#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ ( #የመጨረሻ_ክፍል )
:
✍ድርሰት:-በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
ከአንደኛው መጽሀፍ መሀል ያየቻቸው ሁለት ፎቶዎች ግን ተስፈንጥራ አልጋዋን ለቃ ወለሉ ላይ እንድትቆም አደረጋት…፡፡.ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው..የምታየውን ማመን አልቻለችም..የኮማንዳሩና የወላጅ እናቷ ፎቶ ነው…አንዱ ፎቶ ሁለቱም በዋና ልብስ ሆነው ሙሉ በሙሉ አቅፎት መዋኛ ገንዳ ውስጥ ሆነው የተነሱት ነው…ሌላው ደግሞ ከንፈር ለከንፈር እየተሳሳሙ…… ይሄን ያህል ሄደዋል ብላ አታስብም ነበር ..ስልኮን አነሳችና ደወለች..እሮዝ ጋር ነው..ተነሳ..?
‹‹አሁኑኑ እፈልግሻለው››
‹‹ምነው ልጄ ምን ሆንሺብኝ..?››
‹‹መቀባጠሩን ተይና በአስቸኮይ ኩማደሩ ቤት ነይ››ስልኩን ጠረቀመችው
ሮዝ የለበሰችውን የለሊት ቢጃማ እንኳን ለመቀየር ጊዜ ማባከን አልፈለገችም…ብን ብላ ነው ግቢውን ለቃ ወደኩማንደሩ ቤት የበረረችው ..ልጄን… ልጄን ምን አደረክብኝ....?የሳሎኑን በር በርግዳ ከፈተችና ወደውስጥ ገባች…
‹‹ምን አደረገብኝ ..?ምነ ሆንሺብኝ ..?ተንደርድራ ልትጠመጠምባት ስትል ገፍትራ ከላዬ አራቀቻት….››
‹‹ይሄ የመቼ ፎቶ ነው....?››ሄለን ነች ጠያቂዋ
‹‹የቱ..? እኔጃ..››ግራ ተጋብታ መለሰች
በእጇ የያዘችውን ፎቶ ወረወረችላት .ደረቷ ላይ አርፎ ወደመሬት ወደቀ… ጎንበስ ብላ አነሳችውና ተመለከተችው..
‹‹እሺ መንም አልጀመርንም ብለሽኝ አልነበር..?››ሄለን ነች በሽሙጥ የጠየቀቻት
‹‹ያው ድሮ እኮ ነው…ግን ከተለያየን ብዙ አመት አልፎናል..?››
‹‹በቀደምለታ የመጣሽው እንታረቅ ልትይው ነበር....?››
‹‹አረበፍጽም ..ስንለያይ ተጣልተን ስለነበረ ቂም ይዞብኛል..አንቺን በማጥቃት እንዳይቀለኝ ስለፈራው ከአንቺ እንዲርቅ ልለምነው ነው…››
‹‹ኦኬ አሁን በጣም ገባኝ….ለመሆኑ ኩማደሩን እንደማፈቅረው ታቂያለሽ..?››
‹‹አታደርጊውም ልጄ..እኔ በህይወት እያለው አታደርጊውም››
‹‹አትጠራጠሪ አደርገዋለው..እንደውም ማግባት ሁሉ የምፈልገው እሱን ነው››
‹‹አረ ተይ ልጄ…እራስሽን ወጥመድ ውስጥ ለምን ትከቺያለሽ....?እሱ እኮ ውስጡ በቀል እንጂ ፍቅር የለበትም…..››
እሱ እኔን አይመለከተኝም…እንደውም እኔም አንቺን ለመበቀል ስለምፈልግ ጥሩ አጋጣሚ ነው…ለመሆኑ ምን ያል ብትበድይው ነው .. ..?ለነገሩ አንቺ አይደለሽ ምንም ብታደርጊው አይደንቀኝም….ለማንኛመው ከዛሬ ጀምሮ በመሀከላችን እንዳትገቢ ልነግርሽ ነው..አሁን የድሮ ፎቶሽን ይዘሽ ወጭልኝ…;››
‹‹በፈጠረሽ ልጄ›› እግሯ ላይ ተደፋች..
