✞ ደጓ እናቴ ማርያም ✞
1.21K subscribers
178 photos
11 videos
29 files
137 links
ከፍቅሯ ርቃቹ የምትኖሩ ማርያም ፊደል ናት ኑ ተማሩ
ለአባ ሕርያቆስ ፤
ለቅዱስ ኤፍሬም ፤
ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣
ለአባ ይስሀቅ
የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤
ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!
@embtee
@embtee

@Binyama1

@yitayal_bot

Contact @Maryamawit_bot
Download Telegram
ሰ. መጠሪያ ስም
አንዳንዶች ደግሞ የልጆቻቸውን ስም የሚሰይሙት ባለማስተዋልና በግድ የለሽነት ነው፡፡ ሰው በእግዚአብሔር ስም ሊጠራ አይገባውም፣ የእግዚአብሔር ስም የእርሱ ብቻ ነውና፡፡ ነገር ግን የልጆቻቸውን ስም ለምሳሌ አማኑኤል፣ ኤልሻዳይ፣ አዶናይ፣ ኢየሱስ ወዘተ… በማለት የሚሰይሙ ሰዎች የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ እየጠሩ ናቸው፡፡ #አማኑኤል$ ማለት የወልደ እግዚአብሔር የተዋሕዶ ስሙ ነው፣ #እግዚአብሔር ከእኛ ጋር›› ማለት ነው፡፡ የሚገልጠውም እግዚአብሔር ሰው የመሆኑን ምሥጢር ነው፡፡ ታዲያ ይህ ስም ልንጠራበት ይገባናል? #ኤልሻዳይ$ ማለት ‹‹ሁሉን ማድረግ የሚችል›› ማለት ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔርን ከሐሊነት የሚያመለክት ነው፡፡ ማነው #ከሐሌ ኩሉ$ በዚህ ስም ሊጠራ የሚደፍር? ማንም ከቶ ሊኖር አይገባም፡፡ አዶናይም እንዲሁ፡፡ ወልደ አማኑኤል (የአማኑኤል ልጅ)፣ ገብረ ኢየሱስ (የኢየሱስ አገልጋይ)፣ ገብረ እግዚአብሔር (የእግዚአብሔር አገልጋይ) እያሉ መሰየም ግን ስመ ክርስትና በመሆኑ ተገቢና የሚደገፍም ጭምር ነው፡፡ እንግዲህ በስማችን ኃጢአት እንዳንሠራ፣ የእግዚአብሔርንም ስም በከንቱ እንዳንጠራ መጠንቀቅ ተገቢ ነው፡፡