✞ ደጓ እናቴ ማርያም ✞
1.2K subscribers
178 photos
11 videos
29 files
137 links
ከፍቅሯ ርቃቹ የምትኖሩ ማርያም ፊደል ናት ኑ ተማሩ
ለአባ ሕርያቆስ ፤
ለቅዱስ ኤፍሬም ፤
ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣
ለአባ ይስሀቅ
የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤
ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!
@embtee
@embtee

@Binyama1

@yitayal_bot

Contact @Maryamawit_bot
Download Telegram
ግንቦት አንድ ልደታ የአመት ነው
#ድንግል_ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም፤
በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ) (አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም)
#ልደቷን_የጨለማችን መገፈፍ የዐይናችን ማየት የብርሃናችንም መዉጣት ነዉና በፍጹም ደስታ እናስበዋለን እናከብረዋለንም፡፡"
እመቤታችን የተወለደች እለት አባቷ ኢያቄምና እናቷ ሀና ከመጠን በላይ ተደሰቱ:: የእመቤታችን ልደት ዓለም ማየት የጀመረበት ዕለት ነዉ ማለት ነዉ፡፡ በጨለማ ሲያዩት የሚያስፈራዉና ሌላ የሚመስለዉ ጉቶ ቁጥቋጦዉ ድንጋዩ ጉብታዉ ሁሉ ተራ ነገር መሆኑ የተጋለጠባት ሰዎችም የሰገዱለት ሁሉ አምላክና ጌታ መሆኑ ቀርቶ ድንጋይ ጉብታ መሆኑን ማየት የጀመሩባት ከደገኛዉ ፀሐይ ክርስቶስ ከመውጣት በፊት ከረጅሙ ዘመን ጨለማ ጭንቀት የተገላገልንባት ጨረቃ ብርሂት የቀኝ ዐይን እመቤታችን ማርያም ናት ፡፡ ስለዚህም ልደቷን የጨለማችን መገፈፍ የዐይናችን ማየት የብርሃናችንም መዉጣት ነዉና በፍጹም ደስታ እናስበዋለን እናከብረዋለንም፡፡
እመቤታችን_እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ከልደቷ ረድኤት በረከት ይክፈለን አሜን ።