በአዲስ አበባና አካባቢዋ ለልማት ሲባል ከቦታቸዉ ለተነሱ አርሶ አደሮች 20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ምትክ እንዲያገኙ የተወሰነው ከወራት በፊት ነው፤ ውሳኔው አዲስ አይደልም ሲል የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ገለፀ።
የኮርፖሬሽኑ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂኒየር ደሳለኝ ተረፈ ለዶቼ ቬለ (DW) እንደገለፁት በአዲስ አበባ ዳርቻዎች ይኖሩ የነበሩና ከቦታቸዉ የተነሱ አርሶ አደሮች በ20 / 80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች መርሃ ግብር ተጠቃሚ እንዲሆኑ የተወሰነው ታህሳስ 24 ቀን፣ 2011 ዓ.ም ነው።ዉሳኔዉ በከተማዉ ካቢኔ መሰሰጠቱን የገለፁት ኃላፊዉ «ይህ ውሳኔ ደግሞ ግንቦት 2011 ዓ.ም ተግባራዊ ተደርጓል። እንደ አዲስ የሚያወዛግብ ነገር አይደለም » ሲሉ ገልፀዋል። ይሁንና ይህ ውሳኔ የሚመለከታቸው ሰዎች ቁጥር ምን ያህል ነው? በሚል ከDW ለተነሳላቸዉ ጥያቄ ኃላፊው፤ «ማህበራዊ መገናኛዎች ላይ የተምታታ ቁጥር አለ፣ ትክክለኛ ቁጥር የለም ቁጥሩንም አልገልፅም » የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ውሳኔው መጀመርያውኑም እጣ ከመውጣቱ በፊት የተወሰነ ነው ያሉት ኃላፊው አሰራሩ የነበረ እና ምትክ 20 / 80 ቤቱ በሁሉም የቤት ግንባታዎች በሚከናወኑባቸው ቦታዎች የሚሰጥ መሆኑን አብራርተዋል።የልማት ተነሽዎቹ በወቅቱ ካሳ አልተከፈላቸዉም ወይ? በሚል ለተነሳላቸዉ ጥያቄ፤ ምላሽ መስጠት ያለበት ሌላ አካል መሆኑን አመልክተዋል።ተነሺ አርሶአደሮቹ በዚህ የቤት መርሃ ግብር ተጠቃሚ ሊሆኑ የቻሉት ግን መንግስት በግልጽ በወሰነው የቆየ አሠራር ነው ብለዋል።ለ20 / 80 የጋራ መኖሪያ ቤት ለዓመታት ቆጥበው እጣ የወጣላቸው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች፣ እስካሁን ወደ ቤታቸው ያልገቡ እድለኞች አሉ፤ ይህስ የት ደረሰ ብለን የጠየቅናቸው ኃላፊው፦ ጉዳዩ ኮሚቴ ተቋቁሙ እየታየ ነው ብለዋል። በተጨማሪም በሃገር ደረጃ የሚወሰነውን ውሳኔ ተግባራዊ ለማድረግ እየጠበቅን ሲሉ አመልክተዋል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
የኮርፖሬሽኑ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂኒየር ደሳለኝ ተረፈ ለዶቼ ቬለ (DW) እንደገለፁት በአዲስ አበባ ዳርቻዎች ይኖሩ የነበሩና ከቦታቸዉ የተነሱ አርሶ አደሮች በ20 / 80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች መርሃ ግብር ተጠቃሚ እንዲሆኑ የተወሰነው ታህሳስ 24 ቀን፣ 2011 ዓ.ም ነው።ዉሳኔዉ በከተማዉ ካቢኔ መሰሰጠቱን የገለፁት ኃላፊዉ «ይህ ውሳኔ ደግሞ ግንቦት 2011 ዓ.ም ተግባራዊ ተደርጓል። እንደ አዲስ የሚያወዛግብ ነገር አይደለም » ሲሉ ገልፀዋል። ይሁንና ይህ ውሳኔ የሚመለከታቸው ሰዎች ቁጥር ምን ያህል ነው? በሚል ከDW ለተነሳላቸዉ ጥያቄ ኃላፊው፤ «ማህበራዊ መገናኛዎች ላይ የተምታታ ቁጥር አለ፣ ትክክለኛ ቁጥር የለም ቁጥሩንም አልገልፅም » የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ውሳኔው መጀመርያውኑም እጣ ከመውጣቱ በፊት የተወሰነ ነው ያሉት ኃላፊው አሰራሩ የነበረ እና ምትክ 20 / 80 ቤቱ በሁሉም የቤት ግንባታዎች በሚከናወኑባቸው ቦታዎች የሚሰጥ መሆኑን አብራርተዋል።የልማት ተነሽዎቹ በወቅቱ ካሳ አልተከፈላቸዉም ወይ? በሚል ለተነሳላቸዉ ጥያቄ፤ ምላሽ መስጠት ያለበት ሌላ አካል መሆኑን አመልክተዋል።ተነሺ አርሶአደሮቹ በዚህ የቤት መርሃ ግብር ተጠቃሚ ሊሆኑ የቻሉት ግን መንግስት በግልጽ በወሰነው የቆየ አሠራር ነው ብለዋል።ለ20 / 80 የጋራ መኖሪያ ቤት ለዓመታት ቆጥበው እጣ የወጣላቸው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች፣ እስካሁን ወደ ቤታቸው ያልገቡ እድለኞች አሉ፤ ይህስ የት ደረሰ ብለን የጠየቅናቸው ኃላፊው፦ ጉዳዩ ኮሚቴ ተቋቁሙ እየታየ ነው ብለዋል። በተጨማሪም በሃገር ደረጃ የሚወሰነውን ውሳኔ ተግባራዊ ለማድረግ እየጠበቅን ሲሉ አመልክተዋል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
የህወሓት ማዕካላዊ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው!
የህወሓት ማዕካላዊ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት ማካሄድ ጀመረ።ማዕከላዊ ኮሚቴው በስብሳበው የ2011 ዓ.ም ቁልፍ እና ዓበይት ተግባራትን የሚገመግም ሲሆን፥ በተለይ መልካም አስተዳደርን በማስፈን እና ልማትን በማረጋገጥ በኩል ያሉትን አፈፃፀሞች በዝርዝር ይመለከታል።
ከዚህ ባለፈም በ2012 ዓ.ም አቅድ ዙሪያ በዝርዝር በመወያየት እቅዱን እንደሚያፀድቅ ነው የሚጠበቀው። እንዲሁም የድርጅቱን መመሪያዎች እና አሰራሮችን በመገምገም ያሻሽላል ተብሎ ይጠበቃል።በተጨማሪም በ2011 ዓ.ም የነበሩ ሀገራዊ እና አለማቀፋዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ጥንካሬዎችን እና ጉድለቶችን በዝርዝር በማየት ያሉትን ተግዳሮቶች ለመከላከል የሚያስችል አቅጣጫ እንደሚያስቀምጥም ተጠቁሟል።እነዚህ ተግዳሮች የሚፈጥሩትን ጫና ከክልሉ ህዝብ ነበራዊ ሁኔታ ጋር በማያያዝ በመልካም አስተዳደር፣ ልማት እና የህዝብ ህልውና ያሉትን ሁኔታዎች ገምግሞ የውሳኔ ሃሳብ እንደሚያስቀምጥ ተነግሯል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
የህወሓት ማዕካላዊ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት ማካሄድ ጀመረ።ማዕከላዊ ኮሚቴው በስብሳበው የ2011 ዓ.ም ቁልፍ እና ዓበይት ተግባራትን የሚገመግም ሲሆን፥ በተለይ መልካም አስተዳደርን በማስፈን እና ልማትን በማረጋገጥ በኩል ያሉትን አፈፃፀሞች በዝርዝር ይመለከታል።
ከዚህ ባለፈም በ2012 ዓ.ም አቅድ ዙሪያ በዝርዝር በመወያየት እቅዱን እንደሚያፀድቅ ነው የሚጠበቀው። እንዲሁም የድርጅቱን መመሪያዎች እና አሰራሮችን በመገምገም ያሻሽላል ተብሎ ይጠበቃል።በተጨማሪም በ2011 ዓ.ም የነበሩ ሀገራዊ እና አለማቀፋዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ጥንካሬዎችን እና ጉድለቶችን በዝርዝር በማየት ያሉትን ተግዳሮቶች ለመከላከል የሚያስችል አቅጣጫ እንደሚያስቀምጥም ተጠቁሟል።እነዚህ ተግዳሮች የሚፈጥሩትን ጫና ከክልሉ ህዝብ ነበራዊ ሁኔታ ጋር በማያያዝ በመልካም አስተዳደር፣ ልማት እና የህዝብ ህልውና ያሉትን ሁኔታዎች ገምግሞ የውሳኔ ሃሳብ እንደሚያስቀምጥ ተነግሯል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የ2019 የኖቤል የሰላም ሽልማት ሊያሸንፉ እንደሚችሉ ተጠቆመ!
በመጪው አርብ በኖርዌይ መዲና ኦስሎ በሚዘጋጀው የ2019 የኖቤል የሰላም ሽልማት ያሸንፋሉ ተብለው ከሚጠበቁ ሰዎች አንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ሊሆኑ እንደሚችሉ ታይም መፅሄት አስነብቧል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ከሁለት አስርት አመታት ፍጥጫ እልባት በመስጠት፤ ሰላም በማምጣት፣ የፖለቲካ እስረኞችን በመፍታትና ሌሎች ባመጧቸውም መሻሻሎች ሽልማቱን ሊያሸንፉ እንደሚችሉ በእንግሊዝ የተለያዩ ፖለቲካዊ ትንበያዎችን በመስጠት የሚወራረደው ላድብሮክ አሳውቋል። ድርጅቱ (4/1)(Odd) ሊያሸንፉ እንደሚችሉ ግምቱን አስቀምጧል።
ዓመታዊው ሽልማት በአለም ውስጥ ለሰላም አስተዋፅኦ ያደረጉ ግለሰቦችን ወይም ድርጅቶችን እውቅና ይሰጣል። በባለፈው ዓመት የኮንጎ ዜግነት ያለው ዶክተር ዴኒስ ሙክዌጋና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቿ ናዲያ ሙራድ ወሲባዊ ጥቃትን ለጦርነት መሳሪያነት መጠቀሚያነት ለማቆም በሰሩት ስራ አሸናፊ ሆነዋል።በዚህ ዓመቱ ሽልማት 301 ዕጩዎች ያሉ ሲሆን፤ 223 ግለሰቦች እንዲሁም 78 ድርጅቶች መሆናቸውንም የኖቤል ተቋም አስታውቋል። ምንም እንኳን እነማን ዕጩዎች እንደሆኑ ባይታወቁም የተለያዩ ግለሰቦችና ድርጅቶች ግምቶቻቸውን እያስቀመጡ ነው።ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ በተጨማሪ የአየር ንብረት ለውጥ ተሟጋቿ ግሬታ ተንበርግና የኒውዚላንዷ ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አርደርን ግምት ተሰጥቷቸዋል።
ምንጭ፡-ቢቢሲ
@YeneTube @FikerAssefa
በመጪው አርብ በኖርዌይ መዲና ኦስሎ በሚዘጋጀው የ2019 የኖቤል የሰላም ሽልማት ያሸንፋሉ ተብለው ከሚጠበቁ ሰዎች አንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ሊሆኑ እንደሚችሉ ታይም መፅሄት አስነብቧል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ከሁለት አስርት አመታት ፍጥጫ እልባት በመስጠት፤ ሰላም በማምጣት፣ የፖለቲካ እስረኞችን በመፍታትና ሌሎች ባመጧቸውም መሻሻሎች ሽልማቱን ሊያሸንፉ እንደሚችሉ በእንግሊዝ የተለያዩ ፖለቲካዊ ትንበያዎችን በመስጠት የሚወራረደው ላድብሮክ አሳውቋል። ድርጅቱ (4/1)(Odd) ሊያሸንፉ እንደሚችሉ ግምቱን አስቀምጧል።
ዓመታዊው ሽልማት በአለም ውስጥ ለሰላም አስተዋፅኦ ያደረጉ ግለሰቦችን ወይም ድርጅቶችን እውቅና ይሰጣል። በባለፈው ዓመት የኮንጎ ዜግነት ያለው ዶክተር ዴኒስ ሙክዌጋና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቿ ናዲያ ሙራድ ወሲባዊ ጥቃትን ለጦርነት መሳሪያነት መጠቀሚያነት ለማቆም በሰሩት ስራ አሸናፊ ሆነዋል።በዚህ ዓመቱ ሽልማት 301 ዕጩዎች ያሉ ሲሆን፤ 223 ግለሰቦች እንዲሁም 78 ድርጅቶች መሆናቸውንም የኖቤል ተቋም አስታውቋል። ምንም እንኳን እነማን ዕጩዎች እንደሆኑ ባይታወቁም የተለያዩ ግለሰቦችና ድርጅቶች ግምቶቻቸውን እያስቀመጡ ነው።ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ በተጨማሪ የአየር ንብረት ለውጥ ተሟጋቿ ግሬታ ተንበርግና የኒውዚላንዷ ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አርደርን ግምት ተሰጥቷቸዋል።
ምንጭ፡-ቢቢሲ
@YeneTube @FikerAssefa
📌ኢህአዴግ ውህድ ፓርቲ ቢሆን ኖሮ አሁን እያስተዋልን ያለነውን የአማራና ትግራይ ክልሎች ህዝብን በተለያየ መንገድ እየቀሰቀሱ ግጭት ውስጥ አይገቡም ነበር፤
📌 ኢህአዴግ ተከፋፍሎ አገርን አንድ ማድረግ አይችልም፣ መጀመሪያ ራሱ አንድ መሆን መቻል አለበት፣
📌 ስለኢትዮጵያ አንድነት ማውራት አሃዳዊነት አይደለም “Unity & Unitary” ይለያያል፤ ውህድ ፓርቲ አህዳዊነትን አያመጣም፤ ይልቁንም አንድነትን ያጠናክራል።
📌 አሜሪካ የሚመሩት ውህድ ፓርቲዎች ናቸው፤ አገሪቱ ግን ፌዴራላዊ ናት፤
📌 ኢህአዴግ ከተዋሃደ ኃላፊነት የሚሰማው ድርጅት ይሆናል ብዬ አስባለሁ፤ አፈናም ሆነ የመብት ጥበቃ ካለ በሁሉም አካባቢዎች እኩል ይሆናል ማለት ነው። አሁን ላይ ትግራይ ውስጥ ከህወሃት ውጪ ሌላ ፓርቲ አናስተናግድም እየተባለ ሌላው እየተገፋ ነው ያለው።
ኢህአዴግ ወደ ውህድ ፓርቲነት የሚያደርገው ጉዞን በተመለከተ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ከኤፍ ቢሲ ጋር ካደረጉት ቆይታ የተወሰደ።
@YeneTube @FikerAssefa
📌 ኢህአዴግ ተከፋፍሎ አገርን አንድ ማድረግ አይችልም፣ መጀመሪያ ራሱ አንድ መሆን መቻል አለበት፣
📌 ስለኢትዮጵያ አንድነት ማውራት አሃዳዊነት አይደለም “Unity & Unitary” ይለያያል፤ ውህድ ፓርቲ አህዳዊነትን አያመጣም፤ ይልቁንም አንድነትን ያጠናክራል።
📌 አሜሪካ የሚመሩት ውህድ ፓርቲዎች ናቸው፤ አገሪቱ ግን ፌዴራላዊ ናት፤
📌 ኢህአዴግ ከተዋሃደ ኃላፊነት የሚሰማው ድርጅት ይሆናል ብዬ አስባለሁ፤ አፈናም ሆነ የመብት ጥበቃ ካለ በሁሉም አካባቢዎች እኩል ይሆናል ማለት ነው። አሁን ላይ ትግራይ ውስጥ ከህወሃት ውጪ ሌላ ፓርቲ አናስተናግድም እየተባለ ሌላው እየተገፋ ነው ያለው።
ኢህአዴግ ወደ ውህድ ፓርቲነት የሚያደርገው ጉዞን በተመለከተ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ከኤፍ ቢሲ ጋር ካደረጉት ቆይታ የተወሰደ።
@YeneTube @FikerAssefa
በትናንትናዉ ዕለት በዳውሮ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ 2 የሞት 29 ቀላል እና 14 ከባድ አደጋ መድረሱ ተገለፀ!
ትናንት 27/01/2012 ዓ.ም በደረሰዉ የትራፊክ አደጋ 2 የሞት 29 ቀላል እና 14 ከባድ አደጋ መድረሱን የዳዉሮ ዞን ወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ዋና ሥራ ሂደት አስተባባሪ ኮማንደር አክሊሉ አሥራት ገልፀዋል።ትናንት ጠዋት ከወላይታ ሶዶ መነሃሪያ ወደ ዳዉሮ ዋካ መድረሻ ያደረገዉ ደህ-18375 የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ 43 ተሣፋሪዎችን የጫነ ሲሆን ዋካ ከተማ ለመድረስ በግምት 10 ኪ.ሜ ሲቀረዉ የመገልበጥ አደጋ ደርሶበታል።
እንደ ዞኑ ወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ዋና ሥራ ሂደት አስተባባሪ ገለጻ የአደጋዉ መነሻ ሁለት የኋላ ጎማ መፈንዳት ሲሆን ከፍተኛ የሆነ ፍጥነት አደጋዉ እንዲባባስ አድርጎታል።በፍጥነት ሲጓዝ የነበረዉ ተሽከርካሪ በሾፈሩ በኩል ከወደቀ በኋላ 30ሜትር ያህል በአስፓልት ተንሸራቶ ከመንገዱ በስተቀኝ በኩል ወደሚገኘዉ ተዳፋት ቦታ ነበር የገባው።በአደጋዉ የሞቱት አንድ ወንድ እና አንድ ሴት ሲሆኑ ዕድሜያቸዉ ከ30 የማይበልጥ 25 ወጣቶች ተሣፋሪዎች የአደጋዉ ተጎጂ መሆናቸዉን የዞኑ ወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ኃላፊዉ ገልፀዋል።
ምንጭ:የዳዉሮ ዞን ህዝብ ግኑኝነት ጽ/ቤት
@YeneTube @FikerAssefa
ትናንት 27/01/2012 ዓ.ም በደረሰዉ የትራፊክ አደጋ 2 የሞት 29 ቀላል እና 14 ከባድ አደጋ መድረሱን የዳዉሮ ዞን ወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ዋና ሥራ ሂደት አስተባባሪ ኮማንደር አክሊሉ አሥራት ገልፀዋል።ትናንት ጠዋት ከወላይታ ሶዶ መነሃሪያ ወደ ዳዉሮ ዋካ መድረሻ ያደረገዉ ደህ-18375 የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ 43 ተሣፋሪዎችን የጫነ ሲሆን ዋካ ከተማ ለመድረስ በግምት 10 ኪ.ሜ ሲቀረዉ የመገልበጥ አደጋ ደርሶበታል።
እንደ ዞኑ ወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ዋና ሥራ ሂደት አስተባባሪ ገለጻ የአደጋዉ መነሻ ሁለት የኋላ ጎማ መፈንዳት ሲሆን ከፍተኛ የሆነ ፍጥነት አደጋዉ እንዲባባስ አድርጎታል።በፍጥነት ሲጓዝ የነበረዉ ተሽከርካሪ በሾፈሩ በኩል ከወደቀ በኋላ 30ሜትር ያህል በአስፓልት ተንሸራቶ ከመንገዱ በስተቀኝ በኩል ወደሚገኘዉ ተዳፋት ቦታ ነበር የገባው።በአደጋዉ የሞቱት አንድ ወንድ እና አንድ ሴት ሲሆኑ ዕድሜያቸዉ ከ30 የማይበልጥ 25 ወጣቶች ተሣፋሪዎች የአደጋዉ ተጎጂ መሆናቸዉን የዞኑ ወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ኃላፊዉ ገልፀዋል።
ምንጭ:የዳዉሮ ዞን ህዝብ ግኑኝነት ጽ/ቤት
@YeneTube @FikerAssefa
ጅማ ዩንቨርስቲ አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች መግቢያ ቀን ጥቅምት 10 እና 11 መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሰበት ቀን እንድትገቡ ዩንቨርስቲው ያሳስባል።
መረጃውን ያደረሰን ዶክተር ታመነ
@YemeTube @FikerAssefa
መረጃውን ያደረሰን ዶክተር ታመነ
@YemeTube @FikerAssefa
⬆️
ፌስቡክ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ10 የአፍሪካ ሀገራት ሀሰተኛ መረጃዎችን መቀነስ የሚያስችለውን ፕሮግራም ጀመረ!
ፌስቡክ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሃራ በታች በሚገኙ ሀገራት በዛምቢያ ፣ ሶማሊያ ፣ ቡሪኪና ፋሶ ፣ ኡጋንዳ ፣ ታንዛኒያ ፣ በዲሞክራሲያዊ ረፐብሊክ ኮንጎ ፣ ኮትዲቫር ፣ ጊኔ ኮናክሬ እና ጋና ነው ሀሰተኛ መረጃዎችን መቀነስ የሚያስችለውን ፕሮግራም ነው የጀመረው:: ሶስተኛ ወገን መረጃ ማጥሪያ የተሰኘው ይህ ፕሮግራም ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመቀነስ የሚያስችል መሆኑን ፌስቡክ አስታውቋል::
ሀሰተኛ የፌስቡክ ገፆችን መዝጋት፣ እውነተኛ የዜና አማራጮችን ማስተዋወቅ እና የማያስፈልጉ መልዕክቶችን ለሚልኩ አካላት የገንዝብ ድጋፍ የሚያደርጉትን መከላከል ይህ ፕሮግራም ከሚያከናውናቸው አሰራሮች ውስጥ ይካተታሉ ተብሏል፡፡
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ፌስቡክ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ10 የአፍሪካ ሀገራት ሀሰተኛ መረጃዎችን መቀነስ የሚያስችለውን ፕሮግራም ጀመረ!
ፌስቡክ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሃራ በታች በሚገኙ ሀገራት በዛምቢያ ፣ ሶማሊያ ፣ ቡሪኪና ፋሶ ፣ ኡጋንዳ ፣ ታንዛኒያ ፣ በዲሞክራሲያዊ ረፐብሊክ ኮንጎ ፣ ኮትዲቫር ፣ ጊኔ ኮናክሬ እና ጋና ነው ሀሰተኛ መረጃዎችን መቀነስ የሚያስችለውን ፕሮግራም ነው የጀመረው:: ሶስተኛ ወገን መረጃ ማጥሪያ የተሰኘው ይህ ፕሮግራም ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመቀነስ የሚያስችል መሆኑን ፌስቡክ አስታውቋል::
ሀሰተኛ የፌስቡክ ገፆችን መዝጋት፣ እውነተኛ የዜና አማራጮችን ማስተዋወቅ እና የማያስፈልጉ መልዕክቶችን ለሚልኩ አካላት የገንዝብ ድጋፍ የሚያደርጉትን መከላከል ይህ ፕሮግራም ከሚያከናውናቸው አሰራሮች ውስጥ ይካተታሉ ተብሏል፡፡
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
የኬሚስትሪ ዘርፍ የኖቤል ሽልማትን 3 ሳይንቲስቶች ተጋሩት!
የዘንድሮውን የኬሚስትሪ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት የሊቲየም አየን ባትሪን (Lithium-ion battery) ለዓለም ያበረከቱ ሶስት ሳይንቲስቶች ተጋርተውታል።በትውልድ ጀርመናዊ በዜግነት አሜሪካዊ የሆኑት ፕሮፌሰር ጆን ጉድኢነፍ፣ እንግሊዛዊው ስታንሊ ዊቲንግሃም እና ጃፓናዊው አኪራ ዮሺኖ ሽልማቱን በጋራ ወስደዋል።
የ97 ዓመቱ ፕሮፌሰር ጉድኢነፍ ከእስካሁኖቹ ኖቤል ሎሬቶች በእድሜ ትልቁ መሆናቸው ተነግሯል፡፡የሊቲየም አየን ባትሪ በየጊዜው ሊሞላ የሚችል እና ተንቀሳቃሽ ለሆኑ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች የሚውል ነው።የኖቤል ኮሚቴ አባል የሆኑት ኦሎፍ ራምስትሮም እንደተናገሩት ይህ ባትሪ የሞባይሉን ዓለም ያነቃቃ የዘርፉ ይበል የሚያሰኝ ፈጠራ ነው።9 ሚሊዮን ክሮነር ወይም 738 ሺህ ፓውንድ የሚደርሰውን የገንዘብ ሽልማት ሶስቱ ሳይንቲስቶች ይካፈሉታል ተብሏል።
ምንጭ፡- ቢቢሲ/ETV
@YeneTube @FikerAssefa
የዘንድሮውን የኬሚስትሪ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት የሊቲየም አየን ባትሪን (Lithium-ion battery) ለዓለም ያበረከቱ ሶስት ሳይንቲስቶች ተጋርተውታል።በትውልድ ጀርመናዊ በዜግነት አሜሪካዊ የሆኑት ፕሮፌሰር ጆን ጉድኢነፍ፣ እንግሊዛዊው ስታንሊ ዊቲንግሃም እና ጃፓናዊው አኪራ ዮሺኖ ሽልማቱን በጋራ ወስደዋል።
የ97 ዓመቱ ፕሮፌሰር ጉድኢነፍ ከእስካሁኖቹ ኖቤል ሎሬቶች በእድሜ ትልቁ መሆናቸው ተነግሯል፡፡የሊቲየም አየን ባትሪ በየጊዜው ሊሞላ የሚችል እና ተንቀሳቃሽ ለሆኑ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች የሚውል ነው።የኖቤል ኮሚቴ አባል የሆኑት ኦሎፍ ራምስትሮም እንደተናገሩት ይህ ባትሪ የሞባይሉን ዓለም ያነቃቃ የዘርፉ ይበል የሚያሰኝ ፈጠራ ነው።9 ሚሊዮን ክሮነር ወይም 738 ሺህ ፓውንድ የሚደርሰውን የገንዘብ ሽልማት ሶስቱ ሳይንቲስቶች ይካፈሉታል ተብሏል።
ምንጭ፡- ቢቢሲ/ETV
@YeneTube @FikerAssefa
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሲዳማ ብሄር የህዝበ ውሳኔ ማስፈጸሚያ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት በመጪው የህዳር ወር መግቢያ ለሚያካሂደው ህዝበ ውሳኔ የዝግጅት ስራዎችን በማከናወን ላይ አንደሚገኝ አስታውቋል ።
የፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አዳነ ገበየሁ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ «ፅህፈት ቤቱ የክልሉ መንግስትና የሲዳማ ዞን መስተዳድር በህዝበ ውሳኔው የሁሉንም አካላት ጥቅምና ፍላጎት ለማጣጣም የሚያስችሉ አስተዳደራዊና የህግ ማዕቀፎች በመዘጋጀት ላይ ይገኛሉ » ብለዋል ።
Via :-DW
@YeneTube @Fikerassefa
የፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አዳነ ገበየሁ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ «ፅህፈት ቤቱ የክልሉ መንግስትና የሲዳማ ዞን መስተዳድር በህዝበ ውሳኔው የሁሉንም አካላት ጥቅምና ፍላጎት ለማጣጣም የሚያስችሉ አስተዳደራዊና የህግ ማዕቀፎች በመዘጋጀት ላይ ይገኛሉ » ብለዋል ።
Via :-DW
@YeneTube @Fikerassefa
ሰሞኑን በጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ተከስቶ የነበረውን ግጭት ሙሉ ለሙሉ ማስቆም ተችሏል፡፡
ከመስከረም 24/2012 ጀምሮ ተከስቶ የነበረው ግጭት በሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ በሀገር ሽማግሌዎች እና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ባደረጉት ርብርብ ማስቆም ተችሏል፡፡ግጭቱ ተከስቶባቸው ከነበሩ እዝግዬ፣ አርባዋዩ እና መረዋ ሀደሬ ቀበሌዎች ተፈናቅለው የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ወደየ ቀያቸው እንዲመለሱ የማድረግ ስራ ተጀምሯል፡፡የመንግሥት መስሪያ ቤቶች አገልግሎት እንዲጀምሩ ተደርጓል፡፡አከባቢውን ወደ ቀድሞ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለመመለስ እየተሰራ ነው፡፡
ምንጭ:የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን
@YeneTube @FikerAssefa
ከመስከረም 24/2012 ጀምሮ ተከስቶ የነበረው ግጭት በሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ በሀገር ሽማግሌዎች እና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ባደረጉት ርብርብ ማስቆም ተችሏል፡፡ግጭቱ ተከስቶባቸው ከነበሩ እዝግዬ፣ አርባዋዩ እና መረዋ ሀደሬ ቀበሌዎች ተፈናቅለው የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ወደየ ቀያቸው እንዲመለሱ የማድረግ ስራ ተጀምሯል፡፡የመንግሥት መስሪያ ቤቶች አገልግሎት እንዲጀምሩ ተደርጓል፡፡አከባቢውን ወደ ቀድሞ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለመመለስ እየተሰራ ነው፡፡
ምንጭ:የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን
@YeneTube @FikerAssefa
በምሥራቅ ጀርመንዋ ከተማ በሃለ ዛሬ ከቀትር በኋላ በእርምታ ተኩስ ቢያንስ ሁለት ሰዎች ተገደሉ።
ፖሊስ በከተማይቱ በሚገኝ ሙክራብ ፊት ለፊት በተፈጸመው በዚሁ ግድያ ከተጠረጠሩት መካከል አንዱን መያዙን አስታውቋል።ሌሎች ተጠርጣሪዎች በመኪና እንዳመለጡም አስታውቋል።
ተኩሱ ከሙክራቡ ጋር ይያያዝ አይያዝ ግልጽ ባይሆንም ቢልድ የተባለው ጋዜጣ እንደዘገበው በአንድ የአይሁዶች የመቃብር ስፍራ ላይም የእጅ ቦምብ ተወርውሯል።
አንድ የዓይን ምስክር ኤን ቴፋው በተባለው የቴሌቪዥን ጣቢያ እንደተናገሩት ደግሞ አንድ የቱርክ ምግብ መሸጫ ሱቅ ላይም ተተኩሷል።
ጥቃቱ የተፈጸመበት የዛሬው እለት በአይሁዶች ዮም ኪፖር የተባለው የዓመቱ የተቀደሰ ቀን ነው።ፖሊስ ተጠርጣሪዎችን በመፈለግ ላይ ሳለ ነዋሪዎች ከቤታቸው እንዳይወጡ አሳስቦ ነበር።
ብሔራዊው የጀርመን የባቡር አገልግሎት ዶቼ ባን እንዳስታወቀው የሃለ ዋናው ባቡር ጣቢያ ተዘግቶ ነበር።ከሀለው ተኩስ በኋላ ላንድስበርግ በተባለችው ጎረቤት ከተማም ተኩስ መሰማቱ ተዘግቧል። ፖሊስ ዝርዝሩን አላሳወቀም።
Via:- Dw
@Yenetube @FikerAssefa
ፖሊስ በከተማይቱ በሚገኝ ሙክራብ ፊት ለፊት በተፈጸመው በዚሁ ግድያ ከተጠረጠሩት መካከል አንዱን መያዙን አስታውቋል።ሌሎች ተጠርጣሪዎች በመኪና እንዳመለጡም አስታውቋል።
ተኩሱ ከሙክራቡ ጋር ይያያዝ አይያዝ ግልጽ ባይሆንም ቢልድ የተባለው ጋዜጣ እንደዘገበው በአንድ የአይሁዶች የመቃብር ስፍራ ላይም የእጅ ቦምብ ተወርውሯል።
አንድ የዓይን ምስክር ኤን ቴፋው በተባለው የቴሌቪዥን ጣቢያ እንደተናገሩት ደግሞ አንድ የቱርክ ምግብ መሸጫ ሱቅ ላይም ተተኩሷል።
ጥቃቱ የተፈጸመበት የዛሬው እለት በአይሁዶች ዮም ኪፖር የተባለው የዓመቱ የተቀደሰ ቀን ነው።ፖሊስ ተጠርጣሪዎችን በመፈለግ ላይ ሳለ ነዋሪዎች ከቤታቸው እንዳይወጡ አሳስቦ ነበር።
ብሔራዊው የጀርመን የባቡር አገልግሎት ዶቼ ባን እንዳስታወቀው የሃለ ዋናው ባቡር ጣቢያ ተዘግቶ ነበር።ከሀለው ተኩስ በኋላ ላንድስበርግ በተባለችው ጎረቤት ከተማም ተኩስ መሰማቱ ተዘግቧል። ፖሊስ ዝርዝሩን አላሳወቀም።
Via:- Dw
@Yenetube @FikerAssefa
በምዕራብ ሸዋ ዞን ጅባት ወረዳ ዛሬ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ። በአደጋው 38 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱም ተገልጿል።
በምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ ማኔጅመንት ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ተሰማ ብሩ እንደገለጹት አደጋው የደረሰው ዛሬ ከረፋዱ 5፡30 ሰዓት ላይ ነው።
አርባ ሰዎችን አሳፍሮ ከኖኖ ወረዳ በመነሳት ወደ አምቦ ከተማ ይጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3–37423 (ኦሮ) የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በመገልበጡ ነው አደጋው ሊደርስ የቻለው።
አደጋው በጅባት ወረዳ ጋሞ ቀበሌ ልዩ ስሙ ጆሬ በተባላ አካባቢ መድረሱን የገለጹት ኮማንደር ተሰማ፣ በእዚህም የሁለት መምህራን ሕይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ በ48 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል። የመኪናው አሽከርካሪ ለጊዜው መሰወሩንና ክትትል እየተደረገበት መሆኑንም ተናግረዋል።
እንደኮማንደር ተሰማ ገለጻ በአደጋው ሕይወታቸውን ያጡ ሰዎች አስከሬን ለቤተሰቦቻቸው ተሰጥቷል።
ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው 11 ሰዎችም በአምቦ ሆስፒታል የሕክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ነው የገለጹት። የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል።
Via:- ENA
@YeneTube @Fikerassefa
በምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ ማኔጅመንት ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ተሰማ ብሩ እንደገለጹት አደጋው የደረሰው ዛሬ ከረፋዱ 5፡30 ሰዓት ላይ ነው።
አርባ ሰዎችን አሳፍሮ ከኖኖ ወረዳ በመነሳት ወደ አምቦ ከተማ ይጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3–37423 (ኦሮ) የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በመገልበጡ ነው አደጋው ሊደርስ የቻለው።
አደጋው በጅባት ወረዳ ጋሞ ቀበሌ ልዩ ስሙ ጆሬ በተባላ አካባቢ መድረሱን የገለጹት ኮማንደር ተሰማ፣ በእዚህም የሁለት መምህራን ሕይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ በ48 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል። የመኪናው አሽከርካሪ ለጊዜው መሰወሩንና ክትትል እየተደረገበት መሆኑንም ተናግረዋል።
እንደኮማንደር ተሰማ ገለጻ በአደጋው ሕይወታቸውን ያጡ ሰዎች አስከሬን ለቤተሰቦቻቸው ተሰጥቷል።
ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው 11 ሰዎችም በአምቦ ሆስፒታል የሕክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ነው የገለጹት። የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል።
Via:- ENA
@YeneTube @Fikerassefa
ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ሕትመት ሊያቆም እንደሚችል ማስጠንቀቁን አዲስ ዘመን አስነብቧል፡፡ በ2 ወራት ውስት ጋዜጦችንና ፈተናዎችን ለማተም እቸገራለሁ ብሏል፡፡ ምክንያቱ ለከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት መጋለጡ ነው፡፡ ከዐመት በፊት እንዲለቀቅለት የጠየቀውን የውጭ ምንዛሬ እስካሁን አላገኘም፡፡ መለዋወጫዎችን፣ አዳዲስ ማሽኖችንና 90 በመቶ የሕትመት ግብዓቶችን በውጭ ምንዛሬ ነው የሚገዛው፡፡
Via Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
Via Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
ቱርክ ወታደሮችዋን ሰሜን ሶሪያ ከማስፈር እንድትቆጠብ ኢራን ጠየቀች።
የኢራን ፕሬዝዳንት ሃሰን ሩሀኒ ዛሬ ለቱርክ ባስተላለፉት ጥሪ ቱርክ ውሳኔዋን እንደገና እንድታጤን ጥሪ አቅርበዋል። ቱርክ የዩናይትድ ስቴትስ ወታደሮች ለቀው በወጡበት በሰሜን ሶሪያ ወታደሮቿን ለማስፈር እየተንቀሳቀሰች ነው። አንድ የቱርክ ባለሥልጣን እንዳሉት የቱርክ ኃይሎች እና ሶሪያ የሚገኙ አማጺያን አጋሮቻቸው በቅርቡ ወደ ሶሪያ ዘልቀው ይገባሉ ብለዋል። የኢራን የምድር ጦርም ከቱርክ ጋር በሚያዋስነው ሰሜን ምዕራብ የሃገሪቱ ክፍል እየዘለቀ ነው። የሶሪያው ፕሬዝዳንት የበሽር አልአሳድ የቅርብ አጋር የሆነችው ኢራን ቱርክ የሶሪያን ድንበር እድታከብር ከዚሁ ጋር ዩናይትድ ስቴትስን ጨምሮ ሶሪያ በሕገ ወጥ መንገድ የሚገኙ የምትላቸው የውጭ ኃይላት ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ በተደጋጋሚ ስትጠይቅ ቆይታለች። ቱርክ እንደምትለው በሰሜን ምሥራቅ ሶሪያ ደህንነቱ የተጠበቀ ቃጣና ለመፍጠር ትሻለች። ዓላማዋም በሚሊዪኖች የሚቆጠሩ ስደተኞችን ወደ አካባቢው መመለስ መሆኑን አስታውቃለች።
ምንጭ:ዶይቼ ወሌ
@YeneTube @FikerAssefa
የኢራን ፕሬዝዳንት ሃሰን ሩሀኒ ዛሬ ለቱርክ ባስተላለፉት ጥሪ ቱርክ ውሳኔዋን እንደገና እንድታጤን ጥሪ አቅርበዋል። ቱርክ የዩናይትድ ስቴትስ ወታደሮች ለቀው በወጡበት በሰሜን ሶሪያ ወታደሮቿን ለማስፈር እየተንቀሳቀሰች ነው። አንድ የቱርክ ባለሥልጣን እንዳሉት የቱርክ ኃይሎች እና ሶሪያ የሚገኙ አማጺያን አጋሮቻቸው በቅርቡ ወደ ሶሪያ ዘልቀው ይገባሉ ብለዋል። የኢራን የምድር ጦርም ከቱርክ ጋር በሚያዋስነው ሰሜን ምዕራብ የሃገሪቱ ክፍል እየዘለቀ ነው። የሶሪያው ፕሬዝዳንት የበሽር አልአሳድ የቅርብ አጋር የሆነችው ኢራን ቱርክ የሶሪያን ድንበር እድታከብር ከዚሁ ጋር ዩናይትድ ስቴትስን ጨምሮ ሶሪያ በሕገ ወጥ መንገድ የሚገኙ የምትላቸው የውጭ ኃይላት ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ በተደጋጋሚ ስትጠይቅ ቆይታለች። ቱርክ እንደምትለው በሰሜን ምሥራቅ ሶሪያ ደህንነቱ የተጠበቀ ቃጣና ለመፍጠር ትሻለች። ዓላማዋም በሚሊዪኖች የሚቆጠሩ ስደተኞችን ወደ አካባቢው መመለስ መሆኑን አስታውቃለች።
ምንጭ:ዶይቼ ወሌ
@YeneTube @FikerAssefa
የደ/ብ/ብ/ህ/ክልል በመጪው ህዳር መጀመሪያ ላይ ለሚካሄደው የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ ዝግጅት ላይ መሆኑን ዐስታወቀ።
