#ጨለማ_እና_ብርሐን
ተፈጥራዊውን ሐቅ በውል ሳያስሰው
ውስብስቡን ምስጢር በወግ ሳይዳስሰው
የብርሃንን ሐይል ከፅልመት ሲያረክሰው
ፋይዳ ቢስ አርጉ ዋጋ ሲያሳንሰው
ማሾ ይዞ ወጣ ሰው የቸገረው ሰው።
እውነት በሌለበት
በገበያ ሥፍራ ከሚርመሰመሰው
ሳያገኝ ቀረና እንድ እውነተኛ ሰው
እውነት የጠፋበት
እውነቱን ፈላጊ ተቆጥሮእንደዘበት
ገብያተኛው ሁሉ በሳቅ አፌዘበት ።
ከሀቅ ያለያያል
እንደቂል ያሳያል ገበያ መሐል ላይ
የማሾ ብርሐን በጠራራ ፀሐይ።
ረቂቅ እውነቱ የብርሐን ውበት
ጎልቶ የሚወጣበት ደምቆ የሚታይበት
ነፍስ የሚዘራበት የሚሰጠው ሕይወት
ጨለማው እኮ ነው ድቅድቁ መስታወት።
ተፈጥራዊውን ሐቅ በውል ሳያስሰው
ውስብስቡን ምስጢር በወግ ሳይዳስሰው
የብርሃንን ሐይል ከፅልመት ሲያረክሰው
ፋይዳ ቢስ አርጉ ዋጋ ሲያሳንሰው
ማሾ ይዞ ወጣ ሰው የቸገረው ሰው።
እውነት በሌለበት
በገበያ ሥፍራ ከሚርመሰመሰው
ሳያገኝ ቀረና እንድ እውነተኛ ሰው
እውነት የጠፋበት
እውነቱን ፈላጊ ተቆጥሮእንደዘበት
ገብያተኛው ሁሉ በሳቅ አፌዘበት ።
ከሀቅ ያለያያል
እንደቂል ያሳያል ገበያ መሐል ላይ
የማሾ ብርሐን በጠራራ ፀሐይ።
ረቂቅ እውነቱ የብርሐን ውበት
ጎልቶ የሚወጣበት ደምቆ የሚታይበት
ነፍስ የሚዘራበት የሚሰጠው ሕይወት
ጨለማው እኮ ነው ድቅድቁ መስታወት።
❤1👍1