#ሕዳር_ሚካኤል !
#እንኳን_ለመላእክት_አለቃ_ለቅዱስ_ሚካኤል #በዓለ_ሲመት_በሠላም_አደረሰን !
በዓለ ሲመቱ ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል (ሕዳር 12)
(አንብባችሁ ስትጨርሱ ለሌሎችም ታሪኩን እንዲያዉቁ #SHARE_SHARE_SHARE
ብታደርጉ ብዙ አተረፋችሁ፡፡)
ቤተ ክርስቲያን ልጆቹዋ የመላእክትን ተራዳኢነት አውቀው እንዲጠቀሙና የመንግሥቱ ወራሾች ለመሆን እንዲበቁ ስትል ለቅዱሳን መላእክት የመታሰቢያ ቀን በመስጠት በእነርሱ የምናገኛቸውን እርዳታዎች እንዲታወሱ ታደርጋለች፡፡
በዚህም መሠረት በህዳር ወር በዐሥራ ሁለተኛው ቀን ቤተ ክርስቲያናችን የታላቁ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን በዓለ ሲመት በታላቅ ድምቀት ታከብረዋለች፡፡ እንደ ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምህሮ ህዳር 12 ቀን ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በኢዮር ባለችው በአራተኛይቷ ከተማ በሚኖሩት ኃይላት እና በአሥሩ ነገደ መላእክት ላይ አለቃ ሆኖ የተሾመበት ቀን ነው፡፡
እግዚአብሔር ሳጥናኤልን በትዕቢቱ ምክንያት ከሥልጣኑ ገፍፎ ወደ ምድር ሲጥለው ቅዱስ ሚካኤል በእርሱ ቦታ በዐሥሩ ከተማ በመቶውም ነገደ መላእክት ላይ ተሹሟል። ይህን ሁለተኛውን ሹመት ያገኘው በሚያዚያ 2 እንደሆነ አክሲማሮስ በተሰኘው የቤተክርስቲያናችን መጽሐፍ ላይ ሰፍሮ አናገኛለን፡፡
የቅዱስ ሚካኤል ሹመት በነገደ መላእክት ላይ ብቻ ግን አይደለም ፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሆኑት ላይም ጭምር ነው ፡፡ ይህም እንደሆነ እንድንረዳ በብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔር ሕዝብ የተባለውን እስራኤል ዘሥጋን ሲራዳና ሲጠብቅ እንደነበረ ተጽፎልን እናገኛለን፡፡ ለምሳሌ መጽሐፍ ቅዱስ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለኢያሱ በኢያሪኮ ምድረ በዳ እንደተገለጠለት “… ዐይኑን አንሥቶ ተመለከተ እነሆም የተመዘዘ ሰይፍ የያዘ ሰው በፊቱ ቆመ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ “ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህ? አለው፡፡ እርሱም “እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት
አለቃ ሆኜ አሁንም ወደ አንተ መጥቼአለሁ” (ኢያ.5፡13) ይለናል፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ሕዝበ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት ነፃ ሲያወጣቸው ይመራቸው የነበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ ሹመቱ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይም በመሆኑ ስለ እነርሱ ዲያብሎስ ይዋጋው፣ በጸሎትም ይራዳቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ኃጢአት ሠርተው ሲያገኛቸው ለእግዚአብሔር አድልቶ ኃጢአተኞችን ስለሚቀጣ እግዚአብሔር ሕዝቡን “በፊቱ ተጠንቀቁ ቃሉንም አድምጡ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት” (ዘጸ.23፡21) ብሎ አስጠንቅቋቸው ነበር፡፡
ይህም ቅዱስ ሚካኤል በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ መሾሙን ያስረዳናል፡፡ ነገር ግን ከላይ የተጠቀሱት ጥቅሶች ሕዝበ እስራኤልን ይራዳቸው የነበረው ቅዱስ ሚካኤል ስለመሆኑ አያረጋግጥም የሚል ካለ “መልአክ” የተባለው ቅዱስ ሚካኤል ስለመሆኑ ቅዱስ ገብርኤል ወደ ነቢዩ ዳንኤል በተላከ ጊዜ ገልጦልን እናገኛለን፡- ቅዱስ ገብርኤል በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ቅዱስ ሚካኤል ስለመሾሙ ሲመሰክር “በእውነት በመጽሐፍ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፤ በዚህም ነገር ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር የሚረዳኝ ማንም
የለም”(ዳን.10፡21) ብሎአል፡፡
ስለዚህም ለኢያሱ የተገለጠውና እስራኤላውያንንም የመራው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል መሆኑን እንረዳለን፡፡
@christian930 💚
@christian930 💛
@christian930 ❣
የቅዱስ ሚካኤል አለቅነት በሐዲስ ኪዳንም አንደሚቀጥል ይህ ነቢይ በትንቢቱ “በዚያ ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ ሚካኤል ይነሣል..” (ዳን.12፡1) በማለት ተናግሮለታል ፡፡
ስለዚህም ቅዱስ ሚካኤል እኛን ከሰይጣን አሽክላና ወጥመድ ይጠብቀንና በጸሎቱ በእግዚአብሔር ፊት ይቆምልን ዘንድ በእኛም ላይ ሹም ነው። ምክንያቱም እኛ የእግዚአብሔር ሕዝቦችና የርስቱ ወራሾች ነንና፡፡
እግዚአብሔር ነቢዩ ሙሴን የሕዝቡ መሪ አድርጎ መሾሙ እጅግ ትሑትና ስለመንጎቹ ነፍሱን እንኳ አሳልፎ እስከመስጠት ደርሶ ስለሚወዳቸው ነበር፡፡ (ዘኁል.12፡3፤ዘጸአ.32፡32)በሕዝቡም ላይ እርሱን መሾሙ እንዲሠለጥንባቸው ወይም እንዲገዛቸው ሳይሆን በትምህርቱና በጸሎቱ እነርሱን እንዲያግዛቸው ነው፡፡ እንዲህም ስለሆነ ቅዱስ እስጢፋኖስ ስለሙሴ ሲመሰክር “እግዚአብሔር ሹምና ቤዛ አድርጎ ላከው”አለ፡፡ (የሐዋ.7፡35)
እንዲሁ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል እጅግ ትሑትና ለሠራዊቱ ተቆርቋሪ የሆነ መልአክ በመሆኑ በመላእክትና በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ተሾመ፡፡ በመላእክትና በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ መሾሙ ልክ እንደ ሙሴ በእነርሱ ላይ ሊሠለጥንባቸው ወይም ሊገዛቸው ሳይሆን መላእክትን ሊመራ ፣ እኛን ደግሞ ከሰይጣን ጥቃት ሊጠብቀንና በጸሎቱ ሊራዳን ነው (ይሁዳ.12) ፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ቅዱሳን መላእክት እኛን እንደሚጠብቁና እንደሚራዱ እንዲሁም ስለእኛ በፊቱ አንደሚቆሙ ሲያስተምረን “ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን ስንኳ እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፤ መላእክቶቻቸው በሰማያት ሁል ጊዜ በሰማይ ያለውን የአባቴን ፊት ያያሉ እላችኋለሁ” (ማቴ.18፡10) ብሎናል፡፡
እኛን ይጠብቁ ዘንድ የተሰጡን ቅዱሳን መላእክት ስለእኛ እንዲህ የሚቆረቆሩና ስለመዳናችን የሚተጉ ከሆነ በቅድስናው ልቆ የመላእክት አለቃ ሆኖ የተሾመው ቅዱስ ሚካኤል እንዴት ስለእኛ በእግዚአብሔር ፊት ይበልጥ አይቆም? (ሉቃ.13፡6-9) እንዴትስ በተሰጠው ሥልጣንና ኃይል አይረዳን? (መዝ.33፡7) እርሱ “ስለሕዝብህ ልጆች የሚቆመው” መባሉም እኛን በጸሎቱና በተራዳኢነቱ የጽድቅ ሕይወታችንን በሚገባ እንድናከናውን እንደሚራዳን የሚያሳይ ኃይለ ቃል ነው፡፡
የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ጸሎቱና በረከቱ በእኛ ላይ ለዘለዓለሙ ይደርብን አሜን፡፡
@zemaryan
#እንኳን_ለመላእክት_አለቃ_ለቅዱስ_ሚካኤል #በዓለ_ሲመት_በሠላም_አደረሰን !
በዓለ ሲመቱ ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል (ሕዳር 12)
(አንብባችሁ ስትጨርሱ ለሌሎችም ታሪኩን እንዲያዉቁ #SHARE_SHARE_SHARE
ብታደርጉ ብዙ አተረፋችሁ፡፡)
ቤተ ክርስቲያን ልጆቹዋ የመላእክትን ተራዳኢነት አውቀው እንዲጠቀሙና የመንግሥቱ ወራሾች ለመሆን እንዲበቁ ስትል ለቅዱሳን መላእክት የመታሰቢያ ቀን በመስጠት በእነርሱ የምናገኛቸውን እርዳታዎች እንዲታወሱ ታደርጋለች፡፡
በዚህም መሠረት በህዳር ወር በዐሥራ ሁለተኛው ቀን ቤተ ክርስቲያናችን የታላቁ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን በዓለ ሲመት በታላቅ ድምቀት ታከብረዋለች፡፡ እንደ ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምህሮ ህዳር 12 ቀን ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በኢዮር ባለችው በአራተኛይቷ ከተማ በሚኖሩት ኃይላት እና በአሥሩ ነገደ መላእክት ላይ አለቃ ሆኖ የተሾመበት ቀን ነው፡፡
እግዚአብሔር ሳጥናኤልን በትዕቢቱ ምክንያት ከሥልጣኑ ገፍፎ ወደ ምድር ሲጥለው ቅዱስ ሚካኤል በእርሱ ቦታ በዐሥሩ ከተማ በመቶውም ነገደ መላእክት ላይ ተሹሟል። ይህን ሁለተኛውን ሹመት ያገኘው በሚያዚያ 2 እንደሆነ አክሲማሮስ በተሰኘው የቤተክርስቲያናችን መጽሐፍ ላይ ሰፍሮ አናገኛለን፡፡
የቅዱስ ሚካኤል ሹመት በነገደ መላእክት ላይ ብቻ ግን አይደለም ፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሆኑት ላይም ጭምር ነው ፡፡ ይህም እንደሆነ እንድንረዳ በብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔር ሕዝብ የተባለውን እስራኤል ዘሥጋን ሲራዳና ሲጠብቅ እንደነበረ ተጽፎልን እናገኛለን፡፡ ለምሳሌ መጽሐፍ ቅዱስ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለኢያሱ በኢያሪኮ ምድረ በዳ እንደተገለጠለት “… ዐይኑን አንሥቶ ተመለከተ እነሆም የተመዘዘ ሰይፍ የያዘ ሰው በፊቱ ቆመ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ “ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህ? አለው፡፡ እርሱም “እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት
አለቃ ሆኜ አሁንም ወደ አንተ መጥቼአለሁ” (ኢያ.5፡13) ይለናል፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ሕዝበ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት ነፃ ሲያወጣቸው ይመራቸው የነበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ ሹመቱ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይም በመሆኑ ስለ እነርሱ ዲያብሎስ ይዋጋው፣ በጸሎትም ይራዳቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ኃጢአት ሠርተው ሲያገኛቸው ለእግዚአብሔር አድልቶ ኃጢአተኞችን ስለሚቀጣ እግዚአብሔር ሕዝቡን “በፊቱ ተጠንቀቁ ቃሉንም አድምጡ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት” (ዘጸ.23፡21) ብሎ አስጠንቅቋቸው ነበር፡፡
ይህም ቅዱስ ሚካኤል በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ መሾሙን ያስረዳናል፡፡ ነገር ግን ከላይ የተጠቀሱት ጥቅሶች ሕዝበ እስራኤልን ይራዳቸው የነበረው ቅዱስ ሚካኤል ስለመሆኑ አያረጋግጥም የሚል ካለ “መልአክ” የተባለው ቅዱስ ሚካኤል ስለመሆኑ ቅዱስ ገብርኤል ወደ ነቢዩ ዳንኤል በተላከ ጊዜ ገልጦልን እናገኛለን፡- ቅዱስ ገብርኤል በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ቅዱስ ሚካኤል ስለመሾሙ ሲመሰክር “በእውነት በመጽሐፍ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፤ በዚህም ነገር ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር የሚረዳኝ ማንም
የለም”(ዳን.10፡21) ብሎአል፡፡
ስለዚህም ለኢያሱ የተገለጠውና እስራኤላውያንንም የመራው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል መሆኑን እንረዳለን፡፡
@christian930 💚
@christian930 💛
@christian930 ❣
የቅዱስ ሚካኤል አለቅነት በሐዲስ ኪዳንም አንደሚቀጥል ይህ ነቢይ በትንቢቱ “በዚያ ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ ሚካኤል ይነሣል..” (ዳን.12፡1) በማለት ተናግሮለታል ፡፡
ስለዚህም ቅዱስ ሚካኤል እኛን ከሰይጣን አሽክላና ወጥመድ ይጠብቀንና በጸሎቱ በእግዚአብሔር ፊት ይቆምልን ዘንድ በእኛም ላይ ሹም ነው። ምክንያቱም እኛ የእግዚአብሔር ሕዝቦችና የርስቱ ወራሾች ነንና፡፡
እግዚአብሔር ነቢዩ ሙሴን የሕዝቡ መሪ አድርጎ መሾሙ እጅግ ትሑትና ስለመንጎቹ ነፍሱን እንኳ አሳልፎ እስከመስጠት ደርሶ ስለሚወዳቸው ነበር፡፡ (ዘኁል.12፡3፤ዘጸአ.32፡32)በሕዝቡም ላይ እርሱን መሾሙ እንዲሠለጥንባቸው ወይም እንዲገዛቸው ሳይሆን በትምህርቱና በጸሎቱ እነርሱን እንዲያግዛቸው ነው፡፡ እንዲህም ስለሆነ ቅዱስ እስጢፋኖስ ስለሙሴ ሲመሰክር “እግዚአብሔር ሹምና ቤዛ አድርጎ ላከው”አለ፡፡ (የሐዋ.7፡35)
እንዲሁ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል እጅግ ትሑትና ለሠራዊቱ ተቆርቋሪ የሆነ መልአክ በመሆኑ በመላእክትና በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ተሾመ፡፡ በመላእክትና በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ መሾሙ ልክ እንደ ሙሴ በእነርሱ ላይ ሊሠለጥንባቸው ወይም ሊገዛቸው ሳይሆን መላእክትን ሊመራ ፣ እኛን ደግሞ ከሰይጣን ጥቃት ሊጠብቀንና በጸሎቱ ሊራዳን ነው (ይሁዳ.12) ፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ቅዱሳን መላእክት እኛን እንደሚጠብቁና እንደሚራዱ እንዲሁም ስለእኛ በፊቱ አንደሚቆሙ ሲያስተምረን “ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን ስንኳ እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፤ መላእክቶቻቸው በሰማያት ሁል ጊዜ በሰማይ ያለውን የአባቴን ፊት ያያሉ እላችኋለሁ” (ማቴ.18፡10) ብሎናል፡፡
እኛን ይጠብቁ ዘንድ የተሰጡን ቅዱሳን መላእክት ስለእኛ እንዲህ የሚቆረቆሩና ስለመዳናችን የሚተጉ ከሆነ በቅድስናው ልቆ የመላእክት አለቃ ሆኖ የተሾመው ቅዱስ ሚካኤል እንዴት ስለእኛ በእግዚአብሔር ፊት ይበልጥ አይቆም? (ሉቃ.13፡6-9) እንዴትስ በተሰጠው ሥልጣንና ኃይል አይረዳን? (መዝ.33፡7) እርሱ “ስለሕዝብህ ልጆች የሚቆመው” መባሉም እኛን በጸሎቱና በተራዳኢነቱ የጽድቅ ሕይወታችንን በሚገባ እንድናከናውን እንደሚራዳን የሚያሳይ ኃይለ ቃል ነው፡፡
የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ጸሎቱና በረከቱ በእኛ ላይ ለዘለዓለሙ ይደርብን አሜን፡፡
@zemaryan
ወደ ዝምታዬ ተመለስኩ
~የልቤ ደስታ የእረፍቴ ከተማ ሆይ~~
ድንግል ሆይ በማን እና በምን እንድመስልሽ አሰብኩ። በዚህ አለም በሚገኙ ሁሉ አንቺን ይገልጹሽ ዘንድ አወጣሁ አወረድኩ ግን አላገኘሁም። መንፈሴንም አየር አየራት ብልክ ከፍጡራን አንቺን የሚመስልሽ ስላጣሁ ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን ሁሉ በላይ መሆንሽን በማወቅ ልቤ ወደማደሪያው ተመለሰ።
የልቤ ደስታ ሆይ፥- የአዳም ተስፋው ነሽ ብልሽ ለአዳም እና ለእኛ ለልጆቹ ተስፋ ስለሆንሽ ነው፤ ቀስተ ደመናይቱ ሆይ፥- ከጥፋት ውሃ በኋላ እግዚአብሔር ምድርን ዳግመኛ በንፍር ውሃ እንዳያጠፋ ለኖህ የገባለት የኪዳኑ ምልክት ቀስተደመና ነሽ፤ እግዚአብሔር በኃጢያታችን ተቆጥቶ እንዳያጠፋን የባህሪያችን መመኪያ የሆንሽ ቀስተ ደመናችን ነሽ
፥- በኖህ መርከብ ብንመስልሽ ኖህ በመርከቡ የሰበሰባቸውን ፍጥረታት ከጥፋት ውሃ እንደተጠበቁ ሁሉ በአማላጅነትሽ ለምንተማመን ሁሉ በመከራ ከሚመጣ ሞተ ስጋ እና በሃጥያት ከሚመጣ ሞተ ነፍስ ስለምታድኝን ነው።
እናቴ ሆይ፥- ያለውንድ ዘር የወለድሽው ልጅ ሃይል ምርኩዛችን ነው። እጸ ጳጦስ ዘሲና ሆይ፥- ሙሴ በሲና ያየሽ በእሳት የተከበብሽ ቁጥቋጦ አንቺ ነሽ፥-መለኮትን በማህጸንሽ የተሸከምሽ፣ ከነፍስሽ ነፍስ ከስጋሽ ስጋ በነሳ ጊዜ ባህርየ መለኮት ያላቃጠለሽ እና ያለወጠሽ። ያዕቆብ ሎዛ በተባለች ስፍራ በራዕይ መላዕክት ሲወጡና ሲወርዱባት ያየው መሰላሉ ሆይ፥- በአማላጅነትሽ መሰላልነት የሰው ሁሉ ልመና ወደ ባህርይ አምላክ ይደርሳልና።
የእረፍቴ ከተማ ጽዮን ሆይ፥- በታቦተ ጽዮን አስርቱ ትዕዛዛት አድሯል አንቺ ከታቦተ ጽዮን ትበልጫለሽ የህጉ ባለቤት ጌታ በማህጸንሽ አድሯልና። እስራኤላውያን በታቦተ ጽዮን ፍልስጤማውያንን ድል እንዳደረጉ እኛ የሰው ልጆችም ኣንቺ በወለድሽው ልጅ ከዲያቢሎስ እጅ ድነናልና።
@embtee
@embtee
እንዲህ እና እንዲህ እያልኩ ብመስልሽ እንኳ ሁሉ ስላንቺ ያንስብኛል፣ ከምሳሌዎቹ ሁሉ በላይ ነሽ።
ድንግል ሆይ አንቺን እኮ ማመስገን የሚቻለው ልጅሽ ሲፈቅድ ብቻ ነው፣ መልአኩ ከሰማይ አንቺን ለማመስገን ሲመጣ የላከው እግዚአብሔር እንዲያመሰግንሽ ስለፈቀደለት ነው፣ አንቺን እናመሰግንሽ ዘንድ የሚበቃ ማንነትስ ያለን እኛ ማን ነን? እንዲያው በፈቃዱ ሆነ እንጂ። ጽዮን ሆይ እንዲያው ዝም ብዬ እወድሻለሁ አልኩሽ። እኔ ባላመስግንሽ ቢጎልብኝ እንጂ ለአንቺ ዘውትር የምስጋና ወንዘ በፊትሽ ይፍሳል።
ምንም ብል ምንም ብጽፍ ምንም ሆነብኝና ወደ ዝምታዬ ተመለስኩ!!!!!
ድንግል ማርያም ህልማችሁን እውን ታድርግላችሁ
@embtee
@embtee
~የልቤ ደስታ የእረፍቴ ከተማ ሆይ~~
ድንግል ሆይ በማን እና በምን እንድመስልሽ አሰብኩ። በዚህ አለም በሚገኙ ሁሉ አንቺን ይገልጹሽ ዘንድ አወጣሁ አወረድኩ ግን አላገኘሁም። መንፈሴንም አየር አየራት ብልክ ከፍጡራን አንቺን የሚመስልሽ ስላጣሁ ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን ሁሉ በላይ መሆንሽን በማወቅ ልቤ ወደማደሪያው ተመለሰ።
የልቤ ደስታ ሆይ፥- የአዳም ተስፋው ነሽ ብልሽ ለአዳም እና ለእኛ ለልጆቹ ተስፋ ስለሆንሽ ነው፤ ቀስተ ደመናይቱ ሆይ፥- ከጥፋት ውሃ በኋላ እግዚአብሔር ምድርን ዳግመኛ በንፍር ውሃ እንዳያጠፋ ለኖህ የገባለት የኪዳኑ ምልክት ቀስተደመና ነሽ፤ እግዚአብሔር በኃጢያታችን ተቆጥቶ እንዳያጠፋን የባህሪያችን መመኪያ የሆንሽ ቀስተ ደመናችን ነሽ
፥- በኖህ መርከብ ብንመስልሽ ኖህ በመርከቡ የሰበሰባቸውን ፍጥረታት ከጥፋት ውሃ እንደተጠበቁ ሁሉ በአማላጅነትሽ ለምንተማመን ሁሉ በመከራ ከሚመጣ ሞተ ስጋ እና በሃጥያት ከሚመጣ ሞተ ነፍስ ስለምታድኝን ነው።
እናቴ ሆይ፥- ያለውንድ ዘር የወለድሽው ልጅ ሃይል ምርኩዛችን ነው። እጸ ጳጦስ ዘሲና ሆይ፥- ሙሴ በሲና ያየሽ በእሳት የተከበብሽ ቁጥቋጦ አንቺ ነሽ፥-መለኮትን በማህጸንሽ የተሸከምሽ፣ ከነፍስሽ ነፍስ ከስጋሽ ስጋ በነሳ ጊዜ ባህርየ መለኮት ያላቃጠለሽ እና ያለወጠሽ። ያዕቆብ ሎዛ በተባለች ስፍራ በራዕይ መላዕክት ሲወጡና ሲወርዱባት ያየው መሰላሉ ሆይ፥- በአማላጅነትሽ መሰላልነት የሰው ሁሉ ልመና ወደ ባህርይ አምላክ ይደርሳልና።
የእረፍቴ ከተማ ጽዮን ሆይ፥- በታቦተ ጽዮን አስርቱ ትዕዛዛት አድሯል አንቺ ከታቦተ ጽዮን ትበልጫለሽ የህጉ ባለቤት ጌታ በማህጸንሽ አድሯልና። እስራኤላውያን በታቦተ ጽዮን ፍልስጤማውያንን ድል እንዳደረጉ እኛ የሰው ልጆችም ኣንቺ በወለድሽው ልጅ ከዲያቢሎስ እጅ ድነናልና።
@embtee
@embtee
እንዲህ እና እንዲህ እያልኩ ብመስልሽ እንኳ ሁሉ ስላንቺ ያንስብኛል፣ ከምሳሌዎቹ ሁሉ በላይ ነሽ።
ድንግል ሆይ አንቺን እኮ ማመስገን የሚቻለው ልጅሽ ሲፈቅድ ብቻ ነው፣ መልአኩ ከሰማይ አንቺን ለማመስገን ሲመጣ የላከው እግዚአብሔር እንዲያመሰግንሽ ስለፈቀደለት ነው፣ አንቺን እናመሰግንሽ ዘንድ የሚበቃ ማንነትስ ያለን እኛ ማን ነን? እንዲያው በፈቃዱ ሆነ እንጂ። ጽዮን ሆይ እንዲያው ዝም ብዬ እወድሻለሁ አልኩሽ። እኔ ባላመስግንሽ ቢጎልብኝ እንጂ ለአንቺ ዘውትር የምስጋና ወንዘ በፊትሽ ይፍሳል።
ምንም ብል ምንም ብጽፍ ምንም ሆነብኝና ወደ ዝምታዬ ተመለስኩ!!!!!
ድንግል ማርያም ህልማችሁን እውን ታድርግላችሁ
@embtee
@embtee
•እንኳን ደስ አላችሁ የዳዊት ዜማ በዩቲዩብ መቷል!«ተከፈተ»
መንፈስን አዳሽ የሆኑ ዝማሬዎችን አውደ ስብከቶችን ግጥሞች በምስል እና በቪዲዬ በታገዘ ወቅታዊ የሆኑ ዝግጅቶችን ይዘን እንቀርባለን እንዳያመልጦ ከስር የተቀመጠው ሊንኩን ከፍተው ሰብስክራይብ 🔻 ያድርጉት የደወል 🔔 ምልክቱንም ይጫኑ በየእለቱ ወደናንተ የምንለቀው ይደርሶታል እናመሰግናለን !
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://m.youtube.com/channel/UCuzDApz9RTu02VXXFRnwQtg
👆👆👆👆ይክፈቱት👆👆👆👆
(
መንፈስን አዳሽ የሆኑ ዝማሬዎችን አውደ ስብከቶችን ግጥሞች በምስል እና በቪዲዬ በታገዘ ወቅታዊ የሆኑ ዝግጅቶችን ይዘን እንቀርባለን እንዳያመልጦ ከስር የተቀመጠው ሊንኩን ከፍተው ሰብስክራይብ 🔻 ያድርጉት የደወል 🔔 ምልክቱንም ይጫኑ በየእለቱ ወደናንተ የምንለቀው ይደርሶታል እናመሰግናለን !
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://m.youtube.com/channel/UCuzDApz9RTu02VXXFRnwQtg
👆👆👆👆ይክፈቱት👆👆👆👆
(
Watch "|| እግዚአብሔርን የምትወዱ || በሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ tewodros yosef ||| Ethiopia mezmure" on YouTube
https://youtu.be/F0BtpQ7nMIg
https://youtu.be/F0BtpQ7nMIg
YouTube
|| እግዚአብሔርን የምትወዱ || በሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ tewodros yosef ||| Ethiopia mezmure
የእኛን መንፈሳዊ አገልግሎት መደገፍ ማስቀጠል ይፈልጋሉ እንግዲያውስ #SUBSCRIBE በማድረግ ብቻ እኛን ማበረታታት ይችላሉ ።
➠ ለ Telegram
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAFLulNC2J1Sz43spAw
➠ ለ Facebook - https://m.facebook.com/yedawitzema
አስተያየት መልዕክት ጥያቄ ካለዎት
♦️ Email ♦️
➠ yitaya41@gmail.com…
➠ ለ Telegram
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAFLulNC2J1Sz43spAw
➠ ለ Facebook - https://m.facebook.com/yedawitzema
አስተያየት መልዕክት ጥያቄ ካለዎት
♦️ Email ♦️
➠ yitaya41@gmail.com…
እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል በሠላም አደረሳችሁ!
ታህሳስ 19 ቀን በዚህ ቀን ሰለስቱ ደቂቅ "የምናመልከው አምላካችን ከሚነደው ከእሳቱ እቶኑ ሊያድነን ይችላል" ያሉበት ዕለትና ቅዱስ ገብርኤል ከእሣት ያዳቸው ዕለት መታሰቢያ በዓል ነው።
ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን አባቶቻችን እንዳስተማሩን ነገሩ እንዲህ ነው። ዘመኑ ጣኦት የሚመለክበት ንጉስ ናቡከደነፆር የእግዚአብሔር ሰዎች የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች የነበሩት ወጣቶች ሥም አይጣላልናንያ (ሲድራቅ) ፤ አዛርያ (ሚሣቅ) ፤ ሚሣኤል (አብድናጎ) ነበሩ። ት/ዳንኤል 3፡1-30 ታሪኩ እንደሚግረን ንጉስ የጣኦት ምስል አሰራ በገሊላ አውራጃ ያለውን ሕዝብ ጠርቶ ለጣኦቴ ያልሰገደ ወደ እሣት ውስጥ ብሎ አወጀ።
በዚህ መካከል ሰልስቱ ደቂቅ ነበሩ። የንጉስ ትህዛዝ ነውና ሕዝቡ ሁሉ ለጣኦቱ ሲንበረከክ እነርሱ ግን ቆመው ያዩ ነበር። የእግዚአብሔር የሆነ ሰው ምንም ነገር አያስፈራውምና ናቡከደነፆር እርሱ ላስቆመው ጣኦት አለመስገዳቸውን ሲሰማ ተናደደ ፤ ተበሳጨም እሳቱን 7 እጥፍ እንዲነድ አስደረገ ሦስቱንም አስሮ እሣቱን እያሳየ "ከመቃጠል ወይስ ለእኔ ጣኦት መስገድ የቱ ይሻል?" ባላቸው ጊዜ የምናመልከው አምላካችን ከሚነደው ከእሳቱ እቶን ሊያድነን ይችላል ባያድነንም እንኳን አንተ ለመታመልከው ጣኦት አንሰግድም አሉት።
በዚህ ጊዜ ጉልበት ያላቸው ሠዎች ተፈልገው ሦስቱን ወጣቶች አስረው ወደ እሣት ቶን ውስጥ ጣሏቸው አስረው የጣሉቸው ወታደሮች የእሣቱ ወላፈን አቃጠላቸው ሠልስቱ ደቂቅን ግን መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ እሳቱን አበረደላቸው አጠፋላቸው።
በዚህም ጊዜ ንጉስ ናቡከደነፆር እንዲህ በማለት መሰከረ "እኛ አስረን የጣልናቸው ሦስት ነበሩ አሁን ግን አራተኛው ሰው በእሳቱ ሲመላለስ ይታየኛል እንዲያውም የአማልክትን ልጆች ይመስላል " አለ። የእግዚአብሔር የማዳኑ ስራ ሲገለጥ ቅዱስ ገብርኤል ሲታይ አዋጁ ሁሉ ተሻረ ጉልበት ሁሉ ለጣኦት ተብሎ የነበረው "ጉልበት ሁሉ ለሰልስቱ ደቂቅ አምላክ ይስገድ ይንበርከክ" ተባለ ይህን ሁሉ ታህሳስ 19 ቀን ሆነ በዚህም ምክንያት በታላቅ ደስታ እናከብረዋለን!
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የመላዕክት የቅዱስ ገብርኤል ጥበቃው ረድኤት በረከቱ አይለየን አሜን!
ታህሳስ 19 ቀን በዚህ ቀን ሰለስቱ ደቂቅ "የምናመልከው አምላካችን ከሚነደው ከእሳቱ እቶኑ ሊያድነን ይችላል" ያሉበት ዕለትና ቅዱስ ገብርኤል ከእሣት ያዳቸው ዕለት መታሰቢያ በዓል ነው።
ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን አባቶቻችን እንዳስተማሩን ነገሩ እንዲህ ነው። ዘመኑ ጣኦት የሚመለክበት ንጉስ ናቡከደነፆር የእግዚአብሔር ሰዎች የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች የነበሩት ወጣቶች ሥም አይጣላልናንያ (ሲድራቅ) ፤ አዛርያ (ሚሣቅ) ፤ ሚሣኤል (አብድናጎ) ነበሩ። ት/ዳንኤል 3፡1-30 ታሪኩ እንደሚግረን ንጉስ የጣኦት ምስል አሰራ በገሊላ አውራጃ ያለውን ሕዝብ ጠርቶ ለጣኦቴ ያልሰገደ ወደ እሣት ውስጥ ብሎ አወጀ።
በዚህ መካከል ሰልስቱ ደቂቅ ነበሩ። የንጉስ ትህዛዝ ነውና ሕዝቡ ሁሉ ለጣኦቱ ሲንበረከክ እነርሱ ግን ቆመው ያዩ ነበር። የእግዚአብሔር የሆነ ሰው ምንም ነገር አያስፈራውምና ናቡከደነፆር እርሱ ላስቆመው ጣኦት አለመስገዳቸውን ሲሰማ ተናደደ ፤ ተበሳጨም እሳቱን 7 እጥፍ እንዲነድ አስደረገ ሦስቱንም አስሮ እሣቱን እያሳየ "ከመቃጠል ወይስ ለእኔ ጣኦት መስገድ የቱ ይሻል?" ባላቸው ጊዜ የምናመልከው አምላካችን ከሚነደው ከእሳቱ እቶን ሊያድነን ይችላል ባያድነንም እንኳን አንተ ለመታመልከው ጣኦት አንሰግድም አሉት።
በዚህ ጊዜ ጉልበት ያላቸው ሠዎች ተፈልገው ሦስቱን ወጣቶች አስረው ወደ እሣት ቶን ውስጥ ጣሏቸው አስረው የጣሉቸው ወታደሮች የእሣቱ ወላፈን አቃጠላቸው ሠልስቱ ደቂቅን ግን መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ እሳቱን አበረደላቸው አጠፋላቸው።
በዚህም ጊዜ ንጉስ ናቡከደነፆር እንዲህ በማለት መሰከረ "እኛ አስረን የጣልናቸው ሦስት ነበሩ አሁን ግን አራተኛው ሰው በእሳቱ ሲመላለስ ይታየኛል እንዲያውም የአማልክትን ልጆች ይመስላል " አለ። የእግዚአብሔር የማዳኑ ስራ ሲገለጥ ቅዱስ ገብርኤል ሲታይ አዋጁ ሁሉ ተሻረ ጉልበት ሁሉ ለጣኦት ተብሎ የነበረው "ጉልበት ሁሉ ለሰልስቱ ደቂቅ አምላክ ይስገድ ይንበርከክ" ተባለ ይህን ሁሉ ታህሳስ 19 ቀን ሆነ በዚህም ምክንያት በታላቅ ደስታ እናከብረዋለን!
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የመላዕክት የቅዱስ ገብርኤል ጥበቃው ረድኤት በረከቱ አይለየን አሜን!
Watch "|| ተወለደ ጌታ ተወለደ || ሊቀ መዘምራን ይልማ ሀይሉ | Tewlde geta tewlde | Zemary Yilma haylu// New Ethiopia ortodox" on YouTube
https://youtu.be/pEz5zY17f2s
https://youtu.be/pEz5zY17f2s
YouTube
|| ተወለደ ጌታ ተወለደ || ሊቀ መዘምራን ይልማ ሀይሉ | Tewlde geta tewlde | Zemary Yilma haylu// New Ethiopia ortodox
የእኛን መንፈሳዊ አገልግሎት መደገፍ ማስቀጠል ይፈልጋሉ እንግዲያውስ #SUBSCRIBE በማድረግ ብቻ እኛን ማበረታታት ይችላሉ ።
➠ ለ Telegram
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAFLulNC2J1Sz43spAw
➠ ለ Facebook - https://m.facebook.com/yedawitzema
አስተያየት መልዕክት ጥያቄ ካለዎት
♦️ Email ♦️
➠ yitaya41@gmail.com…
➠ ለ Telegram
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAFLulNC2J1Sz43spAw
➠ ለ Facebook - https://m.facebook.com/yedawitzema
አስተያየት መልዕክት ጥያቄ ካለዎት
♦️ Email ♦️
➠ yitaya41@gmail.com…
የማንቂያው ደወል ልዩ ጉባኤ የተዋህዶ ልጆችን የማንቃት ጉዞውን በመቀጠል፣ ከጥር 21-24 /2012/ዓ/ም በወላይታ ሶዶ ከተማ ታላቅ ጉባኤ ያደርጋል ።ይህ ጉባኤ፣ የጠላትን ምሽግ የሚያፈራርስ፣ የጠፉትን ልጆች ወደቤታቸው የሚመልስ፣ እግዚአብሔር አምላክ ትልቅ ሥራ የሚሰራበት ጉባኤ ሊሆን እንደሚችልም ይታመናል።እግዘአብሔር አምላክ በጉዞአችን ሁሉ ሳይለየን፣በኛ በደካሞቹ ላይ አድሮ ትልቅ ሥራን እንዲሰራ በጸሎታችሁ አግዙን።ሼር በማድረግም ፣ ላልሰሙት እያሰማን ፣የመልካም ሥራ ተካፋዮች እንሁን።
╔═★══════════📄══╗
⛓ @Zemaryan ⛓
⛓ @Zemaryan ⛓
⛓ @Zemaryan ⛓
╚══📃══════════★═╝
╔═★══════════📄══╗
⛓ @Zemaryan ⛓
⛓ @Zemaryan ⛓
⛓ @Zemaryan ⛓
╚══📃══════════★═╝
እንኳን በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ለጸናች ለዓለም ሁሉ እመቤት ለአምላክ እናት ለንጽህት ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የእረፍት በዓል አደረሳችሁ!!!
💟በዓለ አስተርእዮ "ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ” ጥር 21 በዓለ አስተርእዮ (የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት) እንኳን ለዚህች ታላቅ በዓሏ አደረሰን፡፡
✔🌿🌿 ወላዲተ አምላክ ምንም እንኳን የአምላክ እናት ብትሆንም ሞተ ሥጋ ለሁሉም ዕጣ ፈንታ በመሆኑ በስድሳ አራት አመቷ ከሞት ወደ ሕይወት ከመከራ ወደ ደስታ የተሸጋገረችበት ዕለት ነው፡፡
@Sihela_adhno
🌿🌿💟ታላቁ የቤተክርስቲያን አባት ቅዱስ ያሬድም “ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ” ትርጉሙ ሞት ለማናኛቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል በማለት አደነቀ በመሆኑም በዓሉ የወላዲተ አምላክ በዓለ ዕረፍት ከመሆኑ የተነሳ ታላቅ በረከት የሚያስገኝ ስለሆነ በየዓመቱ ይከበራል፡፡
@Sihela_adhno
🌿🌿💟 ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ መካነ ፍሥሓ ምጡቀ ፤ በአእባነ ባሕርይ ዘተነድቀ ፤ ማርያም ደብተራ እንተ ኢትትከደኒ ሠቀ፤` እመቤታችን በ5485 ዓ.ዓ ከአባቷ ከኢያቄም ከእናቷ ከሐና “እም ሊባኖስ ትወጽዕ መርዓት ከሊባኖስ ሙሽራ ትወጣለች” ተብሎ በተነገረው መሠረት ነሐሴ 7 ቀን ተጸነሰች፡፡
🌿🌿💟 ግንቦት አንድ ቀን ሊባኖስ በምትባል ቦታ በብጽዓት እንደተወለደች የቤተክርስቲያን ታሪክ በሰፊው ያስረዳል፡፡ በጾም በጸሎት በአስተብቁዖት የተገኘች ናት፡፡ ንጽሕት በመሆኗም ማኅደረ ወልድ ሆናለች፡፡
✔ 🌿🌿💟 እመቤታችን ከእናትና ከአባቷ ዘንድ ሦስት ዓመት፣ ✔በቤተ መቅደስ 12 ዓመት፣ 💟ውስተ ቤተ መቅደስ ነበረት በድንግልና። ✔መድኃኔዓለምን በማኀጸንዋ ጸንሳ ዘጠኝ ወር። ✔ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ 33 ዓመት ከሦስት ወር፣ ✔ከዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ዘንድ 14 ዓመት ከዘጠኝ ወር 🌿🌿💟ጠቅላላ ድምር 64 ዓመት ሲሆናት ጥር 21 ቀን በ49 ዓመተ ምሕረት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፡፡
@Sihela_adhno
🌿🌿💟የእረፍቷስ ነገር እንደምን ነው ቢሉስድሳ አራት ዓመት በዚህ ዓለም ኖራ ጥር 21 እሁድ ቀን ጌታ እልፍ አዕላፋት መላዕክቱን አስከትሎ መጥቶ እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም ድካም ላሳርፍሽ መጣሁ አላት፡፡ ልጄ ሰማይና ምድር የማይወስኑ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማህጸኔ ተሸክሜ በድንግልና ወልጄህ እሞታለሁミ አለችው፡፡ በሲዖል የሚሰቃዩ ነፍሳትን አሳይቶ እናቴ ሆይ ሞትሽ ለእነዚህ ቤዛ ይሆንላቸዋል አላት፡፡ እኚህን ከማርክልኝስ ይሁን አለችው፡፡
@Sihela_adhno
🌿🌿💟 ቅድስት ሥጋዋን ከቅስስት ነፍሷ ለይቶ በቃለ አቅርንት በዝማሬ መላእክት አሳረጋት፡፡ ደቀመዛሙርቱንም ከያሉበት በደመና ጠቅሶ ካለችበት አድርሶ እመቤታችሁን ቅበሩ አላቸው፡፡ ባባ ይዘወት ወደ ጌሰማኒ ሲስደት አይተው ልጇን ተነሳ አረገ እያሉ ሲውኩን ይኖራሉ አሁን ደግሞ እሷን ተነሳች አረገች እያሉ ሊያውኩን አይደለም ብሎ ኑ እናቃጥላት ተባባሉ፡፡ ከመካከላቸው አንዱ ታውፋንያ ዘሎ ያልጋውን ሸንኮር ያዘ፡፡ የታዘዘው መላእክት መጥቶ በሰይፍ ሁለት እጁን ቀጣው፡፡ በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማጸናት ድኖለታል፡፡ ከዚህ ቦሃላ ዮሐንስን ጨምሮ ከመካከላቸው ነጥቆ በእጸ ሕይወት ሥር አኑሯታል፡፡
@Sihela_adhno
🌿🌿💟 አንድም በዓሉ-፡ እግዚአብሔር ወልድ በሰውነት ተወልዶና ማንነቱ በይፋ ታውቆ በተገለጠበት በዘመነ አስተርእዮ ውስጥ ስለሚከበር የ“አስተርእዮ ማርያም” ተብሏል፡፡ አስቀድመው አሥራ ሁለቱም ሐዋርያት ለስብከተ ወንጌል ወደ ዓለም ሁሉ ተበትነው ነበርና በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ሁሉም ደመናን ጠቅሰው ወደ ኢየሩሳሌም መጡ፡፡ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ መርቶ አመጣቸው እንጂ ለምን እንደመጡ አያውቁም ነበር፡፡ እመቤታችንም ለምን እንደመጡ ጠየቀቻቸው፡፡
@Sihela_adhno
🌿🌿💟 ቅዱስ ጴጥሮስም፡- “ጸጋን የተመላሽ ቅድስት ሆይ! የመምጣታችን ምሥጢርማ እኛ አንቺን እንጠይቅ እንጂ አንቺም እኛን ትጠይቃለሽን? ሁላችንም ለምን እንደመጣን አናውቅም፡፡ ለምሳሌ እኔ አስቀድሜ በአንጾክያ ነበርኩኝ አሁን ግን እነሆ እዚህ ነኝ፡፡ ለምን እንደመጣሁኝ ግን አላውቅም” አላት፡፡ እርሷም ሁሉም በአጠገቧ በተሰበሰቡ ጊዜ የሚሆነውን ነገር አስቀድማ ከልጇ ከወዳጇ አውቃ ተዘጋጅታ ነበርና ለምን እንደመጡ (ዕረፍተ ሥጋዋን ለማየት እንደሆነ) ነገረቻቸው፡፡ ሌሊቱንም በሙሉ በጸሎትና በማኅሌት ደግሞም በዝማሬ ሲያመሰግኑ አደሩ፡፡
🌿🌿💟 ከዚህ በኋላ የተወደደችው እናት በረከቷን አሳድራባቸው በሰላም አንቀላፋች፡፡ ነፍሷም በዐብይ ዕልልታና በታላቅ ምስጋና በመላእክት እጅ ወደ አምላኳ ሄደች፡፡ ኋላ ሐዋርያቱ ዮሐንስን ሲያገኙት፡- “እመቤታችን እንደምን ሆነች?” አሉት፡፡ እርሱም “በገነት በዕጸ ሕይወት ሥር ዐርፋለች” አላቸው፡፡ የቀሩት ሐዋርያት “ዮሐንስ ያን ድንቅ የእግዚአብሔርን ሥራ አይቶ እኛስ ሳናይ እንዴት እንቀራለን?! አቤቱ ለእኛም ቸርነትህን አድርግልን” ብለው በነሐሴ መባቻ በአንድነት ሆነው ወደ ፈጣሪያቸው የሚቀርብ የአንድ ሳምንት ጾምና ጸሎት ጀመሩ፡፡
@Sihela_adhno
🌿🌿💟በሁለተኛው ሱባዔ ማብቂያ ዕለት ነሐሴ 14 ቀን እሑድ የእመቤታችንን ትኩስ ሥጋ መልአኩ ከገነት አምጥቶ ለሐዋርያቱ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ልመናቸው ስለ ተፈጸመላቸው ፈጣሪያቸውን በጸሎት አመስግነው በዚያችው ዕለተ እሑድ ቅዱስ ሥጋዋን ወስደው ቀብረውታል፡፡ እርሷም በሦስተኛው ቀን ነሐሴ 16 ቀን ማክሰኞ ተነሥታለች፡፡ ትንሣኤዋ “ከመ ትንሣኤ ወልዳ- እንደ ልጇ ትንሣኤ” ያሰኘው ይህ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይታ የመነሣቷ እውነታ ነው፡፡@Sihela_adhno
የአዛኚቱ ድንግል አማለጅነትና በረከት አይለየን፡፡ ሁላችንም ባለንበት ይህ ታላቅ በዓሏን እያሰብን ጸልየን የበረከቷ ተካፋዮች እንሆን ዘንድ ልዑል እግዚአብሔር ይርዳን አሜን አሜን አሜን በዓሉን በዓለ ሠላም ወሐሴት ያድርግልን
መልካም በዓል !!
