ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
930 photos
24 videos
271 files
193 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
ባለ ታሪክ ኃያሉ ሶምሶም

#ለፍቅር_የተከፈለ መሰዋህትነት

ሶምሶም ከተወለደ ጀምሮ በእራሱ ላይ ምላጭ አርፎበት የማያውቅ የእግዚአብሔር ኃይል በጸጉሩ ላይ ያደረበት እስራኤላውያንን ይጠብቁ ዘንድ ከተነሱ መሳፍንት መካከል ኃያሉ ናዝራዊ ሰው ነበር ::

ከዚህም በኋላ በሶሬቅ ሸለቆ የነበረች ደሊላ የተባለች አንዲት ሴትን ወደደ። የፍልስጥኤማውያንም መኳንንት ወደ እርስዋ ወጥተው፦ እርሱን ሸንግለሽ በእርሱ ያለ ታላቅ ኃይል በምን እንደ ሆነ፥ እኛስ እርሱን ለማዋረድ እናስረው ዘንድ የምናሸንፈው በምን እንደ ሆነ እወቂ፤ እኛም እያንዳንዳችን ሺህ አንድ መቶ ብር ሺህ አንድ መቶ ብር እንሰጥሻለን አሏት።


ደሊላም ሶምሶምን ይህ ከሰው ሁሉ ልዮ የሚያደርግህ የኃይል ምሥጢር ምንድን ነው ? ከወደድከኝ ንገረኝ እያለች ዕለት ዕለት ትነዘንዘው ጀመር ። መጻሕፍ ቅዱስ እንደውም ይህን ንዝነዛዋን እንዲ ሲል ይገልጠዋል “ዕለት ዕለትም በቃልዋ ነዘነዘችው አስቸገረችውም፥ ነፍሱም እስከ ሞት ድረስ ተጨነቀች”መሳ 16፥16

ሶምሶም ከደሊላ ምሥጢር ከሚያስወጣ ጥያቄዋ ለማምለጥ የራሱን ጥረት አድርጓል:: በእርጥብ ጠፈር ብታስሪኝ፣ በአዲስ ገመድም ብትቋጥሪኝ፣ የእራስ ፀጉሬን በችንካር ብትቸነክሪው ኃይሌ ከእኔ ይጠፋል እንደ ሌላም ሰው እሆናለሁ እያለ ምሥጢርም ሳያወጣ ደሊላንም ሳያጣ እስከ ጊዜው ለመቆየት ችሎ ነበር :: “ልባም ሴት ለባልዋ ዘውድ ናት፤ አሳፋሪ ሴት ግን በአጥንቱ ውስጥ እንደ ቅንቅን ናት።” ምሳሌ 12፥4 እንዲል መጻሕፍ አንተ፦ እወድሻለሁ እንዴት ትለኛለህ፥ ልብህ ከእኔ ጋር አይደለም? ስታታልለኝ ይህ ሦስተኛ ጊዜህ ነው፥ ታላቅ ኃይልህም በምን እንደ ሆነ አልነገርኸኝም አለችው። ዕለት ዕለትም በቃልዋ ነዘነዘችው አስቸገረችውም፥ ነፍሱም እስከ ሞት ድረስ ተጨነቀች።

ንዝነዛዋ የበዛበት ሶምሶም የልቡን ሁሉ ገለጠላት የኃይሉ ምንጭ ጸጉሩ እንደሆነና ጸጎሩን ቢላጭ ኃይሉ ከእርሱ እደሚርቅ ነገራት ደሊላም የልቡን ሁሉ እንደገለጠላት ባየች ጊዜ በጕልበትዋ ላይ አስተኛችው በተኛበትም፤ አንድ ሰውም ጠራች፥ እርሱም ሰባቱን የራሱን ጕንጕን (ቁንድላ) ላጨው። ልታዋርደውም ጀመረች፥ ኃይሉም ከእርሱ ሄደ።” ከተኛበት ቀስቅሳም ሶምሶም ሆይ ፍልስጤማውያን መጡብህ አለችው ተነስቼ እንደ ቀድሞ እሆናለው ቢል ኃይል ከእርሱ እርቆልና አንዱን በጡጫ ሌላውን በርግጫ ማለት ተሳነው::ሶምሶምም ለምርኮ ተዳረገ ፍልስጥኤማውያንም ይዘው ዓይኖቹን አወጡት፤ ወደ ጋዛም አምጥተው በናስ ሰንሰለት አሰሩት፤ በግዞትም ሆኖ እህል ይፈጭ ነበር። መሳፍ 16፥21


በጣም ያሳዝናል ሶምሶም ስለ ሴት ፍቅር ሲል ፍቅር እግዚአብሔርን አጥቶታል ኃይሉም ከእርሱ እርቆ ዐይኖቹ ወጥተው ለግዞትም ተዳርጓል

👉ወንድሞች ሶምሶምን ብትሆኑ ምን ታደርጉ ነበር! ?
*ስለ ወደዳችዋት ሴት ምሥጢሩን ታወጡ ነበር?
👉እህቶችስ ደሊላን ብትሆኑ ምን ታደርጉ ነበር?
*ለገንዘብ ብላችሁ ሶምሶምን ትከዱትና ታዋርዱት ነበርን?

እርሶ ቢሆኑ ምን ያደርጋሉ?
#ለነፃ_ሀሳብዎ_እነዚህን_ይጠቀሙ
👇👇👇👇
@Abenma
@YEAWEDIMERITE

🤦‍♀ደሊላና ሶምሶም ዛሬም በጸጸት ሆነው ሀሳቦቻችሁን እየጠበቁ ነው🤦‍♂


#ዓውደ_ምሕረት_የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
👆👆👆👆👆👆
እኔ ደሊላን ብሆን ለገንዘብ ብዬ አልክደዉም ምክንያቱም ብር አላፊ ጠፊ ነው ስለዚህ እሱን ከምክድ ገንዘቡን ቢቀርብኝ እመርጣለሁ
ሰላም ለእናንተ የክርስቶስ ቤተሰቦች የእማምላክ ወዳጆች በያላችሁበት ሰላማችሁ ብዝት ይበል

እኔ ደሊላ ብሆን ለገንዘብ ብዬ ሶምሶምን አሳልፌ አልሰጠውም ፍልስጤማውያንም እጅጉን ቢያስቸግሩኝ ሊገድሉኝም ቢመጡ እንኳን ሶምሶን የእግዚአብሔር ሀይል ስላለው ይከላከልልኛል ።

ፀጋውን ለማወቅ ፈልጌ እጠይቀዋለሁ ቢነግረኝ ባነግረኝም ግን በምንም ምክንያት አሳልፌ አልሰጠውም ።
#ኃበ_ብዙኃን_አባታችን_አብርሃም ደግሶ ያበላቸው ዘንድ እንደ ወትሮው ይጠብቅ የነበረው ብዙ ሰዎችን ነበር።
ጸላዬ ሰናያት የበጎ ነገር ሁሉ ጠላት ዲያቢሎስ ግን ከመንገድ ቆሞ እራሱን በምትአት ገምሶ ደሙን አፍስሶ እያንጠባጠበ ወደ አብርሃም የሚመጡትን እንግዶች የድሮ አብርሃም ያለ መስሏችሁ ወደ አብርሃም አትሂዱ አብርሃም የድሮ ደግነቱን ትቷል።
#ይህው_እኔም እንደ ወትሮው መስሎኝ ያበላኛል ያጠጣኛል ብዬ ወደ እርሱ ብሄድ እራሴን ገምሶ ደሜን አፍሶ መለሰኝ ይላቸው ጀመር ። ሕዝቡም መቼም ደግ ሰው አይበረክትም እያሉ እያዘኑ ተመለሱ።
#ምስኪኑ_አብርሃም ግን እነርሱ መጥተው ሳይበሉማ እኔ አልበላም ብሎ ሳይበላ ፣ሳይጠጣ ከነገ ዛሬ ይመጣሉ እያለ ሦስት ቀን በተስፋ ጠበቃቸው ማንም ግን ዝር አላለም።
በሦስተኛው ቀን በቀትር ሰዓት ከድንኳኑ በር ቁጭ ብሎ ሳለ ከመምሬ የአድባር ዛፍ ሥር ሦስት ሽማግሌ ሰዎችን ተመለከተ ሰው የተራቡ አይኞቹም በደስታ ተሞሉ ሰው መቀበል የለመዱ እጆቹ ተዘረጉ እግሮቹም ወደ ፊት ሮጡ። በቀረባቸውም ጊዜ ስለ ግርማቸው ከፊታቸው ተምበርክኮ ሰገደላቸው።
#ጥቂት_ውኃ ይምጣላችሁ፥ እግራችሁን ታጠቡ፥ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ፤ ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፥ ልባችሁንም ደግፋ ከዚያም በኋላ ትሄዳላችሁ፤ ስለዚህ ወደ ባሪያችሁ መጥታችኋልና ። እነርሱም፦ እንዳልህ አድርግ አሉት።
አብርሃምም ወደ ድንኳን ወደ ሣራ ዘንድ ፈጥኖ ገባና፦ ሦስት መስፈሪያ የተሰለቀ ዱቄት ፈጥነሽ አዘጋጂ፥ ለውሺውም፥ እንጎቻም አድርጊ አላት።
#አብርሃምም ወደ ላሞቹ ሮጠ፥ እጅግ የሰባም ታናሽ ጥጃ ያዘና ለብላቴናው ሰጠው፥ ያዘጋጅም ዘንድ ተቻኰለ። እርጎና ወተትም ያዘጋጀውንም ጥጃ አመጣ፥ በፊታቸውም አቀረበው፤ እርሱም ከዛፉ በታች በፊታቸው ቆሞ ነበር፥ እነርሱም በሉ። የዛሬ ዓመትም ልጅ በመስጠት ወደእርሱ በረድኤት እንደሚመጡ ቃል ገብተውለት ተሰናብተውት ሄዱ ።

ሰው ብቀህ ሰው ቀርቶብ ብዙ ጊዜ ሐዝነህ ታውቅ ይሆናል ነገር ግን ሁል ጊዜ ሰው ሲቀር እግዚአብሔር ይመጣልና ሰው በቀረብህ ጊዜ ደስ ይበልህ! ሰው በዲያቢሎስ የሐሰት ወሬና ምክር ከመንገድ ሊቀር ይችላል ሰው ቀረ ብለህ ግን የቀደመ ልማድህን አትተው ሳትበላ የምጠብቃቸው ከሆነ ቢመጡም ቢቀሩም ሳትበላ ጠብቃቸው እነርሱ ቢቀሩ ሥላሴ አይቀሩምና! ግን ወዳጄ ሥላሴ ሲመጡ እኔ ሥላሴ ነኝ እያሉ ላይመጡ ይችላሉ ።

#የተቀዳደደ ልብስ ለብሰው ጎልዳፉ አንደበት ይዘው አንድ ወይም ሦስት ሆነው ሊመጡ ይችላሉ ያን ጊዜ በእነርሱ ደስ ብሎህ ለሌላው የምታደርገውን ሳታጓድል አድርገህ ደስ አሰኝተህ ላካቸው እንጂ እኔ የጠራሁት ነጭ ለባሽ የመጣብኝ ብጣሽ ለባሻ ብለት ከመቀበል ወደ ኋላ አትበል። "ተርቤ አላበላህኝም፥ ተጠምቼ አላጠጣህኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበልከኝምና " ትባለለህና #ማቴ 24÷42

“ የወንድማማች መዋደድ ይኑር። #እንግዶችን_መቀበል አትርሱ፤ #በዚህ_አንዳንዶች_ሳያውቁ_መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና።” #ዕብ 13፥1-2
" ሰው ሲቀር እግዚአብሔር ይመጣል! "
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክ ኤል ኃ ማርያም
ሐምሌ ፯/ቀን ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
#ይህን ያለው ሻለቃ ኃይለ ገብረ ሥላሴ አይደለም ። እንዲ ያለው የደማስቆው ሯጭ ቅዱስ ጳውሎስ ነው ። “በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።” #1ኛ ቆሮ 9፥24 ክርስቲያኖች የዚህች ዓለም ዙር እስኪያልቅ ድረስ በትጋት እና በውድድር መንፈስ መሮጥ አለባቸው ። ያሸነፉ ሁሉ እንጂ የሮጡ ሁሉ ጥሩ ዋጋን አይሸለሙም። “ እላችኋለሁና ጽድቃችሁ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን ጽድቅ ካልበለጠ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።” #ማቴ 5፥20 በእርግጥ የኑሮ ሩጫ ለየ ቅል ነው እግዚአብሔር ወንዱን ከሴቱ ሕጻኑን ከአዋቂው ደምሮ በአንድ መስፈርት አያወዳድርም ለሁሉም እንደስራው መደብ በጽድቅ ይፈርድለታል እንጂ። ጻድቁ ወደፊት ይጽደቅ ቅዱሱም ወደፊት ይቀደስ ጠማማውም ወደ ፊት ይጥመም "እነሆ በቶሎ እመጣለሁ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍለው ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ዘንድ አለ እንዳለ ራእይ .ዮሐ22÷12

#ቅዱስ_ጳውሎስ ምርጥ ዕቃዬ ከመባሉ በፊት ሳዉል ይባል ነበር። ሁል ጊዜ ለኦሪት ሕግ የሚቀና ስለነበር ክርስቶስን እንከተላለን የሚሉ ክርስቲያኖች ሲመጡ ከኦሪቷ ሕግ ያፈነገጡ ስለመሰለው እነርሱን ያጠፉ ዘንድ ሌሊትና ቀን ሳይታክት ተሯሩጧል ። #ሐዋ 8፥3

ክርስቲያኖችን ለማሰር ብዙ ጊዜ ሮጧል፤ ክርስቲያኖችን ለማስደብደብ ብዙ ጊዜ ጥሯል፤ ክርስቲያኖችን ለማሳደድ ብዙ ጊዜ ሽምጥ ጋልቧል፤ክርስቲያኖችም በድንጋይ ተወግረው ሲሞቱ የገዳዮችን ልብሶች በደስታ ጠብቆል። ሳውል በዚህ ነገር ሁሉ ሮጧል ግን በምድርም ሆነ በሰማይ ኒሻን የሚሸልመው አልነበረም።

#በመጨረሻ ግን ክርስቲያኖችን ጨርሶ ይፈጅ ዘንድም የፍቃድ ደብዳቤ ሊያጽፍ ወደ ደማስቆ ሽምጥ ጋለበ በአጥፊነት መንፈስም ሮጠ #ሐዋ 9÷15

ወደ ከተማዋ ሲገባ ግን በታላቅ ብርሃን ተመታ ከፈረሱም ወድቆ ከብርሃኑ ጸዳል የተነሳ ዐይኑ ታውሮ ማየት ተሳነው ወዲያውም ሳውል ሳውል ስለምን ታሳድደኛለህ የሚል ቃል ሰማ።

#የማሳድድህ_አንተ ማነህ ? ብሎ ጠየቀ የምታሳድደኝ የናዝሬቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ የመውጊያውን ብረት ብትረግጥ ላንተ ይብስብሃል አለው ሳውልም ጌታ ሆይ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ አለው ወደ ደማስቆም ግባ ሐናንያ የሚባል የእግዚአብሔር ሰው ታገኛለህ እርሱ ይፈውስሃል አለው ።

ሳዉልም ከምድር ተነሳ ዐይኖቹም እንደታወሩ ነበሩ እየመሩም ወደ ከተማዋ አገቡት ለሐናንያም የጠርሴስ ሰው ሳውል ወደ እርሱ እንደሚመጣ በራዕይ ተነገረው ።

#ሐናንያ_ግን ስለ ሳውል ክፋት ብዙ ይሰማ ነበርና እንዴት እፈውሰው ዘንድ ይገባልን አለው ። ጌታም ይህ በአሕዛብም በነገሥታትም በእስራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤ ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁና አለው። #ሐዋ 9÷ 13-15

#እግዚአብሔር እንዲህ ነው እያሳደድከውም ይወድሃል እየገደልከው ያኖርሃል እያሰርከው ይፈታሃል እየሸሸህው በፍቅር ይከተልሃል ሰዎች እንደ ሸክም ሲቆጥሩህ ሁሉን ቻይ ትከሻህ ያለው ይሆናል ብሎ ይመሰክርልሃል ሰው ኃጢያተኛ እያለህ እርሱ ግን ምርጤ ይልሃል። #እግዚአብሔር እንዲህ ነው!
ሐናንያም ሄዶ ወደ ቤቱ ገባ፥ እጁንም ጭኖበት፦ ወንድሜ ሳውል ሆይ፥ ታይ ዘንድና መንፈስ ቅዱስ ይሞላብህ ዘንድ ላከኝ አለ። #ወዲያውም_እንደ_ቅርፊት_ያለ ከዓይኑ ወደቀ፥ ያን ጊዜም ደግሞ አየ፤ ተነሥቶም ተጠመቀ፥ በክፉት መንገድ ሮጦ ያተረፈው እውርነትን ተረዳ አሁን ግን በጽድቁም መንገድ መሮጥን መረጠ።“
#እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በመንገድ ላይ ቁሙ #ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ እነርሱ ግን ” ያለ ዐይን መመልከት፣ መሄድ እንዲሁም መሮጥ አይቻልም።
በሥጋ ለመሮጥ ዓይነ ሥጋ በመንፈሳዊ ሕይወት ለመሮጥ ዐይነ ልቡና ሊኖረን ይገባል ያለ ዐይን እንኳን መሮጥ በደህንነትና በምቶት መራመድ አይቻልም። ዐይን ለሰውነት ሁሉ ወሳኝ አካል ናት በእርግጥ ዐይን አይሮጥም የሚሮጠው እግር ነው ሆኖም መነሻውን መገስገሻውንና መዳረሻውን ዐይን ካላመለከተችሁ እግር ወስዶ ወስዶ ገደል ይከታል ። “ዕውርም ዕውርን ቢመራው ሁለቱም ወደ ጉድጓድ ይወድቃሉ አለ።” #ማቴ 15፥14
ስለሆነም በእግረ ሥጋ ለመሮጥ ዐይነ ሥጋ በእግረ ልቡና ለመሮጥ ዐይነ ልቡና የግድ ያስፈልገናል። #ታገኙ_ዘንድ_ሩጡ " ብሎ ስለ መንፈሳዊ ሩጫ የመከረን ቅዱስ ጳውሎስ ከሥጋው ዐይንና ከልቦናው ዐይን ላይ ጋርዶት የነበረው ቅርፊት ከወደቀለት በኋላ ነው።
#አሁን የሚያሯሩጠው ሳውል ተብሎ አይጠራም ፤ አሁን የሚያሳድደው ሳውል መባሉ ቀርቷል፤አሁን ደብዳቢ መሆኑ አብቅቷል። አሁን ስለ ስሙ ከቦታ ቦታ የሚሯሯጥ ምርጥ ዕቃ ጳውሎስ ሆኗልና አሁን ስለስሙ ከሀገር ወደ ሀገር የሚንከራተት ስደተኛው ሆኗልና ። 2ቆሮ 11÷23-27
ዋጋ ለማግኘት መሮጥ እንዳናይ የጋረደንን ግርዶሽ ከመጣል ይጀምራል ። ከሳውል ዐይን ቅርፊት መሳይ ነገር ወደቀ ሲል ከአስተሳሰቡና ከልቦናውም ዐይን ጭምር ቅርፊቱ እንደወደቀለት ማስተዋል ያስፈልጋል። ክርስቶስን ወዶ እናቱን ማሳደድ ክርስቶስን ወዶ ክርስቲያኖችን መጥላት ይህ የልቡና ግርዶሽ ፣ ይህ የልቡና ሽፋን፣ ይህ የዕሊና ቅርፊትም ነውና። #እግዚአብሔር እንደ ሳውል ነቅሎ ይጣልላቸው አጥርተው ያዮ ዘንድም የተንሸዋረረ ዐይነ ልቦናቸውን ሐናንያ በመሰሉ የቅዱሳኑ ጸሎትና ምልጃ ያብራላቸው።

