#መጉደልን_ወረስኩት
አንቺን እየፈለግከ፣ . . .
ስንት እዳሪ አለማሁ፣ ስንት ችግኝ ተከልኩ ፤
ስንት ጥቅምት አብቤ፣ ማፈራት እንዳማረኝ፤
የናፍቆትሽ ግንቦት፣ አክስሞ አረገፈኝ፡፡
በናፍቆት ሰማይ ላይ፣ በምናብ ጨረቃ ፤
አልሜሽ ሳልነቃ፣
አንግሼሽ ሳበቃ ፤
እውኔ ላደርግሽ፣ መኖርሽን ናፍቄ ፤
ከያበባው ዱቄት፣ ውብ ቀለም ጠምቄ፣
ስንት ግጥም ጻፍኩኝ፣ ስንት ዜማ ደረስኩ!
አንቺን እየጠበቅኩ፡፡
ደግሞ ተመልሼ፣ . .
ምኞቴ ሸራ ላይ፣ በተስፋ ብሩሼ ፣
እምቡጥ ሳፈነዳ፤
ቅጠል ሳለመልም ፧
ኩሬ እየቆፈርኩ፣ በረሀ ሳጠጣ ፤
አንኳን እጽዋቱ፡፤ አጽም ስጋ ለብሶ፣ አለት ስር አወጣ፡፡
ምን ያደርጋል ግና . . .
ያለ ፍሬ የቀረው፣ የተከልኩት ችግኝ፤
ውዳሴ ያደረግከት፣ የቋጠርኩት ስንኝ ፤
አብሮኝ አረጀና . . .
አብሮኝ አረጀና
የናፍቆትሽ ችግኝ ፤
የናፍቆትሽ ስንኝ ፤
የናፍቆትሽ ስእል፤
መጉደልን ለመድከት፣ ሆነኝ የራስ ምስል፡፡
🔘በደሉ ዋቅጅራ🔘
ጥቅምት፣ 2012፣ አዲስ አበባ
አንቺን እየፈለግከ፣ . . .
ስንት እዳሪ አለማሁ፣ ስንት ችግኝ ተከልኩ ፤
ስንት ጥቅምት አብቤ፣ ማፈራት እንዳማረኝ፤
የናፍቆትሽ ግንቦት፣ አክስሞ አረገፈኝ፡፡
በናፍቆት ሰማይ ላይ፣ በምናብ ጨረቃ ፤
አልሜሽ ሳልነቃ፣
አንግሼሽ ሳበቃ ፤
እውኔ ላደርግሽ፣ መኖርሽን ናፍቄ ፤
ከያበባው ዱቄት፣ ውብ ቀለም ጠምቄ፣
ስንት ግጥም ጻፍኩኝ፣ ስንት ዜማ ደረስኩ!
አንቺን እየጠበቅኩ፡፡
ደግሞ ተመልሼ፣ . .
ምኞቴ ሸራ ላይ፣ በተስፋ ብሩሼ ፣
እምቡጥ ሳፈነዳ፤
ቅጠል ሳለመልም ፧
ኩሬ እየቆፈርኩ፣ በረሀ ሳጠጣ ፤
አንኳን እጽዋቱ፡፤ አጽም ስጋ ለብሶ፣ አለት ስር አወጣ፡፡
ምን ያደርጋል ግና . . .
ያለ ፍሬ የቀረው፣ የተከልኩት ችግኝ፤
ውዳሴ ያደረግከት፣ የቋጠርኩት ስንኝ ፤
አብሮኝ አረጀና . . .
አብሮኝ አረጀና
የናፍቆትሽ ችግኝ ፤
የናፍቆትሽ ስንኝ ፤
የናፍቆትሽ ስእል፤
መጉደልን ለመድከት፣ ሆነኝ የራስ ምስል፡፡
🔘በደሉ ዋቅጅራ🔘
ጥቅምት፣ 2012፣ አዲስ አበባ