Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
" ወድቀህ ብትሰግድልኝ ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ !"
________________________________
#ማቴ ፬÷፱
#ንግግሩ_ብዙ_ጊዜ ዲያቢሎስና የግብር ልጆቹ ሰዎችን በፍቅረ ነዋይ ሊጥሉ
ከሃይማኖትም መንገድ ሊያስወጡ ሲፈልጉ የሚናገሩት የተንኮል ንግግር ነው። የሚሰጥ
መስፈርት ወይም ቅድመ ሆኔታ አያስቀምጥም ዝም ብሎ በፍቅር ይሰጣል ተንኮለኞች ግን
ለተንኮል ይሰጣሉ ። #እግዚአብሔር ቸር ሰጪ ነው ሲሰጥም የሰገደልኝ ያልሰገደልኝ
ያመነኝ ያላመነኝ አይልም ያመነው ይበልጡኑ ያተርፍበታል ያላመነው በሥራው ይከሥርበታል
እንጂ አያስገድደውም ።“ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና
በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።” #ማቴ ፭ ፥ ፵፬-፵ ፭
ከፍቅረ ነዋይ የተነሳ ብዙዎች " ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ" ለሚላቸው አካል ልቡናቸው ክፍት
ነው። ዲያቢሎስም ይህን ስለሚያውቅ በብዙ ይፈትናቸዋል ስለዚህ እግሮቻቸውን " ይህን
ሁሉ እሰጥሃለሁ " ወደሚል ወደ ጠንቋይ ቤት ያነሳሉ በእውነቱ ግን ጠንቋይ ሁሉን
ሊሰጣቸው ቀርቶ ያላቸውንም አራቁቶ ባዶ ያስቀራቸዋል። ጠንቋይ ማለት ጠንቀ ነዋይ
ማለት ነውና። የንጽሕ ገንዘብ ምንጭ አይደለም ሰርቶ ባለ ፀጋ መሆን ይቻላል!
አያስኮንንም። ሰርቆ መክበር ግን ያዋርዳል።
ብዙ ጊዜ ባለ ጸጎች # ከእግዚአብሔር መንግሥ የራቁ ናቸው። ለዚህም ነው " ለባለ ጸጋ
መንግሥተ ሰማያት መግባት ጭንቅ ይሆንበታል፤ ባለ ጸጋ መንግሥተ ሰማያት ከሚገባ
ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ብትሾልክ ይቀላል "ተብሎ የተነገረው #ማቴ ፲ ፱÷፳ ፫
ዲያቢሎስ በጠንቋይ እያደረ " ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ" ያለንን ሁሉ ያሳጣናል በዚህ የፍቅረ
ነዋይ ፈተና #እግዚአብሔር ሁሉ ሳይቀር ይህን "ሁሉ እሰጥሀለሁ " ብሎ ለመፈተን
ሞክሯል። ግን አልተሳካለትም # እግዚአብሔር ሰጪ እንጂ ተቀባይ አይደለምና በዚህም
ፈተና ተፈተነ ሲባል ሰይጣን የእግዚአብሔር የሚፈትነው ሆኖ አይደለም ወደ ፊት ለሚነሱ
ጾሚ ተአራሚዎች እንዴት ድል እንደሚያደርጉት ድል ማድረጌያውን ሊያስተምራቸው ወዶ
ነው እንጂ።
