YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
483 videos
79 files
3.85K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የካቲት 18 ቀን 2012 ዓ/ም በአዲስ አበባ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ክልል ቆሬ አካባቢ ተብሎ በሚጠራዉ ስፍራ በደረሰው የትራፊክ አደጋ ከሞቱት መካከል የ11 ወር ህጻን እና ነፍሰ ጡር ሴት እንደሚገኙበት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ ፡፡

የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3-56868 ኢት የሆነ ከባድ ተሸከርካሪ እንጨት ጭኖ ከብስራተ ገብርኤል ወደ መካኒሳ አቅጣጫ እየተጓዘ ዓለም ሰላም ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ሲደርስ 30 ሜትር ያህል ርቀት ካለዉ ድልድይ ላይ በመውደቅ እና ከድልድዩ ስር የሚገኝ መኖርያ ቤት ጥሶ በመግባት የሞትና የአካል ጉዳት እንዲከሰት ምክንያት ሆኗል፡፡

በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ አደጋ መርማሪ ዋና ሳጅን አዳነ ሙሉ እንደገለጹት በመኖሪያ ቤቱ በአክስቱ እቅፍ ውስጥ የነበረ የ11 ወር ህጻን እና ህጻኑን ያቀፈችዉ ነፍሰ ጡር አክስቱ እንዲሁም በወቅቱ መኪናውን ሲያሽከረክር የነበረው አሽከርካሪ በአደጋው ህይወታቸው ማለፉን ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም በመንገድ ላይ ስትጓዝ የነበረች አንዲት ሴት እንዲሁም መኖሪያ ቤቱ ውስጥ የነበሩት የሟች ህጻን ወላጅ እናት እና የህጻኑ ሞግዚት የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ዋ/ሳጅን አዳነ ሙሉ ተናግረዋል፡፡ የአደጋው መንስኤም በመጣራት ላይ ይገኛል፡፡ አሽከርካሪዎች የተሸከርካሪያቸውን ደህንነት ዘወትር መፈተሽና ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል ያሉት ዋና ሳጅን አዳነ ሙሉ በተለይም ከባድ ጭነት ጭነው በሚጓዙበት ወቅት በመታጠፊያና በቁልቁለታማ መንገዶች ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ ፍጥነታቸውን ቀንሰው ሊያሽከረክሩ እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Via Addis Ababa Police Commission
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ከዓለም ሲወዳደሩ ያሉበት ደረጃ ይፋ ተደረገ

እ.አ.አ 2016 ጀምሮ መቀመጫውን የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ያደረገው የዓለም ዩኒቨርሲቲዎች ደረጃ ማእከል የተሰኘ ተቋም ሁለት ሺህ ዩኒቨርሲቲዎችን አወዳድሮ ባወጣው ደረጃ መሠረት አምስት ኢትዮጵያውያን ዩኒቨርሲቲዎችን ተካትተዋል።

ማእከሉ ደረጃውን ለማውጣት ዩኒቨርሲቲዎቹ በየአገራቸው ያላቸውን ደረጃ፣ የሚሰጡትን የትምህርት ጥራት፣ ራሳቸው ያስተማሯቸውን ተማሪዎች የመቅጠር ምጣኔ፣ የፋኩሊቲያቸው ጥራት እንዲሁም በጥናት እና ምርምር ዘርፍ ያላቸው ብቃት በመስፈርትነት ተጠቅሟል።

በዚሁ መሠረት ከሁለት ሺህ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል አዲስ አበባ (1 ሺህ 040ኛ) ፣ ጎንደር (1 ሺህ 547ኛ) ፣ መቀሌ (1 ሺህ 588ኛ) ፣ ጅማ (1 ሺህ 786ኛ) እና ባሕር ዳር (1 ሺህ 780ኛ) ደረጃ በመያዝ የተካተቱ ዩኒቨርሲቲዎች ሆነዋል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ የአሜሪካኖቹ ሀርቫርድ፣ ማሳቹስቴትስ ኢንስቲትዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ እና ስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ ከአንደኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡

ከአንድ እስከ 10ኛ ደረጃ ካሉ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ከእንግሊዞቹ የኦክስፎርድ (4ኛ) እና የካምፕሪጅ (5ኛ) ዩኒቨርሲዎች በስተቀር በሙሉ የአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ናቸው፡፡

ማእከሉ ፖሊሲ፣ ስልታዊ እይታ ብሎም መንግሥታት እና ዩኒቨርሲቲዎች የትምህርት እና ምርምር ውጤታቸውን ለማሻሻል የሚያስችሏቸው የምክር አገልግሎቶች የሚሰጥ ግንባር ቀደም ተቋም መሆኑንም ከድረ ገጹ ላይ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

ማእከሉ እ.አ.አ 2012 ጀምሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለዩኒቨርሲቲዎች ደረጃ የሚሰጥ መሆኑም ተመልክቷል።

ምንጭ:- የዓለም ዩኒቨርሲቲዎች ደረጃ ማእከል
@YeneTube @Fikerassefa
የአውሮፓ ህብረት መጪውን ምርጫ የሚታዘብ ልኡክ እንደሚልክ ይፋ አደረገ!

የአውሮፓ ህብረት የውጪ ግንኙነት እና የደህንነት ፖሊስ ጉዳዮች ተወካይ እና የኮሚሽኑ ምክትል ፕሬዘዳንት ጆሴፍ ቦሬል ዛሬ ጠዋት ከጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ምክክር በነሐሴ ወር ለሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ህብረቱ ታዛቢዎቹን እንደሚልክ ይፋ አደረጉ።ጆሴፍ በትዊተር ገፃቸው ይፋ እንዳደረጉትም መጪው ምርጫ ለኢትዮጵያ መረጋጋት እና ዴሞክራሲን ለማምጣት ወሳኝ መለኪያ እደሆነ ገልፀው ህብረቱ ለዐቢይ አህመድ የለውጥ አጀንዳ ያለውን ድጋፍ ያረጋገጠበት ምክክር እንደነበርም ተናግረዋል።ጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ በተመሰሳይ በግል የትዊተር ገፃቸው ላይ ይፋ እንዳደረጉት ከምክትል ፕሬዘዳንቱ ጋር ‹‹ኢትዮጵያ ስለጀመረችው የብልፅግና ጉዞ እና በቀጠናው ስላሉ መሻሻሎች መክረናል›› ብለዋል።የአውሮፓ ህብረት ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ ያካሄደቻቸውን አገር አቀፍ ምርጫዎች በተደጋጋሚ መታዘቡ ይታወሳል።

Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
መነሻው ከሚሴ በማድረግ ወደ ደራ በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 400 ጩቤዎችን በቁጥጥር ስራ ማዋሉን የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡

የአስተዳደሩ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር መርሀጽድቅ ታዬ እንደተናገሩት ከሆነ በዛሬው እለት ከጠዋቱ 12 ስአት አካባቢ መነሻውን ከሚሴ ያደረገና ወደ ደራ ሲዘዋወር የነበረ 400 ጩቤ ፣ 4 የክላሽ ካርታ መያዣ እንዲሁም በኢትዪጵያ ንግድ ባንክ ጉንዶ መስቀል ቅርንጫፍ አካውንት ደብተር 82 ሺ 444 ብር ይዞ ሲዘዋወር የነበረን ከተጠረጣሪው አቶ ታደሰ ጀማ ገመዳ ጋር በሸዋሮቢት ከተማ 04 ቀበሌ በቁጥጥር ስር ማዋሉንና በተጠርጣሪው ላይም ጥልቅ የሆነ ምርመራ በመደረግ ላይ መሆኑን ገልጸው ምርመራውም ተጠናቆ በሚመለከተው አካል ህጋዊ ውሳኔ ሲተላለፍ ለህብረተሰቡ እንደሚያሳውቁ ተናግረው፡፡

ምንጭ: የሸዋሮቢት ከ/አስ/ከ/ጽ/ቤት
@YeneTube @FikerAssefa
መድረክ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ መተዳደሪያ ደንቡን አሻሻለ!

የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ከዚህ ቀደም አንድ የጥምረቱ አባል የሌላ ጥምረት አባል መሆን አይችልም የሚለውን የመተዳደሪያ ደንቡን አንቀጽ አሻሻለ።ጥር 23/2012 በጠራው አስቸኳይ ጉባኤ ላይ ደንቡን ያሻሻለው መድረክ ለዚህ ውሳኔ መነሻ የጥምረቱ አባላት ይህ አንቀፅ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በጋራ እንዳይሰሩ እያገዳቸው መሆኑን በማንሳታቸው ነው ሲሉ የመድረክ ጸሃፊ ደስታ ዲንቃ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።

ጠቅላላ ጉባኤው በዚህ ጉዳይ ላይ ብቻ ውሳኔ ማሳለፉን የተናገሩት ደስታ የምርጫ ቦርድ ተወካይም በጉባኤው ተገኝተው መታዘባቸውን ተናግረዋል። ትብብር ለዴሞክራሲያዊ ፌደራሊዝም የተሰኘው እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር፣ የኦሮሞ ፌደራሊሰት ኮንግረስ እና የኦሮሞ ብሔራዊ ፓርቲ አዲስ ጥምረት መስርተው ከምርጫ ቦርድ የምስክር ወረቀት ለማግኘት ጥያቄ ማቅረባቸው ይታወሳል። ቦርዱም ኦፌኮ አባል የሆነበት መድረክ መተዳደሪያ ደንብ መስራቸው ፓርቲዎቹ የሌላ ጥምረት አባል መሆን እንደማይችሉ ስለሚገድብ ይህ እንዲታይ መጠየቁ ይታወሳል።

ምንጭ: አዲስ ማለዳ
@YeneTube @FikerAssefa
ኤርሚያስ ጠቅል አመልጋ ከእስር ተፈትቶ ከወዳጆቹ ጋር ተቀላቅሏል፡፡

Via Jano Band
@YeneTube @FikerAssefa
ሕወሀት ብልጽግና ፓርቲ በትግራይ ክልል ቅርንጫፍ እንደሚከፍት አልተነጋገርንም አለ።

የብልጽግና ፓርቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አወሉ አብዲ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ብልጽግና አገር አቀፍ ፓርቲ በመሆኑ ከትግራይ ክልል ጋር በሚኖረው ሕገ መንግሥታዊ ግንኙነት መሠረት አደረጃጀቱን በማስፋት በቅርቡ በክልሉ በሁሉም ዞኖች፣ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ጽሕፈት ቤቶችን ይከፍታል ማለታቸዉ ይታወሳል፡፡

ብልጽግና ፓርቲ በትግራይ ክልል በሁሉም ወረዳዎች ቢሮ እንደሚከፍት ያስታወቀ ቢሆንም የክልሉ መንግስት ግን የሚያዉቀዉ ነገር እንደሌለ የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ጌታቸዉ ረዳ ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታዉቋል፡፡

ብልጽግና ለትግራይ ክልል የተሾሙ ግለሰቦች እንዳሉ ሰምቻለሁ ያሉት አቶ ጌታቸዉ እነማን እንደተሾሙ ግን ወደ ፊት የሚሆነዉን የምናይ ይሆናል ብለዋል፡፡

ብልጽግና በትግራይ ክልል ብዙ ደጋፊ አለው ብዬ አላምንም ያሉት አቶ ጌታቸው ማንኛዉም ፓርቲ ህጋዊ እስከሆነ ድረስ ግን በትግራይ ክልል የመንቀሳቀስ መብት አለዉ ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from HEY Online Market
#ኦሪጂናል ሞባይል ስልኮች ዋስትና

🔸SAMSUNG
#GALAXY A SERIES 
A10S 2019 /32 GB/ 5,599ብር
A20S 2019 /32 GB/ 7,199ብር
A30S 2019 /64 GB/ 8,499 ብር
A50 2019 /64 GB/ 9,499 ብር
A50 2019 /128 GB/ 10,499 ብር
A50S 2019 /128 GB/ 4GB 11,199
A50S 2019 /128 GB/ 6GB 11,999
A51 2020 /128 GB/ 6GB 12,799 ብር
A70 2019 /128 GB/ 6GB 13,899 ብር

🔸SAMSUNG #GALAXY M SERIES 
M10 (2019) /32 GB/ 5,699 ብር
M10S (2019) /32 GB/ 6,200 ብር
M30S (2019) /36 GB/ 9,200ብር

አድራሻ :- ከቦሌ መድሃኔአለም ቤተ ክርስቲያን ወደ ቦሌ ብራስ የሚወስደው መንገድ ላይ

Contact US
0953964175
0925927457
0910695100
@Roviii

@HEYOnlinemarket
በደቡብ ክልል ማጂ ወረዳ ቱም ከተማ በዛሬው ዕለት በተደረገ ተቃውሞ ላይ የጸጥታ ኃይሎች በተኮሱት ጥይት ስድስት ሰዎች መገደላቸውን የሕክምና ተቋም ተናገሩ። የዞኑ ባለሥልጣናት እና የዐይን እማኞችም ጸጥታ ኃይሎች በተኮሱት ጥይት ከተገደሉት በተጨማሪ ሌሎች ከአስር በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን አረጋግጠዋል።

ሰልፉ የተደረገዉ አዲስ በተዋቀረው በምዕራብ ኦሞ ዞን የምትገኘው የማጂ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ እና የጸጥታ ቢሮ ኃላፊ መታሰራቸውን በመቃወም ነበር። «አስራ አንድ ሰው [በጥይት] ተመቷል። ሶስቱ ሴቶች ናቸው። ትልልቅ ሰዎች እና ሕፃናትም አሉበት» የሚሉት የዐይን እማኙ «ሰልፍ ሲደረግ መንገድ ይዘጋል። መንገድ ሲዘጋ መከላከያ እና ልዩ ኃይል መጣ። ከዚያ በአካባቢው በተሰበሰበው ሕዝብ ላይ ምንም ነገር ሳያማክር ተኩስ ጀመረ» ሲሉ መነሾውን አብራርተዋል።

የማጂ ወረዳ ጤና ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከበደ አኩ እንደሚሉት ቱም በተባለችው ከተማ በተደረገው ሰልፍ ስድስት ሰዎች በጸጥታ አስከባሪዎች ተገድለዋል።
አቶ ከበደ "ዛሬ ጠዋት በነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የነበሩ አራት ሰዎች በልዩ ኃይል እና በመከላከያ ሠራዊት በተተኮሰ ጥይት ተመተው እኛ ጋ ተኝተዋል። የሞቱት ሬሳቸው ሳይነሳ እዚያው ነው ያለው። የሞቱት ወደ ስድስት የሚሆኑ ሰዎች ናቸው" ሲሉ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። በአራት ጥይት የቆሰሉ አንድ ሰው ለተጨማሪ ሕክምና ወደ ማጂ መላካቸውን ኃላፊው ጨምረው ተናግረዋል።

Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
የኮሮና ቫይረስ በሽታ (የኮቪድ-19) አስመልክቶ የተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ

➡️ በሁሉም ወደ ሀገር መግቢያ ጣቢያዎች ሶስት መቶ ሰባ ሁለት ሺህ አንደ መቶ (372,100) በሙቀት መለያ (ኢቦላና ኮቪድ-19 በማጣመር) አልፈዋል፡፡

➡️በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በ7ቱ መግቢያዎች ሁለት መቶ ሃያ ሺህ ሶስት መቶ ሃምሳ ሰባት (220,357) በላይ የሚሆኑ መንገደኞች በሙቀት ልየታው ያለፉ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ አምስት ሺህ አራት መቶ ስባ ስድስት (5,476) በሽታውን ሪፖርት ካደረጉ ሃገራት የመጡ ናቸው፡፡