#ሃይማኖት የሌላችሁ ወደ ሃይማኖት ሩጡ
#ሃይማኖት ያላችሁ ወደ ምግባር ገስግሱ
#ምግባር ያላችሁ ወደ ትሩፉት ፍጠኑ ወደ ገነት በር ትደርሳላችሁ ተከፍቶም ታገኙታላችሁ ከየት ናችሁ የሚላችሁም አይኖርም። ያን ጊዜ የደማስቆውን ሯጭ ታኙታላችሁ አብራችሁትም “ መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤” ትላላችሁ ። #2ኛ ጢሞ 4፥7


አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፳፮/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
የሚራሩለት #እሩሩሁ_መላእክ
______
|አሁን መላእክ ይልቁኑ የመላእክት አለቃ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ይራራል እንጂ ይራሩለታልን ያሰኛል። ግን በእርግጥም ቅዱስ ሚካኤል የሚያራራም እሩሩም የሆነ ድንቅ መላእክ ነው።
#ለዚህ አንድ ጥሩ ማሳያ በህዳር ወር ድርሳኑ የተጻፈውን አንጀት የሚበላና የሚራራ የመላእኩን ትዕይንት ማንሳት በቂ ነው።
የጭንቅና የመከራ ቦታ ከሆነችው ሲዖል ያሉ ነፍሳት በስቃይ ሲጮኹ የማያስችለው እሩሩሁ መላእክ የግራ የቀኝ ክንፉን እያፈራረቀ ወደ ሲዖል ያወርዳል ነፍሳትም እንደ ቀፎ ንብ ሰፍረው ከክንፉ ላይ ተጣብቀው ከመከራ ይወጣሉ። መላእኩም ከልዑል ዙፋን ፊት ቆሞ ስለ እነርሱ ይለምናል ልዑለ ባሕሪ እግዚአብሔርም ስለ ቅዱስ ሚካኤል ሲል ነፍሳቱን ይምራቸዋል ቅዱስ ሚካኤልም ወደ ሀገረ ሕይወት ወደ መንግሥተ ሰማያት ያገባቸዋል።

#ዳግመኛም ወደ አብ ዙፋን መጋረጃ ገብቶ በግንባሩ ተደፍቶ ስለ ሕዋዎች ስለ ዝናባት በሰማይ ስለሚበሩ ወፎች በምድ ስለሚሽከረከሩ እንሰሳት ስለ ሰው ዘር ሁሉ ሰለ ባሕራትና ቀላያት ሳይቀር በታላቅ ተማጽኖ ይለምናል አብም ይቅር ብዬልሃለው እንከሚለው ድረስ ከወደቀበት አይነሳም! አንባቢ ሆይ ከዚህ በላይ ምን ያራራል ???

ድሆች አጥተው ቢለምኑ ያራራሉ ግን ያው ስለሌላቸው ነው ያለው ግን ሲለምን ማየት የበለጠ ያንሰፈስፋል። ሥልጣን የሌለው ባሪያ ቢሆን ያው ሥልጣን ስሌለለው ሊያደርገው የሚገባና የሚጠበቅ በመሆኑ አይደንቅም ባላ ሥልጣን ይልቁኑ የመላእክ አለቃ ሆኖ ስለ ሌሎች ተገብቶ ተንበርክኮና ተደፍቶ ማየት እንዴት አንጀት ይበላ ይሆን ???

#የምትራራልን እሩሩህ መላእክ ሆይ #እንራራልሃለን !
#የምትወደን መላእክ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ #እንወድሃለን
#የረከስን እኛን በኋላ ዘመን በምልጃህ ተማጽነህ የምታከብረን አክባሪያችን ሆይ #እናከብርሃለን !

|ቅድስት በረከቱ ትደረብን 🙏

አ.አ ኢትዮጵያ
ሐምሌ 12/2014 ዓ.ም
#ተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
" #ዘር_ያልተዘራብሽ_እርሻ_አንቺ_ነሽ "
_______
ሶሪያዊው
#ቅዱስ_ኤፍሬም
#ውዳሴ_ማርያም ዘሰሉስ


