✞ ደጓ እናቴ ማርያም ✞:
#ስለ_ቅዱሳን_የሚናገሩ_መጻሕፍት_ያስፈልጉናል።
ስለ ቅዱሳት መጻህፍት አለማወቅ ጥልቅ ወደ ሆነ የክህደትና
ስህተት ዐዘቅት ውስጥ ይጥላል፡፡ ጌታችን በወንጌል ‹መጻህፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ።›
ማቴ 22፤29 እንዳለ፡፡ የአበው ቅዱሳንን ተጋድሎ የሚነግሩን
አዋልድ መጻህፍት አሥራው መጻህፍትን (መጽሐፍ ቅዱስን) ያብራራሉ ይተረጉማሉ፡፡
ለአንዳንዶች እንደሚመስላቸው ገድላት ወደ ገደል አይከቱም
ከገደል ያወጣሉ እንጂ፡፡ ገድላት የእግዚአብሔርን ቃል ለመፈጸም
እንደ ቃሉ ለመመላለስ ያግዙናል፡፡ ‹የእግዚአብሔርን ቃል
የተናገሩዋችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ የኑሩዋቸውንም ፍሬ
እየተመለከታችሁ በእምነታችሁ ምሰሉዋቸው› ዕብ 13፤7
‹እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ።›
ኤፌ 5፤1 ‹በነፍሳችሁ ዝላችሁ እነዳትደክሙ እነዲህ ባለ መቃወም የጸናውን
አስቡ።› ዕብ 12 ፤ 2-5 በማለት ቅዱሳንን እንድንከተል
የሚያዙንን የልዑል ቃላት የቅዱሳኑን ታሪክ ተጋድሎ ሕይወት
የሚተርክልንን ገድላቸውን ሳናነብ እንዴት መፈጸም አንችላለን?
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ፈጣሪነት ጌትነት ኃያልነት
እንደሚነግረን የቅዱሳንንም ተጋድሎ ታሪክ ተአምር በሁለት
መንገድ ይነግረናል ፡፡
1ኛ ከሌሎች ታሪኮች ጋር አሰናስሎ አያይዞ ምሳሌ በዘፍጥረት
የአብርሃም የይስኃቅ የሔኖክና የሌሎች ቅዱሳን ታሪክ በዘጸዐት
የሙሴ የኢያሱ የካሌብ በመሳፍንት የጌድዮን የዮፍታሔ
በሐዋርያት ሥራ የሐዋርያትን የሳሙኤልን፤ የኤልሳዕን፤የኤልያስን
፤የናቡቴን፤ የዳዊትን ፤ የሰለሞንን ታሪኮች በመጽሐፈ ነገሥት እና
መጽሐፈ ሳሙኤል መጻሕፍት እናገኛለን ፡፡
2ኛ የቅዱሳኑን ታሪክ ለብቻው ምሳሌ መጽሐፈ አስቴር የአስቴርን
ታሪክ ፤ መጽሐፈ ኢዮብ የኢዮብን ታሪክ ፤ መጽሐፈ ሩት የሩትን
ታሪከ ፤ ፤ መጽሐፈ ጦቢት የጦቢትን ታሪክ ይነግረናል
መጽሐፍ ቅዱስ የቅዱሳንን ታሪክ እንድናነብ አዋልድ መጻሕፍትን
አንድንመለከት ይጋብዘናል ለዚህ አስረጂ የሚሆኑን ጥቂት ኃይለ
ቃላትትን ለማየት ‹የቀረውም የሰለሞንን ነገር ያደረገውም ሁሉ
ጥበቡም እነሆ በሰሎሞን ታሪክ መጽሐፍ ተጽፎዋል።› 1 ነገ 11፤41 ከዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል የሚከተሉትን ቁምነገሮች
መረዳት እነችላለን
👉የነገረ ቅዱሳን ትምህርት መነሻው መጽሐፍ ቅዱስ ነው ፡፡
ነገረ ማርያም ፤ ነገረ ቅዱሳን እንደምንል ነገረ ሰለሞን አለን።
👉የእግዚአብሔር ቅዱሳን ተአምራት ወ መንክራትን መፈጸም
ይችላሉ ሰለሞን ያደረገውም እንዲል ይኀውም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል ‹በእኔ የሚያምን እኔ
የማደርገውን እርሱ ደግሞ ያደርጋል ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል።› ዮሐ 14 ፤ 12 ያረጋግጥልናል፡፡ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊትም በመዝሙሩ ‹እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው ፡፡› መዝ 67፤ 35 እያለ ይዘምራል፡፡ በተጨማሪም ቅዱሳኑ ፀሐይን እንዳቆሙ ኢያሱ 10 ፤12 በሥጋ ከሞቱ በኃላ በአጥንታቸው ሙት እንዳስነሱ 2 ነገ 13፤20 በጨርቃቸው በበትራቸው ባሕር
እንደከፈሉ 14 ፤16 2ነገ 2 ፤8 ክፉዎች መናፍስትን አንዳወጡ
የሐዋ 19፤11 በሰውነታቸው ጥላ (Shadow) ድውያንን እንደፈወሱ አጋንንትን አንዳወጡ ተአምራትን እንዳደረጉ የሐዋ 5፤15 መጽሐፍ ቅዱስ ይመሰክራል፡፡ ታድያ ገድላት ይህን ሲመሰክሩ ለምን ይተቻሉ?