‹‹ምንም ብታርጊ ሀሳቤን አታስቀይሪኝም…ምን አልባት በአንድ ነገር..››
‹‹ምንድነው ልጄ …የፈለግሽውን ጠይቂኝ..ከዚህ ሰይጣን ራቂለኝ እንጂ ያልሺኝን ሁሉ አደርጋለው››
‹‹ያው የእኔን ጥያቄ ታውቂያለሽ… ተመሳሳይና የማይቀየር ነው…የአባቴን ማንነት ከነገርሺኝ እተወዋለው…››
‹‹አባቴን....?››ከተደፋችበት ተነሳችና መቀመጫ ይዛ ተቀመጠች
‹‹አዎ ንገሪኝ..ከእሱ እንድርቅ ከፈለግሽ ንገሪኝ››
‹‹እሺ ቁጭ በይ….ነግርሻለው››
ሁለቱም ፊት ለፊት ተፋጠው ተቀመጡ
‹‹እንግዲያው ንገሪኝ ካልሽ ምርጫ የለኝም ነግርሻለው….ግን ለምትሰሚው ነገር እራስሽን አዘጋጂ››
‹‹ግድ የለሽም መግቢያውን ተይና ወደዋናው ታሪክ በቀጥታ ግቢልኝ››
‹‹ይሄውልሽ ልጄ ግማሽ ዕድሜዬን ይሄንን ታሪክ ለሌላ ሰው ይቅርና ለእኔው ለእራሴው ለመናገር ስሸሸው የኖርኩትን ነገር ነው፡፡ይሄው ዛሬ ሳልወድ በግድ ለመናገር ተገድጄያለው፡፡እስከዛሬ ነገሩን ሚስጥር አድርጌው የኖርኩት ለእናቴ ስል ነበር..አሁን ደግሞ ለመናገር የተገደድኩት ለአንቺ ለልጄ ስል ነው..ከእናቴ ስሜትና ደህንነት ይልቅ የልጄን ስሜት እና ደህንነት አስቀድሜ ነው..መቼስ አናቴ ልጅ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ስለምታውቅ ይቅር ትለኛለች ብዬ አስባለው፡፡
ማንኛውም የሰው ልጅ በትዝታ ፈረስ ፊቱን ወደ ኃላው አዙሮ ትናንትናውን ሲያይ መዝለል የሚፈልገው ወይም አለማሰብ የሚመኘው ወይም ምነው ባልኖርኩት ኖሮ ብሎ የሚጠየፈው በጊዜዎች ክፍተት መሀከል የተከወነ ጨለማ ታሪክ ይኖረዋል፡፡የእኔን የተለየ የሚያደርገው ግን ያለፈ ህይወቴ ውስጥ የተከሰተው ጠባሳ አይደለም መሰረዝ እንዲደበዝዝ ማድረግ እንኳን የማይቻል ስለሆነ ዕድለኛ አይደለውም፡፡
ልጄ አንቺ ለእኔ ማለት የበደሌ ምልክት፤ የክስረቴ ትርፍ ነሽ፡፡ሰው ህይወቱን የሚያሳጣው …ማንነትን የሚያወድመው ነገር ከስሮ በዛው ልክ ህይወቱን የሚያለመልምለት እና ለመኖሩ ምክንያት የሆነ ነገር ያተርፋል…እኔ ማለት እንዲያ ነኝ..የነገ ተስፋዬን፤ለመኖር የሚረዳኝን ሞራሌን፤ማንነቴን አጥቼ በምትኩ ግን አንቺን አገኘው፡፡
‹‹አረ የምትይው ነገር ምንም እየገባኝ አይደለም…››መለሰችላት ሄለን
‹‹የእኔ ህይወት ለእኔም ለእራሴ ብዙ ጊዜ አይገባኝም፡፡ግን ቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ልግባ፡፡አንቺን የወለድኩሽ ተደፍሬ ነው፡፡መቼ? ገና 15 ዓመት ሳይሞላኝ፡፡ማን የደፈረኝ ይመስልሻል..?የምትወጂው አጓቴ ነው፡፡ላስተምርሽ ብሎ ከእናቴ በአደራ ተቀብሎ አዲሳባ ወስዶ ደፈረኝ ..አስረገዘኝ …››
‹አጎቴ!!!!.. አጎቴ ማለት የማዬ ወንድም … አንቺን››
‹‹አዎ አጎቴ እኔን …ያ ማለት ደግሞ አንቺ የእሱ ልጅ ነሽ… አባትሽ ነው፡፡
‹‹እኔ አላምንም…››ሄለን ምትሆነው ምትናገረው ነገር ጠፋት
‹‹ልጄ ነፍስ ካወቅሽበት ጊዜ አንስቶ አባቴ ማን ነው ?ብለሽ ስትጠይቂኝ..የተለያየ ሰበብ እየፈጠርኩ ልነግርሽ ያልቻልኩት ነገሩ ለሰሚውም ግራ ሰለሆነብኝ ነው፡፡ ልጄ እስቲ አስቢው በገዛ አጐቴ ተደፍሬ አንቺን እንደወለድኩሽ ስትሰሚ በአንቺ ሰነ-ልቦና ላይ የሚያደርሰውን መረበሽና ተፅዕኖ በምን ማረጋገጥ እችላለው? እንደእኔ ስብርብር ብትይብኝስ.?.ከሁሉም በላይ ደግሞ ይሄ ጉዳይ እናቴ ጆሮ ይሄ ዜና ቢደርስስ ?የገዛ መንትያ ወንድሟ ከመሀጸኖ ፈልቅቃ አምጣ የወለደቻትን እና አደራ አሳድግልኝ ብላ ያስረከበቻትን ጨቅላ ልጆን በድልዱም ቢላዎ ገዝግዞ እንዳረዳት እና ህይወቷን እንዳበከተባት ብትረዳ በድንጋጤ ህይወቷ ባያልፍ እንኳን ጨርቋን ጥላ ማበዶ ይቀራል ብለሽ ታስቢያለሽ…?.ለዚህ ነው ከአንቺ ጋር ስጋጭ እና ስጣላ የኖርኩት፡፡ ለዚህ ነው እራሴን እንደ ጥፋጠኛ አስቆጥሬ ስባልግ እና ስንዘላዘል በገዛ ስህተቴ እደወለድኩሽ እዲታሰብ አድርጌ ግማሽ ዕድሜዬን እንደጋጠወጥ እና እንደ አለሌ ሸርሙጣ እየታሰብኩ በመኖር እራሴን ያሰቃየውት...እርግጥ አልዋሽም ሸርሙጣ የሚለው ስም አይገባኝም አልልሽም..በደንብ ይገባኛል..፡፡ግን በሽታ ሆኖብኝ ነው፡፡ከመደፈሬ ጋር የተፀናወተኝ እኔ እራሴ የምጠየፈው እና የምፀፀትበት ክፉ በሽታዬ ነው፡፡
ልጄ እንግዲህ እውነቱ ይሄ ነው፡፡አባትሽ የምትወጂው አጐትሽ ነው..ከአሁን ቡኃላስ እሱን መውደድሽን ትቀጥያለሽ…?እንግዲህ እሱ የአንቺ ጉዳይ ነው፡፡እኔን ግን ካጠፋውት በላይ ስቀጣ የኖርኩ ሚስኪን እናት ነኝና እባክሽ ይቅር በይኝ እና ቀሪ ህይወቴን ትንሽም ቢሆን ተስፋ እንዲኖራት እርጂኝ፡፡ከእዚህ ሰውዬ ራቂ..እሱን በጣም በድዬዋለው….ሊያገባኝ ሲዘጋጅ ነው ጥዬው ወደአዲስ አበባ የገባውት ..ስለዚህ ለአመታት ሊበቀልኝ ሲጥር እደነበረ አውቃለው..እና ልጄ ….
