋል፡፡ሙሉ የኦፕሬሽን ስራው እንደተጠናቀቀ መረጃው ለህዝብ ይፋ ይሆናል ብለዋል፡፡ በመተከል ዞን ቡለን እና ወንበራ ወረዳ ላይ የፀጥታ ችግር ከመከሰቱ በፊት በጉባ ወረዳም እነዚህ የታጠቁ ሀይሎች ገብተው በንፁሀን ዜጎች ላይ ጥቃት መሰንዘር የጀምረው እንደነበር ይታወቃል፡፡
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa