✞ ደጓ እናቴ ማርያም ✞
1.21K subscribers
178 photos
11 videos
29 files
137 links
ከፍቅሯ ርቃቹ የምትኖሩ ማርያም ፊደል ናት ኑ ተማሩ
ለአባ ሕርያቆስ ፤
ለቅዱስ ኤፍሬም ፤
ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣
ለአባ ይስሀቅ
የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤
ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!
@embtee
@embtee

@Binyama1

@yitayal_bot

Contact @Maryamawit_bot
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ምን ይባላል አባቶች እንደዚ እስኪሆኑ እስከመቼ ወገን እስከመቼ ዝም የምንለው

መሉውን ነገ እንለቀዋለን 👇
https://youtu.be/aPrhwcuRmmw
ኦርቶዶክሳውያን ጷጉሜን የት ናችሁ ?

+ ጷጉሜን የሲኖዶስ ውሳኔ የምንሰማበት ነው!
+ ጷጉሜን የፈቃድ ጾም ላይ ነን!
+ ጷጉሜን 3 በሰማዩ ጠል እንጠመቃለን!
+ ጷጉሜን 3 የቅዱስ ሩፋኤል ንግሥ በዓል አለብን

ኦርቶዶክሳውያን ጷጉሜንን በረብ የለሽ "ድራማ" ለማሳለፍ ጊዜ የለንም !!!

First thing first!

አባቶቻችን ያቀረቡትን "የሕግ ይከበርልን" ጥያቄ እንዳልሰማ በዝምታ ማለፍ እና ህገወጦች ማኅተም አስቀርጸው በቤተክርስቲያኒቱ ላይ እንዲፈነጩባት መፍቀድ ክብረነክነት ነው!
ለኦርቶዶክሳውያን !

+ አባቶቻችን ነገ ነሐሴ 30 ቀን አስቸኳይ ስብሰባ ያደርጋሉ፡፡

+ ለምን ታዲያ እኛስ እንደ ምእመንነታችን ማድረግ የምንችለውን አናደርግም?

+ ለምን እነርሱ ሲሰበሰቡ እኛም አብረን የዓቅማችንን ያህል በፈቃደኝነት አንጾምም?

+ ለምን የዓቅማችንን ያህል ሌላ ጊዜ ከምንጸልየው በተጨማሪ ጸሎት አናደርስም?

+ አሕዛብ የነበሩ የነነዌ ሰዎች ሊመጣ ከነበረው መዓት በእውነተኛ ንስሐቸው በጾም በጸሎት ከተረፉ፥ ክርስቲያን የኾንን እኛ'ማ እንዲህ እንደ ዓቅማችን ብናደርግ እግዚአብሔር የበለጠ ይሰማናል፡፡

+ ስለዚህ ይህን ጽሑፍ የምታነቡ ወገኖቼ መንግሥት የሚሠራውን በቁዔት የለሽ ድራማ ትተን ይህን ሠናይ ሥራ ብናደርግ መልካም ነው፡፡

@zemaryan
ሲጠበቅ የነበረው ተለቀቀ ተለቀቀ ተለቀቀ

👇👇👇👇👇👇

https://youtu.be/h5FxXUdqZS4
የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ‼️

የቤተክርስቲያን ነገር ያገባኛል የሚል ሁሉ ሰላማዊ ሰልፍ መስከረም 4 / 2012 በመስቀል አደባባይ እንገናኝ !! እየታረድን ቤተክርስቲያን እየተቃጠለ
በፍፁም ዝም አንልም!!

እምዬ " ተዋሕዶን " ሮጦ የቀደማት ፣ ተከራክሮ የረታት ማንም የለም። አንዳንዶች በእሳት አቃጥለው ፣ አንድደው ፤ ዶግ አመድ አድርገው ፤ አንዳንዶች በሰይፍ እና በስለት ከፍ ብለው አንገቷን ዝቅ ብለው ባቷን መትረው ለማጥፈት ሞክረዋል።

አቃጣዮቿ ተቃጥለው ፤ ገዳዮቿ ሞተው ስም አጠራራቸው እስኪጠፋ ድረስ ተረስተዋል ። እሷ ግን ይኸው የገዳዮቿን ሰይፍና ካባ በክብር አስቀምጣ ለትውልድ እያስጎበኘች እንዳለች አለች።

ወደፊትም ሙሽራዋ ክርስቶስ በክብር መጥቶ እስኪቀበላት ወደ እቅፉም እስኪያስገባት ድረስ እንዲሁ እንዳማረባት ፣ እንደፈካች ፣ እንዳበበች ትኖራለች።

ይህ የኳስም አይደለም አንድ የፓለቲካ ግለሰብ ለመደገፍም አይደለም ይህ የነብሳችን ማረፊያ የሀይማኖት ጉዳይ ነው የማህተብ ጉዳይ ነው ማንም እንዳይቀር በየክልሉ ያላቹ በእመብርሀን እላቹአለው እንዳትቀሩ ምክንያት አያስፈልግም እለቱ እሁድ ነውና ኢንተርኔቱ ለማይደርሳቸው ላልሰሙም አሰሙ ስለ ሀይማኖታችን ነው።


እኔ ደግሞ እላለው ዛሬ ይኅን ዝም ካልክ ነገእርስበእርስ እንጨራረሳለን
እባክዎን ለ10 የክርስቶስ ልጆች ሼር በማድረግ ግዴታዎን ይወጡ

#ሼር በማድረግ ለጓደኛ በየግሩፑ በተለያዩ ሶሻል ሚዲያ #ሼር በማድረግ ዘመቻውን ይቀላቀሉ !!!

ተዋህዶ ሁሌም እንዳበበች ትኖራለች

@zemaryan @zemaryan
#አ_ል_ሳ_ተ_ፍ_ም!

ለኦርቶዶክሳዊያን እና ለሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በሙሉ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በኦሮሞ ባህል ማዕከል የተጠራውን ሕገወጥ መርሐ ግብር ከቤተ ክርስቲያኒቷ ዕውቅና ውጪ የሚደረግ መሆኑን ጠቅሶ ይህንን ሕገ ወጥ ድርጊት መንግሥት እንዲያስቆም ነሐሴ 24 ቀን 2011 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ ቢጠይቅም፤ መንግሥት ቤተ ክርስቲያኒቷን በመናቅ መርሐ ግብሩ እንዲካሄድ ፈቅዷል፡፡

በመሆኑም መላው ኦርቶዶክሳውያን እና ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ሁላችን፤ የሀገር ባለውለታ በሆነችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ እየተቃጣ ያለውን ጥቃትና ሤራ አስመልክቶ በሚደረገው የጥፋት አካሄድ ሁሉ እየተባበረ ያለውን መንግሥት ፥ ይህንን ስህተቱን እንዲያርም እና ሕገ ወጡን ቡድኑን እንዲያስቆም በጳጉሜን ወር ሊያዘጋጀው ባሰበው የመንግሥት መርሐ ግብር ላይ ባለመሳተፍ እንጠይቅ፡፡

ሲጀመር ጀምሮም፤ ለብሔራዊ ኩራትና ለሀገራዊ አንድነት፣ ለሰላምና ብልጽግና፣ ለፍትኅና እኩልነት ከማንም ቀድማ ለታገለችና ሀገር ላቆመች ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋንና ጥያቄዋን በመናቅና ባለማክበር ይህን መርሐ ግብር ለማካሄድ ማሰብም ከፈረሱ ጋሪውን እንደማስቀደምና ለኢትዮጵያና ለሕዝቡ ያበረከተቻቸውን እነኚህን እሴቶች መንግሥት በመናቁ ይህን መርሐ ግብር አልሳተፍም!

#አንሳተፍም #አልሳተፍም

CC፦ #Office_of_the_Prime_Minister-Ethiopia

@zemaryan
እህት ወንድሞች በልዑል እግዚአብሔር ስም እንደምን ቆያቹ ።

ያለ ጭንቀት የመኖር ሚስጥር በመምህር ምህረተ አብ አሰፋ የተሰጠ ድንቅ አውደ ስብከት ልናጋራቹ ወደድን ስለ እውነት ይማሩበታል ማን ያልተጨነቀ አለ እመብርሀን ጭንቀታችንን ታቅልልን

ከእርሶ ሚጠበቀው ከታች ባለው ሊንክ ተጭነው subscribe አድርገው በየእለቱ የምንለቃቸው ፕሮግራሞች አያመልጦትም subscribe እናንተም ለኛ ለምንሰራው ብርታት ትሆኑናላቹ ቤተሰብ መሆኖትን አብረውን መሆንዎን ያሳዩን በዩቱባችን ቤተሰብ ይሁኑ።

ነገ ይለቀቃል ለሌሎች አጋሩ ድንቅ አውደ ስብከት ነው ሌሎችም ይሰሙ ዘንድ 👇
👇👇ሼር ለጓደኛዎ👇👇

https://m.youtube.com/channel/UCuzDApz9RTu02VXXFRnwQtg
✞ ደጓ እናቴ ማርያም ✞ pinned «ተለቋል ያዳምጡት https://youtu.be/KMn4FufdgbM»
የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ

የዳዊት ዜማ ቻናል ተከታታዮች እንኳን ደስ አለን ሊቀር ነው ሲባል የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ተፈቀደ

በመጨረሻም የመስከረም 4 ሰልፍ እርግጥ ሆኗል ያውም በአዲስአበባ ብቻ ሳይሆን በመላው አለም ይደረጋል እያንዳንዱ ሰው ከወዲሁ ነጭ ልብስ ለራሱ ያዘጋጅም በማለት የሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴዎች መልእክት አስተላልፈዋል
እባካችሁን ቢያንስ ይህንን መልእክት ለ10ሰው እናስተላልፍ ሼር እናድርግ
👉Join @zemaryan
~ አዋጅ! አዋጅ! አዋጅ !
የመሰከረም 4ቱ ሰላማዊ ሰልፍ
ዝርዝር መርሃ ግብር ወጥቷል
*★★★*

★ ★ ይህን መልእክት በየፔጁ #SHARE አድርጉታ ?።

★ ወደ ቀደመ ኦርቶዶክሳዊ ማንነታችን በቶሎ እንመለስ።

#ETHIOPIA | ~ ኦርቶዶክስ ሀገር መሆኗን ለዓለሙ ሁሉ የምታሳውቅበት ዕለት መጥቷል። አንተ የተኛህ ሁሉ ንቃ።

• ሰልፉ ከኦሮሚያ ቤተ ክህነት ጉዳይ ጋር ምንም የሚያይዘው ጉዳይ የለም። የኦሮሚያ ቤተ ክህነት የሚባለው አጀንዳ የሚፈታው በተጀመረበት በቅድስ ሲኖዶስና በራሷ በቤተክርስቲያኒቱ ልጆች ነው። ይህን በተመለከተ የሚጻፍ መፈክርም ሆነ ባነር መኖር የለበትም። እንዲህ ዓይነት ባነር ጽፈው የሚወጡ ካሉ እነጃዋር የሚልኳቸውና የሰልፉን መንፈስ ለፖለቲካቸው ማራገቢያ የሚያውሉ ሰዎች ሴራ ነውና ወዲያውኑ እንደታዩ ለሕግ አስከባሪዎች በመጠቆም ማስረከብ ይገባል። በመስከረም 4 ቱ ዓለም አቀፍ ሰልፍ ኦሮሞ፣ ዐማራ፣ ትግሬ፣ ደቡብ፣ ነጭ፣ ጥቁር የለም። እስላም ጴንጤ፣ ካቶሊክ የለም። ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን የሚወዱ ሁሉ አደባባይ ይወጣሉ። በደሏን፣ ችግሯን፣ ብሶቷን አብረው ያሰማሉ። መሆን ያለበት ይኼ ነው። ይሠመርበት።

የአባቶቼን ርስት አልሰጥህም፡፡
*** እንደ አምለከ አበው መድኀኔ ዓለም ፈቃድ #ለመስከረም_፬/ ፳፻፲፪ ዓ.ም. #የሚካሄደውን_ሰልፍ_በተመለከተ_የወጣ_መርሐ_ግብር_

••
ሰልፉ በሃገር ውስጥና በውጭ ሃገራት መስከረም ፬ በአደባባዮች ይካሄዳል፡፡ በዕለቱም ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በሰልፉ ላይ ይገኛሉ፡፡

•••
የሰልፉ አስተባባሪዎች ሁሉም ምዕመን በኀላፊነት የሚያስተባብሩት ሲሆን፤ በግንባር ቀደምትነት ግን
• የሰ/ት/ቤቶች አንድነት፤

• የመንፈሳዊ ኰሌጅ ተማሪዎችና ምሩቃን፤

• በሰ/ት/ቤቶችማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን፤

• የወጣቶችና ጎልማሶች ማኅበራት ኅብረት፤

• የሠለስቱ ምዕት ማኅበራት ኅብረት፤

• የአእላፋት ድምፅ የካህናትና ምእመናን ተናሥኦት ኅብረት፤

• የጽዋ ማኅበራት ሙሴና ደርገ ሙሴዎች ናቸው፡፡

የሰልፉ ይህን መስሎ ይካሄዳል።

• መስከረም 4 ጠዋት 2.30-3፡30 ሰዓት ሁሉም የአዲስ አበባ ነዋሪ ነጭ ልብሱን ለብሶ ሌሊት ቅዳሴ ያስቀድሷል። ቅዳሴው እንዳበቃ ከየአብያተ ክርስቲያናቱ እስከ ተመደበላቸው መሰባሰቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ በሚከተለው ሁናቴ ጉዞ ወደ መስቀል አደባባይ ይሆናል።

★ ለምሳሌ ከሰሜን አቅጣጫ የሚመጡ የተዋሕዶ ልጆች በሙሉ መገናኛቸው ገነተ ጽጌ ላይ ይሆናል። የደቡቦቹም፣ የምሥራቆቹም፣ የምዕራቦቹም እንዲሁ የመገናኛ ስፍራ ይነገራል።

★ ሰልፉ መንግሥትን ለመለመን፣ እግሩ ስር ለመደፋት አይደለም። ሰልፉ ዝም ስላልን ለናቁን፣ ቁጥራቸውም ትንሽ ነው ብለው ለተገዳደሩን ተዉን ትንሽ አይደለንም። ከመቻቻል ወደ መከባበር እንሸጋገር ለማለትና በዚያውም በኢትዮጵያ አየር ላይ የነገሰውንና ደም አፍሳሽ ዲያብሎስን በመስቀሉ፣ በዕጣኑ ማዕጠንት፣ በዝማሬ፣ በምህላ ለማስታገስ፣ ለማሰርም ጭምር ነው።

የሰልፉ ሥዕል ይህን ይመስላል።

• ባለ መለከቶችና ባለ ጥሩንባዎች ድምፅ እያሰሙ ባንዲራን እያውለበለቡ ከፊት ይመራሉ፤

• በመከተልም የበገና ዝማሬ የሚያቀርቡ በገናቸውን እየደረደሩ፣ ተው ስማኝ ሀገሬ፣ እርግብና ዋኔ፣ ኪራላይሶ፣ ስማነ አምላክነ ወመድኃኒነ እያሉ ይከተላሉ፡፡

• ማዕጠንት የያዙ ካህናት እያጠኑ፣ በመስቀላቸውም እየባረኩ፣ አቡነ ዘበሰማያት፣ ጸሎተ ኪዳን፣ ጸሎተ ማርያም፣ መልክአ ማርያምና መልክአ ኢየሱስ፣ ዳዊቱንም ፍካሬ ዘጻድቃንን እየጸለዩ ይመራሉ፤

• የየሰንበት ትምህርት ቤት መለያ ልብስ(ዩኒፎርም)ና ጥንግ ድርብ የለበሱ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላትና ተማሪዎች በዝማሬ ጭምር አባቶችን ይከተላሉ፤ /የሰ/ትቤቶች አመራር ያስተባብራሉ/

• የጽዋ ማኅበራት በነጭ ልብስ (በማኅበራቸው መለያ ልብስ) ይከተላሉ /የየማኅበሩ ሙሴና ደርገ ሙሴ ያስተባብራሉ/

• ጥንግ ድርብ የለበሱ መዘምራን ማኅሌታውያን ይከተላሉ /አጋፊሪና መጨኔ ያስተባብራሉ/

• መስቀል የያዙ ዲያቆናትና ካህናት፤ ልብሰ ተክህኖ የለበሱ፥ ጥላና ድባብ የያዙ ካህናት ይከተላሉ፤ /ሊቀ ዲያቆንና ቄሰ ገበዝ ያስተባብራሉ/

• ምዕመናን ነጭ ልብስ፣ ነጠላ (ቲሸርት) በመልበስ ይከተላሉ፡፡ /የሰባካ ጕባኤ አባላት ያስተባብራሉ/


• በተመደበልን ቤተ ክርስቲያን ከተገኘን በኋላ ጠዋት ከ3፡30-4፡30 በሊቃነ ጳጳሳት እየተመራን ወደ መስቀል አደባበይ ጕዞ ይካሄዳል፤

• ከረፋዱ 4፡30-7፡30 በመስቀል አደባባይ ሰልፉ ይካሄዳል፡፡

• የመንፈሳዊ ኰሌጅ ተማሪዎችና ምሩቃን ጥቋቁሩን ቀሚሳቸውን እንደለበሱ /አስተባባሪዎሆነው ያስተባብራሉ/

• የማኅበረ ቅዱሳን አባላትና ተማሪዎችም /የተመደቡላቸው አስተባባሪዎች ያስተባብራሉ፡፡/

★ ስለ ጽዮን ዝም አንልም።

#ልዩ_ማስታወሻ፤ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላትና ምእመናን ተቃውሟቸውን በድጋሚ መስከረም 16 በደመራ ዕለት በትርዒቶቻቸው እንደ የሁኔታው ሊያቀርቡ ይችላሉ፡፡ ተቃውሞው ሁሉ ግን በዝማሬ፣ በምስጋና እንጂ ፉጨት፣ ግርግር፣ የለውም። ስንዱዋ እመቤት የሥርዓት ሁሉ ምንጭ ናትና ልጆቿ ምን ያህል ሥርዓት እንዳላቸው በዐይናቸው ይመለከቱታል።

• ተጨማሪ የሰልፉን ማብራሪያዎች በተመለከተ ነገ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ይሰጣልና ይጠብቁ፡፡

•••
¶ድልና ትንሣኤ ለኢትዮጵያ ሀገሬና ለተዋሕዶ ሃይማኖታችን ! ውድቀትና ጥፋት፤ ለሁለቱም ጠላቶች። አራት ነጥብ።

•••
" እኔ ግን እላለሁ! እምዬ ኦርቶዶክስ አንቺ እናትዓለም፤ የእነ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ፣ የእነ ቅዱስ አትናቴዎስ እና ቅዱስ ቄርሎስ የእነ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ የእነ ቅድስት አርሴማ፣ የእነ አቡነ ተክለሃይማኖት፣ የእነ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ፣ የአባ ሳሙኤል ዘዋልድባ፣ የቅድስት ክርስቶስ ሠምራና የአቡነ አረጋዊ ሃይማኖታቸው የሆንሽ ንጽህት፣ ቅድስት፣ ርትዕት ተዋሕዶ ሃይማኖቴ ሆይ! ብረሳሽና ብከዳሽ ቀኜ ትርሳኝ። ትክዳኝም። ባላስብሽና ባልሟገትልሽ ባልሞትልሽም ምላሴ ከጉሮሮዬ ይጣበቅ። ሳለጎበድድና ሳለከዳሽ እንድኖርም አምላክሽ ይርዳኝ። ይህን ባላደርግና ሳልጮህልሽ ዝም ብዬ ብሞት ስሜ ከህይወት መጽሐፍ ይደምሰስ።

"ጌታ ሆይ! ከዚህ በፊት በሆነው፤ አሁንም እየሆነ ባለው እና ወደፊትም በሚሆነው ነገር፤ ክብሩን ሁሉ አንተ ውሰድ።" አሜን !

"ድንግል ሆይ እናቴ ! አዛኝቱ ዛሬም እንደትናንቱ ቅደሚ ከፊት ከኋላዬ "
•••

ሻሎም ! ሰላም !

ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
ጳጉሜን 4/2011 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ።
✿~~~መስከረም 4 ~~~✿

☞ ኦርቶዶክስ ሀገር መሆኗን ለዐለም የምታሳይበት የምታሳውቅበት ቀን ነው !

