<<ይህ ዓይነቱ ስርዓተ አምልኮ ከምዕራባውያን የተወረሰ ከቤተክርስቲያን ታሪክ ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ የአርጤምስስ ጣኦት በኢትዮጵያ ቆመ እንዴ? የሚያሰኝ ነው። ካህናቱም ይህን አምልኮ ባዕድ መቃወምና ህዝቡን ማስተማር እንጂ አሰሪና አጣኝ መሆን የላባቸውም>> ያሉት ደግሞ #መምህር #ደጉ #ዓለም #ካሳ #በቅድስት ሥላሴ #መንፈሳዊ #ኮሌጅ #የሃዲስ መምህር ናቸው። #መምህር ደጉ በመቀጠልም <<ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በታላላቅ አድባራትና ገዳማት ሳይቀር የጌታችን፣ የእመቤታችን፣ የቅዱሳን መላእክትና የቅዱሳን ሰዎችን የተቀረጸ ምስል ማቆም ለሃውልት መስገድና ማጠን እየተለመደ መቷል። እንዲያውም አንድ ምዕመን 200 ሺህ ብር አውጥተው ማሰራታቸውን ነግረውኛል። እጣንና ጧፍ ያጡ የገጠር አብያተ ክርስቲያናት እየተዘጉ ይኽን ያክል ወጪ ለአምልኮ ባዕድ ማውጣት በእግዚአብሔርም በህሌናም የሚያስከስስ የሚያስወቅስ ነው>> በማለት #አሳሳቢነቱን ገልጸዋል[7]።