“ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን #ቅዱሱን_የእግዚአብሔርን_መንፈስ አታሳዝኑ።”
| ኤፌሶን 4፥30
መቼም በዚህ በ ቲክ ታክ ዘመን እረጅምና ዝርዝር ጉዳዮችን መጻፍ እንደሞኝነት ሳይቆጠር አይቀርም ። አንድና ወጥነት ያለው ዘለግ ያለ ነገር ላይ ከመቆየት ይልቅ አጠር አጠር ያሉ ነገሮችን ለረጅም ጊዜ መከታተል የሚመረጥበት ወቅት ላይ ነን ስለዚህ ብዕሬን በአጭሩ ለማስታጠቅ እወዳለሁ።
#እግዚአብሔር_መንፈስ_ቅዱስ በየዋህቱ እርግብ ይመሰላል። እርግብ ቤት ሰርታ ከምትኖርበት ቦታዋ የፈለገ በደል ቢደርስባት ለቃ አትሄድም በድንጋይ ወርውረው ቢመቷት፣ እንቁላሎቿን ቢያፈርጡባት፣ ጫጭቶቿን ቢገሉባት ከመኖሪያዋ ጎጆ ወዴትም አትሄድም ። ሳይሰማት ሳያማት ሳይቆረቁራት ቀርቶ አይደለም የዋህ ስለሆነች ነው ። ነገር ግን ቤቷን መኖሪያዋን ያፈረሱባት እንደሆነ ላትመለስ እስከወዲያኛው ትሄዳለች።
መንፈሰ እግዚአብሔርም እንዲሁ ነው። #በአብ_በወልድ_በመንፈስ_ቅዱስ ስም አምነን አንድ ጊዜ በአርባና በሰማንያ ቀናችን ተጠምቀን ማደሪያ ቤቱ ካደረገን በኋላ መቼም መች ከኛ አይለይም። በአልዮ፣ በነቢብ ፣በገቢር ኃጢያት ብናሳዝ ነው ፤በምግባራችን ብናስከፋው ከቶ ከኛ አይርቅም። ነገር ግን አናውቅህም ብለን ከካድነው መቅደሱን ሰውነታችንን በክህደት ካፈረስንበት እንደ እርግቢቱ ጨርሶ ይለየናል።
ብዙዎች በራልን ተገለጠልን እያሉ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነውን በጥምቀት የከበረውን ቤተ ልቦናቸውን እያፈረሱ ከመንፈስ ቅዱስ ተለይተው ከፀጋ ተገፈው እንዲሁ ሲባዝኑ ማየት እየተለመደ መቷል። ድሮ ተናግረው አይደለም ገና ሳይናገሩ ሀሳባቸው የሚገባን ሳይቀልዱ የሚያስቁን በዐይናችን ፊት በሞገስ የሚገዝፉብን የጥበብ ሰዎች ዛሬ ግን ሁሉ ቀርቶ ብዙ አውርተው ጥቂቱ ንግግራቸው እንኳን የማይገባን ቀልደውልን ከማሳቅ ይልቅ የሚያናድዱን ግርማ ሞገሳቸው እርቆ ጥላ ቢስ የሆኑብን ብዙዎች እየመጡ ነው። ከነዚህ ሰዎች አንዱ አርቲስት #ሸዋፈራው_ደስአለኝ አንዱ ነው።
ሸዋን የወንዶች ጉዳይ ፣ ያረፈደ አራዳ ....ወዘተ በሚሉ ቆየት ባሉ ሥራዎቹ አስታውሰዋለው በጣም ከምወዳቸውና ከማከብራቸው ተዋንያን ግንባር ቀደሙ ነው ። ፌሽዋል ኤክስፕሬሽን የቃላት አጠቃቀም የድምጽ አወጣት ገጸ ባሕሪን መስሎ ሳይሆን ሆኖ የመጫወት ብቃት ያለው ባለ ግርማ ሞገስ ሙያተኛ ነበር ። ከጥቂት ግዝያት በኋላ ግን ያ ሁሉ ጠፍቶ ቀልዱ የማያምር ትወናው የሚያቅር ንግግሩም የሚያሳፍር እየሆነ መጣብኝ ምን እንደተፈጠረ በትክክል ባይገባኝም ዝም ብሎ ብቻ ከድሮው ቦታው እየወረደ እንደሆነ ይሰማኝ ነበር። ጌታን የተቀበለ ጴንጤ እንደሆነ ስሰማ ለዛ ይሆን ለዛውን የጣብኝ እያልኩ አስብ ነበር ፤ ከሰሞኑ ግን ከተራ ምዕመንነት አልፎ በፖስተር ደረጃ ሲሰብክ ሳይና ስሰማ ግን በእርግጥም የለዛ ቢስነቱ ምንጭ ከአርባ ቀኑ ማዕተብ ከቅዱሱ መንፈስ መለየቱ መሆኑ በእርግጥም ገባኝ።