በሥነ ፍጥረት ትምህርት በእጅ የሚለቀሙ በማጭድ የሚታጨዱ በምሳር የሚቆረጡ
በሥራቸው ፣በግንዳቸው፣ በቅርንጫፋቸው የሚያፈሩ ልዮ ልዮ አትክርት ፣አዝርዕት
በጠቅላላው የእጽዋት ዘሮች የተፈጠሩት በዕለተ ማክሰኞ ነው:: በግዕዙ ዕለተ ሰሉስ
ይለዋል በልማዱ ማክሰኞ በትክክለኛው አጠራር ግን ማግስተ ሰኞ ነው የሚባለው የሰኞ
ማግስ ማለቱ ነው::
የሰሉስ ወይም የማግስተ ሰኞ (የማክሰኞ) ዕለት ፍጡራን ከላይ የተዘረዘሩት የእጽዋት
ዘሮች ሲሆኑ ነገር ግን ለመገኘታቸው ምክንያት የሚሆናቸው የዘራቸው ያጠጣቸው
ያበቀላቸው ገበሬ አልነበረም ። አስገኚያቸው ፈጣሪያቸው ልዑል እግዚአብሔር ብቻ ነው
በዚህም የማክሰኞ ዕለት እርሻ ከሌሎቹ አርሻና የእርሻ ምርቶች ለየት ይላል ። ከማክሰኞ
ዕለት እርሻ በቀር ዘር ሳይዘራበት ገበሬ ሳይተክልበት አድጎ ለምልሞ የታየ የእርሻ ዓይነት
የለምና ። እግዚአብሔር አምላክ ሥነ ፍጥረቱን በሦስት መንገድ ፈጥሯል ይህውም በሐልዮ
ወይም (በማሰብ) ሁለተኛ በነቢብ ወይም (በመናገር) ሦስተኛ በገቢር ወይም (በተግባር
፣በሥራ ፣በመሥራት) ነው። ታድያ የዕለተ ማክሰኞ ፍጥረታት በነቢብ የተፈጠሩ ፍጥረታት
ናቸው ። እግዚአብሔርም፦ ምድር ዘርን የሚሰጥ ሣርንና ቡቃያን በምድርም ላይ እንደ
ወገኑ ዘሩ ያለበትን ፍሬን የሚያፈራ ዛፍን ታብቅል አለ፤ እንዲሁም ሆነ ። ምድርም ዘርን
የሚሰጥ ሣርንና ቡቃያን እንደ ወገኑ ዘሩም ያለበትን ፍሬን የሚያፈራ ዛፍን እንደ ወገኑ
አበቀለች። እግዚአብሔርም ያ መልካም እንደ ሆነ አየ። ዘፍ 1÷11-12
ይህች የዕለተ ማክሰኞ እርሻ የመጀመሪያይቱ ምድርም እየተባለችም ትጠራለች ። ገበሬ
ሳይተክላት ዝናብ ለዘር ጠል ለመከር ሳታገኝ በመብቀሏ ቅድመ ምድር የመጀመሪያይቱ
ምድር ተባለች :: የሚገርመው በዚህ ወቅት የብርሃናት ምንጮች ፀሐይ ጨረቃና ከዋክብት
ገና አልተፈጠሩም ነበር ዝናብም በምድር ላይ ዘንቦ አያውቅም ነበር። ፀሐይ ጨረቃና
ከዋክብት የተፈጠሩት በዕለተ ዕረቡ ነው ስለዚህ በመጀመሪያይቱ ምድር ለማክሰኞ እርሻ
መገኘት አስተዋጽዖ አላደረጉም ያለ ውኃ ያለ ፀሐይ በቅለው ለምልመው ተገኙ እንጂ።
አቡሹ ሳይንስ እጽዋት ያለ ውኃ እና ያለ ፀሐይ መብቀል እንደሚችሉ ገና አልደረሰበትም
ምን አልባት ወደፊት ድሆ ድሆ ሲደርስበት እንደ ለመደው አዲስ ግኝት ብሎ በየ ሚዲያው
ሠላማችንን መንሳቱ እና ከሃይማኖት ዕውቀት በላይ ነኝ በማለት ቤተ ክርስቲያንን
መጨቆኑና ኃላ ቀር አድርጎ መቁጠሩ አይቀርም ። ቤተ ክርስቲያን ግን ባሕረ ጥበባት ነች
አትመረመርም:: ያለ ውኃ አብቅላ ያለ ፀሐይም አብስላ ልጆቾን ከርሃበ ሥጋ ከርሃበ ነፍስ
ታሳርፋቸዋለች ለምሳሌ ቢሉ ቃለ እግዚአብሔሯ አንዱና ዋናው ማሳያ ነው ማለት
እንችላለን ። ቃለ እግዚአብሔር ያለ ዝናብ እና ያለ ፀሐይ የሚያለመልም የሥጋም የነፍስም
ምግብ ነው “እርሱም መልሶ፦ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ
ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው።” ማቴ 4፥4
በምሥጢር "ጥንተ ምድር " ወይም ይህች የመጀመሪያይቱ ምድር (የማክሰኞ እርሻ)
የምትባል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ነች:: በዚህም እመቤታችን ጥንተ ምድር
የማክሰኖ እርሻ ተብላ ትጠራለች። ጥንተ ምድር ያለ ዘር ያለ ገበሬ ያለ ዝናብ ያለ ፀሐይ
በግብረ መንፈስ ቅዱስ (በመንፈስ ቅዱስ ሥራ) ለምልማ አፍርታ እንደተገኘች እመቤታችን
ቅድስት ድንግል ማርያምም ገበሬ የሚባል ወንድ ዘር የሚባል ዘርኃ ብዕሲ ሳይጎበኛት
እንዲሁ በግብረ መንፈስ ቅዱስ (በመንፈስ ቅዱስ ሥራ ) ፀንሳ አብባ ተገኝታለች ። ይህ
ምሥጢር በእውነት ድንቅ ነው መላከ እግዚአብሔር ለእራሷ ለድንግል ማርያም ፀጋን
የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ የልዑል ኃይል ይጋርድሻል መንፈስ ቅዱስም ይጸልልብሻል
ትጸንሻለሽ ወንድ ልጅንም ትወልጃለሽ ሲላት እንዴት ይህ ይሆናል ሴት ያለ ወንድ ምድር ያለ
ዘር ልታፈራ ይቻላታልን አለችሁ ? መላኩም ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም ጥንተ
ምድርን ያለዘር ሳራን ያለ ሙቀት ልምላሜ ዘመድሽ ኤልሳቤጥን በስተ እርጅናዋ ያጸነሰ
አንቺንም ያለ ወንድ ዘር ማጸነስ አይሳነውም አላት ያን ጊዜ እውነት ነው ለእግዚአብሔር
የሚሳነው ነገር የለም "ይኩነኒ በከመ ትቤለነ " አለችሁ በዚሁ ቅጽበትም ወልድ ኢየሱስ
ክርስቶስ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ በማህጸኟ ተቀረጸ። ቅዱስ ጳውሎስም ይህ ያለ
ዘር የመጽነስን ምሥጢር ይህ ምሥጢር ያለ ጥርጥር ድንቅ ነው ሲል ግሩም አርጎ
ገልጦታል::“እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው፤ በሥጋ
የተገለጠ፥ በመንፈስ የጸደቀ፥ ለመላእክት የታየ፥ በአሕዛብ የተሰበከ፥ በዓለም የታመነ፥
በክብር ያረገ።” ሲል 1ኛ ጢሞቴዎስ 3፥16 ። ሶርያዊው ሊቅ ቅዱስ ኤፍሬም በማክሰኞ
ዕለት ውዳሴው የማክሰኞን እርሻ የምትባል መቤታችንን "ዘር ያልተዘራብሽ እርሻ አንቺ ነሽ "
ብሎ በግሩም አመስግኘቀታል እርሻ እርሻ ለመባል ዘር ሊዘራበት ያስፈልገዋል እመቤታችን
ግን ዘር ያልተዘራባት ግን አፍርታ የተገኘች እርሻ ነችና ዘር ልተዘራብሽ እርሻ አንቺ ነሽ አላት
ያለ መታረስ ማፍራት ያለ ሰስኖተ ድንግልና መጸነስ ድንግል ሲሆኑ እናት እናትም ሲሆኑ
ድንግል የመሆን ፀጋ ከሰው ልጆች መካከል ከድንግል በስተቀር ለመን ተሰጠ? ለማንም።
ሆ ድንግል ሆይ አንቲ መንክረ መንክራት።
ቅዱስ ዳዊት “ምድር ፍሬዋን ሰጠችእግዚአብሔር አምላካችንም ይባርከናል”(መዝ.66፥6)
ተብሎ እግዚአብሔር የሚመሰገንበት ሳምንት ነው፡፡ ፍሬውም ከቁር ከበረዶና ከትል ተርፎ
ለጎተራ እንዲበቃ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በጸሎተ ቅዳሴዋ “በእንተ ፍሬ ምድር ናስተበቊእ
ከመ እግዚአብሔር ይሁብ ፍሬሃ ለምድር፣ ለዘርና ለመከር ሊሆን እግዚአብሔር ለምድር
ፍሬዋን ይሰጣት ዘንድ ስለምድር ፍሬ እንማልዳለን” በማለት አምላኳን ትማጸናለች፡፡
ልጇቿ ምእመናንም “ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ” (ማቴ.
24፥20) ሲል መድኃኔዓለም እንዳስተመረው የሃይማኖት ፍሬ ምግባርን፣ ቱሩፋትን ሳይሠሩ
በልምላሜ (በሃይማኖት) ብቻ ሳሉ እንዳይጠሩ ለንስሐ ለሥጋ ወደሙ እንዲበቁ
በማስተማር ነገረ ምጽአቱን በማዘከር “ድልዋኒክሙ ንበሩ፣ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ ” በማለት
ታስተምራለች፡፡ ስለዚህ ይህ ክፍለ ክረምት የዕለተ ምጽአት ምሳሌ ነው፡፡ ወቅቱ የአዝመራ
ወቅት ነው፡፡ ፍሬ መለያ እንደሆነ ሁሉ የሰው ሥጋ ከተቀበረና ትቢያ ከሆነ በኋላ ተነስቶ
በዕለተ ምጽአት በጽድቅና በኃጢአት ይለያልና፡፡(ማቴ.25፥32)
“በመንገድም አጠገብ በለስ አይቶ ወደ እርስዋ መጣ፤ ከቅጠልም ብቻ በቀር ምንም
አላገኘባትምና፦ ለዘላለሙ ፍሬ አይገኝብሽ አላት። በለሲቱም ያንጊዜውን ደረቀች።”
ማቴዎስ 21፥19 ሰው በሃይማኖቱ ቀጥተኛ እውነተኛ ከሆነ አይፈረድበትም በምግባሩ ግን
ይኮነናል ሃይማኖት ቅጠል ምግባር ፍሬ ነች:: “ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ እንዲሁ
ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው።” ያዕቆብ 2፥26 “አሁንስ ምሳር በዛፎች ሥር
ተቀምጦአል፤ እንግዲህ መልካም ፍሬ የማያደርግ ዛፍ ሁሉ ይቈረጣል ወደ እሳትም
ይጣላል።” ማቴዎስ 3፥10
ቅዱስ ጳውሎስም ክርስቲያኖች በሃይማኖት ሲኖሩ የመንፈስ ቅዱስ ፍሬን እንዲያፈሩ
ምግባራትን እንዲያደርጉ " የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥
በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው። እንደዚህ ያሉትን የሚከለክል ሕግ የለም።
ሲል ማፍራት ብቻ ሳይሆን ምን ዓይነት ፍሬም ማፍራት እንደሚገባ ዘርዝሮ ነግሮናል
ገላ5÷22 አስቀድሞ በኢሳይያስ ነቢይ ላይም አድሮ " እሺ ብትሉ ለእኔም ብትታዘዙ
የምድርን በረከት ትበላላችሁ እንቢ ብትሉ ብታምጹ ግን ሰይፍ ይበላችዋል " ብሎ እሺ
ብለን ታዘን የምድርን በረከት እንድንበላ አስቦናል ኢሳ 1÷19 ወላዲ መጥቅ ዮሐንስም
በምስክርነቱ “መንሹም በእጁ ነው፥ አውድማውንም ፈጽሞ ያጠራል፥ ስንዴውንም
በጎተራው ይከታል፥ ገለባውን ግን በማይጠፋ እሳት ያቃጥለዋል።” ማቴዎስ 3፥12
ወላዲተ አምላክ እመቤታችን ዋግ እንዳልመታው ውርጭም እንዳላገኘው ስንዴ እኛንም ንጽሕ ስንዴ አድርጋ ጎተራ በተባለች መንግሥተ ሰማያት እንድንገባ የማክሰኞ እርሻ የእመቤታችን በረከት ይደርብን::
.....ይቆየን......

