ስንክሳር
7.32K subscribers
825 photos
4 videos
37 files
237 links
በስንክሳር channal ስንክሳሩ ተገልጦ ቅዱሳን ይዘከራሉ፣ ወቅቱን የጠበቁ መረጃዎችን ያገኛሉ፡፡ ይከታተሉን!
Download Telegram
#ቅዱሳን_ስምዖንና_ዮሐንስ
በቤተ ክርስቲያን ታሪክ አስደናቂ ታሪክ ካላቸው #ጻድቃን
እነዚህ 2ቱ ቅድሚያውን ይይዛሉ:: እርሱስ እንደ ምን ነው
ቢሉ:-
ቅዱሳኑ በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን ሶርያ አካባቢ ተወልደው
ያደጉ ክርስቲያኖች ናቸው::
ዘመዳሞች ከመሆናቸው ባሻገር አብረው ስላደጉ እጅጉን
ይፋቀሩ ነበር:: የዋሃንም ነበሩ:: ወጣት በሆኑ ጊዜ ትልቁ
#ዮሐንስ ሚስት አገባ:: ታዲያ አንድ ቀን ከጌታችን መቃብር
#ኢየሩሳሌም ደርሰው ሲመለሱ #ገዳመ_ዮርዳኖስ አካባቢ
ደረሱ:: እርስ በርሳቸውም "ይህ ገዳምኮ የመላእክት ማደሪያ
ነው" ተባባሉ::
በዚያውም መንነው ለመቅረት አሰቡ:: ፈረስና ንብረታቸውን
ለዘመዶቻቸው ልከው ጸሎት አደረሱ:: ፈቃደ እግዚአብሔርን
ሊረዱም ዕጣ ተጣጣሉ:: ዕጣውም "ወደ ገዳም ሒዱ"
የሚል ስለሆነ ተቃቅፈው ደስ አላቸው::
ወደ ገዳሙ ሲደርሱም አበ ምኔቱ #አባ_ኒቅዮስ ፈጣሪ
አዞት የገዳሙን በር ከፍቶ ጠበቃቸው:: ተቀብሎ
ሲያስገባቸውም አንድ ደግ መነኮስ ሲያልፍ: ቆቡ ቦግ ቦግ
እያለ እንደ ፋና ሲያበራ እና #መላእክት ከበውት አዩ::
ወዲያውም አበ ምኔቱን "እባክህ አመንኩሰን" አሉት::
እርሱም የአምላክ ፈቃድ ነውና በማግስቱ አመነኮሳቸው::
ፍቅረ ክርስቶስ ገዝቷቸዋልና በጥቂት ዓመታት ተጋድሎ
ከብቃት (ከጸጋ) ደረሱ:: 2ቱም ቆመው በፍቅር ሲጸልዩ
የብርሃን አክሊል በራሳቸው ላይ ይወርድ ነበር:: አካላቸውም
በሌሊት ያበራ ነበር::
እንዲህ ባለ ቅድስና ለዓመታት ቆይተው ከገዳሙ ወደ ጽኑ
በርሃ ሊሔዱ ስለ ፈለጉ የገዳሙ በር በራሱ ተከፈተ:: አበ
ምኔቱ አባ ኒቆን (ኒቅዮስ) እያነባ በጸሎት ሸኛቸው::
በበርሃም በጠባቡ መንገድ: በቅድስና ተጠምደው ለ29
ዓመታት ተጋደሉ:: በዚህ ሰዓት ግን 2ቱን የሚለያይ ምክንያት
ተፈጠረ::
#እግዚአብሔር ቅዱስ ስምዖን ወደ ከተማ እንዲገባ: ቅዱስ
ዮሐንስ ግን በዚያው እንዲቆይ አዘዘ:: 2ቱ ለረዥም ሰዓት
ተቃቅፈው ተላቅሰው ተለያዩ:: ከ50 ዓመታት በላይ
ተለያይተው አያውቁም ነበርና::
#ቅዱስ_ስምዖን ወደ ከተማ ሲገባ ክብሩን ይደብቅ ዘንድ
እንደ እብድ ሆነ:: በዚህ ምክንያትም የወቅቱ ከተሜዎች
ይንቁት: በጥፊም ይመቱት ነበር:: (እባካችሁ ብዙ
በየመንገዱ የወደቁ አባቶች አሉና እንጠንቀቅ!) ቅዱሱ ግን
ስለ እነርሱ ይጸልይ ነበር::
በከተማዋ የነበሩ እብዶችን ሁሉንም በተአምራት
ፈወሳቸው:: አንድ ቀን ግን ክርስቲያን ነን የሚሉ ሰዎች
ደብድበውት ደከመ:: የእግዚእብሔር መልአክ ወርዶ "ና
ልውሰድህ" ብሎ ዮሐንስን ከበርሃ: ስምዖንን ከከተማ
በዚህች ቀን ወሰዳቸው:: እነሆ ብርሃናቸው ዛሬም ድረስ
ለሚያምንበት ሁሉ ያበራል::