ሰ. መጠሪያ ስም
አንዳንዶች ደግሞ የልጆቻቸውን ስም የሚሰይሙት ባለማስተዋልና በግድ የለሽነት ነው፡፡ ሰው በእግዚአብሔር ስም ሊጠራ አይገባውም፣ የእግዚአብሔር ስም የእርሱ ብቻ ነውና፡፡ ነገር ግን የልጆቻቸውን ስም ለምሳሌ አማኑኤል፣ ኤልሻዳይ፣ አዶናይ፣ ኢየሱስ ወዘተ… በማለት የሚሰይሙ ሰዎች የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ እየጠሩ ናቸው፡፡ #አማኑኤል$ ማለት የወልደ እግዚአብሔር የተዋሕዶ ስሙ ነው፣ #እግዚአብሔር ከእኛ ጋር›› ማለት ነው፡፡ የሚገልጠውም እግዚአብሔር ሰው የመሆኑን ምሥጢር ነው፡፡ ታዲያ ይህ ስም ልንጠራበት ይገባናል? #ኤልሻዳይ$ ማለት ‹‹ሁሉን ማድረግ የሚችል›› ማለት ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔርን ከሐሊነት የሚያመለክት ነው፡፡ ማነው #ከሐሌ ኩሉ$ በዚህ ስም ሊጠራ የሚደፍር? ማንም ከቶ ሊኖር አይገባም፡፡ አዶናይም እንዲሁ፡፡ ወልደ አማኑኤል (የአማኑኤል ልጅ)፣ ገብረ ኢየሱስ (የኢየሱስ አገልጋይ)፣ ገብረ እግዚአብሔር (የእግዚአብሔር አገልጋይ) እያሉ መሰየም ግን ስመ ክርስትና በመሆኑ ተገቢና የሚደገፍም ጭምር ነው፡፡ እንግዲህ በስማችን ኃጢአት እንዳንሠራ፣ የእግዚአብሔርንም ስም በከንቱ እንዳንጠራ መጠንቀቅ ተገቢ ነው፡፡
አንዳንዶች ደግሞ የልጆቻቸውን ስም የሚሰይሙት ባለማስተዋልና በግድ የለሽነት ነው፡፡ ሰው በእግዚአብሔር ስም ሊጠራ አይገባውም፣ የእግዚአብሔር ስም የእርሱ ብቻ ነውና፡፡ ነገር ግን የልጆቻቸውን ስም ለምሳሌ አማኑኤል፣ ኤልሻዳይ፣ አዶናይ፣ ኢየሱስ ወዘተ… በማለት የሚሰይሙ ሰዎች የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ እየጠሩ ናቸው፡፡ #አማኑኤል$ ማለት የወልደ እግዚአብሔር የተዋሕዶ ስሙ ነው፣ #እግዚአብሔር ከእኛ ጋር›› ማለት ነው፡፡ የሚገልጠውም እግዚአብሔር ሰው የመሆኑን ምሥጢር ነው፡፡ ታዲያ ይህ ስም ልንጠራበት ይገባናል? #ኤልሻዳይ$ ማለት ‹‹ሁሉን ማድረግ የሚችል›› ማለት ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔርን ከሐሊነት የሚያመለክት ነው፡፡ ማነው #ከሐሌ ኩሉ$ በዚህ ስም ሊጠራ የሚደፍር? ማንም ከቶ ሊኖር አይገባም፡፡ አዶናይም እንዲሁ፡፡ ወልደ አማኑኤል (የአማኑኤል ልጅ)፣ ገብረ ኢየሱስ (የኢየሱስ አገልጋይ)፣ ገብረ እግዚአብሔር (የእግዚአብሔር አገልጋይ) እያሉ መሰየም ግን ስመ ክርስትና በመሆኑ ተገቢና የሚደገፍም ጭምር ነው፡፡ እንግዲህ በስማችን ኃጢአት እንዳንሠራ፣ የእግዚአብሔርንም ስም በከንቱ እንዳንጠራ መጠንቀቅ ተገቢ ነው፡፡