አትሮኖስ
281K subscribers
111 photos
3 videos
41 files
478 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ምንትዋብ


#ክፍል_ሁለት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ


... እሷ የሽማግሌዎቹ ቁርጥ ሳይታወቅ፣ ከጥላዬ ሌላ ለማንም እንድትሰጥ አትፈልግም። ብቻ አባባ ለዝኸ ትኩር ብሎ ሲያየኝ ለነበረው ሰውየ እንዳይሰጡኝ አለች፣ ኢሳያስን እያየች።
ተጨነቀች፤ ተጠበበች፣ ብረሪ ብረሪ አላት። ኸጥላዬ ጋር ተያይዘን እንጠፋለን እንጂ እሱን አላገባም አለች።

እሷ ይህንን ስታሰላስል አባቷ አላስችል ብሏቸው እንግዶቹ
ተመልሰው የመጡበትን ምክንያት በዘዴ ለማወቅ፣ “ኸጐንደር ነው
ኸሌላ የመጣችሁ?” ሲሉ ጠየቁ።
የወለተጊዮርጊስ ጀሮዎች ተነቃቁ።
“ኸጐንደር ነው የመጣን” አለ ኢሳያስ። ትንሽ ካመነታ በኋላ፣
“እንግዲህ እንንገርዎ እንጂ” አለና አብረውት የመጡትን ተመለከተ።
የተግባቡ መሰለው። ፊቱን ወደ ግራዝማች መልሶ ፈገግ አለ። ዐይን ዐይናቸውን እያየ፣ “ግራማች… የዛን ዕለቱ እመምተኛ እኮ ንጉሡ ራሳቸው... አጤ በካፋ ነበሩ” አላቸው።

ግራዝማች ከመደቡ ላይ ተወርውረው ተነሡና፣ “በወፍታው!” አሉ፤ ሰንበት የሚሳለሙትንና በየዓመቱ የሚዘክሩትን ደብራቸውን ወፍታ
ጊዮርጊስን ጠርተው።ራሳቸውን በሁለት እጆቻቸው ይዘው፣ “ጃንሆይ ራሳቸው? እኛ እንደ
ዋዛ ኸዝኸ ተኝተው የነበሩቱ?” አሉ፣ ተቀምጠውበት የነበረውን መደብ በሌባ ጣታቸው እያመለከቱ።

ግራዝማች በህመምና በሐዘን ምንክንያት የንጉሠ
ነገሥቱ የንግሥ ሥርዐት በተከበረበት ወቅትና በበዓል ጊዜ ንጉሠ ነገሥቱን በዐይን ለማየት ዕድል አግኝተው አያውቁም ነበርና ንጉሠ ነገሥቱን ባለማወቃቸው አዝነው ራሳቸውን ነቀነቁ።

“ምነዋ እንደዝኸ ጉድ ትሠሩኝ? እንዲያው እንዴት ያለ ፌዝ ነው
ምትነግሩኝ? እንዳው በወፍታው ምን ጉድ ነው ምትነገሩኝ?” እያሉ
ራሳቸውን በሁለት እጆቻቸው እንደያዙ ቆመው ቀሩ። ሰውነታቸው ብርክ እንደያዘው ተንቀጠቀጠ፤ ትከሻቸው ላይ ያጣፉት ጋቢ ወርዶ መሬት ነካ።

የተነገራቸው ቀልድ መሆኑን የሚያረጋግጥላቸው የፈለጉ
ይመስል ዐይኖቻቸውን ከአንዱ እንግዳ ወደ ሌላው አፈራረቁ።
እንግዶቹ በሁኔታቸው ተደናገጡ። እንኰዬ ባላቸውን እንባ ቀረሽ
ተመለከቱ፤ ተነሥተው ጋቢያቸውን ሊያስተካክሉላቸው ፈልገው
መነሣት አቃታቸው።

“በተክልየ ይቀመጡ ግራማች” አላቸው ኢሳያስ፣ ሁኔታቸው
አስደንግጦት።

ግራዝማች ራሳቸውን እየነቀነቁ ለመራመድ ዐቅም እንዳነሳቸው
ሁሉ ጋቢያቸውን ሰብሰብ አድርገው ቆም አሉና ጉልበታችው
የከዳቸው ይመስል፣ በሁለት እጃቸው ደግፈውት ተመልሰው መደቡ ላይ ተቀመጡ። የሚሉትን ቀርቶ የሚያስቡትን ማወቅ ተስኗቸው፣ ግንባራቸውን ኩምትር አድርገው፣ ዐይኖቻቸውን መሬት የተነጠፈው አጎዛ ላይ ተክለው ቀሩ።

ወይዘሮ እንኰዬና እናታቸው ትኩረታቸው ግራዝማች ላይ ነበርና
መቀመጣቸውን ተከትለው ዐዲስ እንደሰማ፣ “በቁስቋሟ!” አሉና
እርስበርስ ተያዩ። ወለተጊዮርጊስም በቁስቋሟ ብላ አማተበች። አያቷ ሆኑ ቅድመ
አያቶቿ የሚያከብሯትን፣ የሚማጸኗትን፣ የሚዘክሯትን፣ ባለውለታቸውን፣ በዕለተ ቀኗም ብዙ ድል የተቀዳጁባትንና እሷ ራሷም ብትሆን “ግጥሜ”
የምትላትን ቁስቋም ማርያምን ጠርታ። በግራ እጇ ኣፏን ይዛ፣ ንጉሡ ራሳቸው እኛ ኸዝኸ ኸመደብ ላይ ተኝተው የነበሩቱ? እኛ ፊታቸውን ሳጥብ፣ አጥሚት እየሠራሁ ሳጠጣ... እጃቸውን ሳስታጥባቸው የነበሩቱ
እንዴት ብለ? ንጉሡ ራሳቸው? ጉድ ጉድ! የዛሬውስ ቀን ምንያለውን ጉድ ይዞ መጣ እናንተዬ? አለች፣ መጋረጃውን ለቃ፣ ራሷን በሁለት እጆቿ ይዛ። ጥቂት ቆይታ መጋረጃውን እንደገና አጋጥማ ይዛ ወደ እንግዶቹ ተመለከተች፤ ያወጋሉ። የሚሉትን ለመስማት ሞከረች።
ሐሳቧ ግን አልሰበሰብ አለ።
ከጥቂት ሳምንታት በፊት ሕመምተኛ የነበሩት፡ የአሁኑ ንጉስ። ፊቷ ላይ ድቅን እያሉ አስቸገሯት። መላ ቤተሰቡ ንጉሥ መሆናቸውን እንዴት ሳያውቅ፣ ሳይጠረጥር እንደቀረ ገረማት። ነገሩን በቅጡ ለመመርመር ሐሳቧ ወደ ኋላ ነጎደ።....

የመጡ ቀን፣ እንደ ልማዷ ቤታቸው ደጃፍ ላይ ተቀምጣ የእነዚያን
የአስታራቂ ሽማግሌዎች መምጣት ትጠባበቃለች። ግቢው መግቢያ ላይ ሰዎች ስታይ ብድግ አለች። “እረ የታመመ ሰው ነው መሰል ይዘው የመጡ” አለች፣ ዛሬ ከመጡት እንግዶች ውስጥ ሁለቱና ሌሎች ሁለት ሰዎች አንድ ሰው ደግፈው ድንገት ግቢው ውስጥ ሲገቡ አይታ።

“እነማ?” እያሉ እናቷ፣ አባቷና አያቷ ከውስጥ በችኮላ ወጡ።
በርግጥም የታመመ ሰው እንደመጣ ሲያውቁ ደነገጡ፣ “ግቡ! ግቡ!” እያሉ መንገድ ለቀቁ። ነፍጥ የያዙ፣ ፈረስና በቅሎ ሳይቀር ያስከተሉ በርካታ ሰዎች እየተገፋፉ ገቡ። ሁሉም የመረበሽ መልክ ይታይባቸዋል።
እምብዛም ግርግር የማያውቀው ግቢ ትርምስምስ አለ። የተረጋጋው
የእነግራዝማች ቤት ለወከባና ለድንጋጤ ቦታ ለቀቀ።

አራቱ ሰዎች ወደ ቤቱ ውስጥ ገብተው፣ አቅፈው ደግፈው ያመጧቸውን ሕመምተኛ መደብ ላይ አሳረፏቸው። ወለተጊዮርጊስ፣ እኚህ መሣሪያ የያዘ ወጀብ የተከተላቸውና በጽኑ የታመሙ የሚመስሉት ሰው ማን መሆናቸውን ለማወቅ እጇን ደረቷ ላይ አድርጋ ተመለከተች፤ ግንባሯ
ኩምትር፣ አፏ ከፈት ብሏል። እናቷ፣ “ወለቴ እስቲ ውሃ” ሲሏት
በፍጥነት ወጥታ በቅምጫና አምጥታ አቀበለቻቸው።
ያን ሰዐት፣ ዙርያውን በቆሙት ሰዎች መሃል፣ ባለ ንቅሳት አንገቷን
ሰገግ አድርጋ ሕመምተኛውን አየች። በጽኑ እንደታመሙ አስተዋለች፤
ይቃዣሉ፤ ይቃትታሉ፤ ይወራጫሉ፤ ብርክ እንደያዘው ይንዘፈዘፋሉ።
ሮጥ ብላ ከመጋረጃው ጀርባ ቡሉኮ አምጥታ ደረበችላቸው።

