#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
ከቶሎሳ ጋር በስልክ ካወራ በኋላ የአብዱላሂ ፊት አልፈታ አለ፡፡ሊያሳይ የሚሞክረው ፈገግታ ሁሉ የውሽት መሆኑ እያስታወቀበት መጣ፡፡ ጌትነት ግራ ተጋባ፡፡ ተጨነቀ። ከሽመልስ አይዞህ ባይነት በስተቀር የሚተማመንበትና ተስፋ የሚያደርግበት ነገር አጣ፡
"ወይ ፈጣሪዬ አብዱላሂም ሰለቸኝ ማለት ነው? ምን አባቴ ባደርግ ይሻለኛል? ምነው አልሰማህ አልከኝ የአባቴ አምላክ? የሱን አደራ ለመወጣት ነውኮ የምጨነቀው። የዚያች ምስኪን እናቴ አምላክ እባክህ እርዳኝ ይህንን በሃሳቡ ማውጣትና ማውረድ የጀመረው በዚህ ሁለትና ሶስት ቀን ውስጥ የአብዱላሂ ፀባይ ሙሉ ለሙሉ ስለተቀየረበት ነው።
የስድስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ የማታ ትምህርት ፕሮግራም ክፍል አመልካ
ቾች የማትሪክ ውጤቶቻቸውንና ትራንስክሪፕቶቻቸውን በማቅረብ እንዲ
መዘገቡ ማስታወቂያ ለጥፏል። በዚሁ መሃል ሽመልስ የጀመረው ክርክር
የመጨረሻ ውሳኔ የሚሰጥበት ዕለት እየደረሰ ነበር፡፡ ያ ቀን ለጌትነት
የሞት ወይም የሽረት ቀን ነበር፡፡ የምሥራች ወይንም የመርዶውን ዜና
የሚሰማበት ዕለት። ክርክሩ ሲጧጧፍ ሽመልስ አስመላሽ አንድ እውነትን ይዞ፣አቶ አባይነህና አቶ ማንአየህ ደግሞ አድልዎንና ሃስትን ተገን አድርገው ሲያፋልማቸው የቆየው ጉዳይ የሚቋጭበት ቀን መጣ፡፡
አቶ ሽመልስ ያንን ግትር አቋሙን እንዲለውጥ አቶ አባይነህ ብዙ ጥረት
አድርገው ነበር። ሲጨንቃቸው በመለማመጥና በመለመን ትንሽ ፋታ
ሊያገኙ ደግሞ በዛቻና በማስፈራራት ሊያንገዳግዱት ሞክረው ነበር፡፡
ሊወድቅላቸው ግን አልቻለም፡፡ በአማላጅ ብዙ ሞከሩ። ወይ ፍንክች የአባ ቢላዋ ልጅ! አቶ አባይነህ ካደረጓቸው በርካታ ሙከራዎች መካከል በአንዱ ይሸነፍልኛል ብለው ገምተው ነበር። ግን በቀላሉ የሚሸነፍ እጁን የሚሰጥ ሆኖ አልተገኘም። ባቀረበው አቤቱታ መሰረት የድርጅቱ የበላይ ሃላፊ ስለጌትነት መኩሪያና ስለ ፀሃይ አስፋው ቅጥር ጉዳይ የሚያጣራ ሶስት አባላትን የያዘ ኮሚቴ አቋቋሙ። ኮሚቴው ማስታወቂያው ከወጣ በት ቀን ጀምሮ ፀሀይ አስፋው የቅጥር ፎርማሊቲ እንድታሟላ እስከተደረገበት ጊዜ ድረስ የነበረውን ሂደት ማጣራት ጀመረ።
ኮሚቴው የመጀመሪያውን የፅሁፍ ፈተና ውጤትና ለመጨረሻ ጊዜ በተካሄደው የቃለ መጠይቅ ፈተና የተያዘውን ቃለ ጉባኤ በዝርዝር በማጥናት የውሳኔ ሃሳቡን አጠናቅሮ አቀረበ፡፡ ኮሚቴው የመጀመሪያ የፅሁፍ ፈተና የወሰዱትን የስድስቱንም ተፈታኞች የፈተና ወረቀቶች የመረመረ ሲሆን ፀሃይ አስፋው ዶሮ የጫረው ከሚመስለው የእጅ ጽሁፉ ጀምሮ በይዘቱ
በጣም ደካማ ለነበረው ሥራዋ የተሰጣት ከፍተኛ ውጤት አድሎአዊነትን
