ዐውደ ምሕረት
3.67K subscribers
932 photos
24 videos
271 files
195 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
“ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን #ቅዱሱን_የእግዚአብሔርን_መንፈስ አታሳዝኑ።”
| ኤፌሶን 4፥30

መቼም በዚህ በ ቲክ ታክ ዘመን እረጅምና ዝርዝር ጉዳዮችን መጻፍ እንደሞኝነት ሳይቆጠር አይቀርም ። አንድና ወጥነት ያለው ዘለግ ያለ ነገር ላይ ከመቆየት ይልቅ አጠር አጠር ያሉ ነገሮችን ለረጅም ጊዜ መከታተል የሚመረጥበት ወቅት ላይ ነን ስለዚህ ብዕሬን በአጭሩ ለማስታጠቅ እወዳለሁ።
#እግዚአብሔር_መንፈስ_ቅዱስ በየዋህቱ እርግብ ይመሰላል። እርግብ ቤት ሰርታ ከምትኖርበት ቦታዋ የፈለገ በደል ቢደርስባት ለቃ አትሄድም በድንጋይ ወርውረው ቢመቷት፣ እንቁላሎቿን ቢያፈርጡባት፣ ጫጭቶቿን ቢገሉባት ከመኖሪያዋ ጎጆ ወዴትም አትሄድም ። ሳይሰማት ሳያማት ሳይቆረቁራት ቀርቶ አይደለም የዋህ ስለሆነች ነው ። ነገር ግን ቤቷን መኖሪያዋን ያፈረሱባት እንደሆነ ላትመለስ እስከወዲያኛው ትሄዳለች።
መንፈሰ እግዚአብሔርም እንዲሁ ነው። #በአብ_በወልድ_በመንፈስ_ቅዱስ ስም አምነን አንድ ጊዜ በአርባና በሰማንያ ቀናችን ተጠምቀን ማደሪያ ቤቱ ካደረገን በኋላ መቼም መች ከኛ አይለይም። በአልዮ፣ በነቢብ ፣በገቢር ኃጢያት ብናሳዝ ነው ፤በምግባራችን ብናስከፋው ከቶ ከኛ አይርቅም። ነገር ግን አናውቅህም ብለን ከካድነው መቅደሱን ሰውነታችንን በክህደት ካፈረስንበት እንደ እርግቢቱ ጨርሶ ይለየናል።

ብዙዎች በራልን ተገለጠልን እያሉ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነውን በጥምቀት የከበረውን ቤተ ልቦናቸውን እያፈረሱ ከመንፈስ ቅዱስ ተለይተው ከፀጋ ተገፈው እንዲሁ ሲባዝኑ ማየት እየተለመደ መቷል። ድሮ ተናግረው አይደለም ገና ሳይናገሩ ሀሳባቸው የሚገባን ሳይቀልዱ የሚያስቁን በዐይናችን ፊት በሞገስ የሚገዝፉብን የጥበብ ሰዎች ዛሬ ግን ሁሉ ቀርቶ ብዙ አውርተው ጥቂቱ ንግግራቸው እንኳን የማይገባን ቀልደውልን ከማሳቅ ይልቅ የሚያናድዱን ግርማ ሞገሳቸው እርቆ ጥላ ቢስ የሆኑብን ብዙዎች እየመጡ ነው። ከነዚህ ሰዎች አንዱ አርቲስት #ሸዋፈራው_ደስአለኝ አንዱ ነው።
ሸዋን የወንዶች ጉዳይ ፣ ያረፈደ አራዳ ....ወዘተ በሚሉ ቆየት ባሉ ሥራዎቹ አስታውሰዋለው በጣም ከምወዳቸውና ከማከብራቸው ተዋንያን ግንባር ቀደሙ ነው ። ፌሽዋል ኤክስፕሬሽን የቃላት አጠቃቀም የድምጽ አወጣት ገጸ ባሕሪን መስሎ ሳይሆን ሆኖ የመጫወት ብቃት ያለው ባለ ግርማ ሞገስ ሙያተኛ ነበር ። ከጥቂት ግዝያት በኋላ ግን ያ ሁሉ ጠፍቶ ቀልዱ የማያምር ትወናው የሚያቅር ንግግሩም የሚያሳፍር እየሆነ መጣብኝ ምን እንደተፈጠረ በትክክል ባይገባኝም ዝም ብሎ ብቻ ከድሮው ቦታው እየወረደ እንደሆነ ይሰማኝ ነበር። ጌታን የተቀበለ ጴንጤ እንደሆነ ስሰማ ለዛ ይሆን ለዛውን የጣብኝ እያልኩ አስብ ነበር ፤ ከሰሞኑ ግን ከተራ ምዕመንነት አልፎ በፖስተር ደረጃ ሲሰብክ ሳይና ስሰማ ግን በእርግጥም የለዛ ቢስነቱ ምንጭ ከአርባ ቀኑ ማዕተብ ከቅዱሱ መንፈስ መለየቱ መሆኑ በእርግጥም ገባኝ።

አስቀድሜም እንዳልሁ አሁንም ደግሞ እላለሁ “ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን #ቅዱሱን_የእግዚአብሔርን_መንፈስ አታሳዝኑ።”
|ኤፌሶን 4፥30

አ.አ ኢትዮጲያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
የካቲት 27/2017 ዓ.ም
በቅርብ ቀን ይጠብቁን !🙏🙏🙏
#ምስጋና ቢስ ጤና
----------------------------

በሽታውን ለምዶ ለኖረ በጠና
መዳን መታመም ነው መቆየት በጤና

ሕመመ ለምዶ ለምዶ
እኸኸን ለምዶ ለምዶ
ወንጀል ይመስለዋል የዳነ ተገዶ

ከለመደው ሕመመ ካከረመው በደል
ማንም ቢነጣጠል ጸናበት ነው እንጂ
ተፈወሰ አትበል


ጤና ለራቀው ሰው ሕመም ነው ጤንነት
ከለመደው መኖር እኸኸ ከሚልበት
አለመታመም ነው የሱ መጻጉነት

ስለዚህ  ወዳጄ
ማዳንን ስለቻልክ መፈወስ ስላወክ
ልፈውስ አትበለው ሕመሙን አርቀህ ጤናውን እያወክ


ያ ደጉ ጌታ እንኳ ለማዳን የመጣው
ልድን ተወዳለህ? ብሎ ያስፈቀደው
ላንዳንዱ በሽታው
ጤናው  እንደሆነ አስቀድሞ አውቆ ነው
መዳን ጤና የሚሆን ላንዳንዱ ብቻ ነው

ጤናው ጤና ነስቶት በሽታ የሆነበት
ኁልቁ ሰው አለልህ ለቁጥር የሚያዳግት
ያዳነውን መድኅን ሽቅብ የሚያንጓጥጥ
ያዳነኝ ያ ሰው ነው ብሎ የጠቆመው
መድኅኑን በሰው ፊት ኮንኖ ያቆመው
ተኝቶኮ አይደለም በአልጋ ቁራኛ
መጻጉዕ ድኖ ነው የሆነ ሕመምተኛ

እናማ የታመምክም ብትሆ በአልጋ የወደክ
ጤናህን በማጣት በጅጉ የደከምክ
አታማር ግድ የለም
ያንተ ጤንነትህ በደዌክ ውስጥ ነው
መናልባት ሕመም ቀና ያልክ ቀን ነው

#ማስታወሻነቱ :- በደዌ ደኛ በአልጋ ቁራኛ ለተያዙ ሁሉ ይሁንልኝ!

#የምሕረት-እናት-ድንግል-ማርያም  ምሕረቱን ትላክላችሁ:: የወይን ጠጅ አኮ የላቸውም ብሎ አዲስ የወይን ጠጅ ባሰጠ አንደበቷ ዛሬም ጤናኮ የላቸውም ብላ ከቀድሞው የበለጠ አዲሰ ጤናን ታሰጣችሁ ታሰጠን! አሜን!

አ.አ ኢትዮጵያ
ከተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
መጋቢት ፲ ፫ ቀን ፳ ፻ ፲ ፬ ዓ.ም ጥንተ ጽሕፈቱ
ወንድም እህቶቼ መንፈሳዊ አገልግሎት ለሁላችን ጠቃሚ ነውና የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ ወንድም እህቶቼ ሁላችሁ ይህንን ዝማሬዎቼን የምለጥፍበትን የዩትዩብ ገጼን በመቀላቀልና በመከታተል ሌሎች እንዲቀላቀሉኝ በማድረግና በማስደረግ ለአገልግሎቱ ኀይል ይሁኑኝ ድጋፍ ያድርጉልኝ እግዚአብሔር ያክብርልኝ!🙏🙏🙏

https://youtube.com/@zemaridawitkibru2405?si=XABE7A5j_OybqfK5

#subscribe
#share
#like
#forfriends
#forfamily

@zdk24_5_21_official
መኑ ውእቱ ገብር ኄር ወምእመን ዘይረክቦ እግዚኦ በምግባረ ሠናይ ወይሰይሞ ዲበኲሉ"


"ጌታው በበጎ ሥራ የሚያገኘውና በገንዘቡ ሁሉ ላይ የሚሾመው ቸርና ታማኝ አገልጋይ ማነው ?"
ማቴ ፳፭ ÷ ፲፬-፴፩

እህት ወንድሞቼ እግዚአብሔር ቢፈቅድ በዕለተ ቅዳሜ በገብር ኄር ዋዜማ ለሳምንቱ በሚስማማ ዝማሬ ስለምንገናኝ እንዲጠብቁኝ ስንል በእግዚአብሔር ስም እጠይቃለው !

     "በጥቂት ልታመን"
       ዘማሪ ዳዊት ክብሩ

             ግጥም
       ዘማሪ ዳዊት ክብሩ

                ዜማ
       ዘማሪ ዲ/ን ዘላለም ታከለ

       ድምጽ  ቀረጻና ማስተሪንግ
              ዘጎላ ሬከርድስ


እስከምንገናኝ ቻናሉን  ሰብስክራይብ በማድረግና በማስደረግ ያግዙኝ !🙏
            👇👇👇
https://youtube.com/@zemaridawitkibru2405?si=XABE7A5j_OybqfK5
#የዕውቀት_ማኅሌታይ
___

ድንቁርናን ገዳይ ዕውቀትን አክባሪ
የጨረቃ ወዳጅ የሌሊት ተማሪ
ገማልያል ኦሪትን ግዝረት ቢያስተምረው
ክርስቶስ በሌሊት ጥምቀትን ነገረው
ከውኃ ከመንፈስ ተወለድ እያለው
ብሉያት ከሐዲሳት የተባበሩለት
ኒቆዲሞስ ምሁር ልክ ያልተገኘለት
የሌሊት ተማሪ የዕውቀት ማኅሌታይ
ቀን ቀን አስተማሪ ሲያበራ የሚታይ
መጫወቱን ትተ ቆመን ከመንገድ
ተማር ይልቅ አንተ እንድትወደድ
ብለው እንደመከሩን አበው ቀደምት
እንቅሰም ሳንሰለች የአብነት ትምህርት

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጥንተ ጽሕፈቱ #ሚያዝያ ፩ ቀን ፳ ፻ ፲ ፬ ዓ.ም
#ሆሣዕና በአርያም
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
“የሚቀድሙትም ሕዝብ የሚከተሉትም፦ ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር።”
#ማቴዎስ 21፥9
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