…ሄለን ከተቀመጠችበት ተነስታ ተንደርድራ ነው እግሯ ላይ የተደፋችባት….‹‹እማዬ የምትችይ ከሆነ ይቅር በይኝ..ባክሽ ይቅር በይኝ››እየነፈረቀች ተማፀነቻት
ሮዝ ከገባችበት መደንዘዝ ውስጥ እንደምንም ነቃችና እሷም ተከትላት ቁጢጥ በማለት ልጆን ከተደፋችበት አንስታት አቀፈቻት… አገላብጣ ሳመቻት ‹‹ልጄ ….ልጄ
:
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ ( #የመጨረሻ_ክፍል )
:
✍ድርሰት:-በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
ከአንደኛው መጽሀፍ መሀል ያየቻቸው ሁለት ፎቶዎች ግን ተስፈንጥራ አልጋዋን ለቃ ወለሉ ላይ እንድትቆም አደረጋት…፡፡.ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው..የምታየውን ማመን አልቻለችም..የኮማንዳሩና የወላጅ እናቷ ፎቶ ነው…አንዱ ፎቶ ሁለቱም በዋና ልብስ ሆነው ሙሉ በሙሉ አቅፎት መዋኛ ገንዳ ውስጥ ሆነው የተነሱት ነው…ሌላው ደግሞ ከንፈር ለከንፈር እየተሳሳሙ…… ይሄን ያህል ሄደዋል ብላ አታስብም ነበር ..ስልኮን አነሳችና ደወለች..እሮዝ ጋር ነው..ተነሳ..?
‹‹አሁኑኑ እፈልግሻለው››
‹‹ምነው ልጄ ምን ሆንሺብኝ..?››
‹‹መቀባጠሩን ተይና በአስቸኮይ ኩማደሩ ቤት ነይ››ስልኩን ጠረቀመችው
ሮዝ የለበሰችውን የለሊት ቢጃማ እንኳን ለመቀየር ጊዜ ማባከን አልፈለገችም…ብን ብላ ነው ግቢውን ለቃ ወደኩማንደሩ ቤት የበረረችው ..ልጄን… ልጄን ምን አደረክብኝ....?የሳሎኑን በር በርግዳ ከፈተችና ወደውስጥ ገባች…
‹‹ምን አደረገብኝ ..?ምነ ሆንሺብኝ ..?ተንደርድራ ልትጠመጠምባት ስትል ገፍትራ ከላዬ አራቀቻት….››
‹‹ይሄ የመቼ ፎቶ ነው....?››ሄለን ነች ጠያቂዋ
‹‹የቱ..? እኔጃ..››ግራ ተጋብታ መለሰች
በእጇ የያዘችውን ፎቶ ወረወረችላት .ደረቷ ላይ አርፎ ወደመሬት ወደቀ… ጎንበስ ብላ አነሳችውና ተመለከተችው..
‹‹እሺ መንም አልጀመርንም ብለሽኝ አልነበር..?››ሄለን ነች በሽሙጥ የጠየቀቻት
‹‹ያው ድሮ እኮ ነው…ግን ከተለያየን ብዙ አመት አልፎናል..?››
‹‹በቀደምለታ የመጣሽው እንታረቅ ልትይው ነበር....?››
‹‹አረበፍጽም ..ስንለያይ ተጣልተን ስለነበረ ቂም ይዞብኛል..አንቺን በማጥቃት እንዳይቀለኝ ስለፈራው ከአንቺ እንዲርቅ ልለምነው ነው…››
‹‹ኦኬ አሁን በጣም ገባኝ….ለመሆኑ ኩማደሩን እንደማፈቅረው ታቂያለሽ..?››
‹‹አታደርጊውም ልጄ..እኔ በህይወት እያለው አታደርጊውም››
‹‹አትጠራጠሪ አደርገዋለው..እንደውም ማግባት ሁሉ የምፈልገው እሱን ነው››
‹‹አረ ተይ ልጄ…እራስሽን ወጥመድ ውስጥ ለምን ትከቺያለሽ....?እሱ እኮ ውስጡ በቀል እንጂ ፍቅር የለበትም…..››
እሱ እኔን አይመለከተኝም…እንደውም እኔም አንቺን ለመበቀል ስለምፈልግ ጥሩ አጋጣሚ ነው…ለመሆኑ ምን ያል ብትበድይው ነው .. ..?ለነገሩ አንቺ አይደለሽ ምንም ብታደርጊው አይደንቀኝም….ለማንኛመው ከዛሬ ጀምሮ በመሀከላችን እንዳትገቢ ልነግርሽ ነው..አሁን የድሮ ፎቶሽን ይዘሽ ወጭልኝ…;››
‹‹በፈጠረሽ ልጄ›› እግሯ ላይ ተደፋች..
‹‹ምንም ብታርጊ ሀሳቤን አታስቀይሪኝም…ምን አልባት በአንድ ነገር..››
‹‹ምንድነው ልጄ …የፈለግሽውን ጠይቂኝ..ከዚህ ሰይጣን ራቂለኝ እንጂ ያልሺኝን ሁሉ አደርጋለው››
‹‹ያው የእኔን ጥያቄ ታውቂያለሽ… ተመሳሳይና የማይቀየር ነው…የአባቴን ማንነት ከነገርሺኝ እተወዋለው…››
‹‹አባቴን....?››ከተደፋችበት ተነሳችና መቀመጫ ይዛ ተቀመጠች
‹‹አዎ ንገሪኝ..ከእሱ እንድርቅ ከፈለግሽ ንገሪኝ››
‹‹እሺ ቁጭ በይ….ነግርሻለው››
ሁለቱም ፊት ለፊት ተፋጠው ተቀመጡ
‹‹እንግዲያው ንገሪኝ ካልሽ ምርጫ የለኝም ነግርሻለው….ግን ለምትሰሚው ነገር እራስሽን አዘጋጂ››
‹‹ግድ የለሽም መግቢያውን ተይና ወደዋናው ታሪክ በቀጥታ ግቢልኝ››
‹‹ይሄውልሽ ልጄ ግማሽ ዕድሜዬን ይሄንን ታሪክ ለሌላ ሰው ይቅርና ለእኔው ለእራሴው ለመናገር ስሸሸው የኖርኩትን ነገር ነው፡፡ይሄው ዛሬ ሳልወድ በግድ ለመናገር ተገድጄያለው፡፡እስከዛሬ ነገሩን ሚስጥር አድርጌው የኖርኩት ለእናቴ ስል ነበር..አሁን ደግሞ ለመናገር የተገደድኩት ለአንቺ ለልጄ ስል ነው..ከእናቴ ስሜትና ደህንነት ይልቅ የልጄን ስሜት እና ደህንነት አስቀድሜ ነው..መቼስ አናቴ ልጅ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ስለምታውቅ ይቅር ትለኛለች ብዬ አስባለው፡፡
ማንኛውም የሰው ልጅ በትዝታ ፈረስ ፊቱን ወደ ኃላው አዙሮ ትናንትናውን ሲያይ መዝለል የሚፈልገው ወይም አለማሰብ የሚመኘው ወይም ምነው ባልኖርኩት ኖሮ ብሎ የሚጠየፈው በጊዜዎች ክፍተት መሀከል የተከወነ ጨለማ ታሪክ ይኖረዋል፡፡የእኔን የተለየ የሚያደርገው ግን ያለፈ ህይወቴ ውስጥ የተከሰተው ጠባሳ አይደለም መሰረዝ እንዲደበዝዝ ማድረግ እንኳን የማይቻል ስለሆነ ዕድለኛ አይደለውም፡፡
ልጄ አንቺ ለእኔ ማለት የበደሌ ምልክት፤ የክስረቴ ትርፍ ነሽ፡፡ሰው ህይወቱን የሚያሳጣው …ማንነትን የሚያወድመው ነገር ከስሮ በዛው ልክ ህይወቱን የሚያለመልምለት እና ለመኖሩ ምክንያት የሆነ ነገር ያተርፋል…እኔ ማለት እንዲያ ነኝ..የነገ ተስፋዬን፤ለመኖር የሚረዳኝን ሞራሌን፤ማንነቴን አጥቼ በምትኩ ግን አንቺን አገኘው፡፡
‹‹አረ የምትይው ነገር ምንም እየገባኝ አይደለም…››መለሰችላት ሄለን
‹‹የእኔ ህይወት ለእኔም ለእራሴ ብዙ ጊዜ አይገባኝም፡፡ግን ቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ልግባ፡፡አንቺን የወለድኩሽ ተደፍሬ ነው፡፡መቼ? ገና 15 ዓመት ሳይሞላኝ፡፡ማን የደፈረኝ ይመስልሻል..?የምትወጂው አጓቴ ነው፡፡ላስተምርሽ ብሎ ከእናቴ በአደራ ተቀብሎ አዲሳባ ወስዶ ደፈረኝ ..አስረገዘኝ …››
