✞ ደጓ እናቴ ማርያም ✞
1.21K subscribers
178 photos
11 videos
29 files
137 links
ከፍቅሯ ርቃቹ የምትኖሩ ማርያም ፊደል ናት ኑ ተማሩ
ለአባ ሕርያቆስ ፤
ለቅዱስ ኤፍሬም ፤
ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣
ለአባ ይስሀቅ
የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤
ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!
@embtee
@embtee

@Binyama1

@yitayal_bot

Contact @Maryamawit_bot
Download Telegram
#join & #share👉 @embtee


👇ስዐለ አድዐኖ ለመላክ

👇መዝሙሮች ለመላክ

👇በ voice መዝሙርን ለ አምላካችን ለመዘመር👇

👇የተለያዩ መፀሀፍ ቅዱሳዊ ጥቅሶች

👇ትምህርተ ወንጌል ስብከት

👇የተለያዩ ሀሳቦችን


ለመላክ👇👇👇👇👇👇



👇👇👇👇👇👇👇👇just contact us
ይላኩልን👇
@maryamn123bot
@maryamn123bot
@maryamn123bot
4 ቀን ቀረረረረ


ሕዳር ጽዮን!!
(ዉል ዉል አለኝ ደጅሽ፣ ዉል ዉል አለኝ ደጅሽ!!)
“በባቢሎን ወንዞች አጠገብ በዚያ ተቀምጠን፡ ጽዮንንም ባሰብናት ጊዜ አለቀስን”
“ዉስተ አፍላገ ባቢሎን ህየ ነበርነ ወበከይነ ሶበ ተዘከርናሃ ለጽዮን”
መዝሙር 137-1
ህዳር 21፣ ታቦተ ጽዮን የምትከብርበት ታላቅ ክብረ በኣል
ታላቅ የምስራች ይህን ታላቅ በአል ለማክበር የምትናፍቁና ሀሙስ ቀን በመዋሉ
በስራ ምክንያት ማክበር አንችልም ብላችሁ ለነበረ
የዘንድሮ 2010 ዓ.ም ህዳር ማርያም የምትዉልበት ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ
የመዉሊድ በአል በሙስሊሙ ህብረተሰብ ዘንድ የሚከበርበት ቀን በመሆኑ
እንዲሁም የስራ ቀን እንዳይሆን የጊዜ ቀመር ሰሌዳዉ(ካላንደር) ስለሚዘጋዉ
በዚህ ታላቅ የበረከት ቀን በአዲስ አለም ማርያም ከዋዜማዉ ቀን ጀምሮ ማንም
ሳይቀር በደስታ በረከት የምንሰበስብበት እለት እንዲሆን ሁላችሁም
ተጠርታችኋል ፡፡
ማንም እንዳይቀር!!
ርእሰ አድባረት ወገዳማት ዳግሚት ጽዮን አዲስ አለም ማርያም በምእራብ ሸዋ
ሀገረ ስብከት ስር የምትገኝ ስትሆን ከአዲስ አበባ በአንቦ መስመር አቅጣጫ
42 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ናት፡፡ ደርሶ መልስ ትራንስፖርት 18+ 18
በጥቅሉ 36ብር የሚፈጅ ሲሆን የትራነስፖርት አማራጮች በሰፊዉ የሚገኙ
እንደሆነና ከዋናው አውቶብስ ተራ እና ከአስኮ መናህሪያ ማግኘት የምትችሉ
መሆኑን እያሳሰብኩ ከመኪና መንገድ ወደ ጸበሉ እና ወደ ቤተክርስቲያኒቱ
ለመድረስ የ15 ደቂቃ ብቻ የእግር ጉዞ የሚያስኬድ መሆኑንም ማስታወስ
እወዳለሁ፡፡


Share #share ማድረግ እንዳይረሳ በ ማርያም

#join #join 👇
👉👉 @embtee
@embtee
@embtee

ለበለጠ መረጃ ይጠይቁን👇👇👇

Inbox 👉 @maryamn123bot
ደጓ እናቴ ማርያም:
#join & #share👉 @embtee


👇ስዐለ አድዐኖ ለመላክ

👇መዝሙሮች ለመላክ

👇በ voice መዝሙርን ለ አምላካችን ለመዘመር👇

👇የተለያዩ መፀሀፍ ቅዱሳዊ ጥቅሶች

👇ትምህርተ ወንጌል ስብከት

👇የተለያዩ ሀሳቦችን


ለመላክ👇👇👇👇👇👇



👇👇👇👇👇👇👇👇just contact us
ይላኩልን👇
@maryamn123bot
@maryamn123bot
@maryamn123bot
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን ✞
✞ ✞ እንኳን ለሊቀ መልአኩ ለቅዱስ ዑራኤል ክብረ በዓል በሰላም በጤና
አደረሳችሁ አደረሰን አሜን፡፡ ✞ ✞
በፍጹም መጠበቅን ጠብቆ ለዚህ ያደረሰን አምላካችን ክብርና ምስጋን
አምልኮትና ውዳሴ ይድረሰውና ይህን ታላቅ መልአክ በችሎታችን መጠን
እንድናመሰግን እግዚአብሔር ይርዳን፤ አምላክ ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን፤
ምስጢሩን ይግለጥልን አሜን፡፡
“ዑራኤል የተባለ መልአክ ሊረዳኝ መጣ፡፡” መ/ዕዝ. ሱቱ. 2፡1
በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤
እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። በተኵላና በእባብ ላይ
ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። በእኔ ተማምኖአልና
አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ። ይጠራኛል
እመልስለትማለሁ፥ በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋራ እሆናለሁ፤ አድነዋለሁ
አከብረውማለሁ። ረጅምን ዕድሜ አጠግበዋለሁ፥ ማዳኔንም አሳየዋለሁ። መዝ.
90/91/፡11-16
አፈቅሮ ፈድፋደ፡- ዑራኤል ሆይ፣ ከመልኮች ሁሉ ይልቅ ያንተን መልክአ ጸሎት
እወዳለሁ፡፡ የመልክህ ስነ ጸዳል በደመ ወልድ እግዚአብሔር የታተመ ነውና፡፡
ዑራኤል ሆይ፣ እግዚአብሔር ሀይሉን የሚገልጽብን መልአከ ብርሃናት አንተ ነህ፡፡
በዐዕለተ ሥቅለት በደመ ወልድ ዓለምን ለመቀደስ ከሁሉ ይልቅ አንተ
ተሰይመሃልና፡፡ ስለክብርህ የሰማይ መላእክት አደነቁ፡፡
ለተፈጥሮትከ፡-
ዑራኤል ሆይ፡- ያለ መናገር በጥንት አርምሞ ከነፋስና ከእሳት ለተፈጠረ
ተፈጥሮህ ሰላም እላለሁ፡፡ ዑራኤል ሆይ የተፈጥሮና የይቅርታና የቸርነት ክቡር
መልአክ ነህና ስለኛ ስለሰው ልጆች ወደ ልዑል እግዚአብሔር ማልድ
አማላጅነትህ ዘወትር ከጥፋት ያድናልና፡፡
ለዝክረ ስምከ፡-
ዑራኤል ሆይ፡- ከማርና ከወተት ይልቅ ለሚጥመው ስም አጠራርህ ሰላም
እላለሁ፡፡
ዑራኤል ሆይ፡- ክፍልህ /ክንፍህ/ በደመ ወልድ እግዚአብሔር የተከበረ /
የታለለ/ ነውና፡፡ ለዓለሙ ሁሉ መድሃኒት ትሆን ዘንድ ግሩም የሚሆን
የእግዚአብሔር ሥልጣን በክብር ከፍ ከፍ አደረገ፡፡ (መልክአ ዑራኤል)
“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።”
መዝ.33/34/፡7 የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ዑራኤል ረድኤቱ በረከቱ ፍጹም
አማላጅነቱ ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡

#join 👉 @embtee
@Embtee

ይላኩልን👉 @maryamn123bot
#join @embtee @embtee

❤️❤️በምን በምን እንመስላት ድንግል ማርያምን "፪"
ምሳሌ የላትም የላትም ክብራን የሚመስል "፪"
የሙሴ ጽላት ነሽ የምሕረት ቃል ኪዳን
የያዕቆብ መሰላል የአብርሃም ድንኳን
የብርሃን መውጫ የኖኅ ድንቅ መርከብ
የመላእከት እኅት የርህሩሃን እርግብ "፪"
………..አዝ……
የሰሎሞን አክሊል የአሮን በትር
የዕዝራ መሰንቆ የጌዴዎን ፀምር
ድንግል እናቴ ናት የጽድቃኖች በር
ሆና የተገኘች የአምላክ ማኅደር፡"፪"
………..አዝ……
የቅዱሳን እናት የአርያም ንግሥት
ስለ ተሸከመች መለኮት እሳት
በሥጋችን ፈቃድ ወድቀን እንዳንጠፋ
አማልዳ ታስምረን ከዚህ ዓለም ጣጣ "፪"
………..አዝ……
ከማር ይጣፍጣል የድንግል መዓዛ
አምላክን አቅፋለች በሁለት እጇ ይዛ
ዓለሙን የዳነ በልጅሽ ነውና
እናታችን ጽዮን ይድረስሽ ምሥጋና "፪"


ሼር እንዳይረሳ👉 #join @embtee @embtee
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን ✞
እንኳን ለሊቀ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወርሃዊ መታሰቢያ ክብረ በዓል በሰላም
በጤና አደረሳችሁ አደረሰን አሜን፡፡ ሰማዕቱ ባለንበት ጽናትና ብርታቱን ያድለን።
👉 @embtee
† ቅዱስ ጊዮርጊስ †
† “እኔ የክርስቶስ ወታደር ጊዮርጊስ መጣሁባችሁ” ሲላቸው ደንግጠው
ይሸሹ ነበር። †
† † ጊዮርጊስ ማለት ኮከብ፣ ብሩህ፣ ሐረገወይን፣ ፀሐይ ማለት
ነው። ቶማስስ ዘልዳ እንዲለው ሀገሩ ልዳ ነው። አባቱ ዞሮንቶስ (እንስጣስዮስ)
በልዳ መስፍንነት ተሹሞ ይኖር ነበር። እናቱ ትዎብስታ (አቅሌስያ) ትባላለች።
ማርታ ድስያ የሚባሉ እህቶች ነበሩት።
† † አስር አመት ሲሆነው አባቱ ሞቶ ሞቶ ሌላ መስፍን ተሾመ። ደግ
ክርስታናዊ ነበርና ወስዶ እያስተማረ አሳደገው። እርሱም ፈረስ መጋለብ ቀስት
መወርወር ለመደ። ጦር ሜዳ ወጥቶ ከጠላቶቹ መሀል ገብቶ “እኔ የክርስቶስ
ወታደር ጊዮርጊስ መጣሁባችሁ” ሲላቸው ደንግጠው ይሸሹ ነበር።
† † ጽኑ የእምነት አርበኛ በመኳንንቱ በሹማምንቱ በነገስታቱ ፊት
የማይፈራ ድንቅ ወጣትም ነበር። ሃያ ሲሞላው መስፍኑ የ 15 ዓመት ቆንጆ ልጅ
👉 @embtee
ነበረችውና እሷን ድሮለት ሀብቴን ወርሶ ይኑር ብሎ ድግስ ሲያስደግስ ዳስ
ሲያስጥለ ጌታ ቅዱስ ጊዮርጊስን ለዚህ አላጨውምና የመስፍኑን ነፍስ ወሰደ።
እርሱም ሀዘኑን ጨርሶ ወደ ቤሩት ሄደ። ቤሩት በኢያርኮ አቅራቢያ ያለች ሀገር
ናት። በዚያ በቤሩት ሰዎች እግዚአብሔርን የማያውቁ ለዴጎን የተንበረከኩ ናቸው።
† † ቤሩታዊቷንም የሹም ልጅ ለዚሁ ዘንዶ ግብር ሊገብሩለት
ከግንድ ወስዶ አሰሩለት። ቅዱስ ጊዮርጊስም በዚያ ሲያልፍ የልጅቱን የጩኸት
ድምጽ ሰማ። እሱም ምን ሆነሽ ነው? አላት። ለደራጎን ተሰጥቼ ነው አለችው።
አምላካችሁ ወዴት አለ አላት ምግቡን ሊፈልግ ሄዷል አለችው። ይህን እያነጋገራት
እያለ ደራጎኑ ምድሪቱን እያነዋወጠ መጣ። ሂድ ይበለሃል ስትለው፤ እኔማ ምን
አለኝ ከኔ ጋር ያለው ግን ከሱ ይበልጣል አላት። ሊበላው ሲቀርብ ስመ
እግዚአብሔር ጠርቶ ቢያማትብበት በላዩ ያደረው ሰይጣን እንደ ጉም ተኖ
እንደትቢያ በኖ ጠፋ፤ ሃይሉም ደከመ። ቤሩታዊቷ አንገቷን በታሰረችበት ገመድ
አስሮት እሷ እየጎተተች እሱ በፈረስ ሆኖ ከተማ ደረሰ። ሕዝቡን ሊያስፈጅ ነው
ብለው ይሸሹ ጀመር። አጽናንቶ መለሳቸው። ንጉሱ ዱድያኖስ ግን ተነሳስቶበት
ክርስቶስን ካድ ባለው ጊዜ አምላኬ ክርስቶስን አልክድም በማለቱ ተቆጥቶት
ጥጋውን በመቃጥን አስተፍትፎታል፤ ረጅም ችንካሮች ያለበት የብረት ጫማ
አጫምቶታል፤በችንካር አስቸንክሮታል፤ በፈላ ውሃ ውስጥ አስጨምሮታል።
† † አጥንቱን አስከስክሶታል። መሄድ እስኪያቅተው ድረስ፤ መርዝም
በጥብጦ አጠጥቶታል። በመንኩራኩር አስፈጭቶት ከጥልቅ ጉድጓድ ጥሎታል።
ብዙውን ጊዜ በመንኩራኩር ተፈጭቷል፤ በኋላም በደብረ ይድራስ ላይ አጥንቱን
በትኗል። መከራ ፈተና አብዝቶበታል። ፯ ጊዜ ሞቶ ፯ ጊዜ ተነስቷል።
† † አቤት የቅዱሳን መከራቸ፤ ለዚህ እኮ ነው ቅዱስ ጳውሎስ
“እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ፥ ጽድቅን አደረጉ፥ የተሰጠውን የተስፋ
👉 @embtee
ቃል አገኙ፥ የአንበሶችን አፍ ዘጉ፥ የእሳትን ኃይል አጠፉ፥ ከሰይፍ ስለት አመለጡ፥
ከድካማቸው በረቱ፥ በጦርነት ኃይለኞች ሆኑ፥ የባዕድ ጭፍሮችን አባረሩ። ሴቶች
ሙታናቸውን በትንሣኤ ተቀበሉ፤ ሌሎችም መዳንን ሳይቀበሉ የሚበልጠውን
ትንሣኤ እንዲያገኙ እስከ ሞት ድረስ ተደበደቡ፤ ሌሎችም መዘበቻ በመሆንና
በመገረፍ ከዚህም በላይ በእስራትና በወኅኒ ተፈተኑ፤ በድንጋይ ተወግረው ሞቱ፥
👉 @embtee
ተፈተኑ፥ በመጋዝ ተሰነጠቁ፥ በሰይፍ ተገድለው ሞቱ፥ ሁሉን እያጡ መከራን
እየተቀበሉ እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ፤ ዓለም
አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ፥ በዋሻና በምድር ጕድጓድ ተቅበዘበዙ።
እነዚህም ሁሉ በእምነታቸው ተመስክሮላቸው ሳሉ የተሰጠውን የተስፋ ቃል
👉 @embtee
አላገኙም፥ ያለ እኛ ፍጹማን እንዳይሆኑ እግዚአብሔር ስለ እኛ አንዳች የሚበልጥ
ነገርን አስቀድሞ አይቶ ነበርና። † † (ዕብ.፲፩፡፴፫-፵) 11፡33-40
† † ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታል፤ ስለ እኔ ግን ነፍሱን
የሚያጠፋ ሁሉ ያገኛታል። ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን
ይጠቅመዋል? ወይስ ሰው ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል? የሰው ልጅ ከመላእክቱ
👉 @embtee
ጋር በአባቱ ክብር ይመጣ ዘንድ አለውና፤ ያን ጊዜም ለሁሉ እንደ ሥራው
ያስረክበዋል። † † (ማቴ.16፡25-27
† † እኔን የሚወድ ቢኖር እራሱን ይካድ መስቀሌንም ተሸክሞ /መከራዬን
ሳይሰለች/ ዕለት ዕለት ይከተለኝ፡፡ † † ማቴ 10፡38-42 እንዲል
ወንጌል
👉 @embtee
† † ስለ ጽድቅ የሚራቡና የሚጠሙ፣ እንዲሁም የሚሰደዱ ብጹዓን
ይጠግባሉና፣ መጽናናትንም ያገኛሉና… ጌታ በተራራ ስብከቱ ከተናገራቸው፣
ካስተማራቸው የሕይወት ምግብ የሆነ ቃሉ ማቴ.5፡1-ፍጻሜ
† † ጊዮርጊስ ሆይ ጨካኝ ቁጡ በሆነው በዱድያኖስ አደባባይ ልዩ ልዩ
ተዓምራትህን እንደማድረግህ በጠዋት በማታ በከንቱ ነገር የሚነሳሱብኝ ጠላቶቼ
ሁሉ እንደ አመድ በነው እንደ ጢስ ተነው ይጥፉ፡፡
👉 @embtee
ጊዮርጊ ሆይ ሰማዕታት ሁሉ አለቃ እንደመሆንህ ቀድሞ ሰብዓ
ነገስታትን እንደደመሰስካቸው ነበልባላዊ በምትሆን ጸሎትህ ጠላቶቼን
ደምስሳቸው፡፡
ተዓምረኛው ሰማዕት ሆይ ቀድሞ የቢፋሞንን ልጅ ከሰዕበተ ሃጢአት ሰውነቱን
👉 @embtee
እንድቀደስከው መንግስተ ሰማያትን ለመውረስ እበቃ ዘንድ ሰውነቴን በፍጹም
መቀደስ ከሃጢአት ርኩሰት ንጹህ አድርግልኝ፡፡
ተዓምረኛው ሰማዕት ሆይ ሙታንን የማስነሳት ሥልጣን ተሰጥቶሃልና አቤቱ
ቤሩታዊትን ከአፈ ዘንዶ እንዳዳንካት እኔን ከእለተ እኪት ከዘመነ መንሱት
በጸሎትህ አድነኝ፡፡
አቤቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ አምላክ ሆይ ማረን፤አቤቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ
@embtee
አምላክ ሆይ ራራልን፤ አቤቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ አምላክ ሆይ ይቅር በለን፡
እግዚአብሔር አምላካችን ሰማዕታትን በደም ቅዱሳንን በገዳም ሐዋርያትን
በአጽናፍ ዓለም መላዕክትን በአጽራርያም እንዳጸናቸው እኛ ሁላችንንም
በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነታችን በቅድስት ቤተክርስቲያን በበጎ ምግባር በጾም
በጸሎትና በትሩፋት ያጽናን አሜን አሜን አሜን!!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን ። ይቆየን