👉ጠቢቡ ሰለሞን በመጽሀፍ ቅዱስ ከተተረክው ታሪኩ
በተጨማሪ የራሱን ታሪክ ጥበብ ሕይወት የሚተርክ መጽሐፍ
አለው ፡፡‹በሰለሞን ታሪክ መጽሐፍ › አንዲል ገድለ ሰለሞን ማለት
ነው፡፡ ታዲያ ሰለሞን ስለራሱ ታሪክና ስለሰራቸው ሥራዎች
የሚተርክ መጽሐፍ ካለው ያንንም እንድናነብ መጽሐፍ ቅዱስ
ከጋበዘን የሌሎችን ቅዱሳን ታሪክ ለማንበብና ለመቀበል ሰዎች
ለምን የቸገራሉ?
በሌላም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ‹የንጉሱም የዳዊት የፊተኛውና
የኃለኛው ነገር እነሆ በባለ ራዕዩ በሳሙኤል ታሪክ በነቢዩም
በናታን ታሪክ በባለ ራእዩም በጋድ ታሪክ ተጽፏል።› 1ዜና 29፤29
ተብሎ ተጽፋል፡፡ በዚህ ክፍል ሶስት የቅዱሳን የገድል መጻሕፍት ተጠቅሰውልናል
1ኛ የሳሙኤል
2ኛ የናታን
3ኛ የጋድ
መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ቅዱሳን የታሪክ መጻሕፍት ይመራናል::
የቅዱሳን በረከት ይደርብን!
┏━━° •🌺 ° ━━┓
@Embtee
@Embtee
@Embtee
👆 •🌺• 👆 °
#ስለ_ቅዱሳን_የሚናገሩ_መጻሕፍት_ያስፈልጉናል።
ስለ ቅዱሳት መጻህፍት አለማወቅ ጥልቅ ወደ ሆነ የክህደትና
ስህተት ዐዘቅት ውስጥ ይጥላል፡፡ ጌታችን በወንጌል ‹መጻህፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ።›
ማቴ 22፤29 እንዳለ፡፡ የአበው ቅዱሳንን ተጋድሎ የሚነግሩን
አዋልድ መጻህፍት አሥራው መጻህፍትን (መጽሐፍ ቅዱስን) ያብራራሉ ይተረጉማሉ፡፡
ለአንዳንዶች እንደሚመስላቸው ገድላት ወደ ገደል አይከቱም
ከገደል ያወጣሉ እንጂ፡፡ ገድላት የእግዚአብሔርን ቃል ለመፈጸም
እንደ ቃሉ ለመመላለስ ያግዙናል፡፡ ‹የእግዚአብሔርን ቃል
የተናገሩዋችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ የኑሩዋቸውንም ፍሬ
እየተመለከታችሁ በእምነታችሁ ምሰሉዋቸው› ዕብ 13፤7
‹እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ።›
ኤፌ 5፤1 ‹በነፍሳችሁ ዝላችሁ እነዳትደክሙ እነዲህ ባለ መቃወም የጸናውን
አስቡ።› ዕብ 12 ፤ 2-5 በማለት ቅዱሳንን እንድንከተል
የሚያዙንን የልዑል ቃላት የቅዱሳኑን ታሪክ ተጋድሎ ሕይወት
የሚተርክልንን ገድላቸውን ሳናነብ እንዴት መፈጸም አንችላለን?