@Sihela_adhno
?👇👇👇👇👇👇
@Sihela_adhno
@Sihela_adhno
💟በዓለ አስተርእዮ "ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ” ጥር 21 በዓለ አስተርእዮ (የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት) እንኳን ለዚህች ታላቅ በዓሏ አደረሰን፡፡
✔🌿🌿 ወላዲተ አምላክ ምንም እንኳን የአምላክ እናት ብትሆንም ሞተ ሥጋ ለሁሉም ዕጣ ፈንታ በመሆኑ በስድሳ አራት አመቷ ከሞት ወደ ሕይወት ከመከራ ወደ ደስታ የተሸጋገረችበት ዕለት ነው፡፡
@Sihela_adhno
🌿🌿💟ታላቁ የቤተክርስቲያን አባት ቅዱስ ያሬድም “ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ” ትርጉሙ ሞት ለማናኛቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል በማለት አደነቀ በመሆኑም በዓሉ የወላዲተ አምላክ በዓለ ዕረፍት ከመሆኑ የተነሳ ታላቅ በረከት የሚያስገኝ ስለሆነ በየዓመቱ ይከበራል፡፡
@Sihela_adhno
🌿🌿💟 ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ መካነ ፍሥሓ ምጡቀ ፤ በአእባነ ባሕርይ ዘተነድቀ ፤ ማርያም ደብተራ እንተ ኢትትከደኒ ሠቀ፤` እመቤታችን በ5485 ዓ.ዓ ከአባቷ ከኢያቄም ከእናቷ ከሐና “እም ሊባኖስ ትወጽዕ መርዓት ከሊባኖስ ሙሽራ ትወጣለች” ተብሎ በተነገረው መሠረት ነሐሴ 7 ቀን ተጸነሰች፡፡
🌿🌿💟 ግንቦት አንድ ቀን ሊባኖስ በምትባል ቦታ በብጽዓት እንደተወለደች የቤተክርስቲያን ታሪክ በሰፊው ያስረዳል፡፡ በጾም በጸሎት በአስተብቁዖት የተገኘች ናት፡፡ ንጽሕት በመሆኗም ማኅደረ ወልድ ሆናለች፡፡
✔ 🌿🌿💟 እመቤታችን ከእናትና ከአባቷ ዘንድ ሦስት ዓመት፣ ✔በቤተ መቅደስ 12 ዓመት፣ 💟ውስተ ቤተ መቅደስ ነበረት በድንግልና። ✔መድኃኔዓለምን በማኀጸንዋ ጸንሳ ዘጠኝ ወር። ✔ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ 33 ዓመት ከሦስት ወር፣ ✔ከዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ዘንድ 14 ዓመት ከዘጠኝ ወር 🌿🌿💟ጠቅላላ ድምር 64 ዓመት ሲሆናት ጥር 21 ቀን በ49 ዓመተ ምሕረት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፡፡
@Sihela_adhno
🌿🌿💟የእረፍቷስ ነገር እንደምን ነው ቢሉስድሳ አራት ዓመት በዚህ ዓለም ኖራ ጥር 21 እሁድ ቀን ጌታ እልፍ አዕላፋት መላዕክቱን አስከትሎ መጥቶ እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም ድካም ላሳርፍሽ መጣሁ አላት፡፡ ልጄ ሰማይና ምድር የማይወስኑ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማህጸኔ ተሸክሜ በድንግልና ወልጄህ እሞታለሁミ አለችው፡፡ በሲዖል የሚሰቃዩ ነፍሳትን አሳይቶ እናቴ ሆይ ሞትሽ ለእነዚህ ቤዛ ይሆንላቸዋል አላት፡፡ እኚህን ከማርክልኝስ ይሁን አለችው፡፡
@Sihela_adhno
🌿🌿💟 ቅድስት ሥጋዋን ከቅስስት ነፍሷ ለይቶ በቃለ አቅርንት በዝማሬ መላእክት አሳረጋት፡፡ ደቀመዛሙርቱንም ከያሉበት በደመና ጠቅሶ ካለችበት አድርሶ እመቤታችሁን ቅበሩ አላቸው፡፡ ባባ ይዘወት ወደ ጌሰማኒ ሲስደት አይተው ልጇን ተነሳ አረገ እያሉ ሲውኩን ይኖራሉ አሁን ደግሞ እሷን ተነሳች አረገች እያሉ ሊያውኩን አይደለም ብሎ ኑ እናቃጥላት ተባባሉ፡፡ ከመካከላቸው አንዱ ታውፋንያ ዘሎ ያልጋውን ሸንኮር ያዘ፡፡ የታዘዘው መላእክት መጥቶ በሰይፍ ሁለት እጁን ቀጣው፡፡ በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማጸናት ድኖለታል፡፡ ከዚህ ቦሃላ ዮሐንስን ጨምሮ ከመካከላቸው ነጥቆ በእጸ ሕይወት ሥር አኑሯታል፡፡
@Sihela_adhno
🌿🌿💟 አንድም በዓሉ-፡ እግዚአብሔር ወልድ በሰውነት ተወልዶና ማንነቱ በይፋ ታውቆ በተገለጠበት በዘመነ አስተርእዮ ውስጥ ስለሚከበር የ“አስተርእዮ ማርያም” ተብሏል፡፡ አስቀድመው አሥራ ሁለቱም ሐዋርያት ለስብከተ ወንጌል ወደ ዓለም ሁሉ ተበትነው ነበርና በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ሁሉም ደመናን ጠቅሰው ወደ ኢየሩሳሌም መጡ፡፡ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ መርቶ አመጣቸው እንጂ ለምን እንደመጡ አያውቁም ነበር፡፡ እመቤታችንም ለምን እንደመጡ ጠየቀቻቸው፡፡
@Sihela_adhno
🌿🌿💟 ቅዱስ ጴጥሮስም፡- “ጸጋን የተመላሽ ቅድስት ሆይ! የመምጣታችን ምሥጢርማ እኛ አንቺን እንጠይቅ እንጂ አንቺም እኛን ትጠይቃለሽን? ሁላችንም ለምን እንደመጣን አናውቅም፡፡ ለምሳሌ እኔ አስቀድሜ በአንጾክያ ነበርኩኝ አሁን ግን እነሆ እዚህ ነኝ፡፡ ለምን እንደመጣሁኝ ግን አላውቅም” አላት፡፡ እርሷም ሁሉም በአጠገቧ በተሰበሰቡ ጊዜ የሚሆነውን ነገር አስቀድማ ከልጇ ከወዳጇ አውቃ ተዘጋጅታ ነበርና ለምን እንደመጡ (ዕረፍተ ሥጋዋን ለማየት እንደሆነ) ነገረቻቸው፡፡ ሌሊቱንም በሙሉ በጸሎትና በማኅሌት ደግሞም በዝማሬ ሲያመሰግኑ አደሩ፡፡
🌿🌿💟 ከዚህ በኋላ የተወደደችው እናት በረከቷን አሳድራባቸው በሰላም አንቀላፋች፡፡ ነፍሷም በዐብይ ዕልልታና በታላቅ ምስጋና በመላእክት እጅ ወደ አምላኳ ሄደች፡፡ ኋላ ሐዋርያቱ ዮሐንስን ሲያገኙት፡- “እመቤታችን እንደምን ሆነች?” አሉት፡፡ እርሱም “በገነት በዕጸ ሕይወት ሥር ዐርፋለች” አላቸው፡፡ የቀሩት ሐዋርያት “ዮሐንስ ያን ድንቅ የእግዚአብሔርን ሥራ አይቶ እኛስ ሳናይ እንዴት እንቀራለን?! አቤቱ ለእኛም ቸርነትህን አድርግልን” ብለው በነሐሴ መባቻ በአንድነት ሆነው ወደ ፈጣሪያቸው የሚቀርብ የአንድ ሳምንት ጾምና ጸሎት ጀመሩ፡፡
@Sihela_adhno
🌿🌿💟በሁለተኛው ሱባዔ ማብቂያ ዕለት ነሐሴ 14 ቀን እሑድ የእመቤታችንን ትኩስ ሥጋ መልአኩ ከገነት አምጥቶ ለሐዋርያቱ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ልመናቸው ስለ ተፈጸመላቸው ፈጣሪያቸውን በጸሎት አመስግነው በዚያችው ዕለተ እሑድ ቅዱስ ሥጋዋን ወስደው ቀብረውታል፡፡ እርሷም በሦስተኛው ቀን ነሐሴ 16 ቀን ማክሰኞ ተነሥታለች፡፡ ትንሣኤዋ “ከመ ትንሣኤ ወልዳ- እንደ ልጇ ትንሣኤ” ያሰኘው ይህ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይታ የመነሣቷ እውነታ ነው፡፡@Sihela_adhno
የአዛኚቱ ድንግል አማለጅነትና በረከት አይለየን፡፡ ሁላችንም ባለንበት ይህ ታላቅ በዓሏን እያሰብን ጸልየን የበረከቷ ተካፋዮች እንሆን ዘንድ ልዑል እግዚአብሔር ይርዳን አሜን አሜን አሜን በዓሉን በዓለ ሠላም ወሐሴት ያድርግልን
መልካም በዓል !!
@Sihela_adhno
?👇👇👇👇👇👇
@Sihela_adhno
@Sihela_adhno
አዲስ ዓለም ማርያም
እነሆ ብዙ ሰው ስለማያውቃት፤
ቢያውቃትም ስለማያስታውሳት፤
ቢያስታውሳትም መልሶ ስለሚረሳት
አዲስ አለም ከተማና ስለ ርዕሰ
አድባራት ደብረ ጽዮን ማርያም
ቤተክርስቲያን አመሰራረት እፅፋለሁ፡፡
.......
አዲስ አለም ከአዲስ አበባ በስተ ምዕራብ ወደ አምቦ፣ ወደ ወለጋና
አሶሳ በሚወስደው መንገድ 42ኪ.ሜ ርቃ የምትገኝ ትንሽ ከተማ ናት፡፡ አዲስ አበባ አጠገብ ተኝታ የራሷን ህልም
የምታልም፣ የራሷን ቅዠት የምትቃዥ፣ የራሷን ኑሮ የምትገፋ . . .
ለጽሁፌ በምንጭነት የተጠቀምኳቸውን ጽሁፎች ያገኘሁት የአዲስ ዓለም ርዕሰ አድባራት ደብረ ጽዮን ማርያም ቤተክርስቲያንን መቶኛ አመት በማስመልከት በ 1994 ዓ.ም
በወጣው መጽሄት ላይ አንጋፋው የታሪክ ምሁር ፕ/ር ታደሰ
ታምራትና አቶ ፈቃደ ሥላሴ ተፈራ (ሊቀ ጉባኤ) ከጻፏቸው
ግሩም ጽሁፎች ነው፡፡ በዕውነት እኒህ ሁለት ሊቃውንት ማለፊያ
ጽሁፎች ጽፈዋልና ታላቅ ምስጋና ይገባቸዋል፡፡
‹‹እንተ ይዕቲ ሀገሩ ለንጉስ ዓቢይ ምኒልክ››
በቀድሞ ዘመናት የአሁኖቹ የመናገሻ፣ የወጨጫና የአዲስ
ዓለም አካባቢዎች እንደዝነኛው ጨንገሬ ሶኪ ና እንደ ሁኪ ጉላ
ባሉት የሜታ አሮሞ መሪዎች ስር በባላባትነታቸው የግዛት ወሰን
ውስጥ የነበሩ ሲሆን ንጉሰ ነገስት እምዬ ምኒልክ ለመጀመርያ
ግዜ አዲስ አለምን የጎበኟት በ 1874 ግንቦት ወር ወደ እንባቦ
ጦርነት ሲያቀኑ ይሉናል - ሊቀ ጉባኤ ፈቃደ ስላሴ ተፈራ፡፡
(በነገራችን ላይ የቀድሞውን የአካባቢው ባላባት ለማስታወስ
ሲባል በአሁኑ ወቅት የአዲስ ዓለም ከተማ ‹‹ኤጀሬ ጨንገሬ››
በሚባል ወረዳ ስር ትገኛለች፡፡ ፡፡)
አጤ ምኒልክ መጀመርያ እንጦጦ ላይ በኋላም አዲስ አበባ
መቀመጥ ከጀመሩ በኋላ እሳቸውን ተከትሎ በዙርያቸው
የሚኖረው ህዝብ እጅግ በጣም ስለበዛ በአካባቢው የነበረው
ጫካ በጥቂት አመታት ውስጥ እየመነመነ ሄደ፡፡ ሰራዊቱና
ህዝቡ ቤቱን የሚሰራውም ሆነ ለየቀኑ የሚያስፈልገውን ማገዶ
የሚያገኘው ከዚያው ከጫካው ስለሆነ አዲስ አበባ ከተማ ገና
አስራ ስድስት አመት ሳይሞላት በተለይ የማገዶ ችግር
እየተባባሰ ሄደ፡፡ ይሄኔ ታዲያ፤ እምዬ ምኒልክ በደን የተከበበው
የአዲስ ዓለም አካባቢ በጣም ደስ አሰኛቸውና ‹‹ዋና ከተማዬን
ለምን ወደዚህች ውብ ሀገር ኣላዛውርም?›› የሚል ሃሳብ ይዘው
ተነሱ፡፡ እንግዲህ የአዲስ ዓለም ከተማ በአጤ ምኒልክ ልዩ
ትዕዛዝ አዲስ አበባ ገና አስራ ስድስት አመት እንኳን ሳይሞላት
በ 1893 ዓ.ም ተመሰረተች ማለት ነው፡፡ ‹‹እንተ ይዕቲ ሀገሩ
ለንጉስ አቢይ ምኒልክ›› ይሏችኋል እንዲህ ነው፡፡ (ይህች ሀገር
የታላቁ ንጉስ ምኒልክ ሀገር ናት)
የስሟን አሰያየም አስመልክቶ ፕሮፌሰር ታደሰ እንደሚሉት በመጀመርያ አካባቢ የዋና ከተማውን መዛወር በይሁንታ
የተቀበሉት እቴጌ ጣይቱ አዲስ ዓለም ስትመሰረት ስሟን
እንዳወጡላት ሲገልጹ ሊቀ ጉባኤ ፈቃደ ሥላሴ በበኩላቸው
‹‹የለም ነገሩ ወዲህ ነው፤ ንጉስ ምኒልክ ወደ በቾ (ሜታ)
እንጨት ለማስጋዝ ሄደው በነበረበት ዘመን ነው አዲስ ዓለም
የሚለውን ስያሜ ለቦታዋ የሰጡት›› ይላሉ፡፡ እኔም ትንሽ ስንፍና
ያዘኝና ጠለቅ ብዬ በጉዳዩ ላይ ሳልመራመር ቀረሁ፡፡
‹‹ ይኄይስነ ንግበር ዘንተ ሕንጻ ለቤተክርስቲያን ከመ ይኩነነ
መርሐ ለመንግስተ ሰማያት ወውእቱኒ ተወክፈ ነገራ›› @embtee
‹አጤ ምኒልክ መዲናቸውን ከአዲስ አበባ ወደ አዲስ ዓለም
ለማዛወር ከወሰኑ በኋላ ባካባቢው ያለፈ ፈረንጅ ሁሉ
‹‹የወደፊቷ መዲና አዲስ ዓለም ልትሆን ነው፤ ልክ እንደ
አንኮበርና እንደ እንጦጦ አዲስ አበባም እንግዲህ ሊያልቅላት
ነው!›› እያለ መጻፍ ጀመረ፡፡ በዚህ አይነት አሁን የአዲስ አለም
ደብረ ጽዮን ማርያም ባለበት ቦታ ላይ ግሩም ቤተ መንግስት
መሰራት ተጀመረ፡፡ ቤተ መንግስቱ የተመሰረተበት መሬት
ከ‹‹ዳሞቱ››ው ባላባት ከጨንገሬ ሶኪሌ ለአጤ ምኒልክ በገጸ
በረከትነት የተሰጠ ሲሆን ንጉሱ በበኩላቸው ለባላባቱ
ከ‹‹ዳሞቱ›› በላይ ‹‹ኢርበ ዲባዩ›› ከሚባለው አካባቢ
መደዳውን የተያያዘ አስር ጋሻ መሬት ሰጥተዋል፡፡ የአጤ
ምኒልክ መኳንንትም በተመደበላቸው ስፍራ የራስ መኮንን
ሰፈር፣ የፊታውራሪ ሀብተጊዮርጊስ ሰፈር እየተባለ መስፈር
ጀመሩ፡፡ (በነገራችን ላይ ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ይቆዩበት
የነበረ ቤት አሁን ድረስ አዲስ ዓለም እንደሚገኝ የምናውቅ
ስንቶቻችን ነን? ስለዚህ ጉዳይ በቅርቡ መጻፌ አይቀርም፡፡)
እናም ወደ ጨዋታችን ስንመለስ፤ የአጤ ምኒልክን ቤተ
መንግስት አሰራር አስመልክቶ ሊቀ ጉባኤ ፈቃደ ስላሴ
እንደሚተርኩት የቤተ መንግስቱን ግንባታ ያካሂዱ የነበሩት
ባናውያን (መሀመድ ዓሊዎች) ሲሆኑ መጋዝ ሳቢ የሚባሉ
ባለሙያዎች ከቡልጋ መጥተው ለጣራ ስራ፣ ለቅስትና ለመቃን
የሚሆኑ ሁነኛ የጥድ እንጨቶችን ጭረቻ ከሚባል ቦታ
እየቆረጡና እየላጉ ያዘጋጁ ነበር ብለዋል፡፡ ይህ በእንዲህ
እንዳለ ግን ያው መቼም ያልተባለው አይፈጸምምና የዋና
ከተማዋን መዛወር በተመለከተ አንዳንድ ችግሮች መፈጠር
ጀመሩ፡፡ @embtee
ፕሮፌሰር ታደሰ ችግሮቹን ሲያብራሩ፤ በጊዜው የነበሩና ለ15
አመታት ያህል አዲስ አበባ የኖሩ፤ ሀብት ንብረት ያፈሩ
ወገኖች፣ ዲፕሎማቶችና አዲስ የንግድ መስመር መፈጠሩ
ያሰጋቸው ነጋዴዎች የመዲናይቱን መዛወር አስመልክቶ ቅሬታ
ማሰማታቸው ነበር፡፡ ለነገሩ፤ ግድ ካልሆነ በቀር የቆየ ቀየውን
መቀየር ማንስ ይወዳል? ከዚያማ በቃ፤ ይህ ሀሳብ ለአዲስ
አበባ ጽኑ ፍቅር በነበራቸው እቴጌ ጣይቱ ተቀባይነት አገኘና
እርሳቸው ደግሞ በፊናቸው ንጉሰ ነገስቱን ለማሳመን ጥረት
ማድረግ ጀመሩ፡፡ አሏቸውም፤
‹‹ ይኄይስነ ንግበር ዘንተ ሕንጻ ለቤተክርስቲያን ከመ ይኩነነ
መርሐ ለመንግሰተ ሰማያት ወውእቱኒ ተወክፈ ነገራ››
(ለመንግሰተ ሰማያት መግቢያ በር እንዲኖረን ይህንን ሕንጻ
ቤተክርስቲያን እናድርገው)
‹‹አጤ ምኒልክም በሀሳቡ ተስማምተው የአዲስ ዓለም
ከተማቸው ከምድራዊ መንግስት መዲናነት ይልቅ ከዚህ እጅግ
በጣም የላቀ መንፈሳዊ ስፍራ እንዲኖራት አደረጉ፡፡›› @embtee
አንዳንዴ፤ እንዲያው አዲስ ዓለም የሀገሪቱ መዲና ሆና ቢሆን
ኖሮ ስለ አዲስ አበባ የተዜሙት ዜማዎች፣ የተገጠሙት
ግጥሞች፣ የተባሉት ነገሮች ሁሉ ምን ሊሆኑ ይችል ነበር?
እያልኩ አስባለሁ፡፡
‹‹@embtee ነው ቤቴ . . .››
ርዕሰ አድባራት ወ ገዳማት ደብረ ጽዮን አዲስ አለም ማርያም
ንጉሠ ነገሥት ምኒልክ መዲናቸውን ወደ አዲስ ዓለም
ለማዛወር ያለቸውን ሀሳብ ካነሱ በኋላ ለቤተ መንግስትነት
የታሰበው ህንጻ ለቤተክርስቲየንነት በሚሆን መልኩ መገንባት
ጀመረ፡፡ የዚህም የቤተክርስቲያን ስራ እንግዳ አይነት ከዚህ
ቀደም በኢትዮጵያ ተሰርቶ የማያውቅ ነው፤ ይላሉ ሊቀ ጉባኤ
ፈቃደ ሥላሴ፡፡ የቤተ ክርስቲያኑ ግንባታ በተጀመረ ግዜ ለቤተ
መንግስቱ ግንባታ የተዘጋጁት የግንባታ እቃዎች ሁሉ
ለቤተክርስቲያኑ ግንባታ እንዲውሉ ተደረገ፡፡ ያው መቸው
በዘመኑ ሲሚንቶ ስላልነበረ ሕንጻው የተገነባው በጭቃና
በድንጋይ ሲሆን ጭቃው የተቦካው በስንዴ ገለባ፣ በጭድ እና
በበግ ጸጉር እንደሆነ ይተረካል፡፡
የአዲስ ዓለም ማርያም ቤተክርስቲያን ሕንጻ ጎኑ 27.50 ሜ
ወርዱ 24.40 ሜትር ሆኖ በድንጋይና በጭቃ የተገነባ
እንደመሆኑ የግንቡ ውፍረት አንድ ሜትር ሲሆን በአራት ማዕዘን
ቅርጽ የተገነቡ ስድስት የግንብ አምዶች አሉት፡፡
ዳግማዊት ጽዮን አዲስ ዓለም ማርያም እና አክሱም ጽዮን
ማርያም
የአዲስ ዓለም ማርያም በአክሱም ደረጃ የተተከለችበት ዋናው
ምክኒያት፤ ይላሉ ሊቀ ጉባኤ ፈቃደ ሥላሴ፤
እነሆ ብዙ ሰው ስለማያውቃት፤
ቢያውቃትም ስለማያስታውሳት፤
ቢያስታውሳትም መልሶ ስለሚረሳት
አዲስ አለም ከተማና ስለ ርዕሰ
አድባራት ደብረ ጽዮን ማርያም
ቤተክርስቲያን አመሰራረት እፅፋለሁ፡፡
.......
አዲስ አለም ከአዲስ አበባ በስተ ምዕራብ ወደ አምቦ፣ ወደ ወለጋና
አሶሳ በሚወስደው መንገድ 42ኪ.ሜ ርቃ የምትገኝ ትንሽ ከተማ ናት፡፡ አዲስ አበባ አጠገብ ተኝታ የራሷን ህልም
የምታልም፣ የራሷን ቅዠት የምትቃዥ፣ የራሷን ኑሮ የምትገፋ . . .
ለጽሁፌ በምንጭነት የተጠቀምኳቸውን ጽሁፎች ያገኘሁት የአዲስ ዓለም ርዕሰ አድባራት ደብረ ጽዮን ማርያም ቤተክርስቲያንን መቶኛ አመት በማስመልከት በ 1994 ዓ.ም
በወጣው መጽሄት ላይ አንጋፋው የታሪክ ምሁር ፕ/ር ታደሰ
ታምራትና አቶ ፈቃደ ሥላሴ ተፈራ (ሊቀ ጉባኤ) ከጻፏቸው
ግሩም ጽሁፎች ነው፡፡ በዕውነት እኒህ ሁለት ሊቃውንት ማለፊያ
ጽሁፎች ጽፈዋልና ታላቅ ምስጋና ይገባቸዋል፡፡
‹‹እንተ ይዕቲ ሀገሩ ለንጉስ ዓቢይ ምኒልክ››
በቀድሞ ዘመናት የአሁኖቹ የመናገሻ፣ የወጨጫና የአዲስ
ዓለም አካባቢዎች እንደዝነኛው ጨንገሬ ሶኪ ና እንደ ሁኪ ጉላ
ባሉት የሜታ አሮሞ መሪዎች ስር በባላባትነታቸው የግዛት ወሰን
ውስጥ የነበሩ ሲሆን ንጉሰ ነገስት እምዬ ምኒልክ ለመጀመርያ
ግዜ አዲስ አለምን የጎበኟት በ 1874 ግንቦት ወር ወደ እንባቦ
ጦርነት ሲያቀኑ ይሉናል - ሊቀ ጉባኤ ፈቃደ ስላሴ ተፈራ፡፡
(በነገራችን ላይ የቀድሞውን የአካባቢው ባላባት ለማስታወስ
ሲባል በአሁኑ ወቅት የአዲስ ዓለም ከተማ ‹‹ኤጀሬ ጨንገሬ››
በሚባል ወረዳ ስር ትገኛለች፡፡ ፡፡)
አጤ ምኒልክ መጀመርያ እንጦጦ ላይ በኋላም አዲስ አበባ
መቀመጥ ከጀመሩ በኋላ እሳቸውን ተከትሎ በዙርያቸው
የሚኖረው ህዝብ እጅግ በጣም ስለበዛ በአካባቢው የነበረው
ጫካ በጥቂት አመታት ውስጥ እየመነመነ ሄደ፡፡ ሰራዊቱና
ህዝቡ ቤቱን የሚሰራውም ሆነ ለየቀኑ የሚያስፈልገውን ማገዶ
የሚያገኘው ከዚያው ከጫካው ስለሆነ አዲስ አበባ ከተማ ገና
አስራ ስድስት አመት ሳይሞላት በተለይ የማገዶ ችግር
እየተባባሰ ሄደ፡፡ ይሄኔ ታዲያ፤ እምዬ ምኒልክ በደን የተከበበው
የአዲስ ዓለም አካባቢ በጣም ደስ አሰኛቸውና ‹‹ዋና ከተማዬን
ለምን ወደዚህች ውብ ሀገር ኣላዛውርም?›› የሚል ሃሳብ ይዘው
ተነሱ፡፡ እንግዲህ የአዲስ ዓለም ከተማ በአጤ ምኒልክ ልዩ
ትዕዛዝ አዲስ አበባ ገና አስራ ስድስት አመት እንኳን ሳይሞላት
በ 1893 ዓ.ም ተመሰረተች ማለት ነው፡፡ ‹‹እንተ ይዕቲ ሀገሩ
ለንጉስ አቢይ ምኒልክ›› ይሏችኋል እንዲህ ነው፡፡ (ይህች ሀገር
የታላቁ ንጉስ ምኒልክ ሀገር ናት)
የስሟን አሰያየም አስመልክቶ ፕሮፌሰር ታደሰ እንደሚሉት በመጀመርያ አካባቢ የዋና ከተማውን መዛወር በይሁንታ
የተቀበሉት እቴጌ ጣይቱ አዲስ ዓለም ስትመሰረት ስሟን
እንዳወጡላት ሲገልጹ ሊቀ ጉባኤ ፈቃደ ሥላሴ በበኩላቸው
‹‹የለም ነገሩ ወዲህ ነው፤ ንጉስ ምኒልክ ወደ በቾ (ሜታ)
እንጨት ለማስጋዝ ሄደው በነበረበት ዘመን ነው አዲስ ዓለም
የሚለውን ስያሜ ለቦታዋ የሰጡት›› ይላሉ፡፡ እኔም ትንሽ ስንፍና
ያዘኝና ጠለቅ ብዬ በጉዳዩ ላይ ሳልመራመር ቀረሁ፡፡
‹‹ ይኄይስነ ንግበር ዘንተ ሕንጻ ለቤተክርስቲያን ከመ ይኩነነ
መርሐ ለመንግስተ ሰማያት ወውእቱኒ ተወክፈ ነገራ›› @embtee
‹አጤ ምኒልክ መዲናቸውን ከአዲስ አበባ ወደ አዲስ ዓለም
ለማዛወር ከወሰኑ በኋላ ባካባቢው ያለፈ ፈረንጅ ሁሉ
‹‹የወደፊቷ መዲና አዲስ ዓለም ልትሆን ነው፤ ልክ እንደ
አንኮበርና እንደ እንጦጦ አዲስ አበባም እንግዲህ ሊያልቅላት
ነው!›› እያለ መጻፍ ጀመረ፡፡ በዚህ አይነት አሁን የአዲስ አለም
ደብረ ጽዮን ማርያም ባለበት ቦታ ላይ ግሩም ቤተ መንግስት
መሰራት ተጀመረ፡፡ ቤተ መንግስቱ የተመሰረተበት መሬት
ከ‹‹ዳሞቱ››ው ባላባት ከጨንገሬ ሶኪሌ ለአጤ ምኒልክ በገጸ
በረከትነት የተሰጠ ሲሆን ንጉሱ በበኩላቸው ለባላባቱ
ከ‹‹ዳሞቱ›› በላይ ‹‹ኢርበ ዲባዩ›› ከሚባለው አካባቢ
መደዳውን የተያያዘ አስር ጋሻ መሬት ሰጥተዋል፡፡ የአጤ
ምኒልክ መኳንንትም በተመደበላቸው ስፍራ የራስ መኮንን
ሰፈር፣ የፊታውራሪ ሀብተጊዮርጊስ ሰፈር እየተባለ መስፈር
ጀመሩ፡፡ (በነገራችን ላይ ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ይቆዩበት
የነበረ ቤት አሁን ድረስ አዲስ ዓለም እንደሚገኝ የምናውቅ
ስንቶቻችን ነን? ስለዚህ ጉዳይ በቅርቡ መጻፌ አይቀርም፡፡)
እናም ወደ ጨዋታችን ስንመለስ፤ የአጤ ምኒልክን ቤተ
መንግስት አሰራር አስመልክቶ ሊቀ ጉባኤ ፈቃደ ስላሴ
እንደሚተርኩት የቤተ መንግስቱን ግንባታ ያካሂዱ የነበሩት
ባናውያን (መሀመድ ዓሊዎች) ሲሆኑ መጋዝ ሳቢ የሚባሉ
ባለሙያዎች ከቡልጋ መጥተው ለጣራ ስራ፣ ለቅስትና ለመቃን
የሚሆኑ ሁነኛ የጥድ እንጨቶችን ጭረቻ ከሚባል ቦታ
እየቆረጡና እየላጉ ያዘጋጁ ነበር ብለዋል፡፡ ይህ በእንዲህ
እንዳለ ግን ያው መቼም ያልተባለው አይፈጸምምና የዋና
ከተማዋን መዛወር በተመለከተ አንዳንድ ችግሮች መፈጠር
ጀመሩ፡፡ @embtee
ፕሮፌሰር ታደሰ ችግሮቹን ሲያብራሩ፤ በጊዜው የነበሩና ለ15
አመታት ያህል አዲስ አበባ የኖሩ፤ ሀብት ንብረት ያፈሩ
ወገኖች፣ ዲፕሎማቶችና አዲስ የንግድ መስመር መፈጠሩ
ያሰጋቸው ነጋዴዎች የመዲናይቱን መዛወር አስመልክቶ ቅሬታ
ማሰማታቸው ነበር፡፡ ለነገሩ፤ ግድ ካልሆነ በቀር የቆየ ቀየውን
መቀየር ማንስ ይወዳል? ከዚያማ በቃ፤ ይህ ሀሳብ ለአዲስ
አበባ ጽኑ ፍቅር በነበራቸው እቴጌ ጣይቱ ተቀባይነት አገኘና
እርሳቸው ደግሞ በፊናቸው ንጉሰ ነገስቱን ለማሳመን ጥረት
ማድረግ ጀመሩ፡፡ አሏቸውም፤
‹‹ ይኄይስነ ንግበር ዘንተ ሕንጻ ለቤተክርስቲያን ከመ ይኩነነ
መርሐ ለመንግሰተ ሰማያት ወውእቱኒ ተወክፈ ነገራ››
(ለመንግሰተ ሰማያት መግቢያ በር እንዲኖረን ይህንን ሕንጻ
ቤተክርስቲያን እናድርገው)
‹‹አጤ ምኒልክም በሀሳቡ ተስማምተው የአዲስ ዓለም
ከተማቸው ከምድራዊ መንግስት መዲናነት ይልቅ ከዚህ እጅግ
በጣም የላቀ መንፈሳዊ ስፍራ እንዲኖራት አደረጉ፡፡›› @embtee
አንዳንዴ፤ እንዲያው አዲስ ዓለም የሀገሪቱ መዲና ሆና ቢሆን
ኖሮ ስለ አዲስ አበባ የተዜሙት ዜማዎች፣ የተገጠሙት
ግጥሞች፣ የተባሉት ነገሮች ሁሉ ምን ሊሆኑ ይችል ነበር?
