የአምባሳደር ፓርክ በቅርቡ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል።
ኢ/ር ታከለ ኡማ እድሳት ሲደረግለት የቆየውን አምባሳደር ፓርክ ተመልክተዋል።0.4 ሄክታር ላይ ያረፈው ፓርኩ አዳዲስ ዲዛይኖችን አካቶና ለተለያዩ አገልግሎቶች በሚመች መልኩ ነው የታደሰው።ለነዋሪዎችም ተጨማሪ የመዝናኛ ቦታ አማራጭ የሚፈጥር ይሆናል።የከተማ አስተዳደሩ በተለይን አረንጓዴ ስፍራዎችን የማልማትና ነባር ፓርኮችን ደረጃውን በጠበቀ መልኩና መሰረተልማቶችን ባሟላ መልኩ እድሳት እያደረገላቸው ይገኛል።
Via Mayor office
@YeneTube @FikerAssefa
ኢ/ር ታከለ ኡማ እድሳት ሲደረግለት የቆየውን አምባሳደር ፓርክ ተመልክተዋል።0.4 ሄክታር ላይ ያረፈው ፓርኩ አዳዲስ ዲዛይኖችን አካቶና ለተለያዩ አገልግሎቶች በሚመች መልኩ ነው የታደሰው።ለነዋሪዎችም ተጨማሪ የመዝናኛ ቦታ አማራጭ የሚፈጥር ይሆናል።የከተማ አስተዳደሩ በተለይን አረንጓዴ ስፍራዎችን የማልማትና ነባር ፓርኮችን ደረጃውን በጠበቀ መልኩና መሰረተልማቶችን ባሟላ መልኩ እድሳት እያደረገላቸው ይገኛል።
Via Mayor office
@YeneTube @FikerAssefa
#አብን #GERD
ታላቁ የህዳሴ ግድብ የዓለም አቀፍ ድጋፍና እርዳታን ለማግኘት ማስያዣ መሆን እንደሌለበት አብን አስታወቀ።
የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አብን የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ጣሂር መሃመድ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት ግብጽ እስካሁንም የ1929ኙና የ1959ኙ ኢትዮጵያን ያገለለዉ ስምምነት እንዲመለስ ነዉ የምትፈልገዉ ያሉ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት ጠንካራ አቋም ሊኖረዉ ይገባል ብለዋል።
ይህ የሉዓላዊነት ጉዳይ በመሆኑ መንግስት ከህዝቡ ጋር መምከርና ቀደም ሲል በነበረበት አቋም ጸንቶ ነዉ መቀጠል ያለበት ብለዋል፡፡
ንቅናቄዉ አሁን ላይ በተለይም ከአረቡ ዓለም ጋር መስመር የሳቱ የሚመስሉ ግንኙነቶች አሉ ብሎ እንደሚያምን ገልጾ በፖለቲካ ዓለም ዉስጥ ፍጹም ታማኝ ወዳጅ ባለመኖሩ ግንኙነታችን ግልጽ መስመር ሊኖረዉ ይገባል ብሏል፡፡
Via :- Ethio FM
@YeneTube @Fikerassefa
ታላቁ የህዳሴ ግድብ የዓለም አቀፍ ድጋፍና እርዳታን ለማግኘት ማስያዣ መሆን እንደሌለበት አብን አስታወቀ።
የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አብን የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ጣሂር መሃመድ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት ግብጽ እስካሁንም የ1929ኙና የ1959ኙ ኢትዮጵያን ያገለለዉ ስምምነት እንዲመለስ ነዉ የምትፈልገዉ ያሉ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት ጠንካራ አቋም ሊኖረዉ ይገባል ብለዋል።
ይህ የሉዓላዊነት ጉዳይ በመሆኑ መንግስት ከህዝቡ ጋር መምከርና ቀደም ሲል በነበረበት አቋም ጸንቶ ነዉ መቀጠል ያለበት ብለዋል፡፡
ንቅናቄዉ አሁን ላይ በተለይም ከአረቡ ዓለም ጋር መስመር የሳቱ የሚመስሉ ግንኙነቶች አሉ ብሎ እንደሚያምን ገልጾ በፖለቲካ ዓለም ዉስጥ ፍጹም ታማኝ ወዳጅ ባለመኖሩ ግንኙነታችን ግልጽ መስመር ሊኖረዉ ይገባል ብሏል፡፡
Via :- Ethio FM
@YeneTube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ምኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው የአሜሪካ ግምዣ ቤት በታላቁ የኅዳሴ ግድብ ድርድር ላይ ያወጣው መግለጫ "ተቀባይነት የሌለው እና እጅጉን ለአንድ ወገን ያደላ ነው" ሲሉ ወቀሱ።
Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
#አሳዛኝ_ዜና የማስታወቂያ ባለሞያው ጋሽ ውብሸት ወርቅ አለማው ከዚህ አለም በሞት እንደተለዩ ethio FM(ታዲየስ አዲስ) ዘግቧል።
የኔቲዩብ ለአድናቂዎቻቸው እንዲህም ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን እንመኛለኝ።
@YeneTube @Fikerassefa
የኔቲዩብ ለአድናቂዎቻቸው እንዲህም ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን እንመኛለኝ።
@YeneTube @Fikerassefa
አንጋፋው የማስታወቂያ ባለሙያ ጋሽ ውብሸት ወርቃለማሁ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ ።
አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያን በተለይም በከተሞች ውስጥ ጋሽ ውብሸት ወርቅ አለማው ሲባል በድምጻቸው ይለያቸዋል የተወለዱት እ.ኤ.አ. በ 1938 ዓ.ም. ማfድ ያፊት በተባለ መንዝ አካባቢ ነበር ይህ ጀግና የቤተሰብ ዘጠነኛ ልጅ ነው የሁለት ልጆች አባት ሲሆን ከልጆቹ አንዱ ፕሮፌሰር ነው ሌላኛው ደግሞ የፋይናንስ ባለሙያ እና ባለሀብት ነው ውብሸት ከኔዘርላንድ በፈጠራ ማስታወቂያ ዲፕሎማ አላቸው በተጨማሪም ከአሜሪካ የባዮግራፊካል ተቋም በማስታወቂያ እና በሕዝብ ግንኙነት ውስጥ ዲፕሎማ አግኝተዋል ጋሽ ውብሸት ፣ አገሩን ከምንም ነገር በላይ ይወዳል በበጎ አድራጎት ስራቸው እና በደም ባንክ አምባሳደርታቸው ይታወቃሉ ከዚያ በላይ ፣ ለሰብአዊ ስራዎች ከ 155,000,000 ብር በላይ ለማሰብሰብ ችለዋል፡፡
የወሎ ህዝብ በድርቅ በተጠቃበት እና የደቡብ ብሔሮች ፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በጎርፍ በተመታበት ወቅት ጋሽ ውብሸት የተለያዩ የገንዘብ ማሰባሰብ እንቅስቃሴዎችን በማደራጀት የራሳቸውን ሃላፊነት ተወጥተዋል በተጨማሪም ከጥቂት ዓመታት በፊት ድሬዳዋ ከተማ በጎርፍ በተጥለቀለቀች ጊዜ ተጎጂዎችን መልሶ የማቋቋም ዓላማ ካለው የሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር በመሆን በቴሌኮን በማዘጋጀት ረገድ ሚና ተጫውተዋል ተጎጂዎችን በተቻለ መጠን በፍጥነት ወደነበሩበት ለመመለስ ትልቅ አስተዋጻኦም አድርገዋል ጋሽ ውብሸት ከዚህ በተጨማሪም የብሄራዊ ድም ባንክ አምባሳደርም በመሆን አገልግለዋል ጋሽ ውብሸት በተወለዱ በ74 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።
የኔ ትዩብ ለቤተሰቦቻቸው ለስራ ባልደረቦቻቸው እንዲሁም ለአድናቂዎቻቸው መጽናናትን ይመኛል::
ምንጭ:- AllAfrica.com ✏️ YeneTube
@Yenetube @Fikerassefa
አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያን በተለይም በከተሞች ውስጥ ጋሽ ውብሸት ወርቅ አለማው ሲባል በድምጻቸው ይለያቸዋል የተወለዱት እ.ኤ.አ. በ 1938 ዓ.ም. ማfድ ያፊት በተባለ መንዝ አካባቢ ነበር ይህ ጀግና የቤተሰብ ዘጠነኛ ልጅ ነው የሁለት ልጆች አባት ሲሆን ከልጆቹ አንዱ ፕሮፌሰር ነው ሌላኛው ደግሞ የፋይናንስ ባለሙያ እና ባለሀብት ነው ውብሸት ከኔዘርላንድ በፈጠራ ማስታወቂያ ዲፕሎማ አላቸው በተጨማሪም ከአሜሪካ የባዮግራፊካል ተቋም በማስታወቂያ እና በሕዝብ ግንኙነት ውስጥ ዲፕሎማ አግኝተዋል ጋሽ ውብሸት ፣ አገሩን ከምንም ነገር በላይ ይወዳል በበጎ አድራጎት ስራቸው እና በደም ባንክ አምባሳደርታቸው ይታወቃሉ ከዚያ በላይ ፣ ለሰብአዊ ስራዎች ከ 155,000,000 ብር በላይ ለማሰብሰብ ችለዋል፡፡
የወሎ ህዝብ በድርቅ በተጠቃበት እና የደቡብ ብሔሮች ፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በጎርፍ በተመታበት ወቅት ጋሽ ውብሸት የተለያዩ የገንዘብ ማሰባሰብ እንቅስቃሴዎችን በማደራጀት የራሳቸውን ሃላፊነት ተወጥተዋል በተጨማሪም ከጥቂት ዓመታት በፊት ድሬዳዋ ከተማ በጎርፍ በተጥለቀለቀች ጊዜ ተጎጂዎችን መልሶ የማቋቋም ዓላማ ካለው የሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር በመሆን በቴሌኮን በማዘጋጀት ረገድ ሚና ተጫውተዋል ተጎጂዎችን በተቻለ መጠን በፍጥነት ወደነበሩበት ለመመለስ ትልቅ አስተዋጻኦም አድርገዋል ጋሽ ውብሸት ከዚህ በተጨማሪም የብሄራዊ ድም ባንክ አምባሳደርም በመሆን አገልግለዋል ጋሽ ውብሸት በተወለዱ በ74 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።
የኔ ትዩብ ለቤተሰቦቻቸው ለስራ ባልደረቦቻቸው እንዲሁም ለአድናቂዎቻቸው መጽናናትን ይመኛል::
ምንጭ:- AllAfrica.com ✏️ YeneTube
@Yenetube @Fikerassefa
#Congratulations
የዲላ ዩኒቨርሲቲ በአርክቴክቸር ትምህርት ክፍል በመደበኛው ፕሮግራም ለ5 ዓመት ከ6 ወር ሲያስተምራቸው የነበሩትን 55 ተማሪዎች በትናንትናው ዕለት በዋናው ግቢ አስመርቋል።
ተመራቂዎች እንኳን ደስ አላችሁ!
@Yenetube @Fikerassefa
የዲላ ዩኒቨርሲቲ በአርክቴክቸር ትምህርት ክፍል በመደበኛው ፕሮግራም ለ5 ዓመት ከ6 ወር ሲያስተምራቸው የነበሩትን 55 ተማሪዎች በትናንትናው ዕለት በዋናው ግቢ አስመርቋል።
ተመራቂዎች እንኳን ደስ አላችሁ!
@Yenetube @Fikerassefa
ካሌብ በህይወት እያለ አንድ ቀን እኔ ከሞትኩ ኢትዮጵያ ወስዳችሁ #ቅበሩኝ #በኢትዮጵያ መሬት መቀበር ነው የምፈልገው እያለ ብዙ ጊዜ ሲናገር ስለነበረ ቀብሩ ከነገ ወዲያ ሰኞ እለት የካቲት 23, 2012 ከቀኑ 8:30 በአዲስ አበባ ጉለሌ በጴጥሮስ ወ ጳውሎስ ይፈፀማል ውድ ኢትዮጵያውያን በቦታው ተገኝታችሁ ወንድማችን ካሌብን በክብር ትሽኙ ዘንድ ትጠየቃላችሁ።
ይህንን መልክት ላልሰሙ አስሙልን ብለውናል
#Share
@YeneTube @Fikerassefa
ይህንን መልክት ላልሰሙ አስሙልን ብለውናል
#Share
@YeneTube @Fikerassefa
‹‹ምናልባትም በትዕግስት ለዘመናት የጠበቁት ኢትዮጵያውያን ከዓባይ ወንዝ የትዕግስታቸውን ጥፍጥና የሚቀምሱበት ጊዜ ሩቅ አይሆን ይሆናል፡፡›› ጋዜጠኛ ሙሐመድ ቫል
በዓባይ ወንዝ ዙሪያ ዛሬን በትናንት ሚዛን እየለኩ ኢትዮጵያን ለመሞገት የሚሞክሩ ሁሉ ሁለት የዘነጓቸው ነጥቦች አሉ፡፡ የመጀመሪያው ጉዳይ በኢትዮጵያ ዓይናቸውን በእንጨት ጭስ እያጨናበሱ እና እያለቀሱ በትዕግስት የሚጠብቁ እናቶች መኖራቸውን መዘንጋታቸው ነው፡፡ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ የምትገነባው ግድብ ቅንጦት ሳይሆን መሠረታዊ ፍላጎት ነው፡፡ በዚህ በሰለጠነ ዘመን ዳገት ወጥተው እና ቁልቁለትን ወርደው ሕይወታቸውን ለአደጋ እያጋለጡ ጭራሮ ለቅመው እንጨት ሰብረው በእሳት ጭስ እየተፈተኑ ‹‹እራት እና መብራት›› የሚሹ እናቶች ቁጥር የትየለሌ ነው፡፡
ሁለተኛው እና ከዓባይ ወንዝ ተጠቃሚነት ጋር ተያይዞ ይህ ትውልድ ለአፍታ ሊደራደርበት የማይፈልገው ጉዳይ ደግሞ ግድቡ የእያንዳንዱን ድሀ ኢትዮጵያዊ ኪስ እና መቀነት ነክቷል፡፡ ግድቡ በብድር ወይም በምዕራባውያን ልግስና የሚገነባ ሳይሆን ነገን ተስፋ አድርጎ ከዛሬ ጠኔ ጋር ትግል በገጠመ ድሀ ኢትዮጵያዊ አንጡራ ሀብት ነው፡፡ ከወታደር እስከ አርሶ አደር፣ ከተማሪ እስከ አስተማሪ፣ ከቀን ሠራተኛ እስከ ጡረተኛ፣ ከሕጻናት እስከ አዛውንት፣ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ዛሬውን እየቀጣ ነገን የተሻለ ለማድረግ አዋጥቷል፤ ኖሮት ሳይሆን ሳይኖረው አምስት አስር ተሰብስቦ እየተገነባ ያለ ግድብ መሆኑን ማስታወስ ቀርቶ ማሰብ የሚፈልጉ አይመስሉም፤ የወቅቱ አደራዳሪዎች ወይም ሞጋቾች፡፡
ከሰሞኑ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ በምትገነባው ግድብ አካባቢ የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተዘዋውሮ የተመለከተው የአልጀዚራው ጋዜጠኛ ሙሐመድ ቫል የአገሬዎቹን ኑሮ ተመልክቶ ‹‹አሁንም ኋላቀር በሆነ የኑሮ ዘይቤ ውስጥ የሚኖሩ›› ሲል ይገልፃቸዋል፡፡ ንጹሕ የመጠጥ ውኃ፣ የኤሌክትሪክ አገልግሎት እና ምቹ የመኖሪያ ቤት የሌላቸው ሕዝቦች፤ ከዚህ አስከፊ የኑሮ ምስቅልቅል ለመውጣት ግድቡን በትዕግስት ይጠብቃሉ፡፡ የትዕግስታቸውን ልክና ወሰንም ‹‹ከአዕምሮ በላይ›› ሲል ይገልጸዋል፡፡
የግድቡን አጠቃላይ ሂደት የመጎብኘት ዕድል ያገኘው ጋዜጠኛ ሙሐመድ ቫል የነዋሪዎቹን ትዕግስት ከግድቡ ሠራተኞች የቀን ከሌት ጥረት ጋር አስናስሎም አንድ ፕሮጀክት ለመጨረስ የሚተጉ ሳይሆን ወገኖቻቸውን ከጨለማ ዘመን ለማሻገር የሚታትሩ መሲሆች ያደርጋቸዋል፡፡ ግድቡ ሦስት የተለያዩ የግንባታ ክፍሎች አሉት፡፡ የእያንዳንዱ ግድብ አፈፃፀም የተለያየ ቢሆንም አጠቃላይ ግንባታው 71 ነጥብ 2 በመቶ መጠናቀቁን ያትታል ጋዜጠኛው፡፡
ግድቡ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቆ በውኃ ሲሞላ ስድስት ሺህ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም አለው፡፡ ጋዜጠኛ ሙሐመድ ቫል በዘገባው እንደሚለው ይህም ኢትዮጵያ የእነዚያን ታጋሽ ዜጎቿን የኤሌክትሪክ ፍላጎት ከማሟላት ባለፈ ለሰባት የአፍሪካ እና ምዕራብ አውሮፓ ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በሽያጭ የማቅረብ አቅም ይኖራታል፡፡ “ከኃይል አቅርቦት ባለፈም የሀገሪቱ መፃኢ ምጣኔ ሀብታዊ ዕድገት ተስፋ ከተጣለባቸው ምሰሶዎች አንዱ ነው” ሲል ዘርፈ ብዙ አስፈላጊነቱን ያትታል ሙሐመድ ቫል በዘገባው።
ከዓባይ ወንዝ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት አንዷ የሆነችው ሱዳን ኢትዮጵያ የምትገነባው ግድብ የሚያደርስባት ጉዳት አለመኖሩ በባለሙያዎች መረጋገጡን ያወሳል፡፡ ነገር ግን አቋሟ ወጥ አለመሆኑን የሚናገረው የአልጀዚራው ጋዜጠኛ ግብጽን ግን አሁንም የዓባይ ወንዝ ታሪካዊ እና ብቸኛ ተጠቃሚ አድርጋ እንደምትመለከት ያትታል፡፡ ግብጽ ሄሮዳተስ ‹‹የዓባይ ስጦታ ናት›› ትርክት አልወጣችም የሚለው ሙሐመድ ቫል አሁን እንኳን ዘመንን የዋጀ ምክንያት ማቅረብ እንደተሳናት ያብራራል፡፡የግድቡ አጠቃላይ ቅርፅ መልክ እየያዘ ባለበት በዚህ ወቅት ከሚቀጥለው ክረምት ጀምሮ በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ውስጥ 74 ቢሊዮን ኪዩ ቢክ ሜትር ውኃ በግድቡ ለመሙላት ኢትዮጵያ ማቀዷን ዘገባው ያትታል፡፡
አሜሪካ እና የዓለም ባንክ ከታዛቢነት ወደ አደራዳሪነት በተሸጋገሩበት የሰሞኑ የዋሽንግተን ውይይት የግብጽ አንዱ መደራደሪያ የውኃው ሙሌት ጊዜ ከሦስት ዓመታት ወደ ሰባት ዓመታት ከፍ ይበል የሚል እንደሆነ ያወሳል፡፡በዚህ ሁሉ የነገሮች ዑደት ውስጥ ግን ይላል ጋዜጠኛው ለዘመናት ከማኅፀኗ እየፈሰሰ የሚነጉደው የዓባይ ወንዝ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ጠብታው የሚገታበት ጊዜ የተቃረበ ይመስላል፡፡ ዝነኛው የዓባይ ወንዝ ለሚሊዮን ዓመታት ከአብራኳ ለምታፈልቀው ሀገረ ኢትዮጵያ ሊገብር የተገደደበት ጊዜ መቃረቡ እውን ይመስላል፡፡ “ምናልባት በትዕግስት ለዘመናት የጠበቁት ኢትዮጵያውያን ከዓባይ ወንዝ የትዕግስታቸውን ጥፍጥና የሚቀምሱበት ጊዜ ሩቅ አይሆን ይሆናል” ይላል፡፡
ምንጭ፡- አልጀዚራ/አብመድ
@YeneTube @FikerAssefa
በዓባይ ወንዝ ዙሪያ ዛሬን በትናንት ሚዛን እየለኩ ኢትዮጵያን ለመሞገት የሚሞክሩ ሁሉ ሁለት የዘነጓቸው ነጥቦች አሉ፡፡ የመጀመሪያው ጉዳይ በኢትዮጵያ ዓይናቸውን በእንጨት ጭስ እያጨናበሱ እና እያለቀሱ በትዕግስት የሚጠብቁ እናቶች መኖራቸውን መዘንጋታቸው ነው፡፡ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ የምትገነባው ግድብ ቅንጦት ሳይሆን መሠረታዊ ፍላጎት ነው፡፡ በዚህ በሰለጠነ ዘመን ዳገት ወጥተው እና ቁልቁለትን ወርደው ሕይወታቸውን ለአደጋ እያጋለጡ ጭራሮ ለቅመው እንጨት ሰብረው በእሳት ጭስ እየተፈተኑ ‹‹እራት እና መብራት›› የሚሹ እናቶች ቁጥር የትየለሌ ነው፡፡