‹አጎቴ!!!!.. አጎቴ ማለት የማዬ ወንድም … አንቺን››
‹‹አዎ አጎቴ እኔን …ያ ማለት ደግሞ አንቺ የእሱ ልጅ ነሽ… አባትሽ ነው፡፡
‹‹እኔ አላምንም…››ሄለን ምትሆነው ምትናገረው ነገር ጠፋት
‹‹ልጄ ነፍስ ካወቅሽበት ጊዜ አንስቶ አባቴ ማን ነው ?ብለሽ ስትጠይቂኝ..የተለያየ ሰበብ እየፈጠርኩ ልነግርሽ ያልቻልኩት ነገሩ ለሰሚውም ግራ ሰለሆነብኝ ነው፡፡ ልጄ እስቲ አስቢው በገዛ አጐቴ ተደፍሬ አንቺን እንደወለድኩሽ ስትሰሚ በአንቺ ሰነ-ልቦና ላይ የሚያደርሰውን መረበሽና ተፅዕኖ በምን ማረጋገጥ እችላለው? እንደእኔ ስብርብር ብትይብኝስ.?.ከሁሉም በላይ ደግሞ ይሄ ጉዳይ እናቴ ጆሮ ይሄ ዜና ቢደርስስ ?የገዛ መንትያ ወንድሟ ከመሀጸኖ ፈልቅቃ አምጣ የወለደቻትን እና አደራ አሳድግልኝ ብላ ያስረከበቻትን ጨቅላ ልጆን በድልዱም ቢላዎ ገዝግዞ እንዳረዳት እና ህይወቷን እንዳበከተባት ብትረዳ በድንጋጤ ህይወቷ ባያልፍ እንኳን ጨርቋን ጥላ ማበዶ ይቀራል ብለሽ ታስቢያለሽ…?.ለዚህ ነው ከአንቺ ጋር ስጋጭ እና ስጣላ የኖርኩት፡፡ ለዚህ ነው እራሴን እንደ ጥፋጠኛ አስቆጥሬ ስባልግ እና ስንዘላዘል በገዛ ስህተቴ እደወለድኩሽ እዲታሰብ አድርጌ ግማሽ ዕድሜዬን እንደጋጠወጥ እና እንደ አለሌ ሸርሙጣ እየታሰብኩ በመኖር እራሴን ያሰቃየውት...እርግጥ አልዋሽም ሸርሙጣ የሚለው ስም አይገባኝም አልልሽም..በደንብ ይገባኛል..፡፡ግን በሽታ ሆኖብኝ ነው፡፡ከመደፈሬ ጋር የተፀናወተኝ እኔ እራሴ የምጠየፈው እና የምፀፀትበት ክፉ በሽታዬ ነው፡፡
ልጄ እንግዲህ እውነቱ ይሄ ነው፡፡አባትሽ የምትወጂው አጐትሽ ነው..ከአሁን ቡኃላስ እሱን መውደድሽን ትቀጥያለሽ…?እንግዲህ እሱ የአንቺ ጉዳይ ነው፡፡እኔን ግን ካጠፋውት በላይ ስቀጣ የኖርኩ ሚስኪን እናት ነኝና እባክሽ ይቅር በይኝ እና ቀሪ ህይወቴን ትንሽም ቢሆን ተስፋ እንዲኖራት እርጂኝ፡፡ከእዚህ ሰውዬ ራቂ..እሱን በጣም በድዬዋለው….ሊያገባኝ ሲዘጋጅ ነው ጥዬው ወደአዲስ አበባ የገባውት ..ስለዚህ ለአመታት ሊበቀልኝ ሲጥር እደነበረ አውቃለው..እና ልጄ ….
…ሄለን ከተቀመጠችበት ተነስታ ተንደርድራ ነው እግሯ ላይ የተደፋችባት….‹‹እማዬ የምትችይ ከሆነ ይቅር በይኝ..ባክሽ ይቅር በይኝ››እየነፈረቀች ተማፀነቻት
ሮዝ ከገባችበት መደንዘዝ ውስጥ እንደምንም ነቃችና እሷም ተከትላት ቁጢጥ በማለት ልጆን ከተደፋችበት አንስታት አቀፈቻት… አገላብጣ ሳመቻት ‹‹ልጄ ….ልጄ