እያልኩ አስባለሁ፡፡
‹‹@embtee ነው ቤቴ . . .››
ርዕሰ አድባራት ወ ገዳማት ደብረ ጽዮን አዲስ አለም ማርያም
ንጉሠ ነገሥት ምኒልክ መዲናቸውን ወደ አዲስ ዓለም
ለማዛወር ያለቸውን ሀሳብ ካነሱ በኋላ ለቤተ መንግስትነት
የታሰበው ህንጻ ለቤተክርስቲየንነት በሚሆን መልኩ መገንባት
ጀመረ፡፡ የዚህም የቤተክርስቲያን ስራ እንግዳ አይነት ከዚህ
ቀደም በኢትዮጵያ ተሰርቶ የማያውቅ ነው፤ ይላሉ ሊቀ ጉባኤ
ፈቃደ ሥላሴ፡፡ የቤተ ክርስቲያኑ ግንባታ በተጀመረ ግዜ ለቤተ
መንግስቱ ግንባታ የተዘጋጁት የግንባታ እቃዎች ሁሉ
ለቤተክርስቲያኑ ግንባታ እንዲውሉ ተደረገ፡፡ ያው መቸው
በዘመኑ ሲሚንቶ ስላልነበረ ሕንጻው የተገነባው በጭቃና
በድንጋይ ሲሆን ጭቃው የተቦካው በስንዴ ገለባ፣ በጭድ እና
በበግ ጸጉር እንደሆነ ይተረካል፡፡
የአዲስ ዓለም ማርያም ቤተክርስቲያን ሕንጻ ጎኑ 27.50 ሜ
ወርዱ 24.40 ሜትር ሆኖ በድንጋይና በጭቃ የተገነባ
እንደመሆኑ የግንቡ ውፍረት አንድ ሜትር ሲሆን በአራት ማዕዘን
ቅርጽ የተገነቡ ስድስት የግንብ አምዶች አሉት፡፡
ዳግማዊት ጽዮን አዲስ ዓለም ማርያም እና አክሱም ጽዮን
ማርያም
የአዲስ ዓለም ማርያም በአክሱም ደረጃ የተተከለችበት ዋናው
ምክኒያት፤ ይላሉ ሊቀ ጉባኤ ፈቃደ ሥላሴ፤
አጤ ምኒልክ ዓድዋ
ጦርነት ሄደው ሳለ የአክሱም ካህናት ከየአድባራቱ አለቆችና
ካህናት ጋር ሱባዔ ይዘው ሰነበቱ፡፡ ከተመለሱም በኋላ ሌሎቹ
በየቤተመቅደሳቸው ምሕላ ይዘው ድሉ የምኒልክ እንዲሆን
ይጸልዩ ነበር፡፡ ወደ ምኒልክም ይላላኩ ነበር፡፡ የአክሱም
ንቡረዕድ ወደ እሳቸው ስላልመጡና ቅሬታ ስለተሰማቸው ንጉሱ
ከድል በኋላ እጅ መንሻ ወይም አምኃ ለቤተ መቅደሱ
በባለሟላቸው አማካይነት ልከው አክሱም ሳይደርሱ ወደ አዲስ
አበባ ተመልሰዋል፡፡ ንቡረዕዱና የአጼ ዮሐንስ ደጋፊዎች ግን
የአገሬውን ተወላጅ ለማንገስ ሽር ጉድ ይሉ እንደነበር ከዚያው
አካባቢ ምስጢረኞች መስማት ተችሎ ነበር፡፡ አጼ ምኒልክ
ከድል በኋላ ወደ አዲስ አበባ ከተማ እንደገቡ የነበረው
ሀሳባቸው ለታቦተ ማርያም ቤተ መቅደስ አሰርተው ሥርዐተ
አክሱምን የሚመሰርቱበት ቦታ መፈለግ ነበር፡፡ የአዲስ አለሙ
ቤተ መንግስታቸው ወደ ቤተ ታቦት ከተለወጠና ቤተ ክርስቲያኑ
ተሰርቶ ካለቀ በኋላ ዓጼ ምኒልክ ደብሯን ዳግማዊት ጽዮን
ብለው የአክሱም ጽዮንንም ክብር ሳይነኩ ማንኛውንም
የአክሱም ስርዓት በአዲስ ዓለም ዳግማዊት ደብረ ጽዮን
መስርተው ገድመዋታል፡፡
ማልዶ የነቃ፤ ቀድሞ ያንቀላፋል
አጤ ምኒልክ ለአዲስ ዓለም ያላቸውን ጽኑ ፍቅር ለመግለጽ
ለቤተ መንግስትነት ያሰቡትን ሕንጻ ወደ ቤተ ታቦትነት
በመለወጥ የቦታውን መንፈሳዊነት ለማስጠበቅ
ከመጣራቸውም በላይ በዘመኑ የነበሩ የስልጣኔ ነጸብራቆችን
ከአዲስ አበባ ቀጥሎ በአዲስ ዓለም እንዲገኙ ይጥሩ
እንደነበር ሊቀ ጉባኤ ፈቃደ ሥላሴ ይተርካሉ፡፡
ልብ በሉ እንግዲህ፤ አጤ ምኒልክ፤
· የውሀ ቧንቧ (መዘውር) አ.አ ሲገባ
አስገብተዋል
(ዛሬ ከአዲስ ዓለም ቧንቧዎች አፍ ታሪክ እንጂ ውሀ
አይቀዳም፡፡ ታሪክ ደግሞ መጠናት እንጂ መጠጣት
አይችልም)
· የስልክና የፖስታ ስራ በ 1892 ሲጀመር
የአዲስ ዓለም ከተማ ወዲያው ስለተመሰረተች
ለአዲስ ዓለም ፖስታ ቤት አቋቁመዋል
(አጤ ምኒልክ አዲስ ዓለም ሆነው ከተጻጻፏቸው
ደብዳቤዎች አንድ ሁለቱን እነሆ፡
1- ‹‹ይድረስ ከቢትወደድ ኢልግ
. . . ለጫማ የሚሆን የብረት ቅርቃር ከዚህ ከኔ ዘንድ
ታጣ፡፡ ምናልባት አንተ ዘንድ ይገኝ እንደሆነ
እንድትሰድልኝ ይሁን፡፡ ሐምሌ 4 ቀን አዲስ ዓለም
ከተማ ተጻፈ 1893 ዓ.ም›› ምንጭ ጳውሎስ ኞኞ
2- ‹‹ይድረስ ለቢትወደድ ኢልግ
የራስ ሚካዔል አሽከር በደጋ ግንድ ስናነሳ ሳንቃ
ከሆዱ ላይ ወድቆበት በብርቱ ታሞ ሊሞት ነው፡፡
አሁንም የኢጣሊያ ሐኪም መጥቶ ሁለት ሶስት
ቀን አይቶ ቢመለስ እወዳለሁና ነገ ነግረኸው
መጥቶ እንዲያየው ይሁን፡፡ ሚያዚያ 1 ቀን
1894 ዓ.ም አዲስ ዓለም ከተማ ተጻፈ፡፡››)
· የቋንቋ ትምህርት አዲስ አበባ ሲከፈት ለአዲስ
ዓለም የጀርመንኛ ቋን ቋ ት/ቤት ከፍተዋል፡፡
· በፈረስና በበሬ የሚጎተተው የጋሪ መንገድ
ሲሰራ ከአዲስ አበባ ቀጥሎ ወደ አዲስ ዓለም
እንዲጠረግ አስደርገዋል
(ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ የሚለው አባባል
ለዚህ መንገድ አይሰራም፡፡ የሄዱት የአዲስ ዓለም
ልጆች እስካሁን አልመጡም፡፡ ወዴት ናችሁ የአዲስ
ዓለም ልጆች? ‹‹ኤሰ ጅርቱ ኢጆሌ አዲስ ዓለሚ?
ኢጆሌ ኤጀሬ››
· በውሀ እንፋሎት የሚነዳ ባቡር በሙሴ ሰርኪስ
አማካይነት ከፈረንሳይ ገዝተው በማስመጣት
ከጅቡቲ እስከ አዲስ አበባ፣ ከአዲስ አበባ አዲስ
ዓለም ያለውን መንገድ የኢጣልያ ተወላጆች
በሆኑ መሀንዲሶች ካስቀየሱ በኋላ ከአዲስ አበባ
እስከ አዲስ ዓለም ያለውን መንገድ በገመድ
እያስለኩ ለእያንዳንዱ ሀገረ ገዢ ሰጡት፡፡ ከወሎ
እስከ ከፋ ያሉት ሀገረ ገዢዎችም በየግዛታቸው
የነበሩትን ገባሮች በወር ተራ እያዘዙ መሬቱን
በማስቆፈርና ድንጋዩን በማስቀጥቀጥ ከአዲስ
አበባ እስከ አዲስ ዓለም ያለውን መንገድ
አስደልድለውታል፡፡ ያንን ዘመን የሸዋ ሰው
‹‹የድንጋይ ቅጥቀጣ ጊዜ›› ብሎ ሰይሞታል፡፡
ያም የሰርኪስ ባቡር በንጉሱ ፍቃድ ሰዎችናና
ዕቃዎችን ወደ አዲስ ዓለም ያጓጉዝ ነበር፡፡
· በ 1900 አንድ ኦቶሞቢል ከፈረንሳይ ቢመጣ
ጃንሆይ አጼ ምኒልክ ኦቶሞቢሉን እያንጰረጰሩ
የተጓዙት ከአዲስ አበባ ወደ አዲስ ዓለም መሆኑ
ታውቋል፡፡
(በመኪና ሰሌዳ ቁጥር ሞላ-ጎደለ የመጫወትን ጥበብ
ለኢትዮጵያ ማቲዎች ያስተዋወቁት የአዲስ ዓለም
ልጆች ሳይሆኑ ይቀራሉ?)
አሁን አዲስ ዓለም እያንጎላዠች ነው፤ ማልዶ የነቃ ቀድሞ
ያንቀላፋልና፡፡
እኛ ግን ቅዠቶቿንም ቢሆን እያነሳሳን እንጨዋወታለን፡፡
ላሁኑ ግን ይብቃን፡፡
‹‹ሰላም!››
@embtee @embtee
Inbox @Maryamawit_bot
ሼር በማድረግ ለሌሎች እናጋራ
ጦርነት ሄደው ሳለ የአክሱም ካህናት ከየአድባራቱ አለቆችና
ካህናት ጋር ሱባዔ ይዘው ሰነበቱ፡፡ ከተመለሱም በኋላ ሌሎቹ
በየቤተመቅደሳቸው ምሕላ ይዘው ድሉ የምኒልክ እንዲሆን
ይጸልዩ ነበር፡፡ ወደ ምኒልክም ይላላኩ ነበር፡፡ የአክሱም
ንቡረዕድ ወደ እሳቸው ስላልመጡና ቅሬታ ስለተሰማቸው ንጉሱ
ከድል በኋላ እጅ መንሻ ወይም አምኃ ለቤተ መቅደሱ
በባለሟላቸው አማካይነት ልከው አክሱም ሳይደርሱ ወደ አዲስ
አበባ ተመልሰዋል፡፡ ንቡረዕዱና የአጼ ዮሐንስ ደጋፊዎች ግን
የአገሬውን ተወላጅ ለማንገስ ሽር ጉድ ይሉ እንደነበር ከዚያው
አካባቢ ምስጢረኞች መስማት ተችሎ ነበር፡፡ አጼ ምኒልክ
ከድል በኋላ ወደ አዲስ አበባ ከተማ እንደገቡ የነበረው
ሀሳባቸው ለታቦተ ማርያም ቤተ መቅደስ አሰርተው ሥርዐተ
አክሱምን የሚመሰርቱበት ቦታ መፈለግ ነበር፡፡ የአዲስ አለሙ
ቤተ መንግስታቸው ወደ ቤተ ታቦት ከተለወጠና ቤተ ክርስቲያኑ
ተሰርቶ ካለቀ በኋላ ዓጼ ምኒልክ ደብሯን ዳግማዊት ጽዮን
ብለው የአክሱም ጽዮንንም ክብር ሳይነኩ ማንኛውንም
የአክሱም ስርዓት በአዲስ ዓለም ዳግማዊት ደብረ ጽዮን
መስርተው ገድመዋታል፡፡
ማልዶ የነቃ፤ ቀድሞ ያንቀላፋል
አጤ ምኒልክ ለአዲስ ዓለም ያላቸውን ጽኑ ፍቅር ለመግለጽ
ለቤተ መንግስትነት ያሰቡትን ሕንጻ ወደ ቤተ ታቦትነት
በመለወጥ የቦታውን መንፈሳዊነት ለማስጠበቅ
ከመጣራቸውም በላይ በዘመኑ የነበሩ የስልጣኔ ነጸብራቆችን
ከአዲስ አበባ ቀጥሎ በአዲስ ዓለም እንዲገኙ ይጥሩ
እንደነበር ሊቀ ጉባኤ ፈቃደ ሥላሴ ይተርካሉ፡፡
ልብ በሉ እንግዲህ፤ አጤ ምኒልክ፤
· የውሀ ቧንቧ (መዘውር) አ.አ ሲገባ
አስገብተዋል
(ዛሬ ከአዲስ ዓለም ቧንቧዎች አፍ ታሪክ እንጂ ውሀ
አይቀዳም፡፡ ታሪክ ደግሞ መጠናት እንጂ መጠጣት
አይችልም)
· የስልክና የፖስታ ስራ በ 1892 ሲጀመር
የአዲስ ዓለም ከተማ ወዲያው ስለተመሰረተች
ለአዲስ ዓለም ፖስታ ቤት አቋቁመዋል
(አጤ ምኒልክ አዲስ ዓለም ሆነው ከተጻጻፏቸው
ደብዳቤዎች አንድ ሁለቱን እነሆ፡
1- ‹‹ይድረስ ከቢትወደድ ኢልግ
. . . ለጫማ የሚሆን የብረት ቅርቃር ከዚህ ከኔ ዘንድ
ታጣ፡፡ ምናልባት አንተ ዘንድ ይገኝ እንደሆነ
እንድትሰድልኝ ይሁን፡፡ ሐምሌ 4 ቀን አዲስ ዓለም
ከተማ ተጻፈ 1893 ዓ.ም›› ምንጭ ጳውሎስ ኞኞ
2- ‹‹ይድረስ ለቢትወደድ ኢልግ
የራስ ሚካዔል አሽከር በደጋ ግንድ ስናነሳ ሳንቃ
ከሆዱ ላይ ወድቆበት በብርቱ ታሞ ሊሞት ነው፡፡
አሁንም የኢጣሊያ ሐኪም መጥቶ ሁለት ሶስት
ቀን አይቶ ቢመለስ እወዳለሁና ነገ ነግረኸው
መጥቶ እንዲያየው ይሁን፡፡ ሚያዚያ 1 ቀን
1894 ዓ.ም አዲስ ዓለም ከተማ ተጻፈ፡፡››)
· የቋንቋ ትምህርት አዲስ አበባ ሲከፈት ለአዲስ
ዓለም የጀርመንኛ ቋን ቋ ት/ቤት ከፍተዋል፡፡
· በፈረስና በበሬ የሚጎተተው የጋሪ መንገድ
ሲሰራ ከአዲስ አበባ ቀጥሎ ወደ አዲስ ዓለም
እንዲጠረግ አስደርገዋል
(ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ የሚለው አባባል
ለዚህ መንገድ አይሰራም፡፡ የሄዱት የአዲስ ዓለም
ልጆች እስካሁን አልመጡም፡፡ ወዴት ናችሁ የአዲስ
ዓለም ልጆች? ‹‹ኤሰ ጅርቱ ኢጆሌ አዲስ ዓለሚ?
ኢጆሌ ኤጀሬ››
· በውሀ እንፋሎት የሚነዳ ባቡር በሙሴ ሰርኪስ
አማካይነት ከፈረንሳይ ገዝተው በማስመጣት
ከጅቡቲ እስከ አዲስ አበባ፣ ከአዲስ አበባ አዲስ
ዓለም ያለውን መንገድ የኢጣልያ ተወላጆች
በሆኑ መሀንዲሶች ካስቀየሱ በኋላ ከአዲስ አበባ
እስከ አዲስ ዓለም ያለውን መንገድ በገመድ
እያስለኩ ለእያንዳንዱ ሀገረ ገዢ ሰጡት፡፡ ከወሎ
እስከ ከፋ ያሉት ሀገረ ገዢዎችም በየግዛታቸው
የነበሩትን ገባሮች በወር ተራ እያዘዙ መሬቱን
በማስቆፈርና ድንጋዩን በማስቀጥቀጥ ከአዲስ
አበባ እስከ አዲስ ዓለም ያለውን መንገድ
አስደልድለውታል፡፡ ያንን ዘመን የሸዋ ሰው
‹‹የድንጋይ ቅጥቀጣ ጊዜ›› ብሎ ሰይሞታል፡፡
ያም የሰርኪስ ባቡር በንጉሱ ፍቃድ ሰዎችናና
ዕቃዎችን ወደ አዲስ ዓለም ያጓጉዝ ነበር፡፡
· በ 1900 አንድ ኦቶሞቢል ከፈረንሳይ ቢመጣ
ጃንሆይ አጼ ምኒልክ ኦቶሞቢሉን እያንጰረጰሩ
የተጓዙት ከአዲስ አበባ ወደ አዲስ ዓለም መሆኑ
ታውቋል፡፡
(በመኪና ሰሌዳ ቁጥር ሞላ-ጎደለ የመጫወትን ጥበብ
ለኢትዮጵያ ማቲዎች ያስተዋወቁት የአዲስ ዓለም
ልጆች ሳይሆኑ ይቀራሉ?)