ሰውየው የመጣላቸውን ውሃ መጠጣት ቀርቶ ዐይናቸውን መግለጥ ሆነ አፋቸውን መክፈት አልቻሉም። ግራዝማች መንበር ተደናግጠው፣
“ምንን ሁነው ነው? እመማቸው ምንድር ነው? እያሉ ከወተወቱ በኋላ፣ አንደኛው እንግዳ፣ “ንዳድ ሳትሆን አትቀርም። ቆላ ሲወርዱ ነድፋቸው ፊት ታመው ያቃሉ። ኸናንተ ዘንድ ይዘነ መጣነ” በማለት መልስ ሰጡ፣ ንጉሠ ነገሥቱን ይዘው ማንም ሰው ቤት ስለማይገቡ፣ ቋራ ውስጥ
የታወቁት ባላባት ቤት የትኛው እንደሆነ ጠይቀው የመጡት መሆኑን ሳይናገሩ።
ግራዝማችም፣ “ኧረ ደግ አረጋችሁ፤ ስንኳንም መጣችሁ። ቤት የአብርሃምም ማዶል?” ብለው አደግድጎ የቆመውን አሳላፊ፣ “እስቲ ኸድና ያነን በሪሁንን ተሎ ይዘህ ና” አሉት፡
መድኃኒተኛው በሪይሁን ከመቅጽበት መጥቶ አንድ እጁን
ሕመምተኛው ግንባር ላይ አስቀምጦ ራሱን ነቀነቀ። ጉንጫቸውን ዳበስ፣ እጆቻቸውን ጨበጥ፣ ጨበጥ አድርጎ መልሶ እጁን ግንባራቸው ላይ አሳረፈና፣ “ንዳድ ነች” አለ።

“ተሎ በልና መዳኒት አርግላቸዋ” አሉ፣ አንደኛው እንግዳ።

በሪሁን ለሰውየው መልስ ሳይሰጥ በቅዎጫና ተቀምጦ የነበረውን
ውሃ ደጅ ወጣ ብሎ ቀነሰለት። ይዞት ከመጣው ከረጢት ውስጥ
የደቀቀ ቅጠል መሳይ ነገር ቆንጠር አድርጎ በውሃው በጠበጠና በርከክ ብሎ የሕመምተኛውን ጭንቅላት በአንድ እጁ ቀና አድርጎ በመዳፉ
ጋታቸውና ቆሞ ተመለከታቸው።
ይህ ሁሉ ሲሆን ሰውየው ዐይናቸውን አልከፈቱም፤ አንገታቸው ወደ አንድ ወገን ዘንበል ብሎ ተኝተዋል። የሚሆነውን ሁሉ የሚያውቁ
አይመስሉም።
“በሪሁን ሁሉም አልገባም። ኸመዳኒቱ ትጨምርላቸው?” አሉ
ግራዝማች መንበር፣ ከሰውየው አፍ ቀስ እያለ የሚንጠባጠበውን ፈሳሽ እያዩ።

በሪሁን፣ “ግድ የለም የገባው ይበቃል” ሲል ሰውየው አስመለሳቸው።
ወለተጊዮርጊስ ፈጠን ብላ ንፁህ ሀጨርቅና ውሃ አምጥታ የሰውየውን አፍ ጠራረገችላቸው፤ አካባቢውንም አጸዳች።

“መዳኒቱ ወጥቷል። እንደገና አርግላቸዋ” አሉ ግራዝማች፣ በሪሁንን።
“ትንሽ ይርጋላቸውና አረግላቸዋለሁ።”
መድኃኒቱን እንደገና ግቷቸው በርከክ ብሎ ተጠባበቀ፡፡ ሰውየው
አላስመለሳቸውም።
👍111
#ትኩሳት