አንብቦ ዝም አይባልም ሼር
#join 👇
@embtee
@embtee
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን ✞
✞ ✞ እንኳን ጻድቁ አባታችን ለአቡነ ተክለሐይማኖት
ታላቅ ክብረ በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደረሰን ! ✞ ✞
ህዳር 24 በዚህች ቀን ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ
ሃይማኖት ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ እንደ አንዱ ሁነው መንበረ ጸባዎትን ያጠኑበት
ታላቅ ዓመታዊ መታሰቢያ ክብረ በዓል በሰላም በጤና በፍቅር እንኳን አደረሳችሁ
አደረሰን
የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሐይማኖት ረድኤት በረከታቸው ምልጃና ጸሎታቸው
ከመላው ህዝበ ክርስቲያን ጋር ይሁን አሜን! እለቱ ካህናተ ሰማይ ተብሎ በቤተ
ክርስቲያናችን ይከብራል እኛንም ከጻድቁ ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡
👇👇👇👇👇👇
#join @embtee👈
@embtee👈
#share
👉የእመቤታችን የድንግል ማርያም የአስራት ልጆች👈:
👉#join @embtee

ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት የመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃ እነሆ!!
1: ስለ ሥላሴ የእግዚአብሔር አንድነትና ሦስትነት:-
ዘፍ 1:26 ዘፍ 3:22
ዘፍ 11:18 ዘፍ 18:1-2
ኢሳ 48:26 ማቴ 3:16-17
ማቴ 28:19 ሉቃ 1:35
ዮሐ 7:28-29 ዮሐ 14:25-26
ሐዋ 3:14 1ኛ ቆሮ 12:4-7
2ኛ ቆሮ 13:14 ኤፌ 4:4-7
2: ስለ እመቤታችን ቅድስናዋ ፣ ክብሯ ፣ ድንግልናዋና አማላጅነቷ:-
መዝ 9:11 መዝ 13:10
መዝ 44:9 መዝ 86:5
መዝ 131:13 መዝ 44:2
መኃ 4:12 ኢሳ 7:14
ኢሳ 49:23 ኢሳ 60:14
ማቴ 1:23 ሉቃ 1:28
ሉቃ 1:42 ዮሐ 2:1-11
ዮሐ 19:16 ሮሜ 11:26-27
2ኛ ቆሮ 11:2 ራዕ 12:16
3: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፈራጅ እንጂ አማላጅ አይደለም፡-
ዘፍ 3:22 1ኛ ሳሙ 16:1
ኢሳ 9:6 ዳን 7:14
ሆሴ 13:4 ዘካ 9:9-10
ሚክ 5:2 ሉቃ 1:32-33
ዮሐ 10:30 ሉቃ 2:12
ዮሐ 14:7 ሮሜ 9:5
ቆላ 2:9-10 ቲቶ 2:11-13
ዕብ 1:3-4 ዕብ 1:10-11
1ኛ ጴጥ 3:23 1ኛ ዮሐ 2:23
ራእ 3:22 ራእ 22:12-13
4: ስለ ታቦትና ጽላት
ዘፀ 24:12 ዘፀ 25:10
ዘፀ 25:21 ዘፀ 26:34
ዘፀ 31:18 ዘፀ 32:15
ዘፀ 34:1 ዘፀ 34:28
ዘፀ 37:1 ዘፀ 40:20
መኃ 7:89 ኢያ 3:3
ኢያ 7:6 2ኛ ቆሮ 6:16
5: ስለ ጾም የመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃ:-
ዘፀ 34:28 ዘፀ 9:9
ሳሙ 20:26 1ሳሙ 7:6
1ሳሙ 31:13 2ኛ ሳሙ 1:12
2ኛ ሳሙ12:16 ዕዝ 8:21
ዕዝ 68:10 ዕዝ 108:24
ኢሳ 48:3 ኤር 36:9
ዳን 9:3 ዳን 20:2-3
ኢዩኤ 2:14 ኢዩኤ 2:12
ዮና 3:5 ማቴ 4:2
ማቴ 6:16:18 ማቴ 9:14-15
ማቴ 17:21 ማር 2:18
ማር 9:29 ሉቃ 2:37
ሉቃ 18:12 የሐ.ስራ 13:3 ሐዋ 14:23 2ኛ ቆሮ 11:17
6: ስለ መስቀል በመጽሐፍ ቅዱስ:-
ማቴ 10:38 ማቴ 16:20
ማር 8:34 ሐዋ 5:30
1ኛ ቆሮ 1:18 ገላ 3:13
ገላ 6:13 ፊል 2:8
ፊል 3:18
7: ጥምቀትን በተመለከተ:-
ሕዝ 36:25 ማቴ 3:5-6
ማቴ 26:19-20 ማር 1:4-5
ማር 16:16 ሉቃ 3:21
ዮሐ 3:5 ዮሐ 3:22
ኤፌ 4:5 ገላ 3:26-27
ሐዋ 19:4 ሐዋ 18:8
ሐዋ 13:24 ሐዋ 10:47 የሐዋ 9:18 1ኛ ቆሮ 1:16
1ኛ ቆሮ 10 :2 1ኛ ቆሮ 12:13
8:ስእለትን በተመለከተ:-
ዘኁ 28:20 ዘኁ 21:2
ዘፀ 23:21 መሳ 11:30
መዝ 49:14 መዝ 75:11
1ኛ ሳሙ 1:11 መክ 5:4-5
ዮና 2:10 ናሆ 1:15
ሐዋ 18:18
9: ጻድቃን ሰማዕታት ያማልዳሉ:-
ዘፍ 18:17-18 ዘፍ 18:23:24
ዘፍ 20:7 ዘፍ 33:3
ዘፍ 42:6 1ኛ ሳሙ 28 :14
2ኛ ሳሙ 1:2 2ኛ ነገ 1:13
2ኛ ነገ 2:15 2ኛ ነገ 4:9
2ኛ ነገ 4:32-35 መዝ 88:34
ማቴ 18:18 ዮሐ 20:23
ሐዋ 10:25 ሐዋ 16 :29
1ቆሮ 6:1-2 ፊሊ 4:6
1ኛጢሞ 5:17 ያዕ 5:14
ራእ 14:13
10: መላእክት ዘወትር በእግዚአብሔር ፊት ይቆማሉ:-
መዝ 148:2 ኢሳ 6:3
ማቴ 4:12 ማቴ 18:10
ማቴ 25:31 ማር 8:38
ራእ 1:11 ሉቃ 1:19
11: መላእክት ጸሎታችንን ወደ እግዚአብሔር ያደርሳሉ:-
ጦቢ 12:15 ሉቃ 15:10
የሐዋ 10:4 ኢዮ 25:3
ኤር 33:22 ዳን 7:10
ሄኖ 10:1 ራእ 5:11
12:ለመላእክት የአክብሮት ስግደት ይገባል:-
ዘፍ 19:1 ዘኁ 22:31
ኢያ 5:14 ዳን 8:16-17
13:መላእክት አብሣሪያን ናቸው:-
ዘፍ 16:11 ሉቃ 1:13
ሉቃ 1:19 ሉቃ 1:30-31
ሉቃ 2:10-11
14:መላእክት በአደጋ ጊዜ ፈጥነው ይደረሳሉ:-
ዘፍ 22:11-12 መዝ 90:11-12
ዳን 6:22 ዳን 10:13
ማቴ 2:13 ሐዋ 5:19-20
ሐዋ 12:7
15: ፀበል መርጨት ያስፈልጋል:-
ዘኁ 19:20
#join👉 @embtee @embtee
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን ✞
✞ ✞ እንኳን ለመድኃኒዓለም ወርኃዊ መታሰቢያ ክብረ በዓል በሰላም በጤና
አደርሳችሁ አደረሰን ! መድሐኒዓለም ክርሰቶስ በምህረቱ በቸርነቱ ይጎብኘን
አሜን !!! ✞ ✞
ጌታችን አምላካችንና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ህይወታችን ነው ፣
ሰላማችንና እረፍታችን እርሱ ነው ፤ የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ የጥበባት ሁሉ
ምንጭ እርሱ ነው ፤ መጀመሪያ የሌለው አልፋ መጨረሻም የሌለው ኦሜጋ እርሱ
ነው ፤ እርሱ ሁሉን የሚወድ ነው ፤ እርሱ የአለም መድሃኒት ነው!!!!
እኔ እንደ ወደድኋችሁ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ ትእዛዜ ይህች ናት ነፍሱን
ስለ ወዳጆቹ ከማኖር ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር የለውም እኔ ያዘዝኋችሁን
ሁሉ ብታደርጉ እናንተ ወዳጆቼ ናችሁ ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም
ባረያ ጌታው የሚያደርገውን አያውቀውምና ወዳጆች ግን ብያችኋለሁ ከአባቴ
የሰማሁትን ሁሉ ለ እናንተ አሳውቄአችኋለሁና እኔ መረጥኋችሁ እንጂ እናንተ
አልመረጣችሁኝም አብም በስሜ የምትለምኑትን እንዲሰጣችሁ ልትሄዱና ፍሬ
ልታፈሩ ፍሬአችሁም ሊኖር ሾምኋችሁ እርስ በርሳችሁ እንድትዋደዱ ይህንን
አዘዝኋችሁ ዮኀ . 15: 12 - 17 ✞ ✞