አሁን አዲስ ዓለም እያንጎላዠች ነው፤ ማልዶ የነቃ ቀድሞ
ያንቀላፋልና፡፡
እኛ ግን ቅዠቶቿንም ቢሆን እያነሳሳን እንጨዋወታለን፡፡
ላሁኑ ግን ይብቃን፡፡
‹‹ሰላም!››
@embtee @embtee
Inbox @Maryamawit_bot
ሼር በማድረግ ለሌሎች እናጋራ
የካቲት_ 2_ፆመ_ነነዌ_ይጀምራል
" ምነው_ተኝተሃል ? እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ያስበን እንደ ሆነ ተነሥተህ አምላክህን ጥራ" አለው። ትንቢተ ዮናስ 1:6 ።
# የዚህ ፆም ጊዜ ሶስት ( 3 ) ቀን ብቻ ነው ። ቀኖቹም በየዓመቱ ሰኞ ማክሰኞ ረቡዕ ናቸው ። የነነዌ ፆም በመባቻ ሐሙስ( አቆጣጠር ) ከፍ እና ዝቅ ስለሚል አንድ ጊዜ በጥር አንድ ጊዜ በየካቲት ይሆናል ።
የቤተ ክርስቲያን አባቶች ይህን ፆም የወሰኑት ልትጠፋ የነበረች ነነዌን በፆም ምክንያት እግዚአብሔር ይቅር ስላላት ይህን አምላካዊ ይቅርታውን ለዘለዓለም ለማሰብና ዛሬም በዚህ ዓለም ከነነዌ የከፋ ርኩሰትንና ኃጢያትን ስላለ የነነዌ ሕዝብ ይቅር ያልክ አምላክ ዛሬን ይቅር በለን ለማለት ነው።
++ የነነዌ ሰዎችም እግዚአብሔርን አመኑ ለፆም አዋጅ ነገሩ
ከትልቁም ጀምሮ እስከ ትንሾቹም ማቅ ለበሱ ወሬውም ለነነዌ ንጉስ ደረሰ። እርሱም ከዙፋኑ ተነስቶ መጎናፀፊያውን አውልቆ ማቅንም ለበሰ። አመድ ላይም ተቀመጠ አዋጅንም አስነገረ።
++ በነነዌም ውስጥ የንጉሱንና የመኳንቱን ትእዛዝ አሳወጀ እንድህም አለ ሰዎችም እንስሶችም አንዳችም እንዳይቀምሱ አይሰማሩም ውኃንም አይጠጡ። ሰወችና እንስሳትም በማቅ ይከደኑ። ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩሁ። ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ። እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይፀፀት እንደሄነ ከፅኑ ቁጣውስ ይመለስ እንደሆነ ምን ያውቃል በማለትም አሳሳበ።
++ እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸውም እንደተመለሱ በስራቸውም አየ። እግዚአብሔር አምላክም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተፀፀቶ አላደረገውም
ት ዮናስ ( ፫ ፤ ፭-፲ )
የነነዌ ህዝብን በምህረቱ የጎበኘ ቸር አባት ለሀገራችንም ለህዝባችንም ምህረትና ቸርነቱን ያብዛልን ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን አሜን ፫
ለመንፈሳዊነት ቅድሚያ እንስጥና የእግዚአብሔርን ብድራት እንጠብቅ፡ እግዚአብሔር ጾማችንን ጾመ ድህነት ጾመ ስርየት ሰይጣንን ድል መንሻ ፣የኃጥያት መደምሰሻ ፣ መንግስተ
ሰማያትን መውረሻ ያድርግልን
ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን
@embtee
@embtee
@embtee
" ምነው_ተኝተሃል ? እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ያስበን እንደ ሆነ ተነሥተህ አምላክህን ጥራ" አለው። ትንቢተ ዮናስ 1:6 ።
# የዚህ ፆም ጊዜ ሶስት ( 3 ) ቀን ብቻ ነው ። ቀኖቹም በየዓመቱ ሰኞ ማክሰኞ ረቡዕ ናቸው ። የነነዌ ፆም በመባቻ ሐሙስ( አቆጣጠር ) ከፍ እና ዝቅ ስለሚል አንድ ጊዜ በጥር አንድ ጊዜ በየካቲት ይሆናል ።
የቤተ ክርስቲያን አባቶች ይህን ፆም የወሰኑት ልትጠፋ የነበረች ነነዌን በፆም ምክንያት እግዚአብሔር ይቅር ስላላት ይህን አምላካዊ ይቅርታውን ለዘለዓለም ለማሰብና ዛሬም በዚህ ዓለም ከነነዌ የከፋ ርኩሰትንና ኃጢያትን ስላለ የነነዌ ሕዝብ ይቅር ያልክ አምላክ ዛሬን ይቅር በለን ለማለት ነው።
++ የነነዌ ሰዎችም እግዚአብሔርን አመኑ ለፆም አዋጅ ነገሩ
ከትልቁም ጀምሮ እስከ ትንሾቹም ማቅ ለበሱ ወሬውም ለነነዌ ንጉስ ደረሰ። እርሱም ከዙፋኑ ተነስቶ መጎናፀፊያውን አውልቆ ማቅንም ለበሰ። አመድ ላይም ተቀመጠ አዋጅንም አስነገረ።
++ በነነዌም ውስጥ የንጉሱንና የመኳንቱን ትእዛዝ አሳወጀ እንድህም አለ ሰዎችም እንስሶችም አንዳችም እንዳይቀምሱ አይሰማሩም ውኃንም አይጠጡ። ሰወችና እንስሳትም በማቅ ይከደኑ። ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩሁ። ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ። እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይፀፀት እንደሄነ ከፅኑ ቁጣውስ ይመለስ እንደሆነ ምን ያውቃል በማለትም አሳሳበ።
++ እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸውም እንደተመለሱ በስራቸውም አየ። እግዚአብሔር አምላክም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተፀፀቶ አላደረገውም
ት ዮናስ ( ፫ ፤ ፭-፲ )
የነነዌ ህዝብን በምህረቱ የጎበኘ ቸር አባት ለሀገራችንም ለህዝባችንም ምህረትና ቸርነቱን ያብዛልን ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን አሜን ፫
ለመንፈሳዊነት ቅድሚያ እንስጥና የእግዚአብሔርን ብድራት እንጠብቅ፡ እግዚአብሔር ጾማችንን ጾመ ድህነት ጾመ ስርየት ሰይጣንን ድል መንሻ ፣የኃጥያት መደምሰሻ ፣ መንግስተ
ሰማያትን መውረሻ ያድርግልን
ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን
@embtee
@embtee
@embtee
እባካችሁ ሠዎች አንድ ነገር ልንገራችሁ እግዚአብሔር መሀሪ እና ቸር ነው
ስለ ምን እምነታችን ጎደለ?
ስለ ምን ፍርሀት በውስጣችን ነገሰ?
ስለ ምን ወሬ ማውራት ከመፀለይ በለጠብን?
ስለ ምን ከመንበርከክ በየፋርማሲው መሰለፍ ቀለለን?
ስለ ምን ወደ እግዚአብሔር ከመጮህ ይልቅ በየሶሻል ሚድያው ሽብር መንዛትን መረጥን ?
እግዚአብሔር ሁላችንንም በማያልቀው ምህረቱ ይቅር ይበለን
እግዚአብሔር ወደእርሱ እንድንቀርብ እና እንድንማልድ ይርዳን !
ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች !
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ !
እግዚአብሔር በክንፎቹ ጥላ ኢትዮጵያን ይጋርድ
╔═★══════════📄══╗
⛓ @Zemaryan ⛓
⛓ @Zemaryan ⛓
⛓ @Zemaryan ⛓
╚══📃══════════★═╝
ስለ ምን እምነታችን ጎደለ?
ስለ ምን ፍርሀት በውስጣችን ነገሰ?
ስለ ምን ወሬ ማውራት ከመፀለይ በለጠብን?
ስለ ምን ከመንበርከክ በየፋርማሲው መሰለፍ ቀለለን?
ስለ ምን ወደ እግዚአብሔር ከመጮህ ይልቅ በየሶሻል ሚድያው ሽብር መንዛትን መረጥን ?
እግዚአብሔር ሁላችንንም በማያልቀው ምህረቱ ይቅር ይበለን
እግዚአብሔር ወደእርሱ እንድንቀርብ እና እንድንማልድ ይርዳን !
ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች !
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ !
እግዚአብሔር በክንፎቹ ጥላ ኢትዮጵያን ይጋርድ
╔═★══════════📄══╗
⛓ @Zemaryan ⛓
⛓ @Zemaryan ⛓
⛓ @Zemaryan ⛓
╚══📃══════════★═╝
በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ በ24 አካባቢ ሁለቱ ወንድሞቻችን ሰማዕታነት የተቀበሉበት ቦታ ለቤተክርስቲያን ተሰጠ።
ዛሬ አመሻሽ ከቤተክህነት አካባቢ የተገኘው መረጃ እንደሚጠቁመው የፊታችን እሁድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያሪክ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ለሚሰራው ህንፃ ቤተክርስትያን የመሰረት ደንጋይ ያስቅምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
💚💛❤️ @ZEMARYAN 💚💛❤️
ዛሬ አመሻሽ ከቤተክህነት አካባቢ የተገኘው መረጃ እንደሚጠቁመው የፊታችን እሁድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያሪክ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ለሚሰራው ህንፃ ቤተክርስትያን የመሰረት ደንጋይ ያስቅምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
💚💛❤️ @ZEMARYAN 💚💛❤️
“ሀገራዊ የጸሎት ጥሪ እንጂ ጾም አልተባለም”
ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ታደለ የኢትዮጵያ የሃይማኖተ ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሓፊ
መጋቢት 28/2012 ዓ/ም
የኮሮና ቫይረስ በሀገራችን መከሰቱን ተከትሎ የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂ አአባቶች በአንድ ላይ ሆነው ብሔራዊ የጸሎት አዋጅ ትናንተ በ27/07/2012 ዓ.ም ማወጃቸው የሚታወስ ነው ፡፡ ይሁን እንጂ የታወጀው የጸሎት አዋጅ ሆኖ እያለ በተለያዩ የማኀበራዊ ድረ ገጾች ለምዕመናን የተሳሳተን መረጃ የሰጡ መሆናቸውን ያነሱት ጠቅላይ ጸሓፊው ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ተደለ የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂ አባቶች ያወጁት ለሁሉም ሃይማኖቶች ለአንድ ወር የሚቆይ ብሔራዊ የጸሎትና የንሥሓ አዋጅ እንጅ የጾም አይደለም ብለዋል፡፡
በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ጾም መሠረት ከትንሣኤ እስከ በዓለ ሃምሳ የጾም ሥርዓት እንደሌለ የሚታወቅ ሲሆን የሃይማኖት ተቋማቱ ጉባኤ በማንኛምው ቤተ እምነት ሕግና ሥርዓት ጣልቃ የማይገባ መሆኑን ብቻ ሳይሆን ፈጽሞ እንደማይችል ጨምረው ገልጠዋል ፡፡
አያይዘውም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሆነ የሌሎች አብያተ እምነት የጋራ ጸሎትና በኮሮና ወረርሽኝ እና መሰል ጉዳዮች የትምህርትና የጸሎት መርሐ ግብር በአራት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ከዛሬ ማለትም ከ28/07/2012 ዓ/ም ከምሽቱ 3፡00-4፡00 ለተመልካች እንደሚደርስ ገልጠው ሁሉም እንዲከታተል ጠቁመዋል ፡፡
በመጨረሻም ጠቅላይ ጸሓፊው ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ታደለ በዘመናችን የተከሰተው ክፉ ወረርሽኝ በሽታ እንዲወገድ ሁላችንም በበረታ ክንድ ልንጸል ይገባልም ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመርሐ ግብር ተራ በአራቱ ጣቢያዎች
ሰኞ፡ በ ETV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ማክሰኞ፡በ FANA ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ረቡዕ፡ በ ADDIS TV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ሐሙስ፡ በ WALTA ከምሽቱ 3፡00-4፡00
አርብ ፡ በ ETV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ቅዳሜ፡ በ FANA ከምሽቱ 3፡00-4፡00
እሑድ፡ በ ADDIS TV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
©EOTC TV
ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ታደለ የኢትዮጵያ የሃይማኖተ ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሓፊ
መጋቢት 28/2012 ዓ/ም
የኮሮና ቫይረስ በሀገራችን መከሰቱን ተከትሎ የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂ አአባቶች በአንድ ላይ ሆነው ብሔራዊ የጸሎት አዋጅ ትናንተ በ27/07/2012 ዓ.ም ማወጃቸው የሚታወስ ነው ፡፡ ይሁን እንጂ የታወጀው የጸሎት አዋጅ ሆኖ እያለ በተለያዩ የማኀበራዊ ድረ ገጾች ለምዕመናን የተሳሳተን መረጃ የሰጡ መሆናቸውን ያነሱት ጠቅላይ ጸሓፊው ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ተደለ የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂ አባቶች ያወጁት ለሁሉም ሃይማኖቶች ለአንድ ወር የሚቆይ ብሔራዊ የጸሎትና የንሥሓ አዋጅ እንጅ የጾም አይደለም ብለዋል፡፡
በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ጾም መሠረት ከትንሣኤ እስከ በዓለ ሃምሳ የጾም ሥርዓት እንደሌለ የሚታወቅ ሲሆን የሃይማኖት ተቋማቱ ጉባኤ በማንኛምው ቤተ እምነት ሕግና ሥርዓት ጣልቃ የማይገባ መሆኑን ብቻ ሳይሆን ፈጽሞ እንደማይችል ጨምረው ገልጠዋል ፡፡
አያይዘውም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሆነ የሌሎች አብያተ እምነት የጋራ ጸሎትና በኮሮና ወረርሽኝ እና መሰል ጉዳዮች የትምህርትና የጸሎት መርሐ ግብር በአራት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ከዛሬ ማለትም ከ28/07/2012 ዓ/ም ከምሽቱ 3፡00-4፡00 ለተመልካች እንደሚደርስ ገልጠው ሁሉም እንዲከታተል ጠቁመዋል ፡፡
በመጨረሻም ጠቅላይ ጸሓፊው ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ታደለ በዘመናችን የተከሰተው ክፉ ወረርሽኝ በሽታ እንዲወገድ ሁላችንም በበረታ ክንድ ልንጸል ይገባልም ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመርሐ ግብር ተራ በአራቱ ጣቢያዎች
ሰኞ፡ በ ETV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ማክሰኞ፡በ FANA ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ረቡዕ፡ በ ADDIS TV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ሐሙስ፡ በ WALTA ከምሽቱ 3፡00-4፡00
አርብ ፡ በ ETV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ቅዳሜ፡ በ FANA ከምሽቱ 3፡00-4፡00
እሑድ፡ በ ADDIS TV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
©EOTC TV
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል አደረሳችሁ።
ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም
«መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው»
/መዝ. ፹፮፥፩/
ስለ እመቤታችን የትውልድ ሐረግ ከመወለዷ በፊት ነብያት በመንፈስ ቅዱስ በመቃኘት ትንቢት ይናገሩ እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ በስፋት ያስተምረናል፡፡ ለምሳሌ ያህልም የዝማሬና የትንቢት ጸጋ በእግዚአብሔር የተሰጠው እንደ ልቤ የተባለ ዳዊት ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አስቀድሞ ስለ ሥርወልደቷ፣ አምላክን እንደምትወልድ፣ ስለ አማላጅነቷ በመዝሙር ተናግሯል ለምሳሌ በመዝ ፹፮፥፩ ላይ ‹‹መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን›› መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፡፡ በማለት ከቤተክህነት ከቅዱሳን እንደምትወለድ በምሳሌ ገልፆታል፡፡