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ፈጣሪነት ጌትነት ኃያልነት
እንደሚነግረን የቅዱሳንንም ተጋድሎ ታሪክ ተአምር በሁለት
መንገድ ይነግረናል ፡፡
1ኛ ከሌሎች ታሪኮች ጋር አሰናስሎ አያይዞ ምሳሌ በዘፍጥረት
የአብርሃም የይስኃቅ የሔኖክና የሌሎች ቅዱሳን ታሪክ በዘጸዐት
የሙሴ የኢያሱ የካሌብ በመሳፍንት የጌድዮን የዮፍታሔ
በሐዋርያት ሥራ የሐዋርያትን የሳሙኤልን፤ የኤልሳዕን፤የኤልያስን
፤የናቡቴን፤ የዳዊትን ፤ የሰለሞንን ታሪኮች በመጽሐፈ ነገሥት እና
መጽሐፈ ሳሙኤል መጻሕፍት እናገኛለን ፡፡
2ኛ የቅዱሳኑን ታሪክ ለብቻው ምሳሌ መጽሐፈ አስቴር የአስቴርን
ታሪክ ፤ መጽሐፈ ኢዮብ የኢዮብን ታሪክ ፤ መጽሐፈ ሩት የሩትን
ታሪከ ፤ ፤ መጽሐፈ ጦቢት የጦቢትን ታሪክ ይነግረናል
መጽሐፍ ቅዱስ የቅዱሳንን ታሪክ እንድናነብ አዋልድ መጻሕፍትን
አንድንመለከት ይጋብዘናል ለዚህ አስረጂ የሚሆኑን ጥቂት ኃይለ
ቃላትትን ለማየት ‹የቀረውም የሰለሞንን ነገር ያደረገውም ሁሉ
ጥበቡም እነሆ በሰሎሞን ታሪክ መጽሐፍ ተጽፎዋል።› 1 ነገ 11፤41 ከዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል የሚከተሉትን ቁምነገሮች
መረዳት እነችላለን
👉የነገረ ቅዱሳን ትምህርት መነሻው መጽሐፍ ቅዱስ ነው ፡፡
ነገረ ማርያም ፤ ነገረ ቅዱሳን እንደምንል ነገረ ሰለሞን አለን።
👉የእግዚአብሔር ቅዱሳን ተአምራት ወ መንክራትን መፈጸም
ይችላሉ ሰለሞን ያደረገውም እንዲል ይኀውም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል ‹በእኔ የሚያምን እኔ
የማደርገውን እርሱ ደግሞ ያደርጋል ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል።› ዮሐ 14 ፤ 12 ያረጋግጥልናል፡፡ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊትም በመዝሙሩ ‹እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው ፡፡› መዝ 67፤ 35 እያለ ይዘምራል፡፡ በተጨማሪም ቅዱሳኑ ፀሐይን እንዳቆሙ ኢያሱ 10 ፤12 በሥጋ ከሞቱ በኃላ በአጥንታቸው ሙት እንዳስነሱ 2 ነገ 13፤20 በጨርቃቸው በበትራቸው ባሕር
እንደከፈሉ 14 ፤16 2ነገ 2 ፤8 ክፉዎች መናፍስትን አንዳወጡ
የሐዋ 19፤11 በሰውነታቸው ጥላ (Shadow) ድውያንን እንደፈወሱ አጋንንትን አንዳወጡ ተአምራትን እንዳደረጉ የሐዋ 5፤15 መጽሐፍ ቅዱስ ይመሰክራል፡፡ ታድያ ገድላት ይህን ሲመሰክሩ ለምን ይተቻሉ?
👉ጠቢቡ ሰለሞን በመጽሀፍ ቅዱስ ከተተረክው ታሪኩ
በተጨማሪ የራሱን ታሪክ ጥበብ ሕይወት የሚተርክ መጽሐፍ
አለው ፡፡‹በሰለሞን ታሪክ መጽሐፍ › አንዲል ገድለ ሰለሞን ማለት
ነው፡፡ ታዲያ ሰለሞን ስለራሱ ታሪክና ስለሰራቸው ሥራዎች
የሚተርክ መጽሐፍ ካለው ያንንም እንድናነብ መጽሐፍ ቅዱስ
ከጋበዘን የሌሎችን ቅዱሳን ታሪክ ለማንበብና ለመቀበል ሰዎች
ለምን የቸገራሉ?
በሌላም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ‹የንጉሱም የዳዊት የፊተኛውና
የኃለኛው ነገር እነሆ በባለ ራዕዩ በሳሙኤል ታሪክ በነቢዩም
በናታን ታሪክ በባለ ራእዩም በጋድ ታሪክ ተጽፏል።› 1ዜና 29፤29
ተብሎ ተጽፋል፡፡ በዚህ ክፍል ሶስት የቅዱሳን የገድል መጻሕፍት ተጠቅሰውልናል
1ኛ የሳሙኤል
2ኛ የናታን
3ኛ የጋድ
መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ቅዱሳን የታሪክ መጻሕፍት ይመራናል::
የቅዱሳን በረከት ይደርብን!
┏━━° •🌺 ° ━━┓
@Embtee
@Embtee
@Embtee
👆 •🌺• 👆 °