#ክፍል_ሁለት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

#እንደወረደ_ነውና_ለአንባቢ
#የማይመቹ_እኛ_ፀያፍ_የምንላቸው
#ቃላቶች_አሉትና_አሁንም
#በድጋሚ_እንደምናገረው
#የማይመቸው_እንዳታነቡት
#እመክራለሁ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

አማንዳ
ለጥቂት ጊዜ


ያን ሰሞን አንዲት ቆንጆ አሜሪካዊት ነበረችኝ፣ አይኗ
ሰማያዊ፣ ፀጉሯ በጣም ንፁህ ቡና አይነት፡፡ እጅግ ደስ ትላለች፣
አልጋ ውስጥ ልብ ታጠፋለች ግን በማልፈልጋት ሰአት ሆቴሌ
እየመጣች አላሰራ ስላለችኝ፤ ቤተ መፃህፍት እየሄድኩ መስራት ግድ
ሆነብኝ፡፡ ሆቴሌ ስታጣኝ ወደ ቤተ መፃህፍቱ መምጣት ጀመረች።

እሷን ለመሸሽና በዚያውም ባህራምን ለማወቅ ስል ሀበሾቹን
እጠጋቸው ጀመር ምግብ ቤት አብሬያቸው እገባለሁ፣ ካፌ
ዶርቢቴል አብሬያቸው ካርታ እጫወታለሁ ከባህራም ጋር ግን ላይ ላዩን እየቀለዱ ለመሳቅ እንጂ፣ የልብ ለመጫወት አጋጣሚ ለጊዜው አላገኘሁም። ይልቅስ ከሀበሾቹ ጋር ግንኙነት በማድረጌ «ሚስቶቻቸውን» በመጠኑ እያወቅኳቸው ሄድኩ፡፡

የነበርንበት ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሴቶች ከወንዶቹ በጣም ይበዛሉ፡፡
ስለዚህ ለሁሉ ሴት 'ሚዳረስ ወንድ የለም....አሉ ሶስት፣ አራት፣
አምስት 'የሆኑ ወንድ 'ሚያድኑ ልጃገረዶች። ታድያ ወንዱን ቆንጆ
ቆንጆዎቹ ይዘውታል፣ ተጠምጥመውበታል። ነፃ የሆነ ወንድ አይገኝም፣ ቢገኝም ወይ የደስ ደስ የለውም፣ ወይ ጥቁር ነው። ጥቁር ደሞ ምን ቢወዱት አገሩ መመለሱ አይቀርም፡፡ ብልጥ ወይም ውብ ወይም እድለኛ ካልሆኑ፣ ፈረንሳይ ወንድ ማግኘት አይቻልም። ሳያገቡ የማርጀት ፍርሀት በወራቱ ዋሻ ሰአመታቱ ጫካ አድፍጦ
ይጠብቃል.

ጥቁሮቹ ወንዶች ገና እንደመጡ፣ በንግድነት ምክንያት ቆንጆ
ሴት ማጥመዱን ለጊዜው ስለማያውቁበት፣ የተገኘችውን እሺ ብለው ይቀበላሉ። የምትገኘው ደሞ ቆንጆ ያልሆነች ናት፣ ስለዚህ ማቆያ
ናት...

«የሀበሾቹ ሚስቶች» ጎደሎ ብጤዎች ነበሩ፡- እዚህ ቅርፅ
ይጎድሳል፣ እዚያ ድምፅ ይጎድላል፣ እዚያ ጠባይ ይጎድሳል። ብቻ፣ሉልሰገድ እንዳለኝ ሁሉም ያ ነገር ኣላቸው ለጊዜው ሀበሾቹ የፈለጉት እሱን ነው:: መልኩ፣ የደስደሱ፣ ደማምነቱ፣ ጠባዩ፣ በኋላ
ዝግ ተብሉ ይፈለጋል ከሁሉም አስቀያሚ አማንዳ ሳትሆን አትቀርም፡፡ ድብልብል
አሜሪካዊት ናት፡፡ ወፍራም አንገቷ ዙርያ ስጋው ተጣጥፏል፣ ሽንጥ
ሚሉት የላትም፣ ስትራመድ የሚንቀጠቀጠው ባቷ ረዥም ቂጥ ይመስላል። በጭራሽ ስሜት አትቀሰቅስም። ሉልሰገድ ለምን
እንደያዛት ለጊዜው ሊገባኝ አልቻለም፡፡ የቸገረው እርጉዝ ያገባል ይባላል፣ እሱ ግን አቅፏት ይዞራል። ወገቧ ዙርያ እጁ ስለማይደርስ ትከሻዋን አቅፎ እሷ ወገቡን አቅፋ ሲሄዱ አያቸዋለሁ። የአማንዳ ፈገግታ ደግና ንፁህ ነው፣ ትንንሽ አይኖቿ ንፁሀ ሰማያዊ ናቸው፣ ረዥም ፀጉሯ በጣም ንፁህ ነጭ ሆኖ፣ ጨረቃ ውስጥ ተነክሮ የወጣ ይመስላል። ግን ይህን ሁሉ ውበት ጮማዋ አፍኖ ይዞ እንደሌለ አድርጎታል። ስታያት ውፋሬዋ ነው 'ሚታይህ፣ ስታስታውሳት ጮማዋ ነው ትዝ ሚልህ