➡️ሰማንያ ሁለት (82) ጭምጭምታዎች ለኢንስቲትዩቱ ድንገተኛ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ምላሽ ማስተባበሪያ ማዕከል (Public Health Emergency Operation Center) ደርሰው በሁሉም ጥቆማዎች ላይ ማጣራት ተደርጓል፡፡

➡️ከነዚህም ጥቆማዎች ሀያ (20) የበሽታውን ተመሳሳይ ምልክቶችን በማሳየታቸው እና የቻይና ጉዞ ታሪክ ስለ ነበራቸው በተለያየ ጊዜ በለይቶ ማቆያ ማእከል እንዲቆዩ ተደርጓል፡፡ በመሆኑም ሁሉም ግለሰቦች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎላቸው ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው በመረጋገጡ ወደ ሕብረተሰቡ እንዲቀላቀሉ ተደርጓል፡፡ በአሁኑ ሠዓት በለይቶ ማቆያ ውስጥ ተለይቶ ያለ በበሽታው የተጠረጠረ ሰው የለም፡፡

➡️በ8335 የነጻ የስልክ መስመር በአጠቃላይ ሶስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሃያ ሁለት (3,922) ጥሪዎች የደረሱ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ አንድ ሺህ ሶስት መቶ አርባ (1,340) ከኮቬድ-19 ጋር የተገናኙ መረጃዎች ናቸው፡፡

-EPHI
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
የኮሮና ቫይረስ በሽታ (የኮቪድ-19) አስመልክቶ የተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ ➡️ በሁሉም ወደ ሀገር መግቢያ ጣቢያዎች ሶስት መቶ ሰባ ሁለት ሺህ አንደ መቶ (372,100) በሙቀት መለያ (ኢቦላና ኮቪድ-19 በማጣመር) አልፈዋል፡፡ ➡️በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በ7ቱ መግቢያዎች ሁለት መቶ ሃያ ሺህ ሶስት መቶ ሃምሳ ሰባት (220,357) በላይ የሚሆኑ መንገደኞች በሙቀት ልየታው ያለፉ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ…
"ይህ መረጃ እስከ ተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በ አገራችን የተረገገጠ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ የለም ነገር ግን እስከ አሁን ድረስ 20 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተጠርጥረዉ በመለያ ማእከል ክትትል ተደርጎላቸዉ ከቫረሱ ነጻመሆናቸዉ ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ጊዜ አንድ ተጠርጣሪ በማለያ ማእከል ተለይቶ ክትትል እየተደረገለት ሲሆን ናሙና ተወስዶ ላብራቶሪ እተሰራ ነዉ፡፡ ዉጤቱም እንደደረሰ እናሳዉቃለን፡፡ ሕብረተሰቡ በቫረይሱ መያዙ የተረጋገጠ ሰዉ አለመኖሩን አዉቆ ሳይዘናጋ የበለጠ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ኢንስቲትዩቱ ያሳስባል፡፡"

-EPHI
@YeneTube @FikerAssefa
ዶ/ር ሊያ ታደሰ | ኮሮና ቫይረስ #Update

ዛሬ አንድ በኮሮና ቫይረስ የተጠረጠረ ግለሰብ በለይቶ ማቆያ መግባቱን የኢትዮጵያ ጤና ሚንስትር ዴታ ሊያ ታደሰ ገልፃለች። ይህ ግለሰብ ከቤንጂንግ በFeb 22 የመጣ ሲሆን እራሱን በቤት ውስጥ ለይቶ ቆይቶ ነበር።

ነገር የግን የራስ ምታቱ መጠን መጨመሩን ተከትሎ የጤና ሚንስትር ማቆያ ውስጥ መግባቱን ሚንስተሯ በቲዊተር ገጷ ላይ አስፍራለች። ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ውጤቱ ዛሬ ማታ እንደሚገለፅ ሚንስተሯ ጨምራ ተናግራለች ።

@Yenetube @Fikerassefa
አስደሳች ዜና፡ ነጻ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ህክምና አገልግሎት ዕድል