# እጅግ ረጅም ወደ ሆነ ተራራ ወሰደው፥ የዓለምንም መንግሥታት ሁሉ ክብራቸውንም
አሳይቶ ብትሰግድልኝ እጅ ብትነሣኝም ይህን ሁሉ እሰጥሀለሁ " አለው፡፡” #ማቴ ፬ ÷ ፰
ወሰደው ”ሲባል፡- ሰይጣን ጌታችንን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የሚወስድ
የሚያመጣው ሆኖ ሳይሆን ‹‹ ነገሥታቱን ድል በምንነሣበት በተራራ ቢሆን መች ድል ይነሳኝ
ነበር›› ብሎ አስቧልና ነው ፡፡ (ነገሥታት በተራራ ቤተ መንግስታቸውን ይሠራሉና) አሁንም
ምክንያት ለማሳጣት ከረጅም ተራራ በራሱ ፍቃድ ወጥቷልና “ወሰደው ” ተባለ፡፡ ሰይጣን
ሳያፍርና ሳይፈራ “ብትሰግድልኝ እጅም ብትነሣኝ ይህን ሁሉ እሰጥሀለሁ” ብሎ ብዙዎችን
ድል ባረገበት በፍቅረ ነዋይ የመጨረሻ ፈተናውን አቀረበ፡፡
በእውነቱ ከሆነ ዛሬ በዚህ ፈተና ያልተሸነፈ የለም፡፡ በዓለም ላይ ያሉ ሁሉም ጦርነቶች
ሌላምክንያት ቢሰጣቸውም ዋናው ምክንያታቸው የኢኮኖሚ ፉክክር ፣የከበርቴነት ውድድር
ፍቅረ ነዋይ ነው፡፡ዘፈኑ፤ዝሙቱ፤ሥርቆቱም ምንጫቸው ፍቅረ ነዋይ ነው፡፡
ባለ ሽቶዋ ማርያም የአልባስጥሮሽ ሽቶ ይዛ መታ የጌታዋን እግር በትቀባ ገንዘብ ወዳዱ
ይሁዳ አልተዋጠለትም "ይህ ሦስት መቶ ዲናር የሚያወጣ ውድ ሽቶ ነው ተሽጦ ለድሆች
በተሰጠ ይሻል ነበር ብሎ ተናገረ፤ ሽቶው ከተሸጠ ከሦስቱ አስር አስር እጅ ማለትም ሰላሳ
የሚጠዱ ዲናሮችን በቀረጥ መልክ ይሰበስብ ነበርና ነው እንጂ ለድሆችሽ ተጨንቆላቸው
አልነበረም እንዲያውም መጻሕፍ " ሌባ "ስለ ነበር ነው ብሎ ይገልጠዋል። ጌታችን
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም ቀጥሎ ሽቶ ስለቀባችኝ ይህችን ሴት ስለምን
ታደክሟታላችሁ? ድሆችስ ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ናቸው ባሻችሁ ጊዜ መልካም
ልታደርጉላቸው ትችላላችሁ አለ።
# ይሁዳ ሠላሳዋን ብር ስላጣ ተቆጨ በዚህም ሰይጣን በልቡ ገባበት ሠላሳውንም ብር
ጌታውን ሽጦ ያገኛት ዘንድ ሰይጣን ልቡን አጸናው ። በመጨረሻም በገንዘብ ፍቅር ታውሮ
ነበርና ወደር ስለማይገኝለት ፍቅሩ ክህደትን ከፈለው ። የሚገርመው ይሁዳን ገንዘብ
መውደደ የሚያውቅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እሱ ሌባ ነው ሳይል የሐዋርያት ገንዘብ ያዢ
አድርጎ ሁሉ ሾሞት ነበር ። ይህ ሁሉ ግን የይሁዳን ድንጋይ ልብ ሊሰብረው አልቻለም።
ፍቅረ ነዋይ እንዲህ ነው!
ብዙዎቻች በዚህ ፈተና ውስጥ እንገኛለን ገንዘብ ከመውደዳችን የተነሳ አስራቱን በአግባቡ
ባለማውጣት ከእግዚአብሔር እንኳን ሳይቀር ሰርቀናል “ሰው # እግዚአብሔርን ይሰርቃልን?
እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም፦ የሰረቅንህ በምንድር ነው? ብላችኋል።
በአሥራትና በበኵራት ነው።” # ሚልክያስ ፫፥፰
# ጌታችን_አምላካችን_መድኀኒታችን_ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ይሄን ሁሉን ተንኮሉን
ያውቃልና “ብትሰግድልኝ ይሄን ሁሉ እሰጥሃለሁ” ብሎ በፍቅረ ነዋይ የፈተነውን ሰይጣን
“አንተ ሰይጣን ከአጠገቤ ሒድ ፤ ለጌታ ለእግዚአብሔር ስገድ እርሱን ብቻ አምልክ ተብሎ
ተፅፏልና ” ብሎ በጸሊአ ነዋይድል አድርጎታል፡፡
.“አንተ ሠይጣን ከአጠገቤ ሒድ”፡- ሲለው እግዚአብሔር አምላክ የሌለበት ቦታ ኖሮ
ወደዚያ ሂድ ያለው አይደለም፡፡ይልቁንም “ ከእኔ በኃላ ከሚነሱ ከኦርቶዶክሳዊያን ልቦና
ሒድ ሲለው” እንጂ # ማቴ. ፲፮፥፳፫፡፡ በእውነት በፍቅረ ነዋይ የሚፈታተነንን ሰይጣን
ዲያቢሎስን ከልቦናችን አርቆ ያስቀርልን “ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ባርያ ማንም
የለም፤ ወይም አንዱን ይጠላልና ሁለተኛውንም ይወዳል፥ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል
ሁለተኛውንም ይንቃል። # ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም።” ተብሏልና
ገዘብን ከመውደድ እግዚአብሔር መውደድን አብዝቶ ያድለን ገንዘብን መውደድ (ፍቅረ
ነዋይን) እንዴት መተው እንችላለን ቢሉ አላፊነቱን፣ ከእግዚአብሔር መንግስት መለየቱንና
የጥፋት ሁሉ ሥር መሆኑን ዕለት ዕለት በማሰብ ጸላሄ ነዋይ መሆን ይቻላል ይህ ለመንፈሳዊ
ሰው ቀላል ነው በገዳመ ቆሮንቶስ ያስተማረን ይህንኑ ነው!
ለሀገራችንና ለዓለማችንም ሠላሙን ይስጥልን # ሉቃስ ፲ ፮ ፥ ፲ ፫
.......ይቆየን.......
ግብሐት:- መጻሕፍ ቅዱስ
ወንጌል ትርጓሜ
መቅረዘ ተዋሕዶ
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፯ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
________________________________
#ማቴ ፬÷፱
#ንግግሩ_ብዙ_ጊዜ ዲያቢሎስና የግብር ልጆቹ ሰዎችን በፍቅረ ነዋይ ሊጥሉ
ከሃይማኖትም መንገድ ሊያስወጡ ሲፈልጉ የሚናገሩት የተንኮል ንግግር ነው። የሚሰጥ
መስፈርት ወይም ቅድመ ሆኔታ አያስቀምጥም ዝም ብሎ በፍቅር ይሰጣል ተንኮለኞች ግን
ለተንኮል ይሰጣሉ ። #እግዚአብሔር ቸር ሰጪ ነው ሲሰጥም የሰገደልኝ ያልሰገደልኝ
ያመነኝ ያላመነኝ አይልም ያመነው ይበልጡኑ ያተርፍበታል ያላመነው በሥራው ይከሥርበታል
እንጂ አያስገድደውም ።“ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና
በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።” #ማቴ ፭ ፥ ፵፬-፵ ፭
ከፍቅረ ነዋይ የተነሳ ብዙዎች " ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ" ለሚላቸው አካል ልቡናቸው ክፍት
ነው። ዲያቢሎስም ይህን ስለሚያውቅ በብዙ ይፈትናቸዋል ስለዚህ እግሮቻቸውን " ይህን
ሁሉ እሰጥሃለሁ " ወደሚል ወደ ጠንቋይ ቤት ያነሳሉ በእውነቱ ግን ጠንቋይ ሁሉን
ሊሰጣቸው ቀርቶ ያላቸውንም አራቁቶ ባዶ ያስቀራቸዋል። ጠንቋይ ማለት ጠንቀ ነዋይ
ማለት ነውና። የንጽሕ ገንዘብ ምንጭ አይደለም ሰርቶ ባለ ፀጋ መሆን ይቻላል!
አያስኮንንም። ሰርቆ መክበር ግን ያዋርዳል።
ብዙ ጊዜ ባለ ጸጎች # ከእግዚአብሔር መንግሥ የራቁ ናቸው። ለዚህም ነው " ለባለ ጸጋ
መንግሥተ ሰማያት መግባት ጭንቅ ይሆንበታል፤ ባለ ጸጋ መንግሥተ ሰማያት ከሚገባ
ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ብትሾልክ ይቀላል "ተብሎ የተነገረው #ማቴ ፲ ፱÷፳ ፫
ዲያቢሎስ በጠንቋይ እያደረ " ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ" ያለንን ሁሉ ያሳጣናል በዚህ የፍቅረ
ነዋይ ፈተና #እግዚአብሔር ሁሉ ሳይቀር ይህን "ሁሉ እሰጥሀለሁ " ብሎ ለመፈተን
ሞክሯል። ግን አልተሳካለትም # እግዚአብሔር ሰጪ እንጂ ተቀባይ አይደለምና በዚህም
ፈተና ተፈተነ ሲባል ሰይጣን የእግዚአብሔር የሚፈትነው ሆኖ አይደለም ወደ ፊት ለሚነሱ
ጾሚ ተአራሚዎች እንዴት ድል እንደሚያደርጉት ድል ማድረጌያውን ሊያስተምራቸው ወዶ
ነው እንጂ።
# እጅግ ረጅም ወደ ሆነ ተራራ ወሰደው፥ የዓለምንም መንግሥታት ሁሉ ክብራቸውንም
አሳይቶ ብትሰግድልኝ እጅ ብትነሣኝም ይህን ሁሉ እሰጥሀለሁ " አለው፡፡” #ማቴ ፬ ÷ ፰
ወሰደው ”ሲባል፡- ሰይጣን ጌታችንን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የሚወስድ
የሚያመጣው ሆኖ ሳይሆን ‹‹ ነገሥታቱን ድል በምንነሣበት በተራራ ቢሆን መች ድል ይነሳኝ
ነበር›› ብሎ አስቧልና ነው ፡፡ (ነገሥታት በተራራ ቤተ መንግስታቸውን ይሠራሉና) አሁንም
ምክንያት ለማሳጣት ከረጅም ተራራ በራሱ ፍቃድ ወጥቷልና “ወሰደው ” ተባለ፡፡ ሰይጣን
ሳያፍርና ሳይፈራ “ብትሰግድልኝ እጅም ብትነሣኝ ይህን ሁሉ እሰጥሀለሁ” ብሎ ብዙዎችን
ድል ባረገበት በፍቅረ ነዋይ የመጨረሻ ፈተናውን አቀረበ፡፡
በእውነቱ ከሆነ ዛሬ በዚህ ፈተና ያልተሸነፈ የለም፡፡ በዓለም ላይ ያሉ ሁሉም ጦርነቶች
ሌላምክንያት ቢሰጣቸውም ዋናው ምክንያታቸው የኢኮኖሚ ፉክክር ፣የከበርቴነት ውድድር
ፍቅረ ነዋይ ነው፡፡ዘፈኑ፤ዝሙቱ፤ሥርቆቱም ምንጫቸው ፍቅረ ነዋይ ነው፡፡
ባለ ሽቶዋ ማርያም የአልባስጥሮሽ ሽቶ ይዛ መታ የጌታዋን እግር በትቀባ ገንዘብ ወዳዱ
ይሁዳ አልተዋጠለትም "ይህ ሦስት መቶ ዲናር የሚያወጣ ውድ ሽቶ ነው ተሽጦ ለድሆች
በተሰጠ ይሻል ነበር ብሎ ተናገረ፤ ሽቶው ከተሸጠ ከሦስቱ አስር አስር እጅ ማለትም ሰላሳ
የሚጠዱ ዲናሮችን በቀረጥ መልክ ይሰበስብ ነበርና ነው እንጂ ለድሆችሽ ተጨንቆላቸው
አልነበረም እንዲያውም መጻሕፍ " ሌባ "ስለ ነበር ነው ብሎ ይገልጠዋል። ጌታችን
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም ቀጥሎ ሽቶ ስለቀባችኝ ይህችን ሴት ስለምን