☞የአባቶቼን ርስት አልሰጥህም፡፡
*** እንደ አምለከ አበው መድኀኔ ዓለም ፈቃድ #ለመስከረም_፬/ ፳፻፲፪ ዓ.ም. #የሚካሄደውን_ሰልፍ_በተመለከተ_የወጣ_መርሐ_ግብር_

••
ሰልፉ በሃገር ውስጥና በውጭ ሃገራት መስከረም ፬ በአደባባዮች ይካሄዳል፡፡ በዕለቱም ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በሰልፉ ላይ ይገኛሉ፡፡

•••
የሰልፉ አስተባባሪዎች ሁሉም ምዕመን በኀላፊነት የሚያስተባብሩት ሲሆን፤ በግንባር ቀደምትነት ግን
• የሰ/ት/ቤቶች አንድነት፤

• የመንፈሳዊ ኰሌጅ ተማሪዎችና ምሩቃን፤

• በሰ/ት/ቤቶችማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን፤

• የወጣቶችና ጎልማሶች ማኅበራት ኅብረት፤

• የሠለስቱ ምዕት ማኅበራት ኅብረት፤

• የአእላፋት ድምፅ የካህናትና ምእመናን ተናሥኦት ኅብረት፤

• የጽዋ ማኅበራት ሙሴና ደርገ ሙሴዎች ናቸው፡፡


••• ለዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ፦
• አዲስ አበባ፣
• ናዝሬት
• ደሴ
• አክሱም
• ሻሸመኔ
• ጅማ
• አዋሳ እስከ አሁን ለሰልፉ መዘጋጀታቸው ተነግሯል። ከኢትዮጵያ ውጪ መስከረም 3 ቀን በጀርመንና በአሜሪካ ዋሽንግተን ሰልፉ መዘጋጀቱ ተነግሯል።

• ሰልፉ ከኦሮሚያ ቤተ ክህነት ጉዳይ ጋር ምንም የሚያይዘው ጉዳይ የለም። የኦሮሚያ ቤተ ክህነት የሚባለው አጀንዳ የሚፈታው በተጀመረበት በቅድስ ሲኖዶስና በራሷ በቤተክርስቲያኒቱ ልጆች ነው። ይህን በተመለከተ የሚጻፍ መፈክርም ሆነ ባነር መኖር የለበትም። እንዲህ ዓይነት ባነር ጽፈው የሚወጡ ካሉ እነጃዋር የሚልኳቸውና የሰልፉን መንፈስ ለፖለቲካቸው ማራገቢያ የሚያውሉ ሰዎች ሴራ ነውና ወዲያውኑ እንደታዩ ለሕግ አስከባሪዎች በመጠቆም ማስረከብ ይገባል። በመስከረም 4 ቱ ዓለም አቀፍ ሰልፍ ኦሮሞ፣ ዐማራ፣ ትግሬ፣ ደቡብ፣ ነጭ፣ ጥቁር የለም። እስላም ጴንጤ፣ ካቶሊክ የለም። ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን የሚወዱ ሁሉ አደባባይ ይወጣሉ። በደሏን፣ ችግሯን፣ ብሶቷን አብረው ያሰማሉ። መሆን ያለበት ይኼ ነው። ይሠመርበት።

• ሰልፉ መንግሥትን ለመለመን፣ እግሩ ስር ለመደፋት አይደለም። ሰልፉ ዝም ስላልን ለናቁን፣ ቁጥራቸውም ትንሽ ነው ብለው ለተገዳደሩን ተዉን ትንሽ አይደለንም። ከመቻቻል ወደ መከባበር እንሸጋገር ለማለትና በዚያውም በኢትዮጵያ አየር ላይ የነገሰውንና ደም አፍሳሽ ዲያብሎስን በመስቀሉ፣ በዕጣኑ ማዕጠንት፣ በዝማሬ፣ በምህላ ለማስታገስ፣ ለማሰርም ጭምር ነው።

መረጃው የ ዘመድኩን በቀለ ነው !

5/13/2011

@Zemaryan @Zemaryan
@zemaryan @Zemaryan
​መስከረም 4 የሚካሄደውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመለክተው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በተለያዩ የአገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩ ማህበራት መግለጫ ሰጥተዋል!