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ዓይን ህክምና ት/ት ክፍል ከሂማሊያን ካታራክት ፕሮጀክትና ቪዥን ኬር ሰርቪስ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ከየካቲት 29

-- መጋቢት 5 2012 ዓ.ም. በጅማ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል የዓይን ህክምና ክፍል ለ500 ተጠቃሚዎች ነጻ የዓይን የሞራ ግርዶሽ ህክምና አገልግሎት ይሰጣል፡፡ በመሆኑም ይህንን አገልግሎት ማግኘት የሚፈልግ ማንኛዉም የህብረተሰብ ክፍል በተጠቀሱት ቀናትና ቦታ በመገኘት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንድትሆኑ እናሳስባለን፡፡

ጅማ ዩኒቨርሲቲ
@Yenetube @Fikerassefa
የመብራት መቋረጥ…

"ወደተለያዩ ቦታዎች ስልክ በመደወል እንዳጣራነው ከአዲስአበባ በተጨማሪ አዳማ ፣መቐለ፣ሀዋሳ፣ሀረር፣ድሬ
ደዋ፣ጅግጅጋ፣ አዲግራት:ጎንደር : ጅማ : ባህር ዳር መብራት ሙሉ ለሙሉ ተቋርጧል።

ስለጉዳዩ ለመጠየቅ ወደ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ባለስልጣን ብንደውልም ስልካቸው ሊሰራልን አልቻለም።"

-Sheger Times
@YeneTube @FikerAssefa
የኤሌክትሪክ መቋረጥ...

በጊቤ 3 የሀይል ማመንጫ ላይ የተፈጠረ ችግር ለመብራት መቋረጡ መንስኤ ሳይሆን እንዳልቀረ Capital ዘግቧል።

@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
የኤሌክትሪክ መቋረጥ... በጊቤ 3 የሀይል ማመንጫ ላይ የተፈጠረ ችግር ለመብራት መቋረጡ መንስኤ ሳይሆን እንዳልቀረ Capital ዘግቧል። @YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር እቶ ሞገስ መኮንንም የኃይል መቋረጥ ማጋጠሙን ለቢቢሲ አረጋግጠዋል::

ለዚህ የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ ምክንያቱ ምን እንደሆነ ለአሁን እለመታወቁን: ነገር ግን ከግልገል ጊቤ ሦስት ከሚቀርበው የኃይል አቅርቦት መስመር ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል አቶ ሞገስ ግምታቸውን ተናግረዋል:: አክለውም የድርጅቱ ባለሙያዎች የኃይል መቋረጡን ምክንያት ለመለየትና አገልግሎቱን ለመመለስ እየሰሩ መሆናቸውንም ጨምረው ገልጸዋል::

በአጭር ጊዜ ውስጥም በአዲስ አበባ ያጋጠመው የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ እንደሚስተካከልና በተከታይነትም የሌሎቹም አካባቢዎች አገልግሎት እንደሚመለስ አቶ ሞገስ ለቢቢሲ ገልጸዋል::በአንዳንድ ስፍራዎችም ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እየተመለሰ መሆኑን ለማወቅ ችለናል::

Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
በኢራን በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 210 ደርሷል ብሏል ቢቢሲ በዘገባው።

የሀገሪቱ መንግሥት ይፋ ባደረገው መረጃ 34 ሰዎች እንደሞቱ ቢያሳውቅም BBC Persian አገኘሁት ባለው መረጃ እስካሁን 210 ሰዎች ሞተዋል። ይህም መንግስታት የሟቾችን ቁጥር እየደበቁ ነው የሚለውን ጥርጣሬ የሚያጎላ ነው ተብሏል።

ከዚው ጋር በተያያዘ CNN በሰራው ዘገባ መንግስታት መረጃን ሚደብቁ ከሆነ በ1918 ከ40 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ህይወት እንደቀጠፈው የእንፍልዌንዛ (Spanish flu) ወረርሽኝ ነገሮችን ወደከፋ ደረጃ ሊያደርስ እንደሚችል ዘግቧል።

Join:- @Coronavirusupdatess

@YeneTube @FikerAssefa