ታደክሟታላችሁ? ድሆችስ ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ናቸው ባሻችሁ ጊዜ መልካም
ልታደርጉላቸው ትችላላችሁ አለ።
# ይሁዳ ሠላሳዋን ብር ስላጣ ተቆጨ በዚህም ሰይጣን በልቡ ገባበት ሠላሳውንም ብር
ጌታውን ሽጦ ያገኛት ዘንድ ሰይጣን ልቡን አጸናው ። በመጨረሻም በገንዘብ ፍቅር ታውሮ
ነበርና ወደር ስለማይገኝለት ፍቅሩ ክህደትን ከፈለው ። የሚገርመው ይሁዳን ገንዘብ
መውደደ የሚያውቅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እሱ ሌባ ነው ሳይል የሐዋርያት ገንዘብ ያዢ
አድርጎ ሁሉ ሾሞት ነበር ። ይህ ሁሉ ግን የይሁዳን ድንጋይ ልብ ሊሰብረው አልቻለም።
ፍቅረ ነዋይ እንዲህ ነው!
ብዙዎቻች በዚህ ፈተና ውስጥ እንገኛለን ገንዘብ ከመውደዳችን የተነሳ አስራቱን በአግባቡ
ባለማውጣት ከእግዚአብሔር እንኳን ሳይቀር ሰርቀናል “ሰው # እግዚአብሔርን ይሰርቃልን?
እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም፦ የሰረቅንህ በምንድር ነው? ብላችኋል።
በአሥራትና በበኵራት ነው።” # ሚልክያስ ፫፥፰
# ጌታችን_አምላካችን_መድኀኒታችን_ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ይሄን ሁሉን ተንኮሉን
ያውቃልና “ብትሰግድልኝ ይሄን ሁሉ እሰጥሃለሁ” ብሎ በፍቅረ ነዋይ የፈተነውን ሰይጣን
“አንተ ሰይጣን ከአጠገቤ ሒድ ፤ ለጌታ ለእግዚአብሔር ስገድ እርሱን ብቻ አምልክ ተብሎ
ተፅፏልና ” ብሎ በጸሊአ ነዋይድል አድርጎታል፡፡
.“አንተ ሠይጣን ከአጠገቤ ሒድ”፡- ሲለው እግዚአብሔር አምላክ የሌለበት ቦታ ኖሮ
ወደዚያ ሂድ ያለው አይደለም፡፡ይልቁንም “ ከእኔ በኃላ ከሚነሱ ከኦርቶዶክሳዊያን ልቦና
ሒድ ሲለው” እንጂ # ማቴ. ፲፮፥፳፫፡፡ በእውነት በፍቅረ ነዋይ የሚፈታተነንን ሰይጣን
ዲያቢሎስን ከልቦናችን አርቆ ያስቀርልን “ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ባርያ ማንም
የለም፤ ወይም አንዱን ይጠላልና ሁለተኛውንም ይወዳል፥ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል
ሁለተኛውንም ይንቃል። # ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም።” ተብሏልና
ገዘብን ከመውደድ እግዚአብሔር መውደድን አብዝቶ ያድለን ገንዘብን መውደድ (ፍቅረ
ነዋይን) እንዴት መተው እንችላለን ቢሉ አላፊነቱን፣ ከእግዚአብሔር መንግስት መለየቱንና
የጥፋት ሁሉ ሥር መሆኑን ዕለት ዕለት በማሰብ ጸላሄ ነዋይ መሆን ይቻላል ይህ ለመንፈሳዊ
ሰው ቀላል ነው በገዳመ ቆሮንቶስ ያስተማረን ይህንኑ ነው!