አስቀድሜም እንዳልሁ አሁንም ደግሞ እላለሁ “ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን #ቅዱሱን_የእግዚአብሔርን_መንፈስ አታሳዝኑ።”
|ኤፌሶን 4፥30
አ.አ ኢትዮጲያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
የካቲት 27/2017 ዓ.ም
| ኤፌሶን 4፥30
መቼም በዚህ በ ቲክ ታክ ዘመን እረጅምና ዝርዝር ጉዳዮችን መጻፍ እንደሞኝነት ሳይቆጠር አይቀርም ። አንድና ወጥነት ያለው ዘለግ ያለ ነገር ላይ ከመቆየት ይልቅ አጠር አጠር ያሉ ነገሮችን ለረጅም ጊዜ መከታተል የሚመረጥበት ወቅት ላይ ነን ስለዚህ ብዕሬን በአጭሩ ለማስታጠቅ እወዳለሁ።
#እግዚአብሔር_መንፈስ_ቅዱስ በየዋህቱ እርግብ ይመሰላል። እርግብ ቤት ሰርታ ከምትኖርበት ቦታዋ የፈለገ በደል ቢደርስባት ለቃ አትሄድም በድንጋይ ወርውረው ቢመቷት፣ እንቁላሎቿን ቢያፈርጡባት፣ ጫጭቶቿን ቢገሉባት ከመኖሪያዋ ጎጆ ወዴትም አትሄድም ። ሳይሰማት ሳያማት ሳይቆረቁራት ቀርቶ አይደለም የዋህ ስለሆነች ነው ። ነገር ግን ቤቷን መኖሪያዋን ያፈረሱባት እንደሆነ ላትመለስ እስከወዲያኛው ትሄዳለች።
መንፈሰ እግዚአብሔርም እንዲሁ ነው። #በአብ_በወልድ_በመንፈስ_ቅዱስ ስም አምነን አንድ ጊዜ በአርባና በሰማንያ ቀናችን ተጠምቀን ማደሪያ ቤቱ ካደረገን በኋላ መቼም መች ከኛ አይለይም። በአልዮ፣ በነቢብ ፣በገቢር ኃጢያት ብናሳዝ ነው ፤በምግባራችን ብናስከፋው ከቶ ከኛ አይርቅም። ነገር ግን አናውቅህም ብለን ከካድነው መቅደሱን ሰውነታችንን በክህደት ካፈረስንበት እንደ እርግቢቱ ጨርሶ ይለየናል።
ብዙዎች በራልን ተገለጠልን እያሉ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነውን በጥምቀት የከበረውን ቤተ ልቦናቸውን እያፈረሱ ከመንፈስ ቅዱስ ተለይተው ከፀጋ ተገፈው እንዲሁ ሲባዝኑ ማየት እየተለመደ መቷል። ድሮ ተናግረው አይደለም ገና ሳይናገሩ ሀሳባቸው የሚገባን ሳይቀልዱ የሚያስቁን በዐይናችን ፊት በሞገስ የሚገዝፉብን የጥበብ ሰዎች ዛሬ ግን ሁሉ ቀርቶ ብዙ አውርተው ጥቂቱ ንግግራቸው እንኳን የማይገባን ቀልደውልን ከማሳቅ ይልቅ የሚያናድዱን ግርማ ሞገሳቸው እርቆ ጥላ ቢስ የሆኑብን ብዙዎች እየመጡ ነው። ከነዚህ ሰዎች አንዱ አርቲስት #ሸዋፈራው_ደስአለኝ አንዱ ነው።
ሸዋን የወንዶች ጉዳይ ፣ ያረፈደ አራዳ ....ወዘተ በሚሉ ቆየት ባሉ ሥራዎቹ አስታውሰዋለው በጣም ከምወዳቸውና ከማከብራቸው ተዋንያን ግንባር ቀደሙ ነው ። ፌሽዋል ኤክስፕሬሽን የቃላት አጠቃቀም የድምጽ አወጣት ገጸ ባሕሪን መስሎ ሳይሆን ሆኖ የመጫወት ብቃት ያለው ባለ ግርማ ሞገስ ሙያተኛ ነበር ። ከጥቂት ግዝያት በኋላ ግን ያ ሁሉ ጠፍቶ ቀልዱ የማያምር ትወናው የሚያቅር ንግግሩም የሚያሳፍር እየሆነ መጣብኝ ምን እንደተፈጠረ በትክክል ባይገባኝም ዝም ብሎ ብቻ ከድሮው ቦታው እየወረደ እንደሆነ ይሰማኝ ነበር። ጌታን የተቀበለ ጴንጤ እንደሆነ ስሰማ ለዛ ይሆን ለዛውን የጣብኝ እያልኩ አስብ ነበር ፤ ከሰሞኑ ግን ከተራ ምዕመንነት አልፎ በፖስተር ደረጃ ሲሰብክ ሳይና ስሰማ ግን በእርግጥም የለዛ ቢስነቱ ምንጭ ከአርባ ቀኑ ማዕተብ ከቅዱሱ መንፈስ መለየቱ መሆኑ በእርግጥም ገባኝ።
አስቀድሜም እንዳልሁ አሁንም ደግሞ እላለሁ “ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን #ቅዱሱን_የእግዚአብሔርን_መንፈስ አታሳዝኑ።”
|ኤፌሶን 4፥30
አ.አ ኢትዮጲያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
የካቲት 27/2017 ዓ.ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
Ethiopia: መቼ ነው ጌታ | ዘማሪ ዳዊት ክብሩ | Zemari Dawit Kibru | Mecha New Geta | New Orthodox Mezmur | መዝሙር
Ethiopia: መቼ ነው ጌታ | ዘማሪ ዳዊት ክብሩ | Zemari Dawit Kibru | Mecha New Geta | New Orthodox Mezmur | መዝሙር
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ቴሌግራም ቻናል
Telegram https://tttttt.me/Mikhadenagil
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ኢንስታግራም
Instagram https://www.instagram.com/mikhadenagil/?hl=en…
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ቴሌግራም ቻናል
Telegram https://tttttt.me/Mikhadenagil
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ኢንስታግራም
Instagram https://www.instagram.com/mikhadenagil/?hl=en…
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
በቅርብ ቀን ይጠብቁን !🙏🙏🙏
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
Track 3- ሰው የለኝም አትበል🛑የንስሓ መዝሙራት ስብስብ🛑|| ለዐቢይ ጾም || collection || በልሳነ ሱራፊ ሚዲያ የተዘጋጀ @lisanesurafi
🛑የንስሓ መዝሙራት ስብስብ🛑
ዲያቆን ባስልዮስ ወንድሙ || ዲያቆን ኢዛና ማለፉ || ዲያቆን ታሪኩ ተስፋዬ || ዲያቆን በረከት ስለሺ
ዘማሪት አርሴማ ወ/አምላክ || ዘማሪት ፍሬ ሕይወት ልደቱ || ዘማሪት ጽዮን መኩሪያ || ዘማሪት ጸዳለ አማረ
በስብስቡ የተካተቱ መዝሙራት
Track 1- ጾምን ቀድሱ
https://youtu.be/TBhYsRf6fuM?si=wO5RuIo62rUXDjv7
Track 2- ለመልካም ኾነልኝ…
ዲያቆን ባስልዮስ ወንድሙ || ዲያቆን ኢዛና ማለፉ || ዲያቆን ታሪኩ ተስፋዬ || ዲያቆን በረከት ስለሺ
ዘማሪት አርሴማ ወ/አምላክ || ዘማሪት ፍሬ ሕይወት ልደቱ || ዘማሪት ጽዮን መኩሪያ || ዘማሪት ጸዳለ አማረ
በስብስቡ የተካተቱ መዝሙራት
Track 1- ጾምን ቀድሱ
https://youtu.be/TBhYsRf6fuM?si=wO5RuIo62rUXDjv7
Track 2- ለመልካም ኾነልኝ…
#ምስጋና ቢስ ጤና
----------------------------
በሽታውን ለምዶ ለኖረ በጠና
መዳን መታመም ነው መቆየት በጤና
ሕመመ ለምዶ ለምዶ
እኸኸን ለምዶ ለምዶ
ወንጀል ይመስለዋል የዳነ ተገዶ
ከለመደው ሕመመ ካከረመው በደል
ማንም ቢነጣጠል ጸናበት ነው እንጂ
ተፈወሰ አትበል
ጤና ለራቀው ሰው ሕመም ነው ጤንነት
ከለመደው መኖር እኸኸ ከሚልበት
አለመታመም ነው የሱ መጻጉነት
ስለዚህ ወዳጄ
ማዳንን ስለቻልክ መፈወስ ስላወክ
ልፈውስ አትበለው ሕመሙን አርቀህ ጤናውን እያወክ
ያ ደጉ ጌታ እንኳ ለማዳን የመጣው
ልድን ተወዳለህ? ብሎ ያስፈቀደው
ላንዳንዱ በሽታው
ጤናው እንደሆነ አስቀድሞ አውቆ ነው
መዳን ጤና የሚሆን ላንዳንዱ ብቻ ነው
ጤናው ጤና ነስቶት በሽታ የሆነበት
ኁልቁ ሰው አለልህ ለቁጥር የሚያዳግት
ያዳነውን መድኅን ሽቅብ የሚያንጓጥጥ
ያዳነኝ ያ ሰው ነው ብሎ የጠቆመው
መድኅኑን በሰው ፊት ኮንኖ ያቆመው
ተኝቶኮ አይደለም በአልጋ ቁራኛ
መጻጉዕ ድኖ ነው የሆነ ሕመምተኛ
እናማ የታመምክም ብትሆ በአልጋ የወደክ
ጤናህን በማጣት በጅጉ የደከምክ
አታማር ግድ የለም
ያንተ ጤንነትህ በደዌክ ውስጥ ነው
መናልባት ሕመም ቀና ያልክ ቀን ነው
#ማስታወሻነቱ :- በደዌ ደኛ በአልጋ ቁራኛ ለተያዙ ሁሉ ይሁንልኝ!
#የምሕረት-እናት-ድንግል-ማርያም ምሕረቱን ትላክላችሁ:: የወይን ጠጅ አኮ የላቸውም ብሎ አዲስ የወይን ጠጅ ባሰጠ አንደበቷ ዛሬም ጤናኮ የላቸውም ብላ ከቀድሞው የበለጠ አዲሰ ጤናን ታሰጣችሁ ታሰጠን! አሜን!
አ.አ ኢትዮጵያ
ከተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
መጋቢት ፲ ፫ ቀን ፳ ፻ ፲ ፬ ዓ.ም ጥንተ ጽሕፈቱ
----------------------------
በሽታውን ለምዶ ለኖረ በጠና
መዳን መታመም ነው መቆየት በጤና
ሕመመ ለምዶ ለምዶ
እኸኸን ለምዶ ለምዶ
ወንጀል ይመስለዋል የዳነ ተገዶ
ከለመደው ሕመመ ካከረመው በደል
ማንም ቢነጣጠል ጸናበት ነው እንጂ
ተፈወሰ አትበል
ጤና ለራቀው ሰው ሕመም ነው ጤንነት
ከለመደው መኖር እኸኸ ከሚልበት
አለመታመም ነው የሱ መጻጉነት
ስለዚህ ወዳጄ
ማዳንን ስለቻልክ መፈወስ ስላወክ
ልፈውስ አትበለው ሕመሙን አርቀህ ጤናውን እያወክ
ያ ደጉ ጌታ እንኳ ለማዳን የመጣው
ልድን ተወዳለህ? ብሎ ያስፈቀደው
ላንዳንዱ በሽታው
ጤናው እንደሆነ አስቀድሞ አውቆ ነው
መዳን ጤና የሚሆን ላንዳንዱ ብቻ ነው
ጤናው ጤና ነስቶት በሽታ የሆነበት
ኁልቁ ሰው አለልህ ለቁጥር የሚያዳግት
ያዳነውን መድኅን ሽቅብ የሚያንጓጥጥ
ያዳነኝ ያ ሰው ነው ብሎ የጠቆመው
መድኅኑን በሰው ፊት ኮንኖ ያቆመው
ተኝቶኮ አይደለም በአልጋ ቁራኛ
መጻጉዕ ድኖ ነው የሆነ ሕመምተኛ
እናማ የታመምክም ብትሆ በአልጋ የወደክ
ጤናህን በማጣት በጅጉ የደከምክ
አታማር ግድ የለም
ያንተ ጤንነትህ በደዌክ ውስጥ ነው
መናልባት ሕመም ቀና ያልክ ቀን ነው
#ማስታወሻነቱ :- በደዌ ደኛ በአልጋ ቁራኛ ለተያዙ ሁሉ ይሁንልኝ!
#የምሕረት-እናት-ድንግል-ማርያም ምሕረቱን ትላክላችሁ:: የወይን ጠጅ አኮ የላቸውም ብሎ አዲስ የወይን ጠጅ ባሰጠ አንደበቷ ዛሬም ጤናኮ የላቸውም ብላ ከቀድሞው የበለጠ አዲሰ ጤናን ታሰጣችሁ ታሰጠን! አሜን!
አ.አ ኢትዮጵያ
ከተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
መጋቢት ፲ ፫ ቀን ፳ ፻ ፲ ፬ ዓ.ም ጥንተ ጽሕፈቱ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
🔴አዲስ ዝማሬ🔴ሰው ያጣ(መጻጉዕ) ዘማሪት ሲስተር #ሕይወት ተፈሪ እና ዘማሪት መቅደላዊት በላቸው#ናና አማኑኤል@AbiStudio117
This is an Ethiopian Orthodox Church song which tells about the 4th Sunday of Abiy fasting. On this day the Church has preached our Lord Jesus had cured many people who had infirmity.
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
አዲስ ዝማሬ "ምራኝ" ዘማሪት ማርያማዊት ሳምሶን | "Meragn" By Zemarit Mariamawit Samson
ዘጎላ ሬከርድስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መዝሙራትን ዶግማ፣ቀኖና እና ትውፊት በመጠበቅ እና በማስተዋወቅ ወደ ዲጂታል ዓለም ለማምጣት ይሰራል።
#zegola_records #mezmur #orthodox #መዝሙር #ኦርቶዶክስ_መዝሙር #ዘጎላ_ሬከርድስ
ምራኝ
ጌታ ሆይ መንገድህን ምራኝ ፍለጋህንም አስተምረኝ
የመድኀኒቴ አምላክ ቃልህ ምርኩዝ ይሁነኝ
- - - - - - - + + + - - …
#zegola_records #mezmur #orthodox #መዝሙር #ኦርቶዶክስ_መዝሙር #ዘጎላ_ሬከርድስ
ምራኝ
ጌታ ሆይ መንገድህን ምራኝ ፍለጋህንም አስተምረኝ
የመድኀኒቴ አምላክ ቃልህ ምርኩዝ ይሁነኝ
- - - - - - - + + + - - …
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
ወንድም እህቶቼ መንፈሳዊ አገልግሎት ለሁላችን ጠቃሚ ነውና የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ ወንድም እህቶቼ ሁላችሁ ይህንን ዝማሬዎቼን የምለጥፍበትን የዩትዩብ ገጼን በመቀላቀልና በመከታተል ሌሎች እንዲቀላቀሉኝ በማድረግና በማስደረግ ለአገልግሎቱ ኀይል ይሁኑኝ ድጋፍ ያድርጉልኝ እግዚአብሔር ያክብርልኝ!🙏🙏🙏
https://youtube.com/@zemaridawitkibru2405?si=XABE7A5j_OybqfK5
#subscribe
#share
#like
#forfriends
#forfamily
@zdk24_5_21_official
https://youtube.com/@zemaridawitkibru2405?si=XABE7A5j_OybqfK5
#subscribe
#share
#like
#forfriends
#forfamily
@zdk24_5_21_official
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
መኑ ውእቱ ገብር ኄር ወምእመን ዘይረክቦ እግዚኦ በምግባረ ሠናይ ወይሰይሞ ዲበኲሉ"
"ጌታው በበጎ ሥራ የሚያገኘውና በገንዘቡ ሁሉ ላይ የሚሾመው ቸርና ታማኝ አገልጋይ ማነው ?"
ማቴ ፳፭ ÷ ፲፬-፴፩
እህት ወንድሞቼ እግዚአብሔር ቢፈቅድ በዕለተ ቅዳሜ በገብር ኄር ዋዜማ ለሳምንቱ በሚስማማ ዝማሬ ስለምንገናኝ እንዲጠብቁኝ ስንል በእግዚአብሔር ስም እጠይቃለው !
"በጥቂት ልታመን"
ዘማሪ ዳዊት ክብሩ
ግጥም
ዘማሪ ዳዊት ክብሩ
ዜማ
ዘማሪ ዲ/ን ዘላለም ታከለ
ድምጽ ቀረጻና ማስተሪንግ
ዘጎላ ሬከርድስ
እስከምንገናኝ ቻናሉን ሰብስክራይብ በማድረግና በማስደረግ ያግዙኝ !🙏
👇👇👇
https://youtube.com/@zemaridawitkibru2405?si=XABE7A5j_OybqfK5
"ጌታው በበጎ ሥራ የሚያገኘውና በገንዘቡ ሁሉ ላይ የሚሾመው ቸርና ታማኝ አገልጋይ ማነው ?"
ማቴ ፳፭ ÷ ፲፬-፴፩
እህት ወንድሞቼ እግዚአብሔር ቢፈቅድ በዕለተ ቅዳሜ በገብር ኄር ዋዜማ ለሳምንቱ በሚስማማ ዝማሬ ስለምንገናኝ እንዲጠብቁኝ ስንል በእግዚአብሔር ስም እጠይቃለው !
"በጥቂት ልታመን"
ዘማሪ ዳዊት ክብሩ
ግጥም
ዘማሪ ዳዊት ክብሩ
ዜማ
ዘማሪ ዲ/ን ዘላለም ታከለ
ድምጽ ቀረጻና ማስተሪንግ
ዘጎላ ሬከርድስ
እስከምንገናኝ ቻናሉን ሰብስክራይብ በማድረግና በማስደረግ ያግዙኝ !🙏
👇👇👇
https://youtube.com/@zemaridawitkibru2405?si=XABE7A5j_OybqfK5
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
አዲሱ ዝማሬዬ ተለቋል ሁላችሁም ታደምጡት ዘንድ እጋብዛለሁ
#Like
#Share
#subscribe
እያደረጋችሁ !🙏🙏🙏
https://youtu.be/M_ZR9bucn4c?si=uDIWo_H0cc6sQZ_d
#Like
#Share
#subscribe
እያደረጋችሁ !🙏🙏🙏
https://youtu.be/M_ZR9bucn4c?si=uDIWo_H0cc6sQZ_d
YouTube
🔴አዲስ ዝማሬ "በጥቂት ልታመን" በዘማሪ ዳዊት ክብሩ | The Hidden Wealth of Ethiopian Mezmur Dn_Mhiret_Melaku_Harvard
በጥቂት ልታመን
በጥቂት ልታመን ፍቃድኽን ልፈጽም
ሕግህን በልቤ ላትመው ላድርግም
ወደጌታህ ተድላ ግባ እንድትለኝ
አቤቱ አምላኬ በጎ ትጋት ስጠኝ
የሰጠኸኝን ጸጋ መንዝሬው ፈቅጄ
አበዛው እንደሆን ያለኝን ወድጄ
ቃልህ ስለሆነ በተድላህ እንድትሾመኝ
አንተ ታማኝ ባርያ አትርፈሃል በለኝ
መከራን መቀበል እንዲሆን መንገዴ
ተላልፎ መሰጠት ውጥኑ መውደዴ
ባልጀራዬንም ከፍርድ ቀንበር ላርቅ
ሥጦታን ላበዛ ልመላለስ…
በጥቂት ልታመን ፍቃድኽን ልፈጽም
ሕግህን በልቤ ላትመው ላድርግም
ወደጌታህ ተድላ ግባ እንድትለኝ
አቤቱ አምላኬ በጎ ትጋት ስጠኝ
የሰጠኸኝን ጸጋ መንዝሬው ፈቅጄ
አበዛው እንደሆን ያለኝን ወድጄ
ቃልህ ስለሆነ በተድላህ እንድትሾመኝ
አንተ ታማኝ ባርያ አትርፈሃል በለኝ
መከራን መቀበል እንዲሆን መንገዴ
ተላልፎ መሰጠት ውጥኑ መውደዴ
ባልጀራዬንም ከፍርድ ቀንበር ላርቅ
ሥጦታን ላበዛ ልመላለስ…
#የዕውቀት_ማኅሌታይ
___
ድንቁርናን ገዳይ ዕውቀትን አክባሪ
የጨረቃ ወዳጅ የሌሊት ተማሪ
ገማልያል ኦሪትን ግዝረት ቢያስተምረው
ክርስቶስ በሌሊት ጥምቀትን ነገረው
ከውኃ ከመንፈስ ተወለድ እያለው
ብሉያት ከሐዲሳት የተባበሩለት
ኒቆዲሞስ ምሁር ልክ ያልተገኘለት
የሌሊት ተማሪ የዕውቀት ማኅሌታይ
ቀን ቀን አስተማሪ ሲያበራ የሚታይ
መጫወቱን ትተ ቆመን ከመንገድ
ተማር ይልቅ አንተ እንድትወደድ
ብለው እንደመከሩን አበው ቀደምት
እንቅሰም ሳንሰለች የአብነት ትምህርት
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጥንተ ጽሕፈቱ #ሚያዝያ ፩ ቀን ፳ ፻ ፲ ፬ ዓ.ም
___
ድንቁርናን ገዳይ ዕውቀትን አክባሪ
የጨረቃ ወዳጅ የሌሊት ተማሪ
ገማልያል ኦሪትን ግዝረት ቢያስተምረው
ክርስቶስ በሌሊት ጥምቀትን ነገረው
ከውኃ ከመንፈስ ተወለድ እያለው
ብሉያት ከሐዲሳት የተባበሩለት
ኒቆዲሞስ ምሁር ልክ ያልተገኘለት
የሌሊት ተማሪ የዕውቀት ማኅሌታይ
ቀን ቀን አስተማሪ ሲያበራ የሚታይ
መጫወቱን ትተ ቆመን ከመንገድ
ተማር ይልቅ አንተ እንድትወደድ
ብለው እንደመከሩን አበው ቀደምት
እንቅሰም ሳንሰለች የአብነት ትምህርት
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጥንተ ጽሕፈቱ #ሚያዝያ ፩ ቀን ፳ ፻ ፲ ፬ ዓ.ም