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፮ /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
#ገብርኤል_ኃያል
_______________
ገብርኤል ኃያል መልአከ ሰላም መልአከ ብሥራት
የምታወጣ #የእግዚአብሔርን ሕዝበ ከሚነድ እሳት
ፍቅርህ ተጽፏል በልባችን ፊትህ ቆመናል ባርከን ብለን
' ' ' ' ' '

#ቂርቆስም ጸና ሞትን ሳይፈራ
አንተህ ስላለህ ከእርሱ ጋራ
አትፍሪ አላት ስለምን ትፍራ
አምነው ድል ነሱት ያንን መከራ "

#ዘማሪ ቴዎድሮስ ዮሴፍ
#በዓለ_ቅዱስ_ገብርኤል

❝... እግዚአብሔር በእርግጥ ያድነናል ..❞
—2ኛ ነገሥት 18: 30

ይህ ዕለት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት ኢየሉጣንና ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስን ከሚነድ ዕቶን እሳት ያዳነበት ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው፡፡

ቅዱስ ቂርቆስ ሀገሩ ሮም ሲሆን አባቱ ቆዝሞስ እናቱ ኢየሉጣ ይባላሉ፡፡ እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ በትውልዷ ከአዝማደ ነገሥት ወገን ናት፡፡ ዲዮቅልጥያኖስ በነገሠ በ20 ዓመት በአባ ባጋግዮስ ምክንያት ‹‹የጣዖታት ቤቶች ይከፈቱ አብያተ ክርስቲያናት ይዘጉ›› ብሎ አሳወጀ፤ በዚህ ጊዜ ግማሾቹ ተሰደዱ ቅድስት ኢየሉጣም ልጇ የ3 ዓመት ሕፃን ነበርና ለርሱ ብላ ወደ ኢቆንዮን ሸሸች፡፡

በዚያም
ሀገረ ገዢው። :- ‹‹ክርስቶስን ካጂ ለጣዖት ስገጂ›› ቢላት
እርሷም: - ‹‹ዓይን እያለው ለማያይ ጆሮ እያለው ለማይሰማ በቃልህ አዘህ በእጅህ ሠርተህ ላቆምከው ምስል አልሰግድም›› ብላ መለሰችለት፡፡
እርሱም መልሶ :- ‹‹እምቢ ካልሽ በሰይፍ እቀጣሻለሁ›› ብሎ ቢያስፈራራትም
እርሷ ግን :- ‹‹ይህን ሕፃን ጠይቀው›› አለችው፡ከዚያም
ሕፃኑን :- ‹‹ወርቅ እሰጥሃለሁ ለዚህ ጣዖት ስገድ›› አለው፡፡
ሕፃኑ ቂርቆስ መንፈስ ቅዱስ አድሮበታልና ‹‹ራሳቸውን እንኳ ማዳን ለማይችሉ ጣዖታትህ አልሰግድም›› ብሎ በመለሰለት ጊዜ ንጉሡ ተበሳጭቶ ‹‹በብረት ጋን ውኃ አፍልታችሁ ከዚያ ውስጥ ጣሏቸው›› ብሎ አዘዘ፡፡

የውኃው መፍላት እንደ ክረምት ነጎድጓድ 42 ምዕራፍ ድረስ ይሰማ ነበር፡፡ የንጉሡ አገልጋዮች ሊከቷቸው ሲወስዷቸው የቅድስት ኢየሉጣ ልቧ በፍርሃት ታወከባት፤ ቅዱስ ቂርቆስ ግን የእናቱን ፍርሃት እንዲያርቅላት ይጸልይ ነበር፤ እርሷንም ሁለተኛ ሞት አያገኘንምና እናቴ ሆይ በርቺ ፣ ጨክኚ፤ አናንያ፣ አዛርያና ሚሳኤልን ያዳነ እኛንም ያድነናል›› በማለት እያጽናናት ልብሷን እየጎተተ ከእሳቱ ቀረቡ፡፡

ከዚህ በኋላ ቅድስት ኢየሉጣ ጨክና በፍጹም ልብ ሆነው ተያይዘው ከእሳቱ ገብተዋል፡፡ እግዚአብሔርም መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ በበትረ መስቀሉ እሳቱን አጥፍቶ የፈላውን ውኃ አቀዝቅዞ አውጥቷቸዋል፡፡ ቅድስት ኢየሉጣ እና ቅዱስ ቂርቆስ በወጡም ጊዜ ልብሳቸውና ሰውነታቸው ሳይቃጠል ተመልክተው ከአሕዛብ ብዙዎቹ አምነው ሰማዕትነት ተቀብለዋል፡፡

ቅዱስ ገብርኤል ከሚፈላ ውኃ ያወጣቸው ሐምሌ 19 ቀን ሲሆን ሰማዕትነት የተቀበሉት ግን ጥር 15 ቀን ነው።

የቅድስት ኢየሉጣ እና የቅዱስ ቂርቆስ በረከታቸው ይደርብን

ሀገራችን ኢትዮጲያ ከሚነደው እሳት መልአኩን ልኮ ይጠብቅልን ! ላዘኑ ሰዎች መጽናናትን ያድልልን።

#ስለ_ሀገር_መጸለይን_አታስታጉሉ !

ዲ/ን እስጢፋኖስ ደ.
18/11/2014 ዓ.ም
#እንኳን ሰው መሬቱ #እንዳይገ ዛልህ አውግዣታለሁ!
Forwarded from Eyob kinfe
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
#አዲስ_መልአክ_ተክለ_ኤል
________
ተፈጥሮ ከመላእክት ወገን ያልሆነ ሰው ሆኖ ሳለ ነገር ግን በሃይማኖቱ ጽናት በምግባሩ ቅንሐት እና በተጋድሎዎ ብዛት ምድራዊ ሲሆን ሰማያዊ አዳማዊ ሲሆን መላእካዊ ለመሆን የበቃ ሐዲስ መላእክ ነው :: ተክለ ኤል

ቅዱሳን መላእክት በዘር የተገኙ አይደሉም ተክለ ኤል ( #ተክለ_ሃይማኖት ) ግን ከሕግ ዘር የተገኘ ሰው የሆነ አዲስ መላእክ ነው ::

#ተክል › ማለት ፍሬያማ ዕንጨት፣ ዛፍ፣ ቅመም፣ ቅጠላ ቅጠል፣፣ የሚሸተት፣ቢበሉት ጥጋብ ፣ቢያርፉበት ጥላ የሚሆን ገነታዊ ዕፅ፣ እንዲሁም ሕግ ሥርዓት ማለት ነው /ማቴ.፲፭፥፲፫/፡፡

" #ኤል " ማለት ደግሞ እግዚአብሔር ማለት ነው :: ስመ መላእክት ስመ እግዚአብሔርን ያዘለ በመሆኑ የሁሉም ቅዱሳን መላእክ ስም "ኤል" የሚል መቀጽል አለው #ለምሳሌ :-ሚካ-ኤል ፣ ገብር-ኤል ፣ ዑራ -ኤል፣ ወዘተ .... ስለዚህ ተክለ ኤል ስንልም #የእግዚአብሔር _ተክል ማለታችን ነው :: ታላቁ ሊቅ ቅዱስ #ባስልዮስ ዘ ቄሳሪያ እኔስ #እግዚአብሔር ባልኩ ጊዜ #አብ_ወልድ_መንፈስ_ቅዱስ ማለቴ ነው ብሎ እንደተናገረ እኛም እግዚአብሔር ስንል አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማለታችንነውና #ተክለ_ኤል ስንለውም የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ተክል ማለታችን ጭምር ነው::

#ቦታው በሸዋ ክፍለ ሀገር ዛሬ ኢቲሳ በመባል በሚታወቀው ከከሰም ጅረት አካባቢ ባለ ቦታ በጥንቱ ፈጠጋር ቡልጋ በደብረ ጽላልሽ አውራጃ ዞረሬ በተባለው ሥፍራ ነው ። በዚሁ ሥፍራ (ዘርዐ ዮሐንስ) ፀጋ ዘአብ የሚባል የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህን የነበረ ጻድቅ ሰው ነበር "ጸጋ ዘአብ " ማለት የአብ ሥጦታ ማለት ነው ካህኑ ጸጋ ዘአብ በሃገሩ ደጋግ ከሆኑ ሰዎች ወገን ሣራ የምትባል ሴት አገባ ።

ሁለቱም ፈሪያ እግዚአብሔር ያደረባቸው በጎ ሥራን የሚሠሩ ሰዎች ነበሩ የፀጋ ዘአብ ሚስት ሣራ ሃይማኖት ከምግባር መልክና ደም ግባት ከሙያ ጋር አሟልቷ የሰጣት ሴት ነበረች ። አማቷ የፀጋ ዘአብ አባት " ወረደ ምሕረት " የሥራዋን ደግነት አይተው " እግዚኀረያ " ብለው ስም አወጡላት ጌታ የመረጣት ማለታቸው ነው።

#በሊቀ_መላእክት_በቅዱስ_ሚካኤል አብሳሪነት ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኀረያ መጋቢት 24 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ተወለዱ ወላጆቻቸውም ፍስሐ ፂዮን ።(የጽዮን ደስታዋ)ብለው ሰየሟቸው፡፡ ጻድቁ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹ አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ›› ማለትም ‹‹አንዱ አብ ቅዱስ ነው አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው አንዱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ነው›› በማለት የፈጠራቸውን አምላክ አመስግነዋል። ይህን ጊዜ እናታቸው እግዚ ኀረያም በመገረም ሆና " ይህ ሥራ የአባት ነው ላንተ የሚገባህ ጡት መጥባት ነው" ብላ ጡቷን አጎረሰችሁ ፡፡

#ቅዱሳን_መላእክት ቀን ከሌት #ቅዱስ_ቅዱስ_ቅዱስ እያሉ ያመሰግናሉ ኢሳ 6፥÷6 ይህም የህጻኑ ሁኔታ መላእካዊ ግብሩን ገና በህጻንነት የገለጠ ሁኔታ ነበር። ካህኑ ፀጋ ዘአብ የወቅቱን የቤተ ክርሰቲያን አገልግሎታቸውን ጨርሰው ወደ ቤታቸው ሲገቡ ሚስታቸው እግዚ ኀረያ በመገረም ሆና የሦስት ቀን ልጃቸው ፍስሐ ፂዮን እንዴት ባለ ምሥጋና ፈጣሪያቸውን እንዳመሰገነ ነገረቻቸው ጸጋ ዘአብም ህጻኑን ተቀብለው ታቅፈው እየሳሙ ልጄ ሺህ ዘመን ኑርልኝ እንዲ እያልክ በቤተ መቅደስ ስትቀድስ አይህ ዘንድ እመኛለው አሉ።
‹‹ #ተክለ_ሃይማኖት ›› ብሎ #የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ፍስሐ ፂዮን የሚለውን ስሙን በፈጣሪው ትዛዝ መሠረት ጠራቸው፡፡ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው ዲቊናን፤ በ22 ዓመታቸው ደግሞ ቅስናን ከግብፃዊው ጳጳስ ከአባ ጌርሎስ ወይም (አባ ቄርሎስ) ዘንድ ተቀብለዋል፡፡

ሐዋርያዊ ተግባርንም በከተታ እና በፈጠጋር (በጽላልሽና በአካባቢዋ፣በዳሞት በምድረ ወላይታና አካባቢው ፣በአምሓራና በሸዋ በሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ፣ በኣድያማተ ትግራይ፣በገዳመ ዋሊ (ዋልድባ) ፣በገነተ ማርያም ላስታ በደብረ ዘመዶ ማርያም ገዳም በዚያው በላስታ፣ በኤርትራ ገዳማት ፣በደብረ ዳሞ አቡነ አረጋዊ ገዳም ወዘተ በአገሪቱ ወንጌል ባልተዳረሰበት ቦታ ሁሉ እየተዘዋወሩ ኢትዮጵያ አንዲት የሐዋርያት ወንጌል ሰፍተዋታል ።
#ጻድቁ_አባታችን ሕይወታቸዉን ሙሉ ለእግዚአብሔር በመስጠት፣ እንደ በሬ ተጠምደው፣ እንደ ገበሬ ታጥቀው፣ ይህንን ዓለም ንቀው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው በብሕትውና በመኖራቸው፤ እርሳቸው በአሚነ ሥላሴ ጸንተው ሌሎችንም እንዲጸኑና እንዲያምኑ በማድረጋቸው፤ እንደዚሁም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ በመስበክ በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድውያነ ሥጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የፈወሱ ሰባኬ ወንጌል በመኾናቸው ‹‹ #ተክለ_ሃይማኖት ›› ተብለው ይጠራሉ::

#በየ_ደረሱበትም ከሥራው ጽናት ከተአምራቱ ብዛት የተነሳ አንተ ሰውነህን ወይስ መላእክ ነህ ንገረን ይሉት ነበር በዚህም በደብረ ዳሞት አቡነ አረጋዊ ገዳም 10 ዓመት ከቆዮ በኃላ ተሰናብቷቸው ሊሄድ ተነሳ ሁሉም ከፍቅሩ ጽናት የተነሳ አለቀሱለት አበምኔቱም ይህን ሰው ኃጢያቴ አባሮታልና ወየውልኝ ብሎ መነኮሳቱን ሰብስቦ ሊሸኙት ተነሱ ከገዳሞም ያለ እረጅም ገመድ (ጠፈር) መውረድም ሆነ መውጣት አይቻልም ነበርና የመውረጃውን ገመድ (ጠፍር) ይዞ ይወርድ ዘንድ ጀመረ ጥንተ ጠላት ዲያቢሎስ ገመዱን ከካስማው ላይ ቆረጠው አባታችንም ይህን አስደንጋጭ ክስሀት ተከትሎ የተሰጣቸው የፀጋ ክንፍ በገዐድ ተገለጠ አበ ምኔቱና መነኮሳቱም ከገዳሙ አፈፍ ሆነው የሚሆነውን ያዮ ነበር ጻድቁም እንደ ሰማያዊ መላእክ በክንፉቸው በረው በደህና ከመሬት ደረሱ መነኮሳቱም መንክር እግዚአብሔር በላዕለ ቅዱሳኒሁ ብለው አደነቁ::
ከዚህም ባለፈ ህዳር 24ቀን መላእኩ ከምድራዊ ቦታቸው ነጥቆ ወስዶ ከሱራፌል ጋር ቀላቀላቸው በልጅነት አንደበታቸው አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ብለው ያመሠገኑት አግአስተ ዓለም ቅድስት ሥላሴን ዛሬ ደግሞ በዙፋኑ ላይ እናዳለ እያዮት በከንፈሮቻቸው ሰለሱት ቀደሱት በወርቅ ማዕጥንትም ዙፋኑን አጠኑ ።ወደ ቀደመም ኑሯቸው መላኩ መለሳቸውና ተጋድሏቸውን ቀጠሉ።

#በገዳመ አስቄጥስ ግብጽ እና ከኢየሩሳሌም።ጉብኝት በኃላ እየዞሩ ወንጌልን ለማስተማር ባይቻላቸው ስለዚህ በአንድ ቦታ መቆምን መረጡ ከፊት ከኃላ ከግራ ከቀኝ የሚያነቃ የሶር ሶማያ ስለው በመትከል በደብረ አስቦ በደብረ አስቦ ዋሻ ከዘረጉ ሳያጥፉ ከቆሙ ሳይቀመጡ ለ22 ዓመታት በጸሎት ጸኑ ጥር 4 ቀን 12 88ዓ.ም በ92 ዓመት ሲሆናቸው አንዲቱ የእግራቸው አገዳ ከመቆም ብዛት ተሰብራ ወደቀች ጸሎታቸውንም ሳያቆርጡ በአንድ እግራቸው 7 ዓመት አክለው በጸሎት ተጎ በድምሩም 29 ዓመት በጸሎት ተጋደሉ :: ከፈጣሪ ዘንድም ብዙ ጸጋና ቃል ኪዳን ከተቀበሉ በኃላ በ99ዓመት ከ10ወር ከ10ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በክብር አርፈዋል:: እንደ ሰው በምድር ተወልደው እንደ መላክት የኖሩ አዲስ መላክ ያልናቸውም ለዚሁ ነው።

የጻድቁ አባት የአቡነ #ተክለ_ሃይማኖት እረድኤት በረከታቸው በአማላጅነታቸው የምትገኝ ጸጋ ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትኑር .....አሜን!