ልጁም ጠቢቡ ሰሎሞን መኃ.መኃ.4.9 ‹‹እቴ መርዓት ሙሽርዬ ከሊባኖስ ነይ" እያለ የተወለደችበትን ሀገር እንደጠቀሰ መመልከት ይቻላል፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ በትንቢቱ ‹‹ትውፅእ በትር እምሥርው እሰይ ወየዐረግ ጽጌ እምኔሃ›› ትርጉሙም ከእሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከርሷ ይወጣል በማለት ተናግሯል ት.ኢሳ ፲፩፩
በሐዲስ ኪዳንም እንደምንመለከተው ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ በወንጌሉ መጀመሪያ የዘር ሐረጉን በዳዊት ጀምሮ እስከ ማታን ይቆጥራል በአይሁድ ልምድ ሴቶች በዘር ቆጠራ ስለማይቆጠሩ ዘፍራን በያዕቆብ ወገን አድርጎ ቆጠረ በዚህም ከዳዊት ወገን መሆኗን አሳውቋል፡፡
የእመቤታችን ወላጆች በምዕራብያውያኑና በምስራቅያውያኑ ዘንድ ታዋቂ በሆነው በመጽሐፈ ያዕቆብ (መጽሐፈ ልደታ ለማርያም) የእናቷ ስም ሐና የአባቷ ስም ኢያቄም እንደሚባል ጽፏል፡፡ ሐና በዕብራይስጥ "ውብ ተወዳጅ" ማለት ነው፡፡ ኢያቄም በዕብራይስጥ እግዚአብሔር የሠራው ያከናወነው ማለት ነው፡፡ እንዳንድ መናፍቃን ለእመቤታችን ካላቸው ጥላቻ የተነሳ አንድ ስለመውለዷ የጻፈ የለም ከአፄ ዘርዓያዕቆብ ውጪ ይላሉ፡፡ ግን ከላይ የተመለከትነው መጽሐፍ በጣም ጥንታዊ በዘመን የማይደራረስ መሆንን የታሪክ ድርሰቶች ይናገራሉ፡፡ አፄ ዘርዓያዕቆብ የነበረው በ1399-1468 ባሉት ዓመታት ሲሆን ሐዋርያው ታናሽ ያዕቆብ የጻፈውን መጽሐፍ በ150-215 ዓ.ም ሊቁ ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ እና ኦርገን እንደተጠቀሙበት እንመለከታለን ቀደምት አባቶቻችን ግን የሐና ቅድመ አባቶቿ ቴክታና ጴጥሪቃ ሲባሉ እግዚአብሔርን የሚፈሩና የሚያከብሩ ደግና ቅዱሳን እንደነበሩ ይህ ቀራቸው የማይባሉ ባለጠጎች ወርቅ ብር የተትረፈረፈላቸው ነበሩ፡፡ ጴጥሪቃ ሀብቱን ሁሉ ከተመለከተ በኋላ ለሚስቱ ይህን ሁሉ ሀብት ምን እናደርገዋለን እንኳን ለእኛ ለልጅ ልጆቻችን ይተርፍ ነበር ግን እኔም አንቺም መካኖች ነን ባላት ጊዜ ቴክታ እግዚአብሔር ከኔ ልጅ ባይሰጥህ ከሌላ ይሰጥህ ይሆነናልና ሌለ አግብተህ ውለድ፡፡ አለችው እሱም ይህን እንኳን ላደርገው እንደማላስበው እግዚአብሔር ያውቃል አላት፡፡ ማታ በህልሟ ቴክታ ነጭ እንቦሳ ከማኅጸኗ ስትወጣ እንቦሳይቱ እንቦሳ እየወለደች እስከ ሰባተኛዋ ደረሰ ሰባተኛዋ ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃ ፀሐይን ስትወልድ አይታ አድንቃ ለባሏ ነገረችው እሱም በልቡ እያደነቀ ወደ ህልም ፈቺ ጋር ሄደ፡፡ ህልም ፈቺውም ነጫጮቹ እንቦሶች ሰባት ደጋግ ልጆች ይወልዳሉ ሰባተኛዋ ግን በመላዕክት ሁሉ የከበረች ትሆናለች የፀሐይ ነገር ግን አልተገለፀልኝም በማለት ተረጎመላት፡፡ ጴጥሪቃ ሄዶ የህልሙን ፍቺ ነገራት እርሷም የእስራኤል አምላክ የሚያደርገውን እርሱ ያውቃል በማለት ፈጣሪዋን አመሰገነች፡፡ በዚያም ፀንሳ ሴት ልጅ ወለደች ስሟንም ሔመን አሏት ሔመን ዴርዴን ወለደች ዴርዴም ቶናን ወለደ ቶናም ሲካርን ወለደች ሲካርም ሴትናን ወለደች ሴትናም ሔርሜላን ወለደች ሔርሜላም የተከበረችና የተመረጠች ዓለሙን ሁሉ ለፈጠረ ጌታ አያት የምትሆን ሐናን ወለደች፡፡ ሐና በመልካም አስተዳደግ አድጋ ለአካለ መጠን ስትደርስ ከነገደ ይሁዳ ወገን ለሚሆን የአላዛር የልጅ ልጅ ለሚሆን የቅስራ ልጅ ከሚሆን ከኢያቄም ዳሯት፡፡ ሐናና ኢያቄም በእግዚዓብሔር የሚወደዱ ደጋጎች ነበሩ ፡፡ ግን ልጅ አልነበራቸውም! ወደ ቤተ መንግስት በመሔድ እግዚዓብሔርን ደጅ ይጠኑት ነበር አንድ ቀን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ርግብ ከልጆቿ ጋር ስትጫወት ተመለከቱ በዚህን ጊዜ ሐና "አቤቱ ጌታዬ ግዑዛን እንስሳ ልጅ የሰጠህ ለኔ ለምን ነሳኸኝ" በማለት ሱባኤ ያዙ ኢያቄም ወደ ምድረ በዳ ሄደ ሐናም በቤቱ አትክልት ስፍራ አካባቢ ሱባኤ ያዘች በሱባኤያቸውም ፍፃሜ ራዕይ ተመለከቱ፡፡
ሐናም ለኢያቄም በህልሜ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማኅጸኔ አደረች ብላ ነገረችው ምስጢሩም ርግብ የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስትሆን ነጭነቷ ንፅህናዋ፣ ቅድስናዋን የሚገልጽ ነው፡፡ ኢያቄምም የተመለከተውን ራዕይ ነገራት በህልሙ ሰባቱ ሰማያት እንደመጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወረደ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ ብሎ ነገራት፡፡ ምስጢሩም ወፍ የተባለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ነጭነቱ ንጹሐ ባሕሪ መሆኑን ሲያመለክት ነው፡፡ ይህን ራዕይ ሐምሌ ፴ ቀን ተመልክተው ልጅ ብንወልድ ለእግዚአብሔር አገልጋይ ትሁን ብለው ተሳሉ እመቤታችን በእግዚአብሔር ፈቃድ በብስራተ ገብርኤል ነሐሴ ሰባት እሑድ ቀን ተፀንሳለች፡፡እመቤታችን በማኅፀንም ሆና ብዙ ተአምራትን አድርጋለች፡፡ ሁለቱን ለአብነት ያህል እናያለን፡፡
ሐና በርሴባ የምትባል አንድ ዓይና አክስት ነበረቻት ልትጠይቃት መጥታ ሳለ እግዚአብሔር በቸርነት ጎበኘሽ ብላ ማኅፀኗን በዳሰሰችበት እጇ የጠፋ ዓይኗን ብታሸው በርቶላታል፡፡ ሌሎችም እንዲሁ ሆዷን እየዳሰሱ ድነዋል፡፡
ሐና የምትወደው ሳምናስ የሚባል የአጎቷ ልጅ ሞቶ በቤተሰብ ልማድ የአልጋውን ሸንኮር ይዛ ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት ሙቱ አፈፍ ብሎ ተነስቶ ሰላም ለኪ ኦ እምሔውቱ ለዘገብረ ሰማየ ወምድረ ሰማይና ምድርን የፈጠረ የአምላክ አያቱ ሐና ሰላም ላንቺ ይሁን ብሎ መስክሮ ተመልሶ አርፏል፡፡
በእናቷ ማኅጸን ሳለችም እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ከአዳም ጅምሮ በዘሩ ሁሉ ሲተላለፍ የነበረው ጥንት አብሶ እመቤታችንን እንዳይነካት ከእናቷ ማኅጸን ጀምሮ ጠብቋታል፡፡
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ግንቦት 1 ቀን በሊባኖስ ተወልዳለች፡፡በሊባኖስ መወለዷም ሰሎሞን ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ መኃ.መኃ ዘሰሎሞን 4.9 ያለው ይፈፀም ዘንድ ነው፡፡ቤተ-ክርስቲያናችንም "ልደተ ለማርያም" በማለት በዓሉን በቅዳሴ፣ በማህሌት በታላቅ መንፈሳዊ ሐሴት ታከብረዋለች፡፡ ሐናና ኢያቄም እግዚአብሔር በሰጣቸው ልጅ ተደስተው በተወለደች በ8 ቀኗ ማርያም ብለው ስም አወጡላት፡፡
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምልጃዋ አትለየን፡፡ሀገራችንን ትጠብቅልን በዓለም ላይ የመጣውን መቅሰፍት ትመልስልን፡፡ዳግመኛ ተሰባስበን በዓሏን ለማክበር ያብቃን አሜን
ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም
«መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው»
/መዝ. ፹፮፥፩/
ስለ እመቤታችን የትውልድ ሐረግ ከመወለዷ በፊት ነብያት በመንፈስ ቅዱስ በመቃኘት ትንቢት ይናገሩ እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ በስፋት ያስተምረናል፡፡ ለምሳሌ ያህልም የዝማሬና የትንቢት ጸጋ በእግዚአብሔር የተሰጠው እንደ ልቤ የተባለ ዳዊት ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አስቀድሞ ስለ ሥርወልደቷ፣ አምላክን እንደምትወልድ፣ ስለ አማላጅነቷ በመዝሙር ተናግሯል ለምሳሌ በመዝ ፹፮፥፩ ላይ ‹‹መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን›› መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፡፡ በማለት ከቤተክህነት ከቅዱሳን እንደምትወለድ በምሳሌ ገልፆታል፡፡
ልጁም ጠቢቡ ሰሎሞን መኃ.መኃ.4.9 ‹‹እቴ መርዓት ሙሽርዬ ከሊባኖስ ነይ" እያለ የተወለደችበትን ሀገር እንደጠቀሰ መመልከት ይቻላል፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ በትንቢቱ ‹‹ትውፅእ በትር እምሥርው እሰይ ወየዐረግ ጽጌ እምኔሃ›› ትርጉሙም ከእሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከርሷ ይወጣል በማለት ተናግሯል ት.ኢሳ ፲፩፩
በሐዲስ ኪዳንም እንደምንመለከተው ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ በወንጌሉ መጀመሪያ የዘር ሐረጉን በዳዊት ጀምሮ እስከ ማታን ይቆጥራል በአይሁድ ልምድ ሴቶች በዘር ቆጠራ ስለማይቆጠሩ ዘፍራን በያዕቆብ ወገን አድርጎ ቆጠረ በዚህም ከዳዊት ወገን መሆኗን አሳውቋል፡፡
የእመቤታችን ወላጆች በምዕራብያውያኑና በምስራቅያውያኑ ዘንድ ታዋቂ በሆነው በመጽሐፈ ያዕቆብ (መጽሐፈ ልደታ ለማርያም) የእናቷ ስም ሐና የአባቷ ስም ኢያቄም እንደሚባል ጽፏል፡፡ ሐና በዕብራይስጥ "ውብ ተወዳጅ" ማለት ነው፡፡ ኢያቄም በዕብራይስጥ እግዚአብሔር የሠራው ያከናወነው ማለት ነው፡፡ እንዳንድ መናፍቃን ለእመቤታችን ካላቸው ጥላቻ የተነሳ አንድ ስለመውለዷ የጻፈ የለም ከአፄ ዘርዓያዕቆብ ውጪ ይላሉ፡፡ ግን ከላይ የተመለከትነው መጽሐፍ በጣም ጥንታዊ በዘመን የማይደራረስ መሆንን የታሪክ ድርሰቶች ይናገራሉ፡፡ አፄ ዘርዓያዕቆብ የነበረው በ1399-1468 ባሉት ዓመታት ሲሆን ሐዋርያው ታናሽ ያዕቆብ የጻፈውን መጽሐፍ በ150-215 ዓ.ም ሊቁ ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ እና ኦርገን እንደተጠቀሙበት እንመለከታለን ቀደምት አባቶቻችን ግን የሐና ቅድመ አባቶቿ ቴክታና ጴጥሪቃ ሲባሉ እግዚአብሔርን የሚፈሩና የሚያከብሩ ደግና ቅዱሳን እንደነበሩ ይህ ቀራቸው የማይባሉ ባለጠጎች ወርቅ ብር የተትረፈረፈላቸው ነበሩ፡፡ ጴጥሪቃ ሀብቱን ሁሉ ከተመለከተ በኋላ ለሚስቱ ይህን ሁሉ ሀብት ምን እናደርገዋለን እንኳን ለእኛ ለልጅ ልጆቻችን ይተርፍ ነበር ግን እኔም አንቺም መካኖች ነን ባላት ጊዜ ቴክታ እግዚአብሔር ከኔ ልጅ ባይሰጥህ ከሌላ ይሰጥህ ይሆነናልና ሌለ አግብተህ ውለድ፡፡ አለችው እሱም ይህን እንኳን ላደርገው እንደማላስበው እግዚአብሔር ያውቃል አላት፡፡ ማታ በህልሟ ቴክታ ነጭ እንቦሳ ከማኅጸኗ ስትወጣ እንቦሳይቱ እንቦሳ እየወለደች እስከ ሰባተኛዋ ደረሰ ሰባተኛዋ ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃ ፀሐይን ስትወልድ አይታ አድንቃ ለባሏ ነገረችው እሱም በልቡ እያደነቀ ወደ ህልም ፈቺ ጋር ሄደ፡፡ ህልም ፈቺውም ነጫጮቹ እንቦሶች ሰባት ደጋግ ልጆች ይወልዳሉ ሰባተኛዋ ግን በመላዕክት ሁሉ የከበረች ትሆናለች የፀሐይ ነገር ግን አልተገለፀልኝም በማለት ተረጎመላት፡፡ ጴጥሪቃ ሄዶ የህልሙን ፍቺ ነገራት እርሷም የእስራኤል አምላክ የሚያደርገውን እርሱ ያውቃል በማለት ፈጣሪዋን አመሰገነች፡፡ በዚያም ፀንሳ ሴት ልጅ ወለደች ስሟንም ሔመን አሏት ሔመን ዴርዴን ወለደች ዴርዴም ቶናን ወለደ ቶናም ሲካርን ወለደች ሲካርም ሴትናን ወለደች ሴትናም ሔርሜላን ወለደች ሔርሜላም የተከበረችና የተመረጠች ዓለሙን ሁሉ ለፈጠረ ጌታ አያት የምትሆን ሐናን ወለደች፡፡ ሐና በመልካም አስተዳደግ አድጋ ለአካለ መጠን ስትደርስ ከነገደ ይሁዳ ወገን ለሚሆን የአላዛር የልጅ ልጅ ለሚሆን የቅስራ ልጅ ከሚሆን ከኢያቄም ዳሯት፡፡ ሐናና ኢያቄም በእግዚዓብሔር የሚወደዱ ደጋጎች ነበሩ ፡፡ ግን ልጅ አልነበራቸውም! ወደ ቤተ መንግስት በመሔድ እግዚዓብሔርን ደጅ ይጠኑት ነበር አንድ ቀን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ርግብ ከልጆቿ ጋር ስትጫወት ተመለከቱ በዚህን ጊዜ ሐና "አቤቱ ጌታዬ ግዑዛን እንስሳ ልጅ የሰጠህ ለኔ ለምን ነሳኸኝ" በማለት ሱባኤ ያዙ ኢያቄም ወደ ምድረ በዳ ሄደ ሐናም በቤቱ አትክልት ስፍራ አካባቢ ሱባኤ ያዘች በሱባኤያቸውም ፍፃሜ ራዕይ ተመለከቱ፡፡
ሐናም ለኢያቄም በህልሜ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማኅጸኔ አደረች ብላ ነገረችው ምስጢሩም ርግብ የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስትሆን ነጭነቷ ንፅህናዋ፣ ቅድስናዋን የሚገልጽ ነው፡፡ ኢያቄምም የተመለከተውን ራዕይ ነገራት በህልሙ ሰባቱ ሰማያት እንደመጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወረደ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ ብሎ ነገራት፡፡ ምስጢሩም ወፍ የተባለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ነጭነቱ ንጹሐ ባሕሪ መሆኑን ሲያመለክት ነው፡፡ ይህን ራዕይ ሐምሌ ፴ ቀን ተመልክተው ልጅ ብንወልድ ለእግዚአብሔር አገልጋይ ትሁን ብለው ተሳሉ እመቤታችን በእግዚአብሔር ፈቃድ በብስራተ ገብርኤል ነሐሴ ሰባት እሑድ ቀን ተፀንሳለች፡፡እመቤታችን በማኅፀንም ሆና ብዙ ተአምራትን አድርጋለች፡፡ ሁለቱን ለአብነት ያህል እናያለን፡፡
ሐና በርሴባ የምትባል አንድ ዓይና አክስት ነበረቻት ልትጠይቃት መጥታ ሳለ እግዚአብሔር በቸርነት ጎበኘሽ ብላ ማኅፀኗን በዳሰሰችበት እጇ የጠፋ ዓይኗን ብታሸው በርቶላታል፡፡ ሌሎችም እንዲሁ ሆዷን እየዳሰሱ ድነዋል፡፡
ሐና የምትወደው ሳምናስ የሚባል የአጎቷ ልጅ ሞቶ በቤተሰብ ልማድ የአልጋውን ሸንኮር ይዛ ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት ሙቱ አፈፍ ብሎ ተነስቶ ሰላም ለኪ ኦ እምሔውቱ ለዘገብረ ሰማየ ወምድረ ሰማይና ምድርን የፈጠረ የአምላክ አያቱ ሐና ሰላም ላንቺ ይሁን ብሎ መስክሮ ተመልሶ አርፏል፡፡
በእናቷ ማኅጸን ሳለችም እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ከአዳም ጅምሮ በዘሩ ሁሉ ሲተላለፍ የነበረው ጥንት አብሶ እመቤታችንን እንዳይነካት ከእናቷ ማኅጸን ጀምሮ ጠብቋታል፡፡
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ግንቦት 1 ቀን በሊባኖስ ተወልዳለች፡፡በሊባኖስ መወለዷም ሰሎሞን ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ መኃ.መኃ ዘሰሎሞን 4.9 ያለው ይፈፀም ዘንድ ነው፡፡ቤተ-ክርስቲያናችንም "ልደተ ለማርያም" በማለት በዓሉን በቅዳሴ፣ በማህሌት በታላቅ መንፈሳዊ ሐሴት ታከብረዋለች፡፡ ሐናና ኢያቄም እግዚአብሔር በሰጣቸው ልጅ ተደስተው በተወለደች በ8 ቀኗ ማርያም ብለው ስም አወጡላት፡፡
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምልጃዋ አትለየን፡፡ሀገራችንን ትጠብቅልን በዓለም ላይ የመጣውን መቅሰፍት ትመልስልን፡፡ዳግመኛ ተሰባስበን በዓሏን ለማክበር ያብቃን አሜን