ስንክሳር
7.32K subscribers
825 photos
4 videos
37 files
237 links
በስንክሳር channal ስንክሳሩ ተገልጦ ቅዱሳን ይዘከራሉ፣ ወቅቱን የጠበቁ መረጃዎችን ያገኛሉ፡፡ ይከታተሉን!
Download Telegram
እንኩዋን ለታላቁ #ጻድቅና_ገዳማዊ #አባ_ዓቢየ_እግዚእ ዓመታዊ የተአምር በዓል በሰላም አደረሳችሁ
ጻድቅና #ገዳማዊ_አባ_ዓቢየ_እግዚእ
ጐንደር ከተማ ነዋሪ ከሆኑ ወይም ከተማዋን የሚያውቁዋት ከሆነ አንድ ጥያቄ ልጠይቅዎ::
¤ከተማዋ ውስጥ ጅብና እባብን የመሠሉ አራዊት ነዋሪውን
ሲገድሉ ወይም ሲያቆስሉ ተመልክተው: ካልሆነም በታሪክ
ሰምተው ያውቃሉ?
¤መቸም መልስዎ "በጭራሽ አላውቅም" እንደሚሆን
እገምታለሁ:: "ግን ለምን?" ካሉ ነገሬን እንዲረዱኝ ሌሎች
የሃገራችን ዋና ዋና ከተሞችን ልብ ይበሉልኝ:: እንኩዋን
በሌሊት በቀንም አራዊቱ አይጠፉባቸውም::
¤ታዲያ ጐንደር ከተማ ውስጥ ጅብ የማይገባው: እባብና
ጊንጥ ሰው የማይገድለው በጻድቁ በአባ ዓቢየ እግዚእ ቃል
ኪዳን ምክንያት ነው:: (ሁሉም የሃገራችን ከተሞች የተባረኩ
መሆናቸውን ሳንዘነጋ ማለት ነው:: )
☞ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
አባ ዓቢየ እግዚእ የተወለዱት በ14ኛው መቶ ክ/ዘመን
#ትግራይ ተንቤን ( #መረታ) ውስጥ ነው:: የተባረኩ
ወላጆቻቸው #ያፍቅረነ_እግዚእ እና # ጽርሐ_ቅድሳት
ይባላሉ:: አጥምቀው "#ዓቢየ_እግዚእ " ሲሉ ስም
ያወጡላቸው የወቅቱ ዻዻስ #ሰላማ_መተርጉመ_መጻሕፍት
ናቸው:: ትርጉሙም 'በጌታ ዘንድ ታላቅ ሰው' ማለት ነው::
ዓቢየ እግዚእ በሕጻንነታቸው ሌሊት ሌሊት ባሕር ውስጥ
ሰጥመው ሲጸልዩ አድረው ቀን ቀን እየተማሩ ብሉይ ከሐዲስ
ጠነቀቁ:: ገና በወጣትነታቸው ወደ ታላቁ መነኮስ # አቡነ_መድኃኒነ_እግዚእ (ደብረ_በንኮል) ሔደው መንኩሰዋል:: በገዳሙ በጾም: በጸሎትና በስግደት ተወስነው ከኖሩ በሁዋላ ወደ #ዋልድባ ሔደው የተሰወረች ቤተ ክርስቲያን
አግኝተዋል:: በጊዜው በ40 ቀን አንዲት ቅጠል ብቻ
ለቁመተ ሥጋ ይበሉ ነበር::
ከዚያም ወደ ሃገራቸው ተንቤን ተመልሰው ዛሬም ድረስ
ድንቅ ሆኖ የሚታየውን ገዳም መሥርተው ብዙ መናንያንን
አፍርተዋል:: ዓቢየ እግዚእ ገዳማዊና ጻድቅ ብቻ ሳይሆን
#ሐዋርያዊ አባትም ነበሩ:: ከትግራይ እስከ #ደንቢያ ደግሞ
ሃገረ ስብከታቸው ነው::
አንድ ጊዜ ደቀ መዛሙርትን አስከትለው ለስብከት
ሲንቀሳቀሱ #ተከዜ ወንዝ አካባቢ ደረሱ:: ቀኑ ነሐሴ 10
ነውና ተከዜ እስከ ገደፉ ሞልቶ ለ3 ቀናት ባለመጉደሉ
ከ1,000 በላይ ሰዎች ሲያለቅሱ ደረሱ:: ጻድቁ ባካባቢው
የነበሩት ኢ-አማንያን (አሕዛብ) ቢሆኑም ራርተዋልና
"አምላከ_ሙሴ" ብለው ጸልየው ወደ ጥልቁ ውስጥ ገቡ::
#ቅዱስ_ሚካኤል አብሯቸው ነበርና ተከዜ ግራና ቀኝ
ተከፍሎ መሃሉ የብስ ሆነ:: ይሕን ድንቅ ያዩ ከ940 በላይ
አሕዛብም አምነው በጻድቁ እጅ ተጠምቀዋል:: ይሕም
ዘወትር ነሐሴ 10 ቀን በቤተ ክርስቲያናቸው (ጐንደር)
ይከበራል::
+ከዚያም እያስተማሩ ጐንደር ደረሱ:: ያኔ ጐንደር በቀሃና
አንገረብ ወንዞች የታጠረች አንዲት መንደር ነበረች:: ጻድቁ
ቀን ቀን እየሰበኩ ማታ ዛሬ ቤተ ክርስቲያናቸው የታነጸበት
ሥፍራ ላይ ሲጸልዩ ያድሩ ነበር::
+በዚያ ዘመን ጐንደር ውስጥ ጅብ: እባብና መሠል አራዊት
ገብተው ሕዝቡን ጨረሱት:: ይሕንን የተመለከቱት አባ ዓቢየ
እግዚእ ወደ እግዚአብሔር አለቀሱ:: በፍጹም ልባቸውም ስለ
ሕዝቡ ለመኑ::
የለመኑትን የማይነሳ ጌታ ወደ ጻድቁ ቀርቦ "በስምሕ
የተማጸኑ: በቃል ኪዳንህ ያመኑ: በምድር አራዊት
አይሠለጥኑባቸውም:: በሰማይም እሳትን አያዩም::
ጐንደርንም አራዊት ገብተው ሰውን አይጐዱም::" ብሏቸው
አርጉዋል:: ጻድቁም የወንጌል አገልግሎታቸውን ፈጽመው ወደ
ገዳማቸው #ተንቤን ተመልሰዋል:: ይሔው እኛ ምን
ብንከፋ: ጻድቁንም ብንረሳቸው #እግዚአብሔር ግን ዛሬም
በጻድቁ ምልጃ ከተማዋን ጠብቆ ይኖራል:: ነገን ደግሞ እርሱ
ያውቃል:: ዛሬ ቤተ ክርስቲያኑ የታነጸበት ቦታ ( #ጎንደር ቀበሌ
09 #ኪዳነ_ምሕረት ) ጻድቁ የጸለዩበት ቦታ ነው:: እንኩዋን
በወርሃዊ በዓላቸው (በ19) ይቅርና በዓመታዊ በዓላቸው
(ግንቦት 19, ነሐሴ 10) እንኩዋ ለንግስ የሚመጣው ሰው
ቁጥር ያስተዛዝባል::
አባ ዓቢየ እግዚእ በገዳማቸው ተንቤን ለብዙ ዘመናት
በቅድስና ኑረው: 3 ሙታንን አስነስተው: ብዙ ድውያንን
ፈውሰው: #ብሔረ_ብጹዓንን ጎብኝተው: የድኅነት ቃል
ኪዳንም ተቀብለው: በ140 ዓመታቸው ግንቦት 19 ቀን
አርፈዋል:: የጻድቁ ክብር ለሁሉ ነውና እናስባቸው::
ይህች ዕለት ባሕረ ተከዜን ከፍለው ሕዝቡን ያሻገሩባት:
አሕዛብንም ያጠመቁባት ናትና በገዳማቸው: ጐንደር ውስጥ
በሚገኘው ቤተ ክርስቲያናቸውም ይከበራል::
¤በረከታቸው ይደርብን::