Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
"ለሦስት ቀን ነነዌ ላይ እንድናደርገው የታዘዝነው ሐዘንና ሱባኤ በንስሐና በዕንባ ሆነን የእግዚአብሔርን መልስ ለማግኘት ነው። አስተውሉ:: የዐለም መንግሥታት እንዲያዩን ሳይሆን የዐለም ፈጣሪ እንዲያየንና እንዲሰማን ነው። ለአክቲቪዝም ፣ ለፕሮፓጋንዳና ለብሽሽቅ ሳይሆን ልብን በእግዚአብሔር ፊት ለማዋረድና ከእርሱ እርዳታን አግኝተን ለመመለስ ነው። ልብስ ቀይረን ወደ ምሕላ የምንሔድበትን ዓላማ ለአፍታም ቢሆን መርሳት የለብንም...እግዚአብሔር የቲፎዞ፣ የብሽሽቅ፣ የሽንገላ፣ የማስመሰልና በአጠቃላይ ምድራዊ በሆኑ ነገሮች የታጀበን ነገር አይቀበልም። ጾም ጸሎታችንን እንዳናበላሸው እንጠንቀቅ። ከለፍላፊነትና ከተሳዳቢነት በሽታም እንፈወስ... ትኩረታችን ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ግንኙነት ላይ መሆን አለበት ። "
ዲያቆን ብርሀኑ አድማስ
#ኢንፈርህ_ሞተ
#ሞትን_አንፈራውም
#ጸልዩ_በእንተ_ቤተክርስቲያን_ቅድስት
ዲያቆን ብርሀኑ አድማስ
#ኢንፈርህ_ሞተ
#ሞትን_አንፈራውም
#ጸልዩ_በእንተ_ቤተክርስቲያን_ቅድስት