ሲልቪ ግን በጣም ቆንጆ ናት። «እጥር ምጥን» ያለች ፈረንሳዊት ሆና፣ ቡናማ ጉልህ አይኖቿ ውስጥና ውብ ሰፊ አፏ
ዙርያ እንደ ነበልባል የሚውለበለበው ፈገግታዋ ልብ ያሞቃል። ወደ ኋላ የተለቀቀው ንፁህ ጥቁር ፀጉሯ ያብለጨልጫል፣ ስትራመድ
ረዥም አንገቷን እያወዛወዘች ስለሆነ፣ ይሄ ጥቁር ሀር ፀጉሯ ዥው ዥው ይጫወታል። ከታች ደሞ አበጥ ያለው ዳሌዋ ያንኑ ያህል ይወዛወዛል። እግሯ በብዙ ጥንቃቄ የተቀረፀ ውብ ፍጥረት ነው::ፍቅርም ምኞትም የምትቀሰቅስ ወጣት ትመስላለች። ተመስገንን በጣም ትወደዋለች ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡ ይሄ ተመስገን ፈረንሳይ አገር የተስማማው ይመስላል።

ዩኒቨርሲቲውን «ሲቴ» ይሉታል። ሲቴ ውስጥ መኝታ ቤት
ያላቸው ሀበሾች ተመስገን፣ ሉልሰገድ፣ ተካ፣ ሀይለየሱስ ናቸው፡፡
ሌሉቹ እንደኔው የሆቴል ክፍል ወይም የከተማ ቤት ተከራይተው
ይኖራሉ ቆንጆዋን አሜሪካዊት እንዳላገኝ ስፈልግ ከሉልሰገድ ወይም ከተመስገን ቁልፍ ለምኜ መኝታ ቤታቸው ቁጭ ብዬ ሰራለሁ::ሀይለየሱስ ቤት እንዳልሰራ ሰውየውን አልወደውም። ተካ ቤት
እንዳልሰራ ደሞ የተካ ቤት ይገማል። አይ ተካ! እግዜር ይይለት አንዳንዴ እንኳ እግሩን ቢታጠብና እግር ሹራቡን ቢያጥብ ምን ቸገረው ነበር? ዝም ብሎ ብቻ ጥፍሩን እየነከሰ መነጫነጭ ምን ያረግለታል?

ሉልሰገድ ወይም ተመስገን ቤት ቁጭ ብዬ ስስራ አንዳንዴ
ባህራም ይመጣል፡፡ ትንሽ እናወራና ፂሙን ተላጭቶ መልካም ስራ ብሉኝ ይወጣል። ፀጉራም ነው። እጆቹን፣ ደረቱን፣ አንገቱን፣ ፊቱን ፀጉር ወሮታል። ፂሙን ሲላጭ አይኑ፣ አፍንጫውና ጆሮው ብቻ ናቸው መላጨት የሌለባቸው:: ቢሆንም ፀጉሩ አያስቀይምም፡፡ በጣም
ንፁህ ሰው ነው።

አንዳንዴ ደሞ ቁጭ ብዬ ስሰራ ድቡልቡሏ አማንዳ ወይም
ውቢቷ ሲልቪ ይመጣሉ ወዳጃቸውን ፍለጋ፡፡ ቀስ በቀስ እነዚህን ሁለት ልጃገረዶች» እያወቅኳቸው፣ እየወደድኳቸው ሄድኩ፡፡ እነሱም ሊወዱኝ እንደጀመሩ ታወቀኝ። ስለራሳቸው ኑሮ በመጠኑ ይነግሩኝ ጀመር ..

