“ #እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል ”
________________________________
#ያዕ ፬ ፥ ፮
#፩ጴጥ ፭ ÷ ፭
ትዕቢት ከሦስቱ (አርስተ/ ርዕሰ ኃጥዐው) መካከል አንዱ ነው:: ሦስቱ ርዕሰ ኃጥዐው የሚባሉት ስስት ፣ትዕቢትና ፍቅረ ነዋይ ናቸው።
#ስስት፣ ትዕቢትና ፍቅረ ነዋይ የኃጢያት ሁሉ እራሶች ፣ አለቆች ና አውራዎች መባላቸው ኃጢያት ሁሉ ከእነዚህ ስለሚመነጭ ነው።
ዲያቢሎስ መንፈሳዊ ሰውን የሚፈትነው በሦስቱ የፈተና ዐይነቶች ነው በስስት፣ በትዕቢትና በፍቅረ ነዋይ ፤ ሌሎች የኃጢያት ዐይነቶች የነዚህ የሦስቱ ጭፍሮች ወይም ተከታዮች ናቸው።
#ለምሳሌ የትዕቢት መንፈስ የተጠናወተው አንድ ሰው እኔ ከማን አንሳለሁ የሚል የበታችነት ስሜት ውስጥ በመግባት ለግድያ ፣ለስርቆት፣ ብሎም ለዝሙት ኃጢያቶች ተጋላጭ ይሆናል።
ትዕቢት የዲያቢሎስ ልዮ መገለጫው ነው ስለሆነም ዲያቢሎስ ስለ ግብሩ ( ስለ ሥራው) ትዕቢተኛ ብቻ ሳይሆን እራሱ ትዕቢት እየተባለ ይጠራል። ለዚህ ነው ሐዋርያው እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል" ካለ በኋላ " እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤ " ሲል ትዕቢተኞች ብሎ በተውላጠ ስም የጠራቸውን ዲያቢሎስና ጭፍሮቹን አስከትሎ ደግሞ "ዲያቢሎስን" ብሎ በግልጥ የተናገረው #ያዕ ፬÷፮ - ፯
#ለዚህ ትልቁ ማሳያ የገዳመ ቆሮንቶስ ሁለተኛ ፈተና ትዕቢት የተሞላበት መሆኑ ነው "ዲያብሎስ ወደ ቅድስት ከተማ ወሰደውና (ወሰደው ሲል በፍቃዱ ሄደለት ለማለት እንጂ ለዲያቢሎስስ ታዛዢ ሆኖ አይደለም) እርሱን በመቅደስ ጫፍ ላይ አቁሞ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝልሃል እግርህንም በድንጋይ ከቶ እንዳትሰናከል በእጃቸው ያነሡሃል ተብሎ ተጽፎአልና የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ፥ ወደ ታች ራስህን ወርውር አለው። “ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ጌታን አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ደግሞ ተጽፎአል" ብሎ የትዕቢትን ፈተና በትሕትና ድል ነሳው ። የካህናት ፆራቸው ትዕቢት ነው ፤‹ ‹ እኛ አእምሮአችን ረቂቅ ማዕረጋችን ምጡቅ ›› እያሉ በትዕቢት ይፈተናሉ፡፡ ዲያብሎስ በካህናት ቦታ በቤተመቅደስ በትዕቢት ቢመጣበት በትህትና ድል አድርጎላቸዋል፡፡ #የትዕቢትን ፈተና ማሸነፍ የሚቻለው በትሕትና ብቻ ነው! #ማቴ ፬÷ ፭- ፰ .
“ከእኔም_ተማሩ_እኔ_የዋህ_በልቤም_ትሑት_ነኝና"
#ማቴ ፲ ፩ ፥ ፳ ፱
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፬ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
________________________________
#ያዕ ፬ ፥ ፮
#፩ጴጥ ፭ ÷ ፭
ትዕቢት ከሦስቱ (አርስተ/ ርዕሰ ኃጥዐው) መካከል አንዱ ነው:: ሦስቱ ርዕሰ ኃጥዐው የሚባሉት ስስት ፣ትዕቢትና ፍቅረ ነዋይ ናቸው።
#ስስት፣ ትዕቢትና ፍቅረ ነዋይ የኃጢያት ሁሉ እራሶች ፣ አለቆች ና አውራዎች መባላቸው ኃጢያት ሁሉ ከእነዚህ ስለሚመነጭ ነው።
ዲያቢሎስ መንፈሳዊ ሰውን የሚፈትነው በሦስቱ የፈተና ዐይነቶች ነው በስስት፣ በትዕቢትና በፍቅረ ነዋይ ፤ ሌሎች የኃጢያት ዐይነቶች የነዚህ የሦስቱ ጭፍሮች ወይም ተከታዮች ናቸው።
#ለምሳሌ የትዕቢት መንፈስ የተጠናወተው አንድ ሰው እኔ ከማን አንሳለሁ የሚል የበታችነት ስሜት ውስጥ በመግባት ለግድያ ፣ለስርቆት፣ ብሎም ለዝሙት ኃጢያቶች ተጋላጭ ይሆናል።
ትዕቢት የዲያቢሎስ ልዮ መገለጫው ነው ስለሆነም ዲያቢሎስ ስለ ግብሩ ( ስለ ሥራው) ትዕቢተኛ ብቻ ሳይሆን እራሱ ትዕቢት እየተባለ ይጠራል። ለዚህ ነው ሐዋርያው እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል" ካለ በኋላ " እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤ " ሲል ትዕቢተኞች ብሎ በተውላጠ ስም የጠራቸውን ዲያቢሎስና ጭፍሮቹን አስከትሎ ደግሞ "ዲያቢሎስን" ብሎ በግልጥ የተናገረው #ያዕ ፬÷፮ - ፯
#ለዚህ ትልቁ ማሳያ የገዳመ ቆሮንቶስ ሁለተኛ ፈተና ትዕቢት የተሞላበት መሆኑ ነው "ዲያብሎስ ወደ ቅድስት ከተማ ወሰደውና (ወሰደው ሲል በፍቃዱ ሄደለት ለማለት እንጂ ለዲያቢሎስስ ታዛዢ ሆኖ አይደለም) እርሱን በመቅደስ ጫፍ ላይ አቁሞ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝልሃል እግርህንም በድንጋይ ከቶ እንዳትሰናከል በእጃቸው ያነሡሃል ተብሎ ተጽፎአልና የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ፥ ወደ ታች ራስህን ወርውር አለው። “ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ጌታን አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ደግሞ ተጽፎአል" ብሎ የትዕቢትን ፈተና በትሕትና ድል ነሳው ። የካህናት ፆራቸው ትዕቢት ነው ፤‹ ‹ እኛ አእምሮአችን ረቂቅ ማዕረጋችን ምጡቅ ›› እያሉ በትዕቢት ይፈተናሉ፡፡ ዲያብሎስ በካህናት ቦታ በቤተመቅደስ በትዕቢት ቢመጣበት በትህትና ድል አድርጎላቸዋል፡፡ #የትዕቢትን ፈተና ማሸነፍ የሚቻለው በትሕትና ብቻ ነው! #ማቴ ፬÷ ፭- ፰ .
“ከእኔም_ተማሩ_እኔ_የዋህ_በልቤም_ትሑት_ነኝና"
#ማቴ ፲ ፩ ፥ ፳ ፱
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፬ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
“ #እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል ”
________________________________
#ያዕ ፬ ፥ ፮
#፩ጴጥ ፭ ÷ ፭
ትዕቢት ከሦስቱ (አርስተ/ ርዕሰ ኃጥዐው) መካከል አንዱ ነው:: ሦስቱ ርዕሰ ኃጥዐው የሚባሉት ስስት ፣ትዕቢትና ፍቅረ ነዋይ ናቸው።
#ስስት፣ ትዕቢትና ፍቅረ ነዋይ የኃጢያት ሁሉ እራሶች ፣ አለቆች ና አውራዎች መባላቸው ኃጢያት ሁሉ ከእነዚህ ስለሚመነጭ ነው።
ዲያቢሎስ መንፈሳዊ ሰውን የሚፈትነው በሦስቱ የፈተና ዐይነቶች ነው በስስት፣ በትዕቢትና በፍቅረ ነዋይ ፤ ሌሎች የኃጢያት ዐይነቶች የነዚህ የሦስቱ ጭፍሮች ወይም ተከታዮች ናቸው።
#ለምሳሌ የትዕቢት መንፈስ የተጠናወተው አንድ ሰው እኔ ከማን አንሳለሁ የሚል የበታችነት ስሜት ውስጥ በመግባት ለግድያ ፣ለስርቆት፣ ብሎም ለዝሙት ኃጢያቶች ተጋላጭ ይሆናል።
ትዕቢት የዲያቢሎስ ልዮ መገለጫው ነው ስለሆነም ዲያቢሎስ ስለ ግብሩ ( ስለ ሥራው) ትዕቢተኛ ብቻ ሳይሆን እራሱ ትዕቢት እየተባለ ይጠራል። ለዚህ ነው ሐዋርያው እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል" ካለ በኋላ " እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤ " ሲል ትዕቢተኞች ብሎ በተውላጠ ስም የጠራቸውን ዲያቢሎስና ጭፍሮቹን አስከትሎ ደግሞ "ዲያቢሎስን" ብሎ በግልጥ የተናገረው #ያዕ ፬÷፮ - ፯
#ለዚህ ትልቁ ማሳያ የገዳመ ቆሮንቶስ ሁለተኛ ፈተና ትዕቢት የተሞላበት መሆኑ ነው "ዲያብሎስ ወደ ቅድስት ከተማ ወሰደውና (ወሰደው ሲል በፍቃዱ ሄደለት ለማለት እንጂ ለዲያቢሎስስ ታዛዢ ሆኖ አይደለም) እርሱን በመቅደስ ጫፍ ላይ አቁሞ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝልሃል እግርህንም በድንጋይ ከቶ እንዳትሰናከል በእጃቸው ያነሡሃል ተብሎ ተጽፎአልና የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ፥ ወደ ታች ራስህን ወርውር አለው። “ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ጌታን አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ደግሞ ተጽፎአል" ብሎ የትዕቢትን ፈተና በትሕትና ድል ነሳው ። የካህናት ፆራቸው ትዕቢት ነው ፤‹ ‹ እኛ አእምሮአችን ረቂቅ ማዕረጋችን ምጡቅ ›› እያሉ በትዕቢት ይፈተናሉ፡፡ ዲያብሎስ በካህናት ቦታ በቤተመቅደስ በትዕቢት ቢመጣበት በትህትና ድል አድርጎላቸዋል፡፡ #የትዕቢትን ፈተና ማሸነፍ የሚቻለው በትሕትና ብቻ ነው! #ማቴ ፬÷ ፭- ፰ .
“ከእኔም_ተማሩ_እኔ_የዋህ_በልቤም_ትሑት_ነኝና"
#ማቴ ፲ ፩ ፥ ፳ ፱
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፬ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
________________________________
#ያዕ ፬ ፥ ፮
#፩ጴጥ ፭ ÷ ፭
ትዕቢት ከሦስቱ (አርስተ/ ርዕሰ ኃጥዐው) መካከል አንዱ ነው:: ሦስቱ ርዕሰ ኃጥዐው የሚባሉት ስስት ፣ትዕቢትና ፍቅረ ነዋይ ናቸው።
#ስስት፣ ትዕቢትና ፍቅረ ነዋይ የኃጢያት ሁሉ እራሶች ፣ አለቆች ና አውራዎች መባላቸው ኃጢያት ሁሉ ከእነዚህ ስለሚመነጭ ነው።
ዲያቢሎስ መንፈሳዊ ሰውን የሚፈትነው በሦስቱ የፈተና ዐይነቶች ነው በስስት፣ በትዕቢትና በፍቅረ ነዋይ ፤ ሌሎች የኃጢያት ዐይነቶች የነዚህ የሦስቱ ጭፍሮች ወይም ተከታዮች ናቸው።
#ለምሳሌ የትዕቢት መንፈስ የተጠናወተው አንድ ሰው እኔ ከማን አንሳለሁ የሚል የበታችነት ስሜት ውስጥ በመግባት ለግድያ ፣ለስርቆት፣ ብሎም ለዝሙት ኃጢያቶች ተጋላጭ ይሆናል።
ትዕቢት የዲያቢሎስ ልዮ መገለጫው ነው ስለሆነም ዲያቢሎስ ስለ ግብሩ ( ስለ ሥራው) ትዕቢተኛ ብቻ ሳይሆን እራሱ ትዕቢት እየተባለ ይጠራል። ለዚህ ነው ሐዋርያው እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል" ካለ በኋላ " እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤ " ሲል ትዕቢተኞች ብሎ በተውላጠ ስም የጠራቸውን ዲያቢሎስና ጭፍሮቹን አስከትሎ ደግሞ "ዲያቢሎስን" ብሎ በግልጥ የተናገረው #ያዕ ፬÷፮ - ፯
#ለዚህ ትልቁ ማሳያ የገዳመ ቆሮንቶስ ሁለተኛ ፈተና ትዕቢት የተሞላበት መሆኑ ነው "ዲያብሎስ ወደ ቅድስት ከተማ ወሰደውና (ወሰደው ሲል በፍቃዱ ሄደለት ለማለት እንጂ ለዲያቢሎስስ ታዛዢ ሆኖ አይደለም) እርሱን በመቅደስ ጫፍ ላይ አቁሞ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝልሃል እግርህንም በድንጋይ ከቶ እንዳትሰናከል በእጃቸው ያነሡሃል ተብሎ ተጽፎአልና የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ፥ ወደ ታች ራስህን ወርውር አለው። “ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ጌታን አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ደግሞ ተጽፎአል" ብሎ የትዕቢትን ፈተና በትሕትና ድል ነሳው ። የካህናት ፆራቸው ትዕቢት ነው ፤‹ ‹ እኛ አእምሮአችን ረቂቅ ማዕረጋችን ምጡቅ ›› እያሉ በትዕቢት ይፈተናሉ፡፡ ዲያብሎስ በካህናት ቦታ በቤተመቅደስ በትዕቢት ቢመጣበት በትህትና ድል አድርጎላቸዋል፡፡ #የትዕቢትን ፈተና ማሸነፍ የሚቻለው በትሕትና ብቻ ነው! #ማቴ ፬÷ ፭- ፰ .
“ከእኔም_ተማሩ_እኔ_የዋህ_በልቤም_ትሑት_ነኝና"
#ማቴ ፲ ፩ ፥ ፳ ፱
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፬ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም