♥ እንኩዋን ለእመቤታችን
#ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ የጽንሰት በዓል
በሰላም አደረሳችሁ♥
✝ቁጽረታ ( #ጽንሰታ ) ለማርያም✝
ይህችን ዕለት አበው ሊቃውንት "ጥንተ
መድኃኒት_የድኅነት መነሻ ቀን" ሲሉ ይጠሯታል:: ስለ ምን
ነው ቢሉ:- ለዓለም ድኅነት ምክንያት የሆነች የአምላክ እናቱ
የተጸነሰችበት ዕለት በመሆኑ ነው:: አንድም ከአዳም ስሕተት
በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተጸነሰች የመጀመሪያ ሰው እርሷ
ናትና እንዲህ ይላሉ::
"ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ
እማሕጸን ቅዱስ::"
" #ድንግል_ሆይ ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው:
የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ
ነው::" ( መጽሐፈ_ሰዓታት , ኢሳ. 1:9, መኃ. 4)
ይሕች ዕለት ለኢያቄምና ለሐና ብቻ ሳይሆን ለፍጥረት ሁሉ
የተስፋ ድኅነት ቀን ናትና ሐሴትን ልናደርግ ይገባል::
የእመቤታችን መጸነስስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
ከነገደ #ይሁዳ የሚወለድ #ቅዱስ_ኢያቄም የሚባል ደግ
ሰው ከነገደ #ሌዊ ( #አሮን ) የተወለደች #ሐና የምትባል ደግ
ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ
ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች "ልጅ የላችሁም" በሚል
ይናቁ ነበር::
ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን "ኅጡአ በረከት-ከጸጋ
#እግዚአብሔር የራቀ" ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና
ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ
አረጁ:: እነሱ ግን የሚያመልኩት #የአብርሃምና_ሣራን
አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::
የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን
አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር
ሲጫወቱ የተመለከተች #ቅድስት_ሐና ፈጽማ አለቀሰች::
"እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ
የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ
ፈጥረሃታልን?" ብላ አዘነች::
ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ
ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን
2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- #ነጭ_ርግብ ሰማያትን
ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ
አየ::እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ
ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም
ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው "ፈቃደ
እግዚአብሔር ይሁን" አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ
እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::
በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7)
#መልአከ_ብሥራት_ቅዱስ_ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ
እነርሱ ወረደ:: "ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ
የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ" ብሏቸው ተሠወራቸው::
እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::
እንደ ሥርዓቱም በዚህች ቀን አብረው አድረው
#እመ_ብርሃን ተጸነሰች::
" #ኦ_ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ
¤ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ
አይደለም" እንዳለ ሊቁ:: ( #ቅዳሴ_ማርያም )
#ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ የጽንሰት በዓል
በሰላም አደረሳችሁ♥
✝ቁጽረታ ( #ጽንሰታ ) ለማርያም✝
ይህችን ዕለት አበው ሊቃውንት "ጥንተ
መድኃኒት_የድኅነት መነሻ ቀን" ሲሉ ይጠሯታል:: ስለ ምን
ነው ቢሉ:- ለዓለም ድኅነት ምክንያት የሆነች የአምላክ እናቱ
የተጸነሰችበት ዕለት በመሆኑ ነው:: አንድም ከአዳም ስሕተት
በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተጸነሰች የመጀመሪያ ሰው እርሷ
ናትና እንዲህ ይላሉ::
"ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ
እማሕጸን ቅዱስ::"
" #ድንግል_ሆይ ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው:
የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ
ነው::" ( መጽሐፈ_ሰዓታት , ኢሳ. 1:9, መኃ. 4)
ይሕች ዕለት ለኢያቄምና ለሐና ብቻ ሳይሆን ለፍጥረት ሁሉ
የተስፋ ድኅነት ቀን ናትና ሐሴትን ልናደርግ ይገባል::
የእመቤታችን መጸነስስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
ከነገደ #ይሁዳ የሚወለድ #ቅዱስ_ኢያቄም የሚባል ደግ
ሰው ከነገደ #ሌዊ ( #አሮን ) የተወለደች #ሐና የምትባል ደግ
ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ
ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች "ልጅ የላችሁም" በሚል
ይናቁ ነበር::
ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን "ኅጡአ በረከት-ከጸጋ
#እግዚአብሔር የራቀ" ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና
ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ
አረጁ:: እነሱ ግን የሚያመልኩት #የአብርሃምና_ሣራን
አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::
የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን
አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር
ሲጫወቱ የተመለከተች #ቅድስት_ሐና ፈጽማ አለቀሰች::
"እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ
የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ
ፈጥረሃታልን?" ብላ አዘነች::
ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ
ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን
2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- #ነጭ_ርግብ ሰማያትን
ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ
አየ::እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ
ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም
ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው "ፈቃደ
እግዚአብሔር ይሁን" አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ
እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::
በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7)
#መልአከ_ብሥራት_ቅዱስ_ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ
እነርሱ ወረደ:: "ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ
የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ" ብሏቸው ተሠወራቸው::
እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::
እንደ ሥርዓቱም በዚህች ቀን አብረው አድረው
#እመ_ብርሃን ተጸነሰች::
" #ኦ_ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ
¤ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ
አይደለም" እንዳለ ሊቁ:: ( #ቅዳሴ_ማርያም )