ክልሉ የሲዳማ ብሔር የህዝበ ውሳኔ ማስፈጸሚያ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ገበየሁ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ህዳር 3 ቀን፤ 2012 ዓም ከሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ በፊት በህዝበ ውሳኔው ወቅት እና ከህዝበ ውሳኔው በኋላ የሚከናወኑ ተግባራት ተለይተዋል። ኃላፊው እንዳሉት የክልሉ መንግሥት እና የሲዳማ ዞን መስተዳድር በህዝበ ውሳኔው የሁሉንም አካላት ጥቅም እና ፍላጎት ማጣጣም የሚያስችሉ አስተዳደራዊ እና የሕግ ማዕቀፎችን እያዘጋጁ ነው። በህዝበ ውሳኔው ሲዳማ ራሱን ችሎ የሚደራጅ ከሆነ የጋራ የሀብት ክፍፍል እና የሥልጣን ርክክብን እንዴት እንደሚሆን ተጠይቀውም መልስ ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ ዝግጅቱ ከክልሉ መንግሥት እና ከሲዳማ ዞን መስተዳደር በኩል ተጓቷል ሲል ዐስታውቋል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
ክልሉ የሲዳማ ብሔር የህዝበ ውሳኔ ማስፈጸሚያ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ገበየሁ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ህዳር 3 ቀን፤ 2012 ዓም ከሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ በፊት በህዝበ ውሳኔው ወቅት እና ከህዝበ ውሳኔው በኋላ የሚከናወኑ ተግባራት ተለይተዋል። ኃላፊው እንዳሉት የክልሉ መንግሥት እና የሲዳማ ዞን መስተዳድር በህዝበ ውሳኔው የሁሉንም አካላት ጥቅም እና ፍላጎት ማጣጣም የሚያስችሉ አስተዳደራዊ እና የሕግ ማዕቀፎችን እያዘጋጁ ነው። በህዝበ ውሳኔው ሲዳማ ራሱን ችሎ የሚደራጅ ከሆነ የጋራ የሀብት ክፍፍል እና የሥልጣን ርክክብን እንዴት እንደሚሆን ተጠይቀውም መልስ ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ ዝግጅቱ ከክልሉ መንግሥት እና ከሲዳማ ዞን መስተዳደር በኩል ተጓቷል ሲል ዐስታውቋል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
Audio
በማዕከላዊ ጎንደር በቅማንት ማኅበረሰብና በአማራ ማኅበረሰብ መካከል ደም እያፋሰሰ ያለውን ችግር የፈጠሩ ናቸው የተባሉ ኃይሎች በህግ መጠየቅ አለባቸው ሲሉ የክልሉ ፕሬዚዳንት የህግ አማካሪ አስታወቁ፡፡አማራ ክልላዊ መንግሥት ችግሩን ለመፍታት አውንታዊ ርምጃዎች ወስዷል ቢባልም ዳተኛም እንደሆነም ተጠቆመ፡፡ የፌዴራል መንግሥቱ አስቸኳይ ህጋዊ ዕርምጃ አንዲወስድም ተጠይቋል፡፡
⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️
የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Via VOA
@YeneTube @FikerAssefa
⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️
የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Via VOA
@YeneTube @FikerAssefa
እንደምን አደርሽ ኢትዮጵያ። ዛሬ የመደመር እሳቤ ማሳያ የሆነው የአንድነት ፓርክ ምረቃ ሲሆን፣ ያለፉትን ታሪካዊና ማህበራዊ እሴቶቻችን እየዘከርንና ለመጪው ትውልድ እያጎለበትን እንድንሄድ ተጋብዘናል። አንድነት ፓርክ ለጋራ ግባችን በአንድነት ቆመን የፍፃሜውን ምዕራፍ ዘመን ተሻጋሪ በሆነ የሕብረት አቅም ማጠናቀቅ የመቻላችን ተምሳሌት ነው።
__________________________________
የብሔራዊ ቤተ መንግስትን ለመጎብኘት የሚያስችልዎትን ትኬት ሊንኩን በመጫን ማግኘት ይችላሉ።
Book your ticket here the link below.
https://ticket.ethiotelecom.et/unitypark/ticket/
_____________________________
Via :-PMOffice
@YeneTube @Fikerassefa
__________________________________
የብሔራዊ ቤተ መንግስትን ለመጎብኘት የሚያስችልዎትን ትኬት ሊንኩን በመጫን ማግኘት ይችላሉ።
Book your ticket here the link below.
https://ticket.ethiotelecom.et/unitypark/ticket/
_____________________________
Via :-PMOffice
@YeneTube @Fikerassefa
የአንድነት ፓርክ የምረቃ ፕሮግራም ላይ የሚገኙ የሀገራት መሪዎች አዲስ አበባ እየገቡ ነው!
አዲሱ የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላህ ሀምዶክ ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን የሶማልያ እና የኬንያ መሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መሪዎችም ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Via EPA/Elias Meseret
@YeneTube @FikerAssefa
አዲሱ የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላህ ሀምዶክ ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን የሶማልያ እና የኬንያ መሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መሪዎችም ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Via EPA/Elias Meseret
@YeneTube @FikerAssefa