አንዳንድ ቅዳሜ ማታ ሀበሾቹና ጓደኞቻቸው «ሱርፕሪዝ ፓርቲ»
ያደርጋሉ። «ሰርፕሪዝ ፓርቲ» ድንገተኛ ብጤ ነው። ታስቦ የታቀደ
ፓርቲ ሳይሆን፣ ጓደኛሞች ሲገናኙ «ዛሬ ምን እናርግ? ሲኒማ
እንግባ ወይስ ምን ይሻላል?» ይባባሉና ለምን ሰርፕሪዝ ፓርቲ
አናረግም?» ይላሉ፡፡ ያን እለት ማታ ፓርቲው ይደረጋል። የተገኙ
ሰዎች ይጠራሉ፣ የራሳቸውን መጠጥ ይዘው እንደሚመጡ የታወቀ ነው:: አንዱ ቤት ፓርቲው ይደረጋል። ለዚህ ጉዳይ ሀበሾቹን
ባህራም ያገለግላቸዋል
ይጀምራል፤ ወንዶቹን ይጠራል፣ ሴቶቹን ይጋብዛል፣ እዚህ ትእዛዝ
እንደ አውሎ ነፋስ በፍጥነት መዘዋወር ይጀምራል ወንዶቹን ይጠራል ሴቶቹን ይጋብዛል እዚህ ትእዛዝ እዚያ ምክር ይሰጣል፣ ከዚህ ዲስክ ከዚያ ሴት ይዋሳል፣ ፓርቲው ይጀመራል። ተሳታፊዎቹ ወንዶች ኣብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያንና ኢራናውያን ናቸው፣ የሁለቱ አገሮች ማህበር ይመስላል።

እንዲህ አይነት ፓርቲ ውስጥ ነበር ሉልሰገድ አማንዳን ያገኛት። ፓርቲው ውስጥ ጥቂት ሴቶች ብቻ ነበሩ፣ እነሱም ተይዘዋል፡፡ ያልተያዙ አንዲት በጣም ደቃቃ የሆነች የሩቅ ምስራቅ
ልጅና እንዲት አስቀያሚ ድቡልቡል ኣሜሪካዊት ብቻ ናቸው::ምስራቃዊቷ በጣም ደስ ትላለች፣ ግን ሉልሰገድ እሷን ይዞ አልጋ ውስጥ ሲገባ ሊታየው አልቻለም። «ዎ! ብትሞትብኝስ?» ብሎ አሰበ፡፡ ተዋት። ድቡልቡሏ አሜሪካዊት ፈፅማ ደስ አትልም፣ ግን ሙዚቃውና መጠጡ እየገፋፉ ወደሷ ወሰዱት። ተዋወቃት። ስሜ
አማንዳ ነው አለችው፣ አብረው ይደንሱ ጀመር፡፡ በእንግሊዝኛ
እያወሩ ሁለቱም በብሉይ ጠጡ፣ ሞቅ አላቸው:: ስታቅፈው
ስታናግረው በጣም ደስ እያለችው ሄደች ይስማት ጀመር

«ተው እዚህ አትሳመኝ» አለችው

«ምናለበት?» አላት ጆሮዋን እየሳመ አልችልም፡፡ ስሜቴ በጣም ይቀሰቀሳል» አለችው:: ድምፅዋ
በጣም አቆመበት።

ታድያ ምናለበት?» አለ እየተሻሻት

"ያኔ መሳም ብቻ አይበቃኝም» ብላ በሀይል ተጠጋችው::

ሉልሰገድ ቀስ ብሎ ወደ አንዱ መኝታ ክፍል ገብቶ እዚያ
ይሳሳሙ የነበሩትን ሁለት ፈረንሳዮች አስወጣቸው። (መኝታው የማን እንደሆነ እንጃ መብራቱን አጠፋ። ተመልሶ መጥቶ አማንዳን ወደዚህ ጭለማ መኝታ ቤት ወሰዳት፡፡ በሩን ቆለፈ። አልጋው ላይ አጋድሞ ይስማት ጀመር። እየሳመ፣ እያሻሽ ሙታንታዋን አስወለቃት። ጭለማ በመሆኑ አስቀያሚ መልኳ ስለማይታየውና፣አሳሳም ከማወቁም በላይ ወፍራም ገላዋ ምቹ ስለሆነ፣ እጅግ በጣም ተደሰተባት ጠግቦ ከላይዋ ሊነሳ ሲል፣ እቅፍ አደረገችውና እንዳይነሳ ከለከለችው
👍231