ሁለተኛው እና ከዓባይ ወንዝ ተጠቃሚነት ጋር ተያይዞ ይህ ትውልድ ለአፍታ ሊደራደርበት የማይፈልገው ጉዳይ ደግሞ ግድቡ የእያንዳንዱን ድሀ ኢትዮጵያዊ ኪስ እና መቀነት ነክቷል፡፡ ግድቡ በብድር ወይም በምዕራባውያን ልግስና የሚገነባ ሳይሆን ነገን ተስፋ አድርጎ ከዛሬ ጠኔ ጋር ትግል በገጠመ ድሀ ኢትዮጵያዊ አንጡራ ሀብት ነው፡፡ ከወታደር እስከ አርሶ አደር፣ ከተማሪ እስከ አስተማሪ፣ ከቀን ሠራተኛ እስከ ጡረተኛ፣ ከሕጻናት እስከ አዛውንት፣ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ዛሬውን እየቀጣ ነገን የተሻለ ለማድረግ አዋጥቷል፤ ኖሮት ሳይሆን ሳይኖረው አምስት አስር ተሰብስቦ እየተገነባ ያለ ግድብ መሆኑን ማስታወስ ቀርቶ ማሰብ የሚፈልጉ አይመስሉም፤ የወቅቱ አደራዳሪዎች ወይም ሞጋቾች፡፡
ከሰሞኑ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ በምትገነባው ግድብ አካባቢ የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተዘዋውሮ የተመለከተው የአልጀዚራው ጋዜጠኛ ሙሐመድ ቫል የአገሬዎቹን ኑሮ ተመልክቶ ‹‹አሁንም ኋላቀር በሆነ የኑሮ ዘይቤ ውስጥ የሚኖሩ›› ሲል ይገልፃቸዋል፡፡ ንጹሕ የመጠጥ ውኃ፣ የኤሌክትሪክ አገልግሎት እና ምቹ የመኖሪያ ቤት የሌላቸው ሕዝቦች፤ ከዚህ አስከፊ የኑሮ ምስቅልቅል ለመውጣት ግድቡን በትዕግስት ይጠብቃሉ፡፡ የትዕግስታቸውን ልክና ወሰንም ‹‹ከአዕምሮ በላይ›› ሲል ይገልጸዋል፡፡
የግድቡን አጠቃላይ ሂደት የመጎብኘት ዕድል ያገኘው ጋዜጠኛ ሙሐመድ ቫል የነዋሪዎቹን ትዕግስት ከግድቡ ሠራተኞች የቀን ከሌት ጥረት ጋር አስናስሎም አንድ ፕሮጀክት ለመጨረስ የሚተጉ ሳይሆን ወገኖቻቸውን ከጨለማ ዘመን ለማሻገር የሚታትሩ መሲሆች ያደርጋቸዋል፡፡ ግድቡ ሦስት የተለያዩ የግንባታ ክፍሎች አሉት፡፡ የእያንዳንዱ ግድብ አፈፃፀም የተለያየ ቢሆንም አጠቃላይ ግንባታው 71 ነጥብ 2 በመቶ መጠናቀቁን ያትታል ጋዜጠኛው፡፡
ግድቡ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቆ በውኃ ሲሞላ ስድስት ሺህ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም አለው፡፡ ጋዜጠኛ ሙሐመድ ቫል በዘገባው እንደሚለው ይህም ኢትዮጵያ የእነዚያን ታጋሽ ዜጎቿን የኤሌክትሪክ ፍላጎት ከማሟላት ባለፈ ለሰባት የአፍሪካ እና ምዕራብ አውሮፓ ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በሽያጭ የማቅረብ አቅም ይኖራታል፡፡ “ከኃይል አቅርቦት ባለፈም የሀገሪቱ መፃኢ ምጣኔ ሀብታዊ ዕድገት ተስፋ ከተጣለባቸው ምሰሶዎች አንዱ ነው” ሲል ዘርፈ ብዙ አስፈላጊነቱን ያትታል ሙሐመድ ቫል በዘገባው።
ከዓባይ ወንዝ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት አንዷ የሆነችው ሱዳን ኢትዮጵያ የምትገነባው ግድብ የሚያደርስባት ጉዳት አለመኖሩ በባለሙያዎች መረጋገጡን ያወሳል፡፡ ነገር ግን አቋሟ ወጥ አለመሆኑን የሚናገረው የአልጀዚራው ጋዜጠኛ ግብጽን ግን አሁንም የዓባይ ወንዝ ታሪካዊ እና ብቸኛ ተጠቃሚ አድርጋ እንደምትመለከት ያትታል፡፡ ግብጽ ሄሮዳተስ ‹‹የዓባይ ስጦታ ናት›› ትርክት አልወጣችም የሚለው ሙሐመድ ቫል አሁን እንኳን ዘመንን የዋጀ ምክንያት ማቅረብ እንደተሳናት ያብራራል፡፡የግድቡ አጠቃላይ ቅርፅ መልክ እየያዘ ባለበት በዚህ ወቅት ከሚቀጥለው ክረምት ጀምሮ በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ውስጥ 74 ቢሊዮን ኪዩ ቢክ ሜትር ውኃ በግድቡ ለመሙላት ኢትዮጵያ ማቀዷን ዘገባው ያትታል፡፡
አሜሪካ እና የዓለም ባንክ ከታዛቢነት ወደ አደራዳሪነት በተሸጋገሩበት የሰሞኑ የዋሽንግተን ውይይት የግብጽ አንዱ መደራደሪያ የውኃው ሙሌት ጊዜ ከሦስት ዓመታት ወደ ሰባት ዓመታት ከፍ ይበል የሚል እንደሆነ ያወሳል፡፡በዚህ ሁሉ የነገሮች ዑደት ውስጥ ግን ይላል ጋዜጠኛው ለዘመናት ከማኅፀኗ እየፈሰሰ የሚነጉደው የዓባይ ወንዝ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ጠብታው የሚገታበት ጊዜ የተቃረበ ይመስላል፡፡ ዝነኛው የዓባይ ወንዝ ለሚሊዮን ዓመታት ከአብራኳ ለምታፈልቀው ሀገረ ኢትዮጵያ ሊገብር የተገደደበት ጊዜ መቃረቡ እውን ይመስላል፡፡ “ምናልባት በትዕግስት ለዘመናት የጠበቁት ኢትዮጵያውያን ከዓባይ ወንዝ የትዕግስታቸውን ጥፍጥና የሚቀምሱበት ጊዜ ሩቅ አይሆን ይሆናል” ይላል፡፡
ምንጭ፡- አልጀዚራ/አብመድ
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሞ ፌድራሊስ ኮንግረስ በአዳማ ከተማ ከነዋሪዎች ጋር ሊደርግ ያሰበውን ውይይት ፖሊስ በመከልከሉ፣ ውይይቱን ለመታደም የተገኙ ዜጎች ተቃውሞ በማሰማት ላይ ይገኛሉ።
Via Ethiopia Live Updates
@YeneTube @FikerAssefa
Via Ethiopia Live Updates
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ የራሷን ሰነድ ለድርድር ልታቀርብ ነው #itsmydam