#join #share
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAEzwE8Rx0_ELfmMHsg
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
#ማርያም_ደስ_ይበልሽ


ማርያም/3/ ደስ ይበልሽ በገብርኤል ሰላምታ 
በአንቺ ስለአደረ የዓለም ሁሉ ጌታ /2/ 
የአምላክ ቸርነቱ ፈቃዱ ሲሆን 
ጨለማ ተገፎ ሲወጣ ብርሃን 
አዝ --- 
መድኃኒት ሲመጣ ሰይጣን እንዳፈረ 
የዜናው አብሣሪ ገብርኤል ነበረ 
አዝ --- 
ድንግል ተቀምጣ በቤተመቅደስ 
አስማምታ ስትፈትል ሐርና ወርቁን
አዝ --- 
ገብርኤል /2/ ዜናዊ ሐዲስ 
የአምላክ መወለድ ሥጋ በመልበስ 
አዝ - - - 
ገብርኤል ሲያበስራት ድንግል ስትሰማ 
በእርሷ ላይ አደረ የመለኮቶ ግርማ 
አዝ --- 
እውነተኛ መልአክ መሆኑን ስላየች 
ይሁንልኝ ብላ ቃሉን ተቀበለች
 
የ እመብርሀን ልጆች 👇👇

👇👇👇👇👇👇
👉 @embtee 👈
👉 @embtee 👈
👉 @embtee 👈
👆👆👆👆👆👆
❤️❤️
❤️❤️
💚💚❤️❤️💛💛
💚💚❤️❤️💛💛
❤️❤️
❤️❤️
❤️❤️
#join #join #join 👆👇👆👇👆
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAEzwE8Rx0_ELfmMHsg
ውድ እህት ወንድሞቼ በክርስቶስ ስም ሼር በማድረግ ላላወቁ እናሳውቅ
"እግዚአብሔር"
እግዚ=>ጌታ
አብ=>አባት
ሔር=>ቸር አፅናኝ፡ መንፈስ
እግዚአ=>ጌታ ገዥ
ብሔር=>አለም
እያንዳንዳቸው ፊደላት የራሱ የሆነ ትርጉም አላቸው፤እኛም ስንፅፍቸው የስሙ ስያሜ ሙሉ ትርጉም እንዲኖረው በጥንቃቄ ቢሆን በረከቱ ለኛ ነው።
👉🏻ስህተት የሆኑ አፃፃፉች፦
=>እ/ር
=>እግ/ር
=>እግዜር
=>እግዛቤር
=>እግዚሀብሔር
=>እግዛሃብሔር
ወንድሞች እህቶች ይህ ስህተት እንደሆነ አውቀን በረከቱን ለማግኘት፦
📝👉🏻እግዚአብሔርተብሎ መፃፍ ይኖርበታል፤
E/r
Eg/r
Egzi
EGZI
Egzaber
Egzhabher
👀👇🏻👇🏻👇🏻👇🏻
EGZIABHER
Egziabher
ብለን የፈጣሪን ስም አስተካክለን መፃፍ ክርስቲያናዊ ግዴታችን ነው ።

"በእኔ ተማምኗልና አስጥለዋለሁ፥ስሜንም አውቋልና እጋርደዋለሁ፤ [መዝ.61:14]
ስለ ቃሉ የቃሉ ባለቤት ልኡል ሀያል ቅዱስ እግዚአብሔር ይመስገን!

አሜን ማለት፦ይሁንልን ይደረግልን……ማለት ነው።
👉🏻ስህተት የሆኑ አፃፃፉች፦
=>አመነ
=>አሚን
=>አመን
=>አሜን አሜን ሁለቴ(2) አሜን ማለት "የስላሴዎችን አንድነትና ሶስትነት"አይወክልም፤(ትርጉም አልባ ነው)
በረከቱን ለማግኘት፦
📝👉🏻አሜን
📝👉🏻አሜን አሜን አሜን
📝👉🏻አሜን ፫
📝👉🏻አሜን(3)
📝👉🏻ተብሎ መፃፍ አለበት ።

Be English Words Lemetsaf ከፈለግን ፦

AMIN
Amin
Amin Amin Amin
Amennnn
Aman
👆🏻እንዲህ አይነት አፃፃፍ ስህተት ሲሆን ፦ 👇🏻👀
AMEN
AMEN AMEN AMEN
Amen
Amen Amen Amen
Amen (3)

Be Englizegnaw Fidel Sntsef Endezih👆🏻 Aderegn Bntsef Bereketu ለእኛ ነው ።

የእስራኤል አምላክ ልኡል እግዚአብሔር ለሁላችንም ማስተዋሉን ያድለን! አሜን

ወስብሐት ለ እግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለ መስቀሉ ክቡር ይቆየን።
#Share ለሁሉም ይድረስ💠

#JOIN👇
🔰🔰🔰🔰🔰
♥️ @embtee ♥️
♥️ @embtee ♥️
♥️ @embtee ♥️
♥️ @embtee ♥️
♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ዱ አምላክ አሜን።
፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩
# እኛ_ኢትዮጵያውያንና_እመቤታችን_ማርያም
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በእኛ በኢትዮጵያውያን በተለይ
በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ እምነት ተከታዮች ዘንድ ከእጅግ በጣም በላይ
የምትወደድና የምትፈቀር ናት። በሙስሊም ወንድሞቻችንም ትከበራለች።
እስኪ በእመቤታችን ማርያም የሚነገሩትን ነገሮች ከብዙ በጥቂቱ እንይ፦
፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩
፩ኛ የማርያም መቀነት፦ በውኃ ሙላት፥ በመብረቅ መውደቅና ዝናብን ተከትሎ
በሚከሰት አደጋ እንዳንጠፋ፤ ለኖኅ ቃል ገብቶለታል፥ ለዚህም እንደ ምልክት
ቀስተ ደመና በሰማይ ይታያል፥ ይህም # የማርያም_መቀነት ይባላል።
፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩
፪ኛ በማርያም እጅ ተይዛለች፦ ሆዷ የገፋ ነፍሰ ጡር ሴት ወረ ግቡ(ዘጠኝ ወር
የሆናት) # በማርያም_እጅ_ተይዛለች ይባላል።
፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩
፫ኛ ማርያም᎐᎐᎐ማርያም᎐᎐᎐፦ ነፍሰ ጡሮች ምጥ ሲይዛቸው ምጣቸው እንዲቀል
አዋላጆች # ማርያም_ማርያም ይሉላቸዋል።
፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩
፬ኛ እንኳን ማርያም ማረችሽ፦ የወለደችን ሴት ሰዎች ሊመርቁ ሲገቡ በቅድሚያ
# እንኳን_ማርያም_ማረችሽ ይላሉ።
፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩
፭ኛ ማርያም በሽልም ታውጣሽ፦ ሰዎች የወለደችውን መርቀው ሲወጡ የደስታ
መግለጫ # ማርያም_በሽልም_ታውጣሽ ይሏታል።
፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩
፮ኛ ማርያም ስታጫውተው፦ ሕጻናት አንቀላፍተው ሲስቁ # ማርያም_
እያጫወተችው_ነው ይባላል።
፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩
፯ኛ ማርያም የሳመችው፦ በሰውነታቸው ላይ ጥቁር ነጥብ ሲታይ # ማርያም_
የሳመችው ይባላል።
፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩
፰ኛ የማርያም ስፌት፦ በሕጻናትና ወጣቶች ከእብርት ወደ ታች/ ወደ ላይ
የሚታይ ስፌት የመሰለ መሥመር # የማርያም_ስፌት ይባላል።
፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩
፱ኛ የማርያም ጣት፦ የተጣሉ ሕጻናት ለመታረቅ ትንሹዋ ጣታቸውን አቆላልፈው
የሚታረቁበት የጣታችን አነስተኛዋ(በብዙ ሰው ትንሽ የሆነ ነገር ስለሚያሳሳው፥
ስለሚወደድም) # የማርያም_ጣት ይባላል።
፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩
፲ኛ በእንተ ስሟ ለማርያም፦ ቁራሽ ለምነው የሚማሩ የቆሎ ተማሪዎች
በማርያም ስም ተለምኖ ማንም አይጨክንም በሚል # በእንተ_ስሟ_ለማርያም
በማለት ሰዎችን ቁራሽ ይጠይቃሉ።
፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩
፲፩ኛ የማርያም ጠላት፦ የማርያም ጠላት የሚባል አባጨጓሬ አለ፥ ሕጻናትና
ወጣቶች አስቸጋሪ ሰው ከመሀላቸው ካለ # የማርያም_ጠላት እያሉ ይመቱታል።
፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩
፲፪ኛ ፀረ ማርያም፦ የእመቤታችንን ድንግልና፥ ቅድስናና አማላጅነት ለሚክዱ
የተሰጠ ስም # ፀረ_ማርያም ነው።
፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩
፲፫ኛ የማርያም መንገድ ስጠኝ፦ ሰዎች ጥቂት ማለፊያ ነገር ሲፈልጉ
# የማርያም_መንገድ_ስጠኝ ይላሉ᎐᎐᎐᎐
፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩ ፳፩
#join 👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAEzwE8Rx0_ELfmMHsg
✞ በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን ✞
† †እንኳን ለአብሳሪ መልአክ፣ ለነገደ አርባብ አለቃ፣ ለራማው ልዑል ቅዱስ
ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደረሰን †

ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱና በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ
ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ በተረዳኢነቱና በአማላጅነቱ በክርስቲያኖች ዘንድ
ይወደዳል፡፡ ምክንያቱም ያዘኑትን ለማጽናናት የምሥራች ለመንገር
ከእግዚአብሔር ወደ ምእመናን ይላካልና፡፡
ገብርኤል ማለት የእግዚአብሔርን ልጅ የሚመስል ጌታና አገልጋይ ማለት ነው፡፡
ብርሃናዊ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል፣ ቅዱሳን ሰማእታት ገድላቸውን እንዲፈጽሙ
እሳቱንና ስለቱን ተሳቀው ወደ ኋላ እንዳይመለሱ ይረዳቸዋል፡፡
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን የቅዱሳን መላእክትን ወርኃዊና ዓመታዊ
በዓላቸውን በፀሎትና በምሥጋና ታከበራለች፤ በተለይ ታህሣሥ 19 ቀን
የሚከበርበት ምክንያት ብርሃናዊ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሠለሥቱ ደቁቅን
ከዕቶነ እሳት ( ከነደደ እሳት ) ያዳነበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡
በጣዖት ፍቅር እጅግ ከመጠን በላይ ልቡ ተቃጥሎ የነበረው የባቢሎን መሪ
ናቡከደነጾር ቁመቱ ስድሳ ወርዱ ስድስት ክንድ የሆነውን የወርቅ ምስል አሰርቶ
መኳንንቱን ሰብስቦ ሕዝቡ በሙሉ ለጣኦት እንዲሰግድ አዋጅ አወጀ፡፡ ያ ዘመን
ለእግዚአብሔር ወዳጆች የፈተና ዘመን ነበር፡፡ አስመሳዮች ለጣኦት ሰገዱ
ተረበረቡ፡፡ እውነተኛው አማኞች ግን በእግዚአብሔር ላይ ያላቸው እምነት ንጉሥ
የወደደው ጊዜ የወለደው በሚል አስተሳሰብ አይለወጥም፡፡
በዚያ ፈታኝ ዘመን ነበር ሶስት ታማኝ የእግዚአብሔር ባለሟሎች የተገኙት፡፡ ንጉሡ
ላቆመው ጣኦት ያልሰገደ ወደ እቶን እሳት ተጥሎ እንደሚሞት ቁርጥ ውሣኔው
መሆኑን ወጣቶቹ በሚገባ ያውቁታል ግን ይህንን አልፈሩም፡፡ ንጉሥ ሆይ
አምላካችንን በመካድ አንተ ላቆምከው ጣኦት አንሰግድም አሉት፡፡ ሶስቱ
ወጣቶች የወሰዱት ይህ አቋም ለንጉሡ ታላቅ ራስ ምታትን ፈጠረ፤ ንጉሡም
አገልጋዮቹን ጠርቶ እሳቱ ሰባት እጥፍ እንዲነድ ትዕዛዝ ሰጠ እሳቱም ሰባት
እጥፍ ነደደ፡፡
ወዲያውኑ የንጉሡ አገልጋዮች አናንያን፣ አዛርያ፣ ሚሳኤልን እያንከበከቡ ወደ
እቶን እሳት ወረወሯቸው ፡፡ ሠለስቱ ደቂቅ ከየት እንደመጣ ከማይታወቅ እንግዳ
ጋር በመሆን በዕቶን እሳት ውስጥ ይንሸራሸሩ ጀመር፡፡ ይህ ተዓምራት ንጉሡንና
መኳንንቱን አስገረመ ንጉሡም በዚህ ወቅት እነሆ እኔ በእሳቱ መካከል
የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ እሳቱ ምንም አላቆሰላቸውም አራተኛውም
የአማልክትን ልጅ ይመስላል አለ፡፡
የነደደ እሳት ውስጥ ገብቶ ከመውጣት ባልተናነሰ መከራ ውስጥ ገብተው
በቅዱስ ገብርኤል አማላጅነት ከሞተ ሥጋ ነፍስ ድነው እውነተኛ
ምሥክርነታቸውን የሚሰጡ ብዙዎች ናቸው፡፡ በመልአኩ ስም በፈለቀው ጠበል
ተጠምቀው ደዌ የራቀላቸው እጅግ በርካታ ናቸው፡፡ በየዓመቱ በቁልቢና በቅዱስ
ገብርኤል ስም በታነጹ አብያተ ክርስቲያናት የሚሰበሰበው ምዕመናን ሥዕለቱ
የሰመረለት ልመናው የተሰማለት እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ስለዚህ ለመላእክት አለቃ
ለቅዱስ ገብርኤል የተሰጠውን ጸጋ ተረድተን የመልአኩን አማላጅነት በመጠቀም
ልናከብረው ይገባል፡፡
የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ረድኤት እና በረከት አይለየን - አሜን
#Join 👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAEzwE8Rx0_ELfmMHsg
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን ✞
ታህሳስ 24
† †እንኳን ለጻድቁ አባታችን ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት የልደት የመታሰቢያ
ክብረ በዓል ዋዜማ በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደረሰን ከጻድቁ አባታችን ከአቡነ
ተክለ ሃይማኖት ረድኤት በረከት ያሳድርብን አምላከ ተክለ ሃይማኖት በቸርነቱ
አይለየን አሜን !!! † †
ታህሳስ 24 በዚህች ቀን ታላቁ ጻድቅ አቡነ ተክለሃይማኖት የተወለዱበት ቀን
ነው። የትውልድ ቦታቸው ሸዋ ጽላልሽ አወራጃ ዞረሬ ነው፤ የአባታቸው ስም ጸጋ
ዘአብ የእናታቸው ስም እግዚ ሐርያ ይባላል መካን ነበሩ ልጅ እንዲሰጣቸው ወደ
እግዚያብሔር ዘወትር ይጸልዩ ነበር፤ መጋቢት 12 ቀን እንዲህ ሆነ፤ ሞተሎሜ
የተባለ ጣኦት አምላኪ ንጉስ አገራቸውን ወረረ መንደሩንም አጠፋ ጸጋ ዘአብ
ወንዝ ውስጥ ገብቶ አመለጠ እግዚ ሐርያ ግን ተማርካ ሄደች፤ በጣም መልከ
መልካም ስለነበረች ሞቶሎሜ ሊያገባት አሰበ ታላቅ ድግስም ደገሰ አገር
ምድሩ ተሰብስቦ ሲዘፍን ሲጨፍር ሳለ ቅዱስ ሚካኤል ታላቅ መብረቅ ነጎድጓድ
አሰማ ብዙዎች ሞቱ እግዚሐርያን በክንፎ ተሸክሞ ዞረሬ ከቤተክርስቲያን ውስጥ
አስቀመጣት ከባለቤቷ ጸጋ ዘአብ ጋር ተገናኙ ተቃቅፈው ተላቀሱ፤ከሁለት ቀን
በኋላ መጋቢት 24 ቀን ተክልዬ ተጸነሱ በ 1167 ዓ/ም ተወለዱ ቀኑ አርብ ነበር፤
በተወለዱ በ3ኛ ቀናቸው እሁድ በ 3 ሰዓት “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ
ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” ብለው ስላሴን አመሰገኑ፤ ሁለተኛ ተአምር
ከዚህ በታች ያለው ስዕል ተክልዬ የአንድ ዓመት ከመንፈቅ ህጻን እያሉ ነው፤
በድፍን ሸዋ ርሃብ ተከስቶ ነበር በተለይም በዞረሬ እግዚሐርያ አዘነች አለቀሰች
ምነው እርቧት ነው ጠምቷት ነው ቢሉ የለም እርቧትስ ጠምቷትስ አይደለም
የቅዱስ ሚካኤል ዝክሩ ታጎለቢኝ ብላ እንጂ፤ ህጻኑ ተክልዬ ከእናቱ ጭን ወርዶ
እየዳኸ ወደ ጓዳ ሄደ አንስታ አቀፈችው እርሱ ግን አለቀሰ ዱቄት የተቀመጠበትን
እንቅብ እንድትሰጠው በእጁ ጠቆማት ሊጫወትበት መስሏት ሰጠችው በትንንሽ
እጆቹ እንቅቡ ላይ አማተበ ዱቄቱ ሞልቱ ፈሰሰ ዳግመኛ የቅቤ የዘይት
ማስቀመጫ ማድጋዎች ላይ በተመሳሳይ አማተበ ሞልቶ ፈሰሰ ቤቱ በበረከት
ተትረፈረፈ፤የቅዱስ ሚካኤልን ዝክሩን አዘከረች አገሬውን ጠርታ
መገበች፤ለተቸገሩትም አብዝታ ሰጠች፤ ይህ በረከት ሁለቱም እስኪሞቱ ድረስ
አላለቀም ይላል ገድላቸው። ተክልዬ በ 99 ዓመት ከ 10 ወር ከ 10 ቀን በዚህ
ምድር ኖረው ነሐሴ 24 ቀን አርፈዋል። በደብረሊባኖስ ገዳማቸው የንፍሮ ውኃ
አይነስውር ያበራል ድውይ ይፈውሳል ገድላቸው ሊነበብ ሲወጣ አጋንንት
ተቃጠልን ይላሉ ሲገርም ምን ያህል ባለጸጎች ነን። ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን።
አሜን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ለመስቀሉ ክቡር አሜን ። ይቆየን
#Join 👇👇👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAEzwE8Rx0_ELfmMHsg
♻️ እግዚአብሔርን አመስግኑ ቸር ነውና ምህረቱ ለዘላለም ነውና
መዝ፣117-29