ጷጉሜን 5፣2011(ዋልታ)
መግለጫውን የሰጡት የሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴዎች በቤተክርስቲያን እየደረሰ ያለውን የመቃጠል፣ የካህናት መገደልና ሌሎች በቤተክርስቲያንቱ ላይ የተቃጣውን ጥቃት ለማውገዝ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ሰልፉን በማስመልከት ዝርዝር መግለጫዎችን በመስከረም 2/2012 ዓ.ም እንደሚሰጥ የገለጹት ኮሚቴዎች፣ የነበራቸው ጥያቄዎች ዙሪያ ከመንግስት አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ እንደሆነና በውይይቱ አጥጋቢ መልስ ካገኙ ሰልፉ ሊቀር እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

ማህበራቱ የሰላማዊ ሰልፍ መካሄድ አለመካሄዱንም በቀጣይ መስከረም 2 በሚኖረው ድጋሚ መግለጫ እንደሚያሳውቁ ገልጸዋል፡፡

በሌላ በኩል ሰልፉ ከኦሮሚያ ክልል ቤተክህነት ምስረታ ጋር የተያያዘ እንዳልሆነ በመጠቆም ከኦሮሚያ ቤተክህነት ምስረታ ጋር በተያያዘ በጉዳዩ ዙሪያ በቅርቡ ሲኖዶሱ የሰጠው መግለጫ በቂ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ሰልፉን ለማዘጋጀት ከባለፈው አንድ ወር ጀምሮ እየተንቀሳቀሱ እንደቆዩም የጠቆሙ ሲሆን፤ የሰልፉ አላማም በሰላማዊ መንገድ በቤተክርስቲያኒቷ ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት ለማውገዝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የታቀደው ሰልፍ በሀገር አቀፍ ደረጃ እንደሚሆንና ህዝበ ክርስቲያኑ ከቤተክርስቲያንቷ ጎን እንዲቆሙም ጠይቀዋል፡፡

👉ማህበረ ቅዱሳን

@zemaryan
​የምንሰለፈው...

የምንሰለፈው "እገሌ ይውረድ" እያልን አይደለም፤ እየዘመርን እንጂ።
"እገሌ ይሾም" እያልንም አይደለም፤ እየጸለይን እንጂ።
እጃችንን ለፀብ አናነሣም፤ ለሽብሸባ እንጂ።
ድንጋይና ጠብ መንጃም አንይዝም፤ ጸናጽልና መቋሚያ እንጂ።
ንብረት አቃጥለን ጢስ አታዩም፤ የካህናቶቻችንን ማዕጠንት እንጂ።
ልብሳችንም የነእገሌ ዓርማ፣ የነእገሌ ባሕልም አይደለም፤ በጸዓዳነቱ የመላእክት እንጂ።
የሚመሩን ጉልበተኞችና አክቲቪስቶች አይደሉም፤ "ኃይሌ እግዚአብሔር ነው" የሚሉ አረጋውያን አበው እንጂ።
የማንንም ብሔር የምንወክል አይደለንም፤ የእግዚአብሔር ዘመዶች ነን እንጂ። (ሐዋ.17:29)።
ሀገራችን በሰማይ፣ ከተማችን ገነት፣ ንጉሠ ነገሥታችን ክርስቶስ፣ ቋንቋችን ፍቅር፣ ብሔራችን የመላእክት ነው።
ጥያቄያችን ተጨማሪ ጥቅምን ፍለጋ አይደለም፤ አትምጡብን አልን እንጂ።
ጩኸታችን ዩሮና ዶላር እንዲሰጠን አይደለም፤ "አትንኩን" እያለ የሚያስተጋባ ነው እንጂ
ቅንጦትን አንፈልግም፤ ከምንም አንሥተን ባቆምናት አገር ግን መገፋትንም አንፈልግም።
ያቃጠሉንን እናቃጥል፣ የገደሉንን እንግደል አላልንም፣ አንልምም፤ ቢቻለን ከሰው ኹሉ ጋር በሰላም ለመኖር ትእዛዝን እናከብራለን እንጂ። (ሮሜ 12:18)።

የምንሰለፈው እኛ ኦርቶዶክሳውያን ነን። ሰልፋችንም ሰማያዊና ሰላማዊ ነው።

አደራ እባካቹ ለሌሎች አካፍሉ። ማንም እንዳይቀር። እናት ቤተክርስቲያን በደል ሰደርስባት ዝም አንልም። ማንም እናቱን ጠላት ሲጎዳበት እያየ ምንም ማድረግ አልችልም ብሎ ዝም አይልም። ሰልፉ ላይ እንዳትቀሩ።

የመንግስት ፍቃድ አያስፈልገንም ተፈቀደ አልተፈቀደ ማንም ማንም እንዳይቀር በዝምታ የምንቀመጥበት ቀን አልፏልና።

ዲ/ን ሕሊና በለጠ

@zemaryan @zemaryan