የኢትዮጵያ መንግሥት የታላቁ ህዳሴ ግድብ የውኃ አሞላልና አለቃቀቅን የተመለከተ ሰነድ አዘጋጅቶ ለድርድር እንደሚያቀርብ ተሰማ። አንድ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው የሪፖርተር ምንጭ እንደገለጹት፣ በአሜሪካና በዓለም ባንክ አመቻችነት የግድቡን የውኃ አሞላልና አለቃቀቅን በተመለከተ ሲደረግ የቆየው ድርድር ውጤት የኢትዮጵያን ጥቅም የሚጎዳ በመሆኑ፣ የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን የአገሪቱን ሉዓላዊነትና ጥቅም የሚያስከብር የድርድር ሰነድ እንዲያዘጋጅ በመንግሥት ታዞ ሰነዱን በማዘጋጀት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ከተደራዳሪ ቡድኑ በተጨማሪ የጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የዓለም አቀፍ ሕግ ስምምነት ባለሙያዎች፣ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለሙያዎች፣ ከተለያዩ የአገር ውስጥና የውጭ ዩኒቨርስቲዎች የተወጣጡ ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ሰነዱን በማዘጋጀት ሒደት ላይ ሌት ተቀን እየሠሩ እንደሚገኙ ማረጋገጥ ተችሏል።
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ጠንካራ ትስስር ያላት አገር በመሆኗ በድርድሩ መሳተፍ ትክክል ቢሆንም፣ አሜሪካ ያዘጋጀችው የመጨረሻው ሰነድ ውስጥ ያልተፈቱ ጉዳዮች መኖራቸውን ምንጩ ጠቁመዋል፡፡ ታዛቢዎቹ በድርድሮች ወቅት በኢትዮጵያ ላይ ግፊት እያደረጉ እንደነበር ተሰምቷል። ይህ የአገሪቱን ጥቅም የሚፃረር ስለሆነ በቀጣዩ ድርድር ላይ ላለመሳተፍ የተሰጠው ውሳኔ ትክክለኛ መሆኑን አክለዋል።
የታዛቢነት ሚና የተሰጣቸው አሜሪካና ዓለም ባንክ ድርድሩን ወደ ሽምግልና መቀየራቸውና በመጨረሻም ራሳቸው አዘጋጅተው ለስምምነት ያቀረቡት ረቂቅ ሰነድ፣ ኢትዮጵያ እንደማትደራደርባቸው የገለጸቻቸውን በርካታ ነጥቦች ያላካተተና ለታችኞቹ የተፋሰሱ አገሮችም ጥቅም በእጅጉ ያደላ በመሆኑ፣ በኢትዮጵያ ተቀባይነት እንደማይኖረው አቋም መያዙን እኚሁ ምንጭ አስታውቀዋል።
የቀረበው ረቂቅ የስምምነት ሰነድ ከላይ ከተገለጸው በተጨማሪ ከህዳሴ ግድብ አልፎ የዓባይ ውኃ ክፍፍልን የሚመለከቱ አንቀጾች የተካተቱበት በመሆኑ፣ ከድርድር አጀንዳው ያፈነገጠ እንደሆነ ተለይቷል ሲሉ ምንጩ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የግድቡ ባለቤትና በግዛቷ ውስጥ የሚገኝ እንደ መሆኑ መጠን፣ እንዴት መሞላት አለበት የሚለውን ጉዳይ በዓለም አቀፍ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞች አጠቃቀም መርሆን መሠረት በማድረግ ለታችኞቹ አገሮች ማሳወቅ፣ አገሮቹ ሊያነሱ የሚችሉት ሥጋትም በዓለም አቀፍ መርሆች ውስጥ የሚወድቅ ከሆነ ለማካተት ድርድር እንደሚደረግበት ያሳወቁት እኚሁ ምንጭ፣ በዚህ አግባብ ሰነዱን የማዘጋጀት ሥራ በመፋጠን ላይ መሆኑን አስረድተዋል። የሰነዱ ዝግጅት ሲጠናቀቅ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለግብፅና ለሱዳን እንደሚላክ ገልጸዋል።
በአሜሪካና ዓለም ባንክ አመቻችነት በሦስቱ አገሮች መካከል ሲደረግ የነበረው ድርድር ባለፈው ሳምንት ይፈረማል ተብሎ ዕቅድ ወጥቶለት የነበረ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ባወጣው መግለጫ ለስምምነት ዝግጁ እንዳልሆነና ልዑካኑንም ወደ አሜሪካ እንደማይልክ በይፋ አስታውቋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ከሳምንት በፊት ለግብፅ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ በላኩት መልዕክት፣ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድርድሩን አስመልክቶ የተረቀቀውን ሰነድ ለማጤን ኢትዮጵያ በቂ ጊዜ እንደምትፈልግ ማስታወቃቸው ይታወሳል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድን መልዕክት ለግብፅ ፕሬዚዳንት ያደረሰው በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የተመራ ልዑክ መሆኑም እንዲሁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በላኩት በዚህ መልዕክት ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ድርድርን በተመለከተ ጊዜ ወስዳ ማጤን እንደምትፈልግ፣ የምትደርሰበትን አቋም እንደምታሳውቅ የሚያስረዳ እንደሆነ መዘገባችን አይዘነጋም። መንግሥት ይህንን አቋሙን ባለፈው ሳምንት ለሕዝብ ይፋ ካደረገ በኋላ፣ በርካታ ኢትዮጵያዊያን የተወሰደውን አቋም በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ሲደግፉ ተስተውለዋል።
ምንጭ:- Reporter
@YeneTube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ መንግሥት የታላቁ ህዳሴ ግድብ የውኃ አሞላልና አለቃቀቅን የተመለከተ ሰነድ አዘጋጅቶ ለድርድር እንደሚያቀርብ ተሰማ። አንድ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው የሪፖርተር ምንጭ እንደገለጹት፣ በአሜሪካና በዓለም ባንክ አመቻችነት የግድቡን የውኃ አሞላልና አለቃቀቅን በተመለከተ ሲደረግ የቆየው ድርድር ውጤት የኢትዮጵያን ጥቅም የሚጎዳ በመሆኑ፣ የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን የአገሪቱን ሉዓላዊነትና ጥቅም የሚያስከብር የድርድር ሰነድ እንዲያዘጋጅ በመንግሥት ታዞ ሰነዱን በማዘጋጀት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ከተደራዳሪ ቡድኑ በተጨማሪ የጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የዓለም አቀፍ ሕግ ስምምነት ባለሙያዎች፣ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለሙያዎች፣ ከተለያዩ የአገር ውስጥና የውጭ ዩኒቨርስቲዎች የተወጣጡ ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ሰነዱን በማዘጋጀት ሒደት ላይ ሌት ተቀን እየሠሩ እንደሚገኙ ማረጋገጥ ተችሏል።
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ጠንካራ ትስስር ያላት አገር በመሆኗ በድርድሩ መሳተፍ ትክክል ቢሆንም፣ አሜሪካ ያዘጋጀችው የመጨረሻው ሰነድ ውስጥ ያልተፈቱ ጉዳዮች መኖራቸውን ምንጩ ጠቁመዋል፡፡ ታዛቢዎቹ በድርድሮች ወቅት በኢትዮጵያ ላይ ግፊት እያደረጉ እንደነበር ተሰምቷል። ይህ የአገሪቱን ጥቅም የሚፃረር ስለሆነ በቀጣዩ ድርድር ላይ ላለመሳተፍ የተሰጠው ውሳኔ ትክክለኛ መሆኑን አክለዋል።
የታዛቢነት ሚና የተሰጣቸው አሜሪካና ዓለም ባንክ ድርድሩን ወደ ሽምግልና መቀየራቸውና በመጨረሻም ራሳቸው አዘጋጅተው ለስምምነት ያቀረቡት ረቂቅ ሰነድ፣ ኢትዮጵያ እንደማትደራደርባቸው የገለጸቻቸውን በርካታ ነጥቦች ያላካተተና ለታችኞቹ የተፋሰሱ አገሮችም ጥቅም በእጅጉ ያደላ በመሆኑ፣ በኢትዮጵያ ተቀባይነት እንደማይኖረው አቋም መያዙን እኚሁ ምንጭ አስታውቀዋል።
የቀረበው ረቂቅ የስምምነት ሰነድ ከላይ ከተገለጸው በተጨማሪ ከህዳሴ ግድብ አልፎ የዓባይ ውኃ ክፍፍልን የሚመለከቱ አንቀጾች የተካተቱበት በመሆኑ፣ ከድርድር አጀንዳው ያፈነገጠ እንደሆነ ተለይቷል ሲሉ ምንጩ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የግድቡ ባለቤትና በግዛቷ ውስጥ የሚገኝ እንደ መሆኑ መጠን፣ እንዴት መሞላት አለበት የሚለውን ጉዳይ በዓለም አቀፍ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞች አጠቃቀም መርሆን መሠረት በማድረግ ለታችኞቹ አገሮች ማሳወቅ፣ አገሮቹ ሊያነሱ የሚችሉት ሥጋትም በዓለም አቀፍ መርሆች ውስጥ የሚወድቅ ከሆነ ለማካተት ድርድር እንደሚደረግበት ያሳወቁት እኚሁ ምንጭ፣ በዚህ አግባብ ሰነዱን የማዘጋጀት ሥራ በመፋጠን ላይ መሆኑን አስረድተዋል። የሰነዱ ዝግጅት ሲጠናቀቅ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለግብፅና ለሱዳን እንደሚላክ ገልጸዋል።
በአሜሪካና ዓለም ባንክ አመቻችነት በሦስቱ አገሮች መካከል ሲደረግ የነበረው ድርድር ባለፈው ሳምንት ይፈረማል ተብሎ ዕቅድ ወጥቶለት የነበረ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ባወጣው መግለጫ ለስምምነት ዝግጁ እንዳልሆነና ልዑካኑንም ወደ አሜሪካ እንደማይልክ በይፋ አስታውቋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ከሳምንት በፊት ለግብፅ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ በላኩት መልዕክት፣ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድርድሩን አስመልክቶ የተረቀቀውን ሰነድ ለማጤን ኢትዮጵያ በቂ ጊዜ እንደምትፈልግ ማስታወቃቸው ይታወሳል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድን መልዕክት ለግብፅ ፕሬዚዳንት ያደረሰው በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የተመራ ልዑክ መሆኑም እንዲሁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በላኩት በዚህ መልዕክት ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ድርድርን በተመለከተ ጊዜ ወስዳ ማጤን እንደምትፈልግ፣ የምትደርሰበትን አቋም እንደምታሳውቅ የሚያስረዳ እንደሆነ መዘገባችን አይዘነጋም። መንግሥት ይህንን አቋሙን ባለፈው ሳምንት ለሕዝብ ይፋ ካደረገ በኋላ፣ በርካታ ኢትዮጵያዊያን የተወሰደውን አቋም በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ሲደግፉ ተስተውለዋል።
ምንጭ:- Reporter
@YeneTube @Fikerassefa
አንድ የካናዳ የተራድኦ ድርጅት 15 ሰራተኞቹ በኢትዮጵያ እንደታሰሩበት አስታወቀ።
በካናዳዋ አልቤርታ ከተማ ዋና መቀመጫውን ያደረገው ይህ የተራድኦ ድርጅት በኢትዮጵያ 15 ሰራተኞች መታሰራቸውን የገለጸ ሲሆን ከታሳሪዎቹ መካከል 13ቱ ካናዳዊያን ሲሆኑ ሁለቱ ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን በድርገጹ አስታውቋል።
እንደ ድርጅቱ ገለጻ ከሆነ ሰራተኞቹን ለእስር የዳረጋቸው የመጠቀሚያ ጊዜው ያለፈበት እና ደህንነቱ ያልተረጋገጠ መድሃኒት ሲያከፋፍሉ በመያዛቸው ነው።
ድርጅቱ የሚያከፋፍላቸው መድሃኒቶች ደህንነት የኢትዮጵያንም ሆነ ዓለም አቀፍ የደህንነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ ናቸው ሰራተኞቹ በፖሊስ መታሰራቸውን አግባብ አይደለም ብሏል።
ሰራተኞቹን ለማስለቀቅም በኢትዮጵያ ካለው የካናዳ ኢምባሲ እና ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
ኢትዮ ኤፍ ኤም እነዚህ ሰራተኞች እንዴት ታሰሩ ያጠፉትስ ምንድን ነው ሲል የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽንን ጠይቋል።
የኮሚሽኑ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ጀይላን አብዲ በበኩላቸው ስለተባለው ነገር እንደማያውቁ ምላሽ ሰጥተውናል።
Via:- Ethio FM
@YeneTube @Fikerassefa
በካናዳዋ አልቤርታ ከተማ ዋና መቀመጫውን ያደረገው ይህ የተራድኦ ድርጅት በኢትዮጵያ 15 ሰራተኞች መታሰራቸውን የገለጸ ሲሆን ከታሳሪዎቹ መካከል 13ቱ ካናዳዊያን ሲሆኑ ሁለቱ ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን በድርገጹ አስታውቋል።
እንደ ድርጅቱ ገለጻ ከሆነ ሰራተኞቹን ለእስር የዳረጋቸው የመጠቀሚያ ጊዜው ያለፈበት እና ደህንነቱ ያልተረጋገጠ መድሃኒት ሲያከፋፍሉ በመያዛቸው ነው።
ድርጅቱ የሚያከፋፍላቸው መድሃኒቶች ደህንነት የኢትዮጵያንም ሆነ ዓለም አቀፍ የደህንነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ ናቸው ሰራተኞቹ በፖሊስ መታሰራቸውን አግባብ አይደለም ብሏል።
ሰራተኞቹን ለማስለቀቅም በኢትዮጵያ ካለው የካናዳ ኢምባሲ እና ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
ኢትዮ ኤፍ ኤም እነዚህ ሰራተኞች እንዴት ታሰሩ ያጠፉትስ ምንድን ነው ሲል የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽንን ጠይቋል።
የኮሚሽኑ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ጀይላን አብዲ በበኩላቸው ስለተባለው ነገር እንደማያውቁ ምላሽ ሰጥተውናል።
Via:- Ethio FM
@YeneTube @Fikerassefa
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቀነኒሳ የሞ ፋራህን የግማሽ ማራቶን ክብረ-ወሰን ሰበረ
በለንደን ከተማ በተካሄደው የቫይታሊቲ ቢግ ግማሽ ማራቶን፤ ቀነኒሳ በቀለ ክብረ-ወሰን በመስበር አሸንፏል።
የ5 ሺህ እና 10 ሺህ ሜትር ውድድሮች የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤቱ ቀነኒሳ በዚህ ውድድር ሲሳተፍ የመጀመሪያው ነው።
1:00:22 በሆነ ሰዓት የገባው ቀነኒሳ፤ በእንግሊዛዊው ሯጭ ሞ ፋራህ የተያዘውን የቫይታሊቲ ቢግ ግማሽ ማራቶን ክብረ-ወሰን ሰብሯል።
ከቀነኒሳ ጋር ይፋጠጣል ተብሎ የተጠበቀው ሞ ፋራህ ከጥቂት ቀናት በፊት በህመም ምክንያት እንዳይማሰተፍ አሳውቆ ነበር።
ምንጭ:- The Vitality Big Half / bbc
በለንደን ከተማ በተካሄደው የቫይታሊቲ ቢግ ግማሽ ማራቶን፤ ቀነኒሳ በቀለ ክብረ-ወሰን በመስበር አሸንፏል።
የ5 ሺህ እና 10 ሺህ ሜትር ውድድሮች የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤቱ ቀነኒሳ በዚህ ውድድር ሲሳተፍ የመጀመሪያው ነው።
1:00:22 በሆነ ሰዓት የገባው ቀነኒሳ፤ በእንግሊዛዊው ሯጭ ሞ ፋራህ የተያዘውን የቫይታሊቲ ቢግ ግማሽ ማራቶን ክብረ-ወሰን ሰብሯል።
ከቀነኒሳ ጋር ይፋጠጣል ተብሎ የተጠበቀው ሞ ፋራህ ከጥቂት ቀናት በፊት በህመም ምክንያት እንዳይማሰተፍ አሳውቆ ነበር።
ምንጭ:- The Vitality Big Half / bbc
BREAKING: The mayor of #Djibouti city, Fatouma Awaleh Osman has resigned in a surprise move. Fatouma was the first ever female mayor in the Horn of Africa region.
Via:- Ferhan jimale
@Yenetube @Fikerassefa
Via:- Ferhan jimale
@Yenetube @Fikerassefa
አስር ቡድኖችን ባሳተፈው "የድህረ ምርጫ የዲጂታል መፍትሄ ውድድር" ያሸነፉት ወጣቶች፤ የድምጽ ቆጠራ እና የምርጫ ውጤቶች የማሳወቅ ሂደትን ለማሳለጥ የሚያስችል አፕልኬሽን የሰሩ ናቸው። ወጣቶቹ ለስራቸው የሚረዳ ሽልማቶች ተበርክቶላቸዋል።
Via:- Ethiopia Election
@Yenetube @Fikerassefa
Via:- Ethiopia Election
@Yenetube @Fikerassefa
ከአድዋ ጦርነት ቡኃላ እራሱን ያጠፋው ጄኔራል ኦሬስቴ ባራቴሬ
አፄ ሚኒሊክ የጣሊያንን ጦር ለመጋፍጥ ሲወስኑ፣ የጣሊያንን ጦር እየመሩ ከመጡት ጀነራሎች ዋነኛው ጄኔራል ኦሬስቴ ባራቴሬ ነበር። ጄኔራል ባራቴሬ የአፄ ሚኒሊክን ከዚህ ቀደም ይከተሉት የነበርን የጦር ስትራቴጂ አጥንቶ ስለነበር፣ የአድዋን ጦርነትም በድል እንደሚወጣው እርግጠኛ ነበር።
አፄ ሚኒሊክ ቀደም በአብዛኛው ይከተሉት የነበርው የጦር ስትራቴጂ ፈረንጆቹ (Battle of annihilation) የሚሉት ወይም ሙሉ ሃይልን በመጠቀም ጠላትን ነጥሎ መደምሰስ ነበር። በአድዋ ጦርነት ላይ ግን ስልታቸውን ቀይረው በተለያየ ግንባር ጀነራሎቻቸውን አሰልፈው ስለነበር፣ የጣሊያን ጦርን በመበተን ታሪካዊ ድል ተጎናፅፈዋል። ጄኔራል ባራቴሬም የአፄ ሚኒሊክን የጦር አሰላለፍ ባለመረዳት አሳፋሪ ሽንፈትን ቀምሷል።
ተጨማሪ እዚህ ላይ ገብተው ያንብቡ ⬇️
https://telegra.ph/Adawa-03-01
አፄ ሚኒሊክ የጣሊያንን ጦር ለመጋፍጥ ሲወስኑ፣ የጣሊያንን ጦር እየመሩ ከመጡት ጀነራሎች ዋነኛው ጄኔራል ኦሬስቴ ባራቴሬ ነበር። ጄኔራል ባራቴሬ የአፄ ሚኒሊክን ከዚህ ቀደም ይከተሉት የነበርን የጦር ስትራቴጂ አጥንቶ ስለነበር፣ የአድዋን ጦርነትም በድል እንደሚወጣው እርግጠኛ ነበር።
አፄ ሚኒሊክ ቀደም በአብዛኛው ይከተሉት የነበርው የጦር ስትራቴጂ ፈረንጆቹ (Battle of annihilation) የሚሉት ወይም ሙሉ ሃይልን በመጠቀም ጠላትን ነጥሎ መደምሰስ ነበር። በአድዋ ጦርነት ላይ ግን ስልታቸውን ቀይረው በተለያየ ግንባር ጀነራሎቻቸውን አሰልፈው ስለነበር፣ የጣሊያን ጦርን በመበተን ታሪካዊ ድል ተጎናፅፈዋል። ጄኔራል ባራቴሬም የአፄ ሚኒሊክን የጦር አሰላለፍ ባለመረዳት አሳፋሪ ሽንፈትን ቀምሷል።
ተጨማሪ እዚህ ላይ ገብተው ያንብቡ ⬇️
https://telegra.ph/Adawa-03-01
#Adawa #አብን
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ለንቅናቄያችን አባላትና ደጋፊዎች፣ ለአማራ እና መላ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንኳን ለ124ኛው የአድዋ የድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል፤
አፍሪካን እንደ ቅርጫ ሥጋ ለመከፋፈል የአውሮጳ ሃያላን በጀርመን በርሊን ኮንፈረንስ ከተሰባሰቡና ስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ጣሊያን ኢትዮጵያን ቅኝ ግዛት ለማድረግና ሀብቷን ለመመዝበር፣ በሂደትም ኮሎኒያሊስት ሰፋሪዎችን አየሩ ተስማሚ በሆነው በኢትዮጵያ ደጋማ መሬቶች ለማስፈር ቋመጠች። ኢትዮጵያን አንበርክካ የቅኝ ግዛትን ኅልሟን ለማሳካት የጦር ክተት ዘመቻዋን አወጀች፡፡
ጠንቃቃና ብልህ የነበሩት የወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገሥት ግርማዊ ዳግማዊ አፄ ምኒሊክ (እምየ ምኒሊክ) የፋሽስት ጣሊያንን ኅልም ለማምከን መስከረም 17 ቀን 1888 ዓ.ም ሕዝባቸው ለአገሩ ነፃነትና ለማንነቱ እንዲፋለም ብሔራዊ የክተት ዘመቻ ጥሪ አወጁ፡፡
ተጨማሪ⬇️
https://telegra.ph/Adawa-03-01-2
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ለንቅናቄያችን አባላትና ደጋፊዎች፣ ለአማራ እና መላ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንኳን ለ124ኛው የአድዋ የድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል፤
አፍሪካን እንደ ቅርጫ ሥጋ ለመከፋፈል የአውሮጳ ሃያላን በጀርመን በርሊን ኮንፈረንስ ከተሰባሰቡና ስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ጣሊያን ኢትዮጵያን ቅኝ ግዛት ለማድረግና ሀብቷን ለመመዝበር፣ በሂደትም ኮሎኒያሊስት ሰፋሪዎችን አየሩ ተስማሚ በሆነው በኢትዮጵያ ደጋማ መሬቶች ለማስፈር ቋመጠች። ኢትዮጵያን አንበርክካ የቅኝ ግዛትን ኅልሟን ለማሳካት የጦር ክተት ዘመቻዋን አወጀች፡፡
ጠንቃቃና ብልህ የነበሩት የወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገሥት ግርማዊ ዳግማዊ አፄ ምኒሊክ (እምየ ምኒሊክ) የፋሽስት ጣሊያንን ኅልም ለማምከን መስከረም 17 ቀን 1888 ዓ.ም ሕዝባቸው ለአገሩ ነፃነትና ለማንነቱ እንዲፋለም ብሔራዊ የክተት ዘመቻ ጥሪ አወጁ፡፡
ተጨማሪ⬇️
https://telegra.ph/Adawa-03-01-2
የሚንስትሮች ምክር ቤት አዲስ የቋንቋ ፖሊሲ አጽድቋል::
በዚህም መሰረት 4ቱ ቋንቋዎች:-
1. አፋን ኦሮሞ
2. ትግሪኛ
3. ሱማሊኛ እና
4. አፋርኛ
ከአማርኛ በተጨማሪ የፌዴራል የስራ ቋንቋ ይሆናሉ ማለት ነው::
እንኳን ደስ አለን! #Fistumarega
@YeneTube @FikerAssefa
በዚህም መሰረት 4ቱ ቋንቋዎች:-
1. አፋን ኦሮሞ
2. ትግሪኛ
3. ሱማሊኛ እና
4. አፋርኛ
ከአማርኛ በተጨማሪ የፌዴራል የስራ ቋንቋ ይሆናሉ ማለት ነው::
እንኳን ደስ አለን! #Fistumarega
@YeneTube @FikerAssefa
የአለም ስጋት ከሆነው የኮሮና ቫይረስ እራሳችንን ለመከላከል ልንወስዳቸው የሚገቡ ቀላልና
ውጤታማ እርምጃዎች፥
- አዘውትሮ በአግባቡ እጅን በሳሙና መታጠብ
- ለሰላምታ በእጅ አለመጨባበጥ
- ፊትን በእጅ አለመንካት
- ትኩሳት፣ ሳል፣ ማስነጠስ ያሉ ምልክቶች ካጋጠሙን የአፍ መሸፈኛ ማስክ ማድረግ
- በሚያስነጥሱ እና በሚያስሉ ጊዜ ክርንዎን አጥፈው በመጠቀም ሌሎችን እንዳይበክሉ መጠንቀቅ።
@Yenetube @Fikerassefa
ውጤታማ እርምጃዎች፥
- አዘውትሮ በአግባቡ እጅን በሳሙና መታጠብ
- ለሰላምታ በእጅ አለመጨባበጥ
- ፊትን በእጅ አለመንካት
- ትኩሳት፣ ሳል፣ ማስነጠስ ያሉ ምልክቶች ካጋጠሙን የአፍ መሸፈኛ ማስክ ማድረግ
- በሚያስነጥሱ እና በሚያስሉ ጊዜ ክርንዎን አጥፈው በመጠቀም ሌሎችን እንዳይበክሉ መጠንቀቅ።
@Yenetube @Fikerassefa