📣ገና እንዘምራለን🔉
♥️የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የመዝሙር ግጥሞችን ወረባቶችን ከነዜማቸው ለማግኘት

#Join👇👇 ይቀላቀሉ
♦️ @mezmurat123
♦️ @mezmurat123
♦️ @mezmurat123

🔰 ኑ አብረን እናመስግን🔰
♦️ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት ,ጥያቄ እንዲሁም
መዝሙሮች ለመላክ
ለመዘመርም
የመዝሙር ግጥም Lyre.ለመላክ👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

Contact👇👇ይላኩልን

1⃣ @bezaale

2⃣ @maryamn123bot

3⃣ @yitaya

⛔️ታይቶ አይታለፍም ሼር ይደረጋል

ተዋህዶ ለዘላለም ትኑር።
👇👇👇👇👇

@Zemaryan
@Zemaryan 🌟 #Join
@Zemaryan 👈👈👈👈
@Zemaryan 🌟

👆👆👆👆👆
Audio
🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻 
#join_share
🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻 
@embtee
🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻 
🛑_አዲስ_የንስሃ_ዝማሬ_"የማደርገውን_አላውቅም"_ሊቀ_መዘምራን_ቴዎድሮስ_ዮሴፍ360p.mp4
25.9 MB
new mezmur

🎤 ሊቀ መዘምር ቴድሮስ ዮሴፍ

🎼የማደርገውን አላውቅም

ሌሎች አዳዲስ መዝሙር ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇👇

🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻 
#join_share
🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻 
@embtee
@embtee
🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻 
🛑_አዲስ_የበገና_ዝማሬ_"ቅዱስ"_|_ዘማሪ_አቤል_ተስፋዬ360p.mp4
20.5 MB
new mezmur

🎤 ዘማሪ አቤል ተስፋዬ

🎼ቅዱስ

ሌሎች አዳዲስ መዝሙር ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇👇

🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻 
#join_share
🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻 
@embtee
@embtee
🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