የሚጠቁም ሆኖ አግኝቶት ነበር። የቃለ መጠይቆቹ ፍሬ ሃሳቦችና የተሰጡት ነጥቦች አቶ ሽመልስ የያዘውና እነ አቶ አባይነህ የያዙት ፍፁም የማይመሳሰል ከመሆኑም በላይ ፀሀይ አስፋው በብርቱ ክንድ እንደተደገፈች የሚያሳዩ በርካታ ጠቋሚ መረጃዎች ተገኙ። ከዚህ በመነሳትም የመጨረሻውን ውሳኔ ለመስጠት እንዲያስችል በሁለተኛነት ደረጃ ተመዝግቦ ወድቋል የተባለው ጌትነት መኩሪያና ፀሀይ አስፋው ብቻ በድጋሚ ተጠርተው ሌላ የመመዘኛ ፈተና እንዲሰጣቸው ኮሚቴው የውሳኔ አስ
ተያየት አቀረበ፡፡ የበላይ ሃላፊውም የኮሚቴውን ሃሳብ አፀደቁት። የኮሚ
ቴውንና የዋና ስራ አስኪያጅን ውሳኔ በሰማበት እለት ሽመልስ የተሰማውን ደስታ የተመለከተ ጉድ ይል ነበር ለእውነት ሲል ተከራክሮ ለሀቅ ሲል ታግሎ የድል ፍንጭ ያየበት ዕለት በመሆኑ ደስታው ልዩ ነበር።ሀቅ ከሃሰት ውቅያኖስ ውስጥ ብትወድቅም ትሟሟ እንደሆነ እንጂ እን
ደማትጠፋ አምኖ በልቡ ተስፋን አሳደረ፡፡ “ዘመዱ ስለሆነ ነው። በእናቱ በኩል የባሌ ሰው ነው፡፡ የአጎቱ ልጅ ነው..." እያሉ አንዳንዶቹ ማስወራት ጀምረው ነበረና በእርግጥም ጌትነትን ያለችሎታው ሊረዳው ጥብቅና የቆመለት መሆን አለመሆኑ የሚታወቅበት፣ እሱ ወይንም እነ አቶ አባይነህ የሚጋለጡበት፣ እንክርዳዱና ስንዴው የሚለይበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ በመድረሱ ደስታው ገደብ አልነበረውም፡፡ በዚሁ መሰረት ጥሩ የብቃት መለኪያ ፈተና በገለልተኛ ወገን እንዲዘጋጅ ተደረገ፡፡ ፀሀይ ውሳኔው ከተ
ሰጠበት ቀን ጀምሮ የሞላችው የቅጥር ፎርማሊቲ ዋጋ የሌለው መሆኑ
ተገልፆ ለአዲሱ ፈተና ራሷን እንድታዘጋጅ በተነገራት ጊዜ ከድንጋጤዋ የተነሳ ዕቃ ሰበረች።
እውነትና ንጋት እያደር ይጠራል አይዞህ ተስፋ አትቁረጥ በማለት ሞራል ሲስጠው የቆየው ሽመልስ የክርክሩ ውጤት ምን ደረጃ ላይ እንደደረሰ የሚያሳውቀው እንደነገ ሆኖ ዛሬ አብዱላሂና ቶሎሳ በያዙት ቀጠሮ መሠረት ተገናኝተው አምሽቶ መግባቱ ነበር። አብዱላሂ ለንቦጩን ጥሏል። ፊቱ እንደ ፊኛ ተነፍቷል። ጌትነት ደነገጠ፡፡
“እንደምን አመሸህ ጋሼ አብዱላሂ?" አለው ፈራ ተባ እያለ፡፡
"ደህና ነኝ!" መልስ አሰጣጡ እንደምንስ ባድር ምናባክ አገባህ? የሚል
ትርጉም ነበረው፡፡ እንደ ውሻ ቡፍ! አለበት።
“ምነው ጋሼ አብዱላሂ ያስቀየምኩህ ነገር አለ እንዴ? ለትንሽ ጊዜ እንጂ
አላስቸግርህም እኮ ቁርጤን እስከማውቅና ጋሼ ሽመልስ የመጨረሻውን ውጤት እስከሚያሳውቀኝ ድረስ ብቻ ብትታገሰኝ ምን አለበት? ሸክም እንደሆንኩብህ ይሰማኛል"
“ወሬውን ተዋ! ወላሂ እኔ ስው እንደዚህ ወሬኛ ሲሆን አልወድም፡፡ሁሉ ነገሬ ፊት ለፊት ነው፡፡ ግልፅ ነኝ፡፡ ግልፅ ሁን!"
“አልገባኝም?" በጭንቀት።
“ከቶሎሳ ጋር በምንድነው የተጣላችሁት?!" ቱግ! አለበት።
"በም.ም. . .ምን. . ነው የተጣላነው?" አፉ ተንተባተበ፡፡
“ውሽታም!! ውሽታም ነህ አንተ! ወላሂ! ውሸታም ነህ፡፡ አምንህ ነበር ታማኝነትህ ግን በገንዘብ ላይ ብቻ ነው፡፡ ይሄ ደግሞ በቂ አይደለም፡፡
ከሌላው ልክስክስ ሌብነት የገንዘብ ሌብነት ይሻላል። ቶሎሳ ወንድምህም
አባትህም ነው ሸዋዬ ደግሞ እህትህም እናትህም ነች አይደለም?!"
"ልክ. . ልክ ነው ጋሼ አብዱላሂ ልክ ነው" በጭንቀት ዐይኑ ቁልጭ ቁልጭ አለ፡፡አብዱላሂ ለምን እንደዚህ በሃይለ ቃል እንደተናገረው ወዲያውኑ አወቀ። በልቡ ሸዋዬ እግዚአብሔር ይይልሽ አለ፡፡ የአልኮል ትሩፋት አይ ስካር? በዚህ አይነት ስንቱ በስካር ቤት ንብረቱ ፈርሷል? ሲል ራሱን ጠየቀ። ወስዋስ ሸዋዬ ወስውሳ ወስውሳ ባስፈፀመችው ድርጊት ምክንያት ጦሱ በየሄደበት ቦታ ሁሉ እየተከተለው ነው። ከሷ ቤት አምልጦ ሲመጣ ይኸውና ዛሬ ደግሞ ጣጣው ተከትሎት አብዱላሂ ቤት እየደረሰ ነው፡፡
ወይ ፍርጃ! ያ ቀን ምን ዓይነት ቀን ነው? ያንን ጠላ ጠጥቶ ድርጊቱን የፈፀመበትን ቀን በጥላቻ አስታወሰው። አብዱላሂ የጌትነት ፊት መለዋወጡን አፉ መንተባተቡን ሲመለከት ቶሎሳ ያጫወተው በሙሉ ትክክል መሆኑን አረጋገጠ፡፡
ንጂስ የሆንክ ሰው ነህ! ሀራም ሥራ! በጣም ብልግና ነው የፈፀምከው።
በል ከነገ ጀምሮ ቤቱን ልቀቅልኝ! ዐይንህን ማየት አልፈለግም! ጓዝህን ጠቅልለህ ወደምትሄድበት ሂድ! እስከዛሬ ያገለገልክበት ዋጋህን ያውልህ!"ሁለት ባለ አሥር ብር ኖቶች ከኪሱ አወጣና ወደ እጁ ዘረጋለት።
“የለም! የለም ግድ የለም ጋሽ አብዱላሂ" ዐይኖቹ እንባ አቀረሩ። ልሳኑ ተዘጋ፡፡ እንደምንም ጉሮሮውን ጠራረገና
“እስከዛሬ ድረስ የዋልክልኝ ውለታ ቀላል አይደለም፡፡ የሰራሁት ተቀጥሬ
ሳይሆን በችግሬ ምክንያት እንድታስጠጋኝ ላምኜህ ነውና ልትከፍለኝ አይገባም፡፡ ውለታህን እግዚአብሔር እንጂ እኔ ልከፍለው የምችለው አይ
ደለም። አንድ የምለምንህ ነገር ቢኖር ግን አሁን አንተ የምትለኝ ሁሉ በፍፁም እኔነቴን ነፃ አእምሮዬን የሚመለከት አለመሆኑን እንድታውቅ ልኝ ነው። ሰው የሚከስሰውና
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
ከቶሎሳ ጋር በስልክ ካወራ በኋላ የአብዱላሂ ፊት አልፈታ አለ፡፡ሊያሳይ የሚሞክረው ፈገግታ ሁሉ የውሽት መሆኑ እያስታወቀበት መጣ፡፡ ጌትነት ግራ ተጋባ፡፡ ተጨነቀ። ከሽመልስ አይዞህ ባይነት በስተቀር የሚተማመንበትና ተስፋ የሚያደርግበት ነገር አጣ፡
"ወይ ፈጣሪዬ አብዱላሂም ሰለቸኝ ማለት ነው? ምን አባቴ ባደርግ ይሻለኛል? ምነው አልሰማህ አልከኝ የአባቴ አምላክ? የሱን አደራ ለመወጣት ነውኮ የምጨነቀው። የዚያች ምስኪን እናቴ አምላክ እባክህ እርዳኝ ይህንን በሃሳቡ ማውጣትና ማውረድ የጀመረው በዚህ ሁለትና ሶስት ቀን ውስጥ የአብዱላሂ ፀባይ ሙሉ ለሙሉ ስለተቀየረበት ነው።
የስድስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ የማታ ትምህርት ፕሮግራም ክፍል አመልካ
ቾች የማትሪክ ውጤቶቻቸውንና ትራንስክሪፕቶቻቸውን በማቅረብ እንዲ
መዘገቡ ማስታወቂያ ለጥፏል። በዚሁ መሃል ሽመልስ የጀመረው ክርክር
የመጨረሻ ውሳኔ የሚሰጥበት ዕለት እየደረሰ ነበር፡፡ ያ ቀን ለጌትነት
የሞት ወይም የሽረት ቀን ነበር፡፡ የምሥራች ወይንም የመርዶውን ዜና
የሚሰማበት ዕለት። ክርክሩ ሲጧጧፍ ሽመልስ አስመላሽ አንድ እውነትን ይዞ፣አቶ አባይነህና አቶ ማንአየህ ደግሞ አድልዎንና ሃስትን ተገን አድርገው ሲያፋልማቸው የቆየው ጉዳይ የሚቋጭበት ቀን መጣ፡፡
አቶ ሽመልስ ያንን ግትር አቋሙን እንዲለውጥ አቶ አባይነህ ብዙ ጥረት
አድርገው ነበር። ሲጨንቃቸው በመለማመጥና በመለመን ትንሽ ፋታ
ሊያገኙ ደግሞ በዛቻና በማስፈራራት ሊያንገዳግዱት ሞክረው ነበር፡፡
ሊወድቅላቸው ግን አልቻለም፡፡ በአማላጅ ብዙ ሞከሩ። ወይ ፍንክች የአባ ቢላዋ ልጅ! አቶ አባይነህ ካደረጓቸው በርካታ ሙከራዎች መካከል በአንዱ ይሸነፍልኛል ብለው ገምተው ነበር። ግን በቀላሉ የሚሸነፍ እጁን የሚሰጥ ሆኖ አልተገኘም። ባቀረበው አቤቱታ መሰረት የድርጅቱ የበላይ ሃላፊ ስለጌትነት መኩሪያና ስለ ፀሃይ አስፋው ቅጥር ጉዳይ የሚያጣራ ሶስት አባላትን የያዘ ኮሚቴ አቋቋሙ። ኮሚቴው ማስታወቂያው ከወጣ በት ቀን ጀምሮ ፀሀይ አስፋው የቅጥር ፎርማሊቲ እንድታሟላ እስከተደረገበት ጊዜ ድረስ የነበረውን ሂደት ማጣራት ጀመረ።
ኮሚቴው የመጀመሪያውን የፅሁፍ ፈተና ውጤትና ለመጨረሻ ጊዜ በተካሄደው የቃለ መጠይቅ ፈተና የተያዘውን ቃለ ጉባኤ በዝርዝር በማጥናት የውሳኔ ሃሳቡን አጠናቅሮ አቀረበ፡፡ ኮሚቴው የመጀመሪያ የፅሁፍ ፈተና የወሰዱትን የስድስቱንም ተፈታኞች የፈተና ወረቀቶች የመረመረ ሲሆን ፀሃይ አስፋው ዶሮ የጫረው ከሚመስለው የእጅ ጽሁፉ ጀምሮ በይዘቱ
በጣም ደካማ ለነበረው ሥራዋ የተሰጣት ከፍተኛ ውጤት አድሎአዊነትን
የሚጠቁም ሆኖ አግኝቶት ነበር። የቃለ መጠይቆቹ ፍሬ ሃሳቦችና የተሰጡት ነጥቦች አቶ ሽመልስ የያዘውና እነ አቶ አባይነህ የያዙት ፍፁም የማይመሳሰል ከመሆኑም በላይ ፀሀይ አስፋው በብርቱ ክንድ እንደተደገፈች የሚያሳዩ በርካታ ጠቋሚ መረጃዎች ተገኙ። ከዚህ በመነሳትም የመጨረሻውን ውሳኔ ለመስጠት እንዲያስችል በሁለተኛነት ደረጃ ተመዝግቦ ወድቋል የተባለው ጌትነት መኩሪያና ፀሀይ አስፋው ብቻ በድጋሚ ተጠርተው ሌላ የመመዘኛ ፈተና እንዲሰጣቸው ኮሚቴው የውሳኔ አስ
ተያየት አቀረበ፡፡ የበላይ ሃላፊውም የኮሚቴውን ሃሳብ አፀደቁት። የኮሚ
ቴውንና የዋና ስራ አስኪያጅን ውሳኔ በሰማበት እለት ሽመልስ የተሰማውን ደስታ የተመለከተ ጉድ ይል ነበር ለእውነት ሲል ተከራክሮ ለሀቅ ሲል ታግሎ የድል ፍንጭ ያየበት ዕለት በመሆኑ ደስታው ልዩ ነበር።ሀቅ ከሃሰት ውቅያኖስ ውስጥ ብትወድቅም ትሟሟ እንደሆነ እንጂ እን
ደማትጠፋ አምኖ በልቡ ተስፋን አሳደረ፡፡ “ዘመዱ ስለሆነ ነው። በእናቱ በኩል የባሌ ሰው ነው፡፡ የአጎቱ ልጅ ነው..." እያሉ አንዳንዶቹ ማስወራት ጀምረው ነበረና በእርግጥም ጌትነትን ያለችሎታው ሊረዳው ጥብቅና የቆመለት መሆን አለመሆኑ የሚታወቅበት፣ እሱ ወይንም እነ አቶ አባይነህ የሚጋለጡበት፣ እንክርዳዱና ስንዴው የሚለይበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ በመድረሱ ደስታው ገደብ አልነበረውም፡፡ በዚሁ መሰረት ጥሩ የብቃት መለኪያ ፈተና በገለልተኛ ወገን እንዲዘጋጅ ተደረገ፡፡ ፀሀይ ውሳኔው ከተ
ሰጠበት ቀን ጀምሮ የሞላችው የቅጥር ፎርማሊቲ ዋጋ የሌለው መሆኑ
ተገልፆ ለአዲሱ ፈተና ራሷን እንድታዘጋጅ በተነገራት ጊዜ ከድንጋጤዋ የተነሳ ዕቃ ሰበረች።
እውነትና ንጋት እያደር ይጠራል አይዞህ ተስፋ አትቁረጥ በማለት ሞራል ሲስጠው የቆየው ሽመልስ የክርክሩ ውጤት ምን ደረጃ ላይ እንደደረሰ የሚያሳውቀው እንደነገ ሆኖ ዛሬ አብዱላሂና ቶሎሳ በያዙት ቀጠሮ መሠረት ተገናኝተው አምሽቶ መግባቱ ነበር። አብዱላሂ ለንቦጩን ጥሏል። ፊቱ እንደ ፊኛ ተነፍቷል። ጌትነት ደነገጠ፡፡
“እንደምን አመሸህ ጋሼ አብዱላሂ?" አለው ፈራ ተባ እያለ፡፡
"ደህና ነኝ!" መልስ አሰጣጡ እንደምንስ ባድር ምናባክ አገባህ? የሚል
ትርጉም ነበረው፡፡ እንደ ውሻ ቡፍ! አለበት።
“ምነው ጋሼ አብዱላሂ ያስቀየምኩህ ነገር አለ እንዴ? ለትንሽ ጊዜ እንጂ
አላስቸግርህም እኮ ቁርጤን እስከማውቅና ጋሼ ሽመልስ የመጨረሻውን ውጤት እስከሚያሳውቀኝ ድረስ ብቻ ብትታገሰኝ ምን አለበት? ሸክም እንደሆንኩብህ ይሰማኛል"
“ወሬውን ተዋ! ወላሂ እኔ ስው እንደዚህ ወሬኛ ሲሆን አልወድም፡፡ሁሉ ነገሬ ፊት ለፊት ነው፡፡ ግልፅ ነኝ፡፡ ግልፅ ሁን!"
“አልገባኝም?" በጭንቀት።
“ከቶሎሳ ጋር በምንድነው የተጣላችሁት?!" ቱግ! አለበት።
"በም.ም. . .ምን. . ነው የተጣላነው?" አፉ ተንተባተበ፡፡
“ውሽታም!! ውሽታም ነህ አንተ! ወላሂ! ውሸታም ነህ፡፡ አምንህ ነበር ታማኝነትህ ግን በገንዘብ ላይ ብቻ ነው፡፡ ይሄ ደግሞ በቂ አይደለም፡፡
ከሌላው ልክስክስ ሌብነት የገንዘብ ሌብነት ይሻላል። ቶሎሳ ወንድምህም
አባትህም ነው ሸዋዬ ደግሞ እህትህም እናትህም ነች አይደለም?!"
"ልክ. . ልክ ነው ጋሼ አብዱላሂ ልክ ነው" በጭንቀት ዐይኑ ቁልጭ ቁልጭ አለ፡፡አብዱላሂ ለምን እንደዚህ በሃይለ ቃል እንደተናገረው ወዲያውኑ አወቀ። በልቡ ሸዋዬ እግዚአብሔር ይይልሽ አለ፡፡ የአልኮል ትሩፋት አይ ስካር? በዚህ አይነት ስንቱ በስካር ቤት ንብረቱ ፈርሷል? ሲል ራሱን ጠየቀ። ወስዋስ ሸዋዬ ወስውሳ ወስውሳ ባስፈፀመችው ድርጊት ምክንያት ጦሱ በየሄደበት ቦታ ሁሉ እየተከተለው ነው። ከሷ ቤት አምልጦ ሲመጣ ይኸውና ዛሬ ደግሞ ጣጣው ተከትሎት አብዱላሂ ቤት እየደረሰ ነው፡፡
ወይ ፍርጃ! ያ ቀን ምን ዓይነት ቀን ነው? ያንን ጠላ ጠጥቶ ድርጊቱን የፈፀመበትን ቀን በጥላቻ አስታወሰው። አብዱላሂ የጌትነት ፊት መለዋወጡን አፉ መንተባተቡን ሲመለከት ቶሎሳ ያጫወተው በሙሉ ትክክል መሆኑን አረጋገጠ፡፡
ንጂስ የሆንክ ሰው ነህ! ሀራም ሥራ! በጣም ብልግና ነው የፈፀምከው።
በል ከነገ ጀምሮ ቤቱን ልቀቅልኝ! ዐይንህን ማየት አልፈለግም! ጓዝህን ጠቅልለህ ወደምትሄድበት ሂድ! እስከዛሬ ያገለገልክበት ዋጋህን ያውልህ!"ሁለት ባለ አሥር ብር ኖቶች ከኪሱ አወጣና ወደ እጁ ዘረጋለት።
“የለም! የለም ግድ የለም ጋሽ አብዱላሂ" ዐይኖቹ እንባ አቀረሩ። ልሳኑ ተዘጋ፡፡ እንደምንም ጉሮሮውን ጠራረገና
“እስከዛሬ ድረስ የዋልክልኝ ውለታ ቀላል አይደለም፡፡ የሰራሁት ተቀጥሬ
ሳይሆን በችግሬ ምክንያት እንድታስጠጋኝ ላምኜህ ነውና ልትከፍለኝ አይገባም፡፡ ውለታህን እግዚአብሔር እንጂ እኔ ልከፍለው የምችለው አይ
ደለም። አንድ የምለምንህ ነገር ቢኖር ግን አሁን አንተ የምትለኝ ሁሉ በፍፁም እኔነቴን ነፃ አእምሮዬን የሚመለከት አለመሆኑን እንድታውቅ ልኝ ነው። ሰው የሚከስሰውና
👍3