ለሀገራችንና ለዓለማችንም ሠላሙን ይስጥልን # ሉቃስ ፲ ፮ ፥ ፲ ፫
.......ይቆየን.......
ግብሐት:- መጻሕፍ ቅዱስ
ወንጌል ትርጓሜ
መቅረዘ ተዋሕዶ
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፯ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
" #ዕለት_ሳበችው_ምሕረትም_ጠቀሰችው"
_______________________________
#አባታችን_ሁልጊዜ እንዲህ ይሉ ነበር። ‹‹የሚጣፍጥ ምግብን መውደድ ኃጢአትን
ያመጣል፣ሞትን ያስከትላል፡፡ ክንፍ ያላቸው የሰማይ ወፎች እንኳን በመብል ምክንያት
ይጠመዳሉ፣ ምግብ በመሻት ከምድር ላይ ይወድቃሉ በወጥመድም ይያዛሉ፡፡የሰው ልጅም
ምግብን በመውደድ በኃጢአት ይወድቃልና እኔስ ለሰውነቴ ምግብ መጠጥን
አልፈልግም፤ልብስም አልሻም ዕራቁቴን ከእናቴ ማኅፀን እንደወጣሁ እንዲሁ ዕረቁቴን ወደ
መቃብር እመለሳለሁ እንጂ፡፡ከዚህ ከኃላፊው ዓለም በሞት በተለየሁ ጊዜ መብል
መጠጥንና ልብስን ማን ያስከትልልኛል?›› አሉ። ዳግመኛም‹‹ሰው:ሊደርስበ
ማይችልበት:በረሃ:እኖራለሁ፣ ነጣቂ ተኩላዎችና አራዊቶች ባሉበት እነርሱ እንዲበሉኝ
ሥጋዬን እጥላለሁ፤ ዳዊት በመዝሙር ‹የጻድቃን ሥጋቸው ለዱር አራዊት ነው› እንዳለ እኔ
ክፉ አውሬዎች፣ ተናዳፊ እባቦችና ዘንዶዎች ወዳሉበት እገባለሁ ምግብም እሆናቸው ዘንድ
እወዳለሁ››በማለት አባታችን ራሳቸውን ለሞት አሳልፈው ይሰጡ ነበር ነገር ግን አራዊቱ
ሁሉ እየሰገዱላቸው ይገዙላቸው ከእግራቸውም በታች ይተኙ ነበር፡፡ እንደሚታዘዝ ደቀ
መዝሙርም ይታዙላቸው ነበር፤ለጸሎትም በሚቆሙበት ጊዜ አብረዋቸው ይቆማሉ፡፡
በፊታቸውም ይጫወታሉ፡፡
#በመጨረሻም ዕለት ሳበችሁ ምሕረትም ጠቀሰችሁ ለሞትም የሚያበቃ ጽኑ ሕማም
ታመመ የሚጠጋበት የዛፍ ጥላ በሌለበት እንደ አንበሳ በበርሃ ወደቀ ለጸሎት ከቆመበት
ጊዜ አንስቶ እስከ ሞተበት ቀን ድረስ እጆቹን በትምህርተ መስቀል እንዳማተበ ነበር ። ብዙ
ግሁሳንም ወደ እርሱ መጡ #እግዚአብሔር አምላክም ብዙ የብዙ ብዙ መላእክትን
አስከትሎ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምን አስቀድሞ ዳዊትንም በገና አስይዞ ተገለጠና
ነብሱን አክብሮ ተቀበላት፣ሳማት፣ ደስታውንም መላት መላእክትም ከዳዊት ጋር "ክቡር ሞቱ
ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር " የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው" እያሉ
በአንድነት ዘመሩለት #መዝ ፻ ፲ ፭ {፻ ፲ ፮ }÷፲ ፭
“ #እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ
እናውቃለን።”
#ሮሜ ፰ ፥፳ ፰
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፭ ቀን ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
_______________________________
#አባታችን_ሁልጊዜ እንዲህ ይሉ ነበር። ‹‹የሚጣፍጥ ምግብን መውደድ ኃጢአትን
ያመጣል፣ሞትን ያስከትላል፡፡ ክንፍ ያላቸው የሰማይ ወፎች እንኳን በመብል ምክንያት
ይጠመዳሉ፣ ምግብ በመሻት ከምድር ላይ ይወድቃሉ በወጥመድም ይያዛሉ፡፡የሰው ልጅም
ምግብን በመውደድ በኃጢአት ይወድቃልና እኔስ ለሰውነቴ ምግብ መጠጥን
አልፈልግም፤ልብስም አልሻም ዕራቁቴን ከእናቴ ማኅፀን እንደወጣሁ እንዲሁ ዕረቁቴን ወደ
መቃብር እመለሳለሁ እንጂ፡፡ከዚህ ከኃላፊው ዓለም በሞት በተለየሁ ጊዜ መብል
መጠጥንና ልብስን ማን ያስከትልልኛል?›› አሉ። ዳግመኛም‹‹ሰው:ሊደርስበ
ማይችልበት:በረሃ:እኖራለሁ፣ ነጣቂ ተኩላዎችና አራዊቶች ባሉበት እነርሱ እንዲበሉኝ
ሥጋዬን እጥላለሁ፤ ዳዊት በመዝሙር ‹የጻድቃን ሥጋቸው ለዱር አራዊት ነው› እንዳለ እኔ
ክፉ አውሬዎች፣ ተናዳፊ እባቦችና ዘንዶዎች ወዳሉበት እገባለሁ ምግብም እሆናቸው ዘንድ
እወዳለሁ››በማለት አባታችን ራሳቸውን ለሞት አሳልፈው ይሰጡ ነበር ነገር ግን አራዊቱ
ሁሉ እየሰገዱላቸው ይገዙላቸው ከእግራቸውም በታች ይተኙ ነበር፡፡ እንደሚታዘዝ ደቀ
መዝሙርም ይታዙላቸው ነበር፤ለጸሎትም በሚቆሙበት ጊዜ አብረዋቸው ይቆማሉ፡፡
በፊታቸውም ይጫወታሉ፡፡
#በመጨረሻም ዕለት ሳበችሁ ምሕረትም ጠቀሰችሁ ለሞትም የሚያበቃ ጽኑ ሕማም
ታመመ የሚጠጋበት የዛፍ ጥላ በሌለበት እንደ አንበሳ በበርሃ ወደቀ ለጸሎት ከቆመበት
ጊዜ አንስቶ እስከ ሞተበት ቀን ድረስ እጆቹን በትምህርተ መስቀል እንዳማተበ ነበር ። ብዙ
ግሁሳንም ወደ እርሱ መጡ #እግዚአብሔር አምላክም ብዙ የብዙ ብዙ መላእክትን
አስከትሎ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምን አስቀድሞ ዳዊትንም በገና አስይዞ ተገለጠና
ነብሱን አክብሮ ተቀበላት፣ሳማት፣ ደስታውንም መላት መላእክትም ከዳዊት ጋር "ክቡር ሞቱ
ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር " የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው" እያሉ
በአንድነት ዘመሩለት #መዝ ፻ ፲ ፭ {፻ ፲ ፮ }÷፲ ፭
“ #እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ
እናውቃለን።”
#ሮሜ ፰ ፥፳ ፰